የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የፌደራል ፍ/ቤቶችን የአስተዳደር ሠራተኞች ረቂቅ ደንብ አፀደቀ
****************
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ.ም ባካሔደው መደበኛ ስብሰባ የፌደራል ፍ/ቤቶችን የአስተዳደር ሠራተኞች ረቂቅ ደንብ ”ደንብ ቁጥር 1/2015” አድርጎ አፀደቀ፡፡
ረቂቅ ደንቡን አስመልክቶ ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት ያቀረቡት የም/ቤቱ የሕግና ፍትሕ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት የተከበሩ ወ/ሮ ዕፀገነት መንግሥቱ ምክር ቤቱ በ2ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ ጥር 16 ቀን 2015 ዓ.ም ባካሔደው 9ኛ መደበኛ ስብሰባ ረቂቅ ደንቡ ለዝርዝር ዕይታ በዋናነት ለም/ቤቱ የሕግና ፍትሕ ቋሚ ኮሚቴ፣ በተባባሪነት ደግሞ ለሰው ሐብት ልማት ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መመራቱን አስታውሰው በዚህ መሠረት ረቂቅ ደንቡን በመመርመር ሒደት የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን ለም/ቤቱ አባላት በዝርዝር አቅርበዋል፡፡
በማብራሪያቸውም በቋሚ ኮሚቴዎቹ ማሻሻያና ማስተካከያ የተደረገባቸውን የረቂቅ ደንቡን ድንጋጌዎች በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን ማብራሪያውን ተከትሎ ከተከበሩ የም/ቤት አባላት ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
በመጨረሻም ረቂቅ ደንቡ በም/ቤቱ አባላት በአብላጫ ድምጽና በአንድ ተቃውሞ ”ደንብ ቁጥር 1/2015” ሆኖ መጽደቁን ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ረቂቅ ደንቡ የፀደቀው በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 55/1 ላይ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አዋጁን ለማስፈጸም ደንብ ሊያወጣ እንደሚችል በተደነገገው መሠረት ነው፡፡
የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
#አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
#ሼር #Share
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
****************
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ.ም ባካሔደው መደበኛ ስብሰባ የፌደራል ፍ/ቤቶችን የአስተዳደር ሠራተኞች ረቂቅ ደንብ ”ደንብ ቁጥር 1/2015” አድርጎ አፀደቀ፡፡
ረቂቅ ደንቡን አስመልክቶ ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት ያቀረቡት የም/ቤቱ የሕግና ፍትሕ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት የተከበሩ ወ/ሮ ዕፀገነት መንግሥቱ ምክር ቤቱ በ2ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ ጥር 16 ቀን 2015 ዓ.ም ባካሔደው 9ኛ መደበኛ ስብሰባ ረቂቅ ደንቡ ለዝርዝር ዕይታ በዋናነት ለም/ቤቱ የሕግና ፍትሕ ቋሚ ኮሚቴ፣ በተባባሪነት ደግሞ ለሰው ሐብት ልማት ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መመራቱን አስታውሰው በዚህ መሠረት ረቂቅ ደንቡን በመመርመር ሒደት የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን ለም/ቤቱ አባላት በዝርዝር አቅርበዋል፡፡
በማብራሪያቸውም በቋሚ ኮሚቴዎቹ ማሻሻያና ማስተካከያ የተደረገባቸውን የረቂቅ ደንቡን ድንጋጌዎች በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን ማብራሪያውን ተከትሎ ከተከበሩ የም/ቤት አባላት ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
በመጨረሻም ረቂቅ ደንቡ በም/ቤቱ አባላት በአብላጫ ድምጽና በአንድ ተቃውሞ ”ደንብ ቁጥር 1/2015” ሆኖ መጽደቁን ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ረቂቅ ደንቡ የፀደቀው በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 55/1 ላይ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አዋጁን ለማስፈጸም ደንብ ሊያወጣ እንደሚችል በተደነገገው መሠረት ነው፡፡
የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
#አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
#ሼር #Share
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
#news
የኢትዮዽያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ተ/ፕሬዚደንት አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው የአፍሪካ ጠበቆች ማህበር (PALU) ም/ፕሬዚደንት ሆነው ተመረጡ!!!
***********************
እ.ኤ.አ ከጁላይ 5 ቀን 2023 ጀምሮ በዛምቢያ ሀገር ሊቪንግስተን ከተማ እየተካሄደ ባለው 13ኛው የአፍሪካ ጠበቆች ማህበራት ህብረት ጉባኤ ከመላው አፍሪካ ፤ ከመካከለኛው ምስራቅ ፤ ከአውሮፓ እና ሰሜን አሜሪካ ክፍለ አህጉሮች የተውጣጡ ከ 250 በላይ የጠበቆች ማህበር ፕሬዝደንቶችና የአመራር አባላት ፤ አካባቢያዊ የባር አሶሲዬሽን መዋቅሮች ፤ አለም አቀፍ የጥብቅና ድርጅቶች ፤ የአፍሪካ ህብረትና የተባበሩት መንግስታት ኤጀንሲዎች ተወካዮች እና የሚመለከታቸው የመንግስት ሀላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ::
በዚሁ ጉባኤ ላይ ለህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች ለተደረገው ምርጫ የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበርን እየመሩ ያሉት አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው ከተወዳዳሪዎቹ ይልቅ ከአባል ሀገራቱ ከፍተኛ ድምፅ በማግኘት የአፍሪካ ጠበቆች ማህበር (PALU) ምክትል ፕሬዚደንት ሆነው ተመርጠዋል::
አቶ ቴዎድሮስን በእጩነት እንዲወዳደሩ የጠቆመው 7 ሀገራትን በአባልነት ያቀፈውና ከ28,000 በላይ አባላት ያሉት የ East African Law Society ነው:: ቴዎድሮስ ከምስራቅ አፍሪካ ፤ ከደቡብ አፍሪካ እና ከማእከላዊ አፍሪካ ዞናት ሙሉ ድጋፍ ያገኙ ሲሆን ከምእራብና ሰሜን አፍሪካ ተወካዮች ደግሞ አብላጫውን ድጋፍ በማግኘት ሊመረጡ ችለዋል::
የአፍሪካ ጠበቆች ማህበራት ህብረትን በም/ፕሬዝደንትነት ለመምራት ኢትዮጵያዊ ሲመረጥ የመጀመሪያው ሲሆን ህብረቱ በአዲስ አበባ በተመሰረተበት ግዜ ከ21 አመታት በፊት አንጋፋው የህግ ባለሙያ አቶ ጌታቸው ቅጣው የህብረቱ ዋና ፀሀፊ ሆነው አገልግለዋል:: ላለፉት 18 አመታት በህብረቱ ከፍተኛ አመራር ላይ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ምንም አይነት ቦታ ማግኘት ሳይችሉ ቆይተዋል:: በአሁኑ ወቅት የህብረቱ ፕሬዚደንት ፈረንሳይኛ ተናጋሪው ካሜሮናዊው የህግ ባለሙያና ጠበቃ ሚ/ር ካሪ አብዶል ባጉይ ሲሆኑ የሴክሬታሪያቱ መቀመጫ በታንዛኒያ አሩሻ እንደሚገኝ ይታወቃል::
የኢትዮዽያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር
ሀምሌ 02 ቀን 2015ዓ.ም
አዲስ አበባ ፤
#መረጃዎች በቶሎ እንዲደርሷችሁ ይፋዊ የፌስቡክ ገፃችንን በሚከተለው ሊንክ ይቀላቀሉ::
https://www.facebook.com/ethiopianbarassociation?mibextid=LQQJ4d
የኢትዮዽያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ተ/ፕሬዚደንት አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው የአፍሪካ ጠበቆች ማህበር (PALU) ም/ፕሬዚደንት ሆነው ተመረጡ!!!
***********************
እ.ኤ.አ ከጁላይ 5 ቀን 2023 ጀምሮ በዛምቢያ ሀገር ሊቪንግስተን ከተማ እየተካሄደ ባለው 13ኛው የአፍሪካ ጠበቆች ማህበራት ህብረት ጉባኤ ከመላው አፍሪካ ፤ ከመካከለኛው ምስራቅ ፤ ከአውሮፓ እና ሰሜን አሜሪካ ክፍለ አህጉሮች የተውጣጡ ከ 250 በላይ የጠበቆች ማህበር ፕሬዝደንቶችና የአመራር አባላት ፤ አካባቢያዊ የባር አሶሲዬሽን መዋቅሮች ፤ አለም አቀፍ የጥብቅና ድርጅቶች ፤ የአፍሪካ ህብረትና የተባበሩት መንግስታት ኤጀንሲዎች ተወካዮች እና የሚመለከታቸው የመንግስት ሀላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ::
በዚሁ ጉባኤ ላይ ለህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች ለተደረገው ምርጫ የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበርን እየመሩ ያሉት አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው ከተወዳዳሪዎቹ ይልቅ ከአባል ሀገራቱ ከፍተኛ ድምፅ በማግኘት የአፍሪካ ጠበቆች ማህበር (PALU) ምክትል ፕሬዚደንት ሆነው ተመርጠዋል::
አቶ ቴዎድሮስን በእጩነት እንዲወዳደሩ የጠቆመው 7 ሀገራትን በአባልነት ያቀፈውና ከ28,000 በላይ አባላት ያሉት የ East African Law Society ነው:: ቴዎድሮስ ከምስራቅ አፍሪካ ፤ ከደቡብ አፍሪካ እና ከማእከላዊ አፍሪካ ዞናት ሙሉ ድጋፍ ያገኙ ሲሆን ከምእራብና ሰሜን አፍሪካ ተወካዮች ደግሞ አብላጫውን ድጋፍ በማግኘት ሊመረጡ ችለዋል::
የአፍሪካ ጠበቆች ማህበራት ህብረትን በም/ፕሬዝደንትነት ለመምራት ኢትዮጵያዊ ሲመረጥ የመጀመሪያው ሲሆን ህብረቱ በአዲስ አበባ በተመሰረተበት ግዜ ከ21 አመታት በፊት አንጋፋው የህግ ባለሙያ አቶ ጌታቸው ቅጣው የህብረቱ ዋና ፀሀፊ ሆነው አገልግለዋል:: ላለፉት 18 አመታት በህብረቱ ከፍተኛ አመራር ላይ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ምንም አይነት ቦታ ማግኘት ሳይችሉ ቆይተዋል:: በአሁኑ ወቅት የህብረቱ ፕሬዚደንት ፈረንሳይኛ ተናጋሪው ካሜሮናዊው የህግ ባለሙያና ጠበቃ ሚ/ር ካሪ አብዶል ባጉይ ሲሆኑ የሴክሬታሪያቱ መቀመጫ በታንዛኒያ አሩሻ እንደሚገኝ ይታወቃል::
የኢትዮዽያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር
ሀምሌ 02 ቀን 2015ዓ.ም
አዲስ አበባ ፤
#መረጃዎች በቶሎ እንዲደርሷችሁ ይፋዊ የፌስቡክ ገፃችንን በሚከተለው ሊንክ ይቀላቀሉ::
https://www.facebook.com/ethiopianbarassociation?mibextid=LQQJ4d
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
በክልሎች ይሰጥ የነበረው የአስመጪና ላኪዎች የንግድ አገልግሎት ከሐምሌ 1/2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ፌዴራል ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር መዞሩ ተገለጸ::
====================================
አዲስ አበባ 03/11/ ከ2015 ዓ.ም (ንቀትሚ) በክልሎች ይሰጥ የነበረው የአስመጪዎችና ላኪዎች ንግድ አገልግሎት ከሐምሌ 1/2015 ዓ.ም ጀምሮ በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በኩል አገልግሎቱ እየተሰጠ ይገኛል፡፡
የኦንላይን ንግድ ምዝገባና ፈቃድ ተግባራዊ ከመደረጉ በፊት በክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች በኩል ይሰጥ የነበረው የአስመጪና ላኪ የንግድ አገልግሎት አስተዳዳራዊ ክፍተቶች የታዩበት፣ የኮንትሮባንድ ንግድ የተበራከተበት በመሆኑና በወቅቱ አገልግሎቱ ያልወረደላቸው ክልሎች የመልካም አስተዳደር ጥያቄ በማንሳታቸው ሚኒስትር መስራ ቤቱ ይህን ችግር ለመፍታት የአስመጪና ላኪዎች ንግድ አገልግሎት ከሃምሌ 1/2015 ዓ.ም ጀምሮ በፌዴራል ተግባራዊ እንዲሆን መወሰኑን ሚኒስትር መስራ ቤቱ አስታውቋል፡፡
የኦንላይን ንግድ ምዝገባና ፍቃድ አገልግሎት ከሃምሌ 1/2013 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ ማንኛውም አስመጪና ላኪ ነጋዴ የትም ማሄድ ሳይጠበቅበት ሲስተሙን በመጠቀም ባለበት ቦታ ሆኖ አገልግሎት ማግኘት የሚችል ሲሆን በአገልግሎቱ ላይ ግልጽ ያልሆኑ ጥያቄዎች ካሉ በ 965 የጥሪ መዕከል ደውሎ መረጃ ማግኘት የሚችል መሆኑም ተጠቁሟል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን:-
Email: fdremotri@gmail.com
fdremotri@motri.gov.et
facebook:- Ethiopianministryof tradeandregionalitegration
For trade license : www.etrade.gov.et
website: www.motri.gov.et
====================================
አዲስ አበባ 03/11/ ከ2015 ዓ.ም (ንቀትሚ) በክልሎች ይሰጥ የነበረው የአስመጪዎችና ላኪዎች ንግድ አገልግሎት ከሐምሌ 1/2015 ዓ.ም ጀምሮ በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በኩል አገልግሎቱ እየተሰጠ ይገኛል፡፡
የኦንላይን ንግድ ምዝገባና ፈቃድ ተግባራዊ ከመደረጉ በፊት በክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች በኩል ይሰጥ የነበረው የአስመጪና ላኪ የንግድ አገልግሎት አስተዳዳራዊ ክፍተቶች የታዩበት፣ የኮንትሮባንድ ንግድ የተበራከተበት በመሆኑና በወቅቱ አገልግሎቱ ያልወረደላቸው ክልሎች የመልካም አስተዳደር ጥያቄ በማንሳታቸው ሚኒስትር መስራ ቤቱ ይህን ችግር ለመፍታት የአስመጪና ላኪዎች ንግድ አገልግሎት ከሃምሌ 1/2015 ዓ.ም ጀምሮ በፌዴራል ተግባራዊ እንዲሆን መወሰኑን ሚኒስትር መስራ ቤቱ አስታውቋል፡፡
የኦንላይን ንግድ ምዝገባና ፍቃድ አገልግሎት ከሃምሌ 1/2013 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ ማንኛውም አስመጪና ላኪ ነጋዴ የትም ማሄድ ሳይጠበቅበት ሲስተሙን በመጠቀም ባለበት ቦታ ሆኖ አገልግሎት ማግኘት የሚችል ሲሆን በአገልግሎቱ ላይ ግልጽ ያልሆኑ ጥያቄዎች ካሉ በ 965 የጥሪ መዕከል ደውሎ መረጃ ማግኘት የሚችል መሆኑም ተጠቁሟል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን:-
Email: fdremotri@gmail.com
fdremotri@motri.gov.et
facebook:- Ethiopianministryof tradeandregionalitegration
For trade license : www.etrade.gov.et
website: www.motri.gov.et
ስትወሰልት የተያዘች ሚስት በባሏ እርዳታ የምትወደውን ሰው አገባች
በሚስትየዋ ድርጊት የተበሳጩ የሰፈሩ ሰዎችም ሚስትየውን እና የሰው ሚስት የሚያባልገውን ሰው እጅ ከፍንጅ ይዘው ለባልየው አስረክበዋል።👇
https://am.al-ain.com/article/india-cheating-women-marrying-lover
በሚስትየዋ ድርጊት የተበሳጩ የሰፈሩ ሰዎችም ሚስትየውን እና የሰው ሚስት የሚያባልገውን ሰው እጅ ከፍንጅ ይዘው ለባልየው አስረክበዋል።👇
https://am.al-ain.com/article/india-cheating-women-marrying-lover
አል ዐይን ኒውስ
ስትወሰልት የተያዘች ሚስት በባሏ እርዳታ የምትወደውን ሰው አገባች
ሴትዮዋ ከምታፈቅረው ሰው ጋር በትዳሯ ላይ ስትወሰልት የመንደሩ ሰው እጅ ከፍንጅ ይዘዋታል
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎች በቅርቡ ባሳተመው ቅፅ 25 ላይ የገጠር መሬትን በተመለከተ ምን አዲስ እይታ ይዞ መጣ?
****
1. የገጠር መሬትን በተመለከተ ሁለት ዳኝነቶች በአንድ ላይ ተጣምረው ሲቀርቡ የፍርድ ቤት ስልጣን በተመለከተ በመሬት አዋጁ፣ በስነ-ስርዓት ህጉ እና የክልል ፍ/ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ መካከል ግጭት ካለ የመሬት አዋጁ ልዩ ህግ በመሆኑ በቀዳሚነት ሊተገበር ይገባል (Special prevails over the geberal)። የሰበር መ/ቁ. 191968
2. ወራሽነትን ቀድሞ በማረጋገጥ የገጠር መሬትን ቀድሞ መያዝ ልዩ የወራሽነት መብትን የማያጎናፅፍ በመሆኑ ሌሎች ወራሾችን ድርሻቸውን ከመጠየቅ አይገድብም። የሰበር መ/ቁ. 181643
3. የገጠር መሬት አዋጁ ላይ የገጠር መሬትን በሽያጭ ዉል ማስተላለፍ ክልከላ የተደረገበት ከሆነ መሬቱ ላይ ቤት ቢኖርበትም ባይኖርበትም ዉሉ ህግን ያለተከተለ ሰለሆነ አይፀናም። የሰበር መ/ቁ. 186431
4. የገጠር መሬት ስጦታ ተደርጎል ተብሎ የሚመዘነው በጊዜው በነበረው የገጠር መሬት ህግ እንጅ ከስጦታው በኋላ ተሻሽሎ በወጣው ህግ አይደለም። (Principle of non-retroactivity) የሰበር መ/ቁ. 185848
5. የገጠር መሬት ስጦታን በተመለከተ የመሬት አዋጆቹ ስራ ላይ ባልነበሩበት ጊዜ ወይም ደግሞ በህጎቹ ባልተሸፈኑ ጉዳዪች ላይ የፍ/ህጉ የማይንቀሳቀስ ንብረት በስጦታ ስለሚተላለፍበት ሁኔታ የተዘረዘሩት ድንጋጌዎች ተፈፃሚ ሊሆኑ ይገባል። (Common approach of the Cassation using the 1960 Civil Code provisions as a gap feeling to rural land matters) የሰበር መ/ቁ. 188853
6. ከሚመለከተው የመንግስት አካል በስተቀር አንድ ግለሰብ የያዘውን መሬት አያያዙ በህገ-ወጥ መንገድ በሚል አስለቅቆ መያዝ አይችልም። (No one can take justice by his own hand) የሰበር መ/ቁ. 187618
7. የገጠር መሬት ኪራይ ይርጋ ጋር በተያያዘ የመሬት አዋጁ በግልፅ ካላስቀመጠ ተፈፃሚነት ያለው የይርጋ ጊዜ የፍ/ህ/ቁ. 1845 ነው። የሰበር መ/ቁ. 187484
8. ትዳር በሞት ምክንያት ከፈረሰ በሌላኛው ተገቢ የተያዘ የገጠር መሬት እንዲመለስ በወራሾች የሚቀርብ ጥያቄ በጋብቸ የተፈራ የንብረት ክፍፍል ጥየቄ ስለሆነ ሰበር ቀደም ብሎ በቅፅ 4 የመ/ቁ. 17937 በሰጠው የህግ ትርጉም መሰረት በ10 ዓመት ይርጋ ቀሪ ይሆናል። የሰበር መ/ቁ. 186461. Credit to #Ayalew Asfaw
****
1. የገጠር መሬትን በተመለከተ ሁለት ዳኝነቶች በአንድ ላይ ተጣምረው ሲቀርቡ የፍርድ ቤት ስልጣን በተመለከተ በመሬት አዋጁ፣ በስነ-ስርዓት ህጉ እና የክልል ፍ/ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ መካከል ግጭት ካለ የመሬት አዋጁ ልዩ ህግ በመሆኑ በቀዳሚነት ሊተገበር ይገባል (Special prevails over the geberal)። የሰበር መ/ቁ. 191968
2. ወራሽነትን ቀድሞ በማረጋገጥ የገጠር መሬትን ቀድሞ መያዝ ልዩ የወራሽነት መብትን የማያጎናፅፍ በመሆኑ ሌሎች ወራሾችን ድርሻቸውን ከመጠየቅ አይገድብም። የሰበር መ/ቁ. 181643
3. የገጠር መሬት አዋጁ ላይ የገጠር መሬትን በሽያጭ ዉል ማስተላለፍ ክልከላ የተደረገበት ከሆነ መሬቱ ላይ ቤት ቢኖርበትም ባይኖርበትም ዉሉ ህግን ያለተከተለ ሰለሆነ አይፀናም። የሰበር መ/ቁ. 186431
4. የገጠር መሬት ስጦታ ተደርጎል ተብሎ የሚመዘነው በጊዜው በነበረው የገጠር መሬት ህግ እንጅ ከስጦታው በኋላ ተሻሽሎ በወጣው ህግ አይደለም። (Principle of non-retroactivity) የሰበር መ/ቁ. 185848
5. የገጠር መሬት ስጦታን በተመለከተ የመሬት አዋጆቹ ስራ ላይ ባልነበሩበት ጊዜ ወይም ደግሞ በህጎቹ ባልተሸፈኑ ጉዳዪች ላይ የፍ/ህጉ የማይንቀሳቀስ ንብረት በስጦታ ስለሚተላለፍበት ሁኔታ የተዘረዘሩት ድንጋጌዎች ተፈፃሚ ሊሆኑ ይገባል። (Common approach of the Cassation using the 1960 Civil Code provisions as a gap feeling to rural land matters) የሰበር መ/ቁ. 188853
6. ከሚመለከተው የመንግስት አካል በስተቀር አንድ ግለሰብ የያዘውን መሬት አያያዙ በህገ-ወጥ መንገድ በሚል አስለቅቆ መያዝ አይችልም። (No one can take justice by his own hand) የሰበር መ/ቁ. 187618
7. የገጠር መሬት ኪራይ ይርጋ ጋር በተያያዘ የመሬት አዋጁ በግልፅ ካላስቀመጠ ተፈፃሚነት ያለው የይርጋ ጊዜ የፍ/ህ/ቁ. 1845 ነው። የሰበር መ/ቁ. 187484
8. ትዳር በሞት ምክንያት ከፈረሰ በሌላኛው ተገቢ የተያዘ የገጠር መሬት እንዲመለስ በወራሾች የሚቀርብ ጥያቄ በጋብቸ የተፈራ የንብረት ክፍፍል ጥየቄ ስለሆነ ሰበር ቀደም ብሎ በቅፅ 4 የመ/ቁ. 17937 በሰጠው የህግ ትርጉም መሰረት በ10 ዓመት ይርጋ ቀሪ ይሆናል። የሰበር መ/ቁ. 186461. Credit to #Ayalew Asfaw
የተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን ሕግ በኢትዮጵያ
በሀገራችን ኢትዮጵያ የተሽከርካሪ አደጋ በእጅጉ እየበዛ እና ከፍተኛ የሆነ ሞት፣ አካል ገዳት እና የንብረት ጉዳት እያስከተለ ይገኛል፡፡ ከአደጋው አስከፊነትና ከሰብአዊነት አንፃር የተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂዎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የሕክምና እርዳታ ማግኘት ይገባቸዋል፡፡ ሆኖም አንዳንድ ጊዜ ጉዳት አድራሹ በመሰወሩ ምክንያት ላይታወቅ የሚችልበት እድል ከመኖሩም በላይ ቢታወቅም እንኳን በወቅቱ ወጪውን ለመሸፈን የሚያስችል አቅም የሌለው የሚሆንባቸው አጋጣሚዎች በርካታ ናቸው፡፡ ይህም ተጎጂዎችን ለተጨማሪ ጉዳትና እንግልት ሊዳርግ ይችላል፡፡
ይህንን ችግር ለማቃለል የተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን ሽፋን አስገዳጅ በሆነ መልኩ በሕግ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ የተሸከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን አዋጅ ቁጥር 799/2005 በአሁኑ ሰዓት በሥራ ላይ የሚገኝ ሕግ ነው፡፡ በዚህ አጭር ፅሑፍ የሕጉን ይዘት እንዳስሳለን፡፡
የተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን ምንነት
መድን ወይም ኢንሹራንስ ስለሚለው ቃል ከተለያየ አቅጣጫ በማየት ትርጉም ሊሰጠው እንደሚችል የዘርፉ ምሁራን ይገልፃሉ፡፡ ከግለሰቦች መነሻ ነጥብ ተነስቶ የሚሰጠው ትርጉም የመጀመሪያው ሲሆን እሱም “አንድ ሰው በንብረቱ፣ በህይወቱ ወይም በአካሉ ላይ ባልተጠበቀ ሁኔታ ሊያጋጥም በሚችል አደጋ ምክንያት የሚደርስ በገንዘብ የሚለካ ጉዳትን ለኢንሹራንስ ድርጅት ማስተላለፊያ መንገድ ነው፡፡” ሁለተኛው መነሻ ነጥብ ከኢንሹራንስ ሰጪው ድርጅት በመነሳት ሲሆን “ኢንሹራንስ ሰጪው በአደጋ ምክንያት የሚያጋጥምን ኪሳራ ለተመሳሳይ አይነት አደጋ ተጋላጭ ለሆኑ ሰዎች የሚያከፋፍልበት መንገድ ወይም ዘዴ ነው፡፡”
በሀገራችንም በነባሩ የንግድ ሕግ አንቀጽ 654(1) ላይ “የኢንሹራስ ውል ፖሊሲ ማለት ኢንሹራንስ ሰጪ የሚባለው በአንድ ወይም በብዙ የተመደበውን የኢንሹራንስ መግቢያ ዋጋ (ፕርምየም) ተቀብሎ በውሉ የተመለከተው አደጋ በደረሰ ጊዜ ኢንሹራንስ ለገባው ሰው የተወሰነ ገንዘብ ለመክፈል ግዴታ የሚገባበት ነው፡፡” በማለት ትርጉሙን አስቀምጧል፡፡ ይህ የጠቅላላው የመድን ውል ትርጓሜ ሲሆን የተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድንን በተመለከተ ደግሞ በአዋጅ ቁጥር 799/2005 አንቀፅ 2(8) እና (10) ስር ከተሰጡት ትርጉሞች ተነስተን መረዳት እንችላለን፡፡ በዚህም መሰረት “የመድን [ውል] ማለት የመድን ገቢው ተሸከርካሪ በሦስተኛ ወገን ላይ ለሚያደርሰው የሞት አደጋ፣ የአካል ጉዳት ወይም የንብረት ኪሳራ ካሳ ለመክፈል እና የአስቸኳይ የሕክምና አገልግሎት ክፍያን ለመፈፀም መድን ሰጪው ውለታ የሚገባበት ሰነድ ነው” ይላል፡፡ ሦስተኛ ወገን ማለት ደግሞ “በመድን [ውሉ] መሰረት ኃላፊነት ያስከተለ የተሽከርካሪ አደጋ በደረሰ ጊዜ ከመድን ገቢው፣ ከመድን ገቢው ቤተሰብ፣ ከአሽከርካሪው ወይም ከመድን ገቢው ተቀጣሪ ሰራተኛ በስተቀር የመድን [ውሉ] ተፈፃሚነት የሚመለከተው ማንኛውም ሌላ ሰው ነው” ይላል፡፡ በመሆኑም የተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን ማለት የተሽከርካሪ አደጋ የደረሰበት ሰው ሊያገኘው የሚገባ ካሳ ወይም የሕክምና ወጪ ሽፋን መሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡
የተሸከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን አስፈላጊነት
የተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን አዋጅ ቁጥር 799/2005 እንሊወጣ ያስፈለገበት አራት ምክንያቶች በመግቢያው ላይ የተጠቀሱ ሲሆን እነዚህም በተሽከርካሪ ምክንያት እየደረሰ ያለው አደጋ ከጊዜ ወደ ጊዜ በጣም እየጨመረ መምጣቱ፣ በተሽከርካሪ አደጋ ምክንያት የሚደርሰው የሰው ሞት፣ የአካል ጉዳትና የንብረት ኪሣራ ማህበራዊ ችግር እያስከተለ ያለ መሆኑ፣ የተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂዎች አስቸኳይ የህክምና አገልግሎት የሚያገኙበት ሥርዓት ማመቻቸት እና የተሽከርካሪ ባለንብረቶች የተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን ሽፋን እዲኖራቸው ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ናቸው፡፡
በአጠቃላይ መድን ወይም ኢንሹራንስ እጅግ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች አሉት፡፡ ከነዚህ ጠቀሜታዎቹ ውስጥ አንደኛው በአንድ ሰው ላይ የሚደርስን ፍትሐብሔራዊ ተጠያቂነትን፣ የንብረት ጉዳትን፣ በሞት ወይም የአካል ጉዳት ምክንያት የሚደርስን የኢኮኖሚያዊ ኪሳራን በካሳ መልክ የኢንሹራንስ ድርጅቱ ስለሚከፍለው በተቻለ መጠን ጉዳት አድራሽ ወይም ጉዳት የደረሰበት ሰው የከፋ ኪሳራና ምስቅልቅል ውስጥ እንዳይገቡ ያደርጋል፡፡
የሕጉ ተፈፃሚነት ወሰን
ህጉ ከብስክሌትና ከአካል ጉዳተኞች ተሽከርካሪ (ዊልቼር) በስተቀር በመንገድ ላይ በሚሄድ በኤሌክትሪክ ወይም በመካኒካ ኃይል በሚሰራ ባለሞተር ተሽከርካሪ፣ ግማሽ ተሳቢ ወይም ተሳቢ ላይ ሁሉ ተፈፃሚ እንደሚሆን ከአዋጁ አንቀጽ 2(5) እና ከአንቀፅ 3 ጣምራ ንባብ መረዳት ይቻላል፡፡ ይህም ማለት ከባጃጅ እንስቶ ቀላልና ከባድ ተሽከርካሪዎች ሁሉ ይህን የመድን የምስክር ወረቀት ሳይዙ መንቀሳቀስ አይችሉም። በአዋጁ አንቀጽ 3(1) ላይ እንደተገለፀው ማንኛውም ሰው ተሽከርካሪው በሦስተኛ ወገን ላይ ለሚያደርሰው አደጋ የፀና የመድን ሽፋን ሳይኖረው ተሽከርካሪውን በመንገድ ላይ መንዳት፣ መጠቀም ወይም ሌላ ሰው እንዲነዳ ወይም እንዲጠቀም ማድረግ ወይም መፍቀድ እንደማይችል ተደንግጎ እናገኛለን፡፡ የሦስተኛ ወገን የመድን ሽፋን ምስክር ወረቀት ካልያዙ ሽፋኑ እንደሌላቸው ተቆጥሮ ተሽከርካሪዎቹ በፖሊስ ተይዘው ይቆያሉ። ተሽከርካሪው የመድን ተለጣፊ ምልክት ከሌለው ወይም በወቅቱ የታደሰ ካልሆነ መድህን ለተሽከርካሪው የመግባት ግዴታ ያለበት ሰው አዋጁን እንደጣሰ ተቆጥሮ በሕግ እንደሚጠየቅ በአዋጁ አንቀጽ 13 ላይ ተደንግጓል። ለተሽከራካሪው የሦስተኛ ወገን መድን የመግባት ግዴታ ያለበት የተሽከርካሪው ባለቤት፣ ተሽከርካሪው ላይ በኪራይ ወይም በውክልና መብት አግኝቶ የሚጠቀም ሰው ወይም ሌሎች እንዲጠቀሙበት መፍቀድ የሚችል ማንኛውም ሰው ነው፡፡
የሦስተኛ ወገን የመድን ሽፋን የሚሸፍነው ጉዳት
በአዋጁ አንቀጽ 4(2) ላይ በተገለፀው መሠረት የሦስተኛ ወገን የመድን ሽፋን ፖሊሲ መድን የተገባለት ተሽከርካሪ ለሚያደርሰው የሰው ሞት፣ የአካል ጉዳትና የንብረት ኪሳራ መከፈል የሚገባውን ካሳና አስቸኳይ የህክምና አገልግሎት ወጪ የሚሸፍን ነው፡፡
ነገር ግን በመድን ገቢው ወይም ቤተሰብ (የትዳር ጓደኛ፣ ልጅ፣ አባት፣ እናት ወይም የሚያስተዳድረው ማንኛውም ሰው) ላይ የሚደርስ ሞት፣ የአካል ጉዳትና የንብረት ጉዳት፣ በመድን ገቢው ተቀጥሮ የሚሰራ ሰው በሥራው ላይ እያለ በሚደርስ የግጭት አደጋ ወይም የሞት ወይም የአካል ጉዳት ወይም የንብረት ጉዳት፣ መድን በተገባለት ተሽከርካሪ ላይ የሚደርስ አደጋ፣ መድን በተገባለት ተሽከርካሪ ላይ በኪራይ ወይም በክፍያ በሚጓጓዝ ንብረት ላይ ለሚደርስ ጉዳት ኃላፊነት እና ከኢትዮጵያ ግዛት ክልል ውጪ የደረሰ የተሽከርካሪ አደጋ ተከትሎ የመጣ ኃላፊነትን የማይሸፍን መሆኑን እና ካሳ እንደማይከፈለው ከአዋጁ አንቀጽ 7 እንረዳለን፡፡ በሌሎች ሕጎች ግን ጉዳት አድራሹን ወይም ተሽከርካሪው የመድህን ሽፋን ካለው መድህን የሰጠውን ኩባንያ ካሳ የመጠየቅ መብታቸው እንደተጠበቀ ነው።
የካሳው መጠን
በሀገራችን ኢትዮጵያ የተሽከርካሪ አደጋ በእጅጉ እየበዛ እና ከፍተኛ የሆነ ሞት፣ አካል ገዳት እና የንብረት ጉዳት እያስከተለ ይገኛል፡፡ ከአደጋው አስከፊነትና ከሰብአዊነት አንፃር የተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂዎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የሕክምና እርዳታ ማግኘት ይገባቸዋል፡፡ ሆኖም አንዳንድ ጊዜ ጉዳት አድራሹ በመሰወሩ ምክንያት ላይታወቅ የሚችልበት እድል ከመኖሩም በላይ ቢታወቅም እንኳን በወቅቱ ወጪውን ለመሸፈን የሚያስችል አቅም የሌለው የሚሆንባቸው አጋጣሚዎች በርካታ ናቸው፡፡ ይህም ተጎጂዎችን ለተጨማሪ ጉዳትና እንግልት ሊዳርግ ይችላል፡፡
ይህንን ችግር ለማቃለል የተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን ሽፋን አስገዳጅ በሆነ መልኩ በሕግ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ የተሸከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን አዋጅ ቁጥር 799/2005 በአሁኑ ሰዓት በሥራ ላይ የሚገኝ ሕግ ነው፡፡ በዚህ አጭር ፅሑፍ የሕጉን ይዘት እንዳስሳለን፡፡
የተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን ምንነት
መድን ወይም ኢንሹራንስ ስለሚለው ቃል ከተለያየ አቅጣጫ በማየት ትርጉም ሊሰጠው እንደሚችል የዘርፉ ምሁራን ይገልፃሉ፡፡ ከግለሰቦች መነሻ ነጥብ ተነስቶ የሚሰጠው ትርጉም የመጀመሪያው ሲሆን እሱም “አንድ ሰው በንብረቱ፣ በህይወቱ ወይም በአካሉ ላይ ባልተጠበቀ ሁኔታ ሊያጋጥም በሚችል አደጋ ምክንያት የሚደርስ በገንዘብ የሚለካ ጉዳትን ለኢንሹራንስ ድርጅት ማስተላለፊያ መንገድ ነው፡፡” ሁለተኛው መነሻ ነጥብ ከኢንሹራንስ ሰጪው ድርጅት በመነሳት ሲሆን “ኢንሹራንስ ሰጪው በአደጋ ምክንያት የሚያጋጥምን ኪሳራ ለተመሳሳይ አይነት አደጋ ተጋላጭ ለሆኑ ሰዎች የሚያከፋፍልበት መንገድ ወይም ዘዴ ነው፡፡”
በሀገራችንም በነባሩ የንግድ ሕግ አንቀጽ 654(1) ላይ “የኢንሹራስ ውል ፖሊሲ ማለት ኢንሹራንስ ሰጪ የሚባለው በአንድ ወይም በብዙ የተመደበውን የኢንሹራንስ መግቢያ ዋጋ (ፕርምየም) ተቀብሎ በውሉ የተመለከተው አደጋ በደረሰ ጊዜ ኢንሹራንስ ለገባው ሰው የተወሰነ ገንዘብ ለመክፈል ግዴታ የሚገባበት ነው፡፡” በማለት ትርጉሙን አስቀምጧል፡፡ ይህ የጠቅላላው የመድን ውል ትርጓሜ ሲሆን የተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድንን በተመለከተ ደግሞ በአዋጅ ቁጥር 799/2005 አንቀፅ 2(8) እና (10) ስር ከተሰጡት ትርጉሞች ተነስተን መረዳት እንችላለን፡፡ በዚህም መሰረት “የመድን [ውል] ማለት የመድን ገቢው ተሸከርካሪ በሦስተኛ ወገን ላይ ለሚያደርሰው የሞት አደጋ፣ የአካል ጉዳት ወይም የንብረት ኪሳራ ካሳ ለመክፈል እና የአስቸኳይ የሕክምና አገልግሎት ክፍያን ለመፈፀም መድን ሰጪው ውለታ የሚገባበት ሰነድ ነው” ይላል፡፡ ሦስተኛ ወገን ማለት ደግሞ “በመድን [ውሉ] መሰረት ኃላፊነት ያስከተለ የተሽከርካሪ አደጋ በደረሰ ጊዜ ከመድን ገቢው፣ ከመድን ገቢው ቤተሰብ፣ ከአሽከርካሪው ወይም ከመድን ገቢው ተቀጣሪ ሰራተኛ በስተቀር የመድን [ውሉ] ተፈፃሚነት የሚመለከተው ማንኛውም ሌላ ሰው ነው” ይላል፡፡ በመሆኑም የተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን ማለት የተሽከርካሪ አደጋ የደረሰበት ሰው ሊያገኘው የሚገባ ካሳ ወይም የሕክምና ወጪ ሽፋን መሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡
የተሸከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን አስፈላጊነት
የተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን አዋጅ ቁጥር 799/2005 እንሊወጣ ያስፈለገበት አራት ምክንያቶች በመግቢያው ላይ የተጠቀሱ ሲሆን እነዚህም በተሽከርካሪ ምክንያት እየደረሰ ያለው አደጋ ከጊዜ ወደ ጊዜ በጣም እየጨመረ መምጣቱ፣ በተሽከርካሪ አደጋ ምክንያት የሚደርሰው የሰው ሞት፣ የአካል ጉዳትና የንብረት ኪሣራ ማህበራዊ ችግር እያስከተለ ያለ መሆኑ፣ የተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂዎች አስቸኳይ የህክምና አገልግሎት የሚያገኙበት ሥርዓት ማመቻቸት እና የተሽከርካሪ ባለንብረቶች የተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን ሽፋን እዲኖራቸው ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ናቸው፡፡
በአጠቃላይ መድን ወይም ኢንሹራንስ እጅግ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች አሉት፡፡ ከነዚህ ጠቀሜታዎቹ ውስጥ አንደኛው በአንድ ሰው ላይ የሚደርስን ፍትሐብሔራዊ ተጠያቂነትን፣ የንብረት ጉዳትን፣ በሞት ወይም የአካል ጉዳት ምክንያት የሚደርስን የኢኮኖሚያዊ ኪሳራን በካሳ መልክ የኢንሹራንስ ድርጅቱ ስለሚከፍለው በተቻለ መጠን ጉዳት አድራሽ ወይም ጉዳት የደረሰበት ሰው የከፋ ኪሳራና ምስቅልቅል ውስጥ እንዳይገቡ ያደርጋል፡፡
የሕጉ ተፈፃሚነት ወሰን
ህጉ ከብስክሌትና ከአካል ጉዳተኞች ተሽከርካሪ (ዊልቼር) በስተቀር በመንገድ ላይ በሚሄድ በኤሌክትሪክ ወይም በመካኒካ ኃይል በሚሰራ ባለሞተር ተሽከርካሪ፣ ግማሽ ተሳቢ ወይም ተሳቢ ላይ ሁሉ ተፈፃሚ እንደሚሆን ከአዋጁ አንቀጽ 2(5) እና ከአንቀፅ 3 ጣምራ ንባብ መረዳት ይቻላል፡፡ ይህም ማለት ከባጃጅ እንስቶ ቀላልና ከባድ ተሽከርካሪዎች ሁሉ ይህን የመድን የምስክር ወረቀት ሳይዙ መንቀሳቀስ አይችሉም። በአዋጁ አንቀጽ 3(1) ላይ እንደተገለፀው ማንኛውም ሰው ተሽከርካሪው በሦስተኛ ወገን ላይ ለሚያደርሰው አደጋ የፀና የመድን ሽፋን ሳይኖረው ተሽከርካሪውን በመንገድ ላይ መንዳት፣ መጠቀም ወይም ሌላ ሰው እንዲነዳ ወይም እንዲጠቀም ማድረግ ወይም መፍቀድ እንደማይችል ተደንግጎ እናገኛለን፡፡ የሦስተኛ ወገን የመድን ሽፋን ምስክር ወረቀት ካልያዙ ሽፋኑ እንደሌላቸው ተቆጥሮ ተሽከርካሪዎቹ በፖሊስ ተይዘው ይቆያሉ። ተሽከርካሪው የመድን ተለጣፊ ምልክት ከሌለው ወይም በወቅቱ የታደሰ ካልሆነ መድህን ለተሽከርካሪው የመግባት ግዴታ ያለበት ሰው አዋጁን እንደጣሰ ተቆጥሮ በሕግ እንደሚጠየቅ በአዋጁ አንቀጽ 13 ላይ ተደንግጓል። ለተሽከራካሪው የሦስተኛ ወገን መድን የመግባት ግዴታ ያለበት የተሽከርካሪው ባለቤት፣ ተሽከርካሪው ላይ በኪራይ ወይም በውክልና መብት አግኝቶ የሚጠቀም ሰው ወይም ሌሎች እንዲጠቀሙበት መፍቀድ የሚችል ማንኛውም ሰው ነው፡፡
የሦስተኛ ወገን የመድን ሽፋን የሚሸፍነው ጉዳት
በአዋጁ አንቀጽ 4(2) ላይ በተገለፀው መሠረት የሦስተኛ ወገን የመድን ሽፋን ፖሊሲ መድን የተገባለት ተሽከርካሪ ለሚያደርሰው የሰው ሞት፣ የአካል ጉዳትና የንብረት ኪሳራ መከፈል የሚገባውን ካሳና አስቸኳይ የህክምና አገልግሎት ወጪ የሚሸፍን ነው፡፡
ነገር ግን በመድን ገቢው ወይም ቤተሰብ (የትዳር ጓደኛ፣ ልጅ፣ አባት፣ እናት ወይም የሚያስተዳድረው ማንኛውም ሰው) ላይ የሚደርስ ሞት፣ የአካል ጉዳትና የንብረት ጉዳት፣ በመድን ገቢው ተቀጥሮ የሚሰራ ሰው በሥራው ላይ እያለ በሚደርስ የግጭት አደጋ ወይም የሞት ወይም የአካል ጉዳት ወይም የንብረት ጉዳት፣ መድን በተገባለት ተሽከርካሪ ላይ የሚደርስ አደጋ፣ መድን በተገባለት ተሽከርካሪ ላይ በኪራይ ወይም በክፍያ በሚጓጓዝ ንብረት ላይ ለሚደርስ ጉዳት ኃላፊነት እና ከኢትዮጵያ ግዛት ክልል ውጪ የደረሰ የተሽከርካሪ አደጋ ተከትሎ የመጣ ኃላፊነትን የማይሸፍን መሆኑን እና ካሳ እንደማይከፈለው ከአዋጁ አንቀጽ 7 እንረዳለን፡፡ በሌሎች ሕጎች ግን ጉዳት አድራሹን ወይም ተሽከርካሪው የመድህን ሽፋን ካለው መድህን የሰጠውን ኩባንያ ካሳ የመጠየቅ መብታቸው እንደተጠበቀ ነው።
የካሳው መጠን
በአዋጁ አንቀጽ 16 መሰረት በሦስተኛ ወገን የተሽከርካሪ መድን ፖሊሲ ለደረሰ ጉዳት የሚሸፍነው የካሳ መጠን የሞት አደጋ ከብር 5 ሺ ያላነሰና ብር 40 ሺ ያልበለጠ የገንዘብ ካሳ፣ በአንድ ሰው ላይ ለሚደርስ ለአካል ጉዳት ከብር 40 ሺ ያልበለጠ የገንዘብ ካሳ እንዲሁም በንብረት ላይ ለሚደርስ ጉዳት ወይም ኪሳራ ከብር 100 ሺ ያልበለጠ የገንዘብ ካሳ የሚከፈል ይሆናል፡፡ ነገር ግን በዚህ ሕግ ከተቀመጠው የገንዘብ መጠን በላይ ጉዳት የደረሰበት ሰው ጉዳት አድራሹን ወይም በሕግ ኃላፊነት ያለበትን ሰው በፍ/ቤት ተገቢነት ባለው ሌላ ሕግ መሠረት ከሶ ካሳ መጠየቅ ይችላል፡፡
በሦስተኛ ወገን የተሽከርካሪ የመድን ዋስትና የአሽከርካሪውን እድሜ፣ የአካል ወይም የአእምሮ ሁኔታ፣ የተሽከርካሪውን ሁኔታ፣ የፈረስ ጉልበት ወይም የሲሊንደር ችሎታ ወይም ዋጋ፣ የሚይዘው ሰው ብዛት፣ የሚጭነውን እቃ ክብደት፣ አካላዊ ባህሪ ወይም ልዩ መሳሪያ፣ ተሽከርካሪው አገልግሎት ላይ የሚውልበትን ጊዜ ወይም አካባቢ ካሳ እንዳይከፈል ገደብ ሊያስደርጉ አይችሉም።
እንዲሁም እንደ ሌሎች የመድን ዋስትናዎች በመድን ውሉ በተስማማነው መሠረት አይደለም በሚል የመድን ኩባንያው ወይም ሌላ አካል ካሳው እንዳይከፈል መቃወም ወይም መከልከል አይችልም። የመድን ፈንድ ኤጀንሲው ጉዳት አድራሹ ተሽከርካሪ ካልታወቀ ወይም የመድህን ሽፋን ከሌለው በተሽከርካሪው ለደረሰ የሞት ወይም የአካል ጉዳት ከላይ የጠቀስነውን የካሳ መጠን ይከፍላል። የአስቸኳይ ህክምና ወጪንም ይሸፍናል፡፡
አስቸኳይ የህክምና እርዳታ
ማንኛውም ሰው በተሽከርካሪ አደጋ ጉዳት ከደረሰበት ከአደጋው ቦታ፣ ወደ ህክምና በሚጓጓዝበት ወቅትና በድንገተኛ ክፍል እስከ ብር 2 ሺህ አስቸኳይ የህክምና እርዳታ የማግኘት መብት አለው፡፡ ማንኛውም የጤና ተቋም ይህን አስቸኳይ የህክምና እርዳታ ክፍያ ሳይጠይቅ የመስጠት ግዴታ አለበት። ክፍያውን አገልግሎቱን ከሰጠ በኋላ ከመድን ኩባንያው ወይም ከመድህን ፈንድ ኤጀንሲው የሚጠይቅ መሆኑን በአዋጁ አንቀጽ 27(3) እና (4) ላይ ተገልጿል።
የመድን ምስክር ወረቀት እና ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ
የመድን ምስክር ወረቀት ማለት የተሽከርካሪው ባለንብረት ወይም ህጋዊ ግዴታ ያለበት ሰው ተሸከርካሪው በሦስተኛ ወገን ላይ ለሚያደርሰው አደጋ በአዋጁ መሠረት መድን የገባለት መሆኑን የሚያረጋግጥ ሰነድ ነው፡፡ መድን ሰጪ ድርጅት ከመድን ገቢው ጋር የመድን ሽፋን ለመስጠት ከተስማሙ የመድን ፖሊሲውን (የመድን ስምምነት ውላቸውን) ለመድን ገቢው ይሰጠዋል፡፡ ከመድን ፖሊሲው በተጨማሪ በአዋጁ አንቀጽ 9(1) እና 12(1) ላይ እንደተገለፀው የመድን ምስክር ወረቀት እና የመድን ተለጣፊ ምልክት ለመድን ገቢው አብሮ መስጠት እንዳለበት ሕጉ በመድን ድርጅቱ ላይ ግዴታ ጥሎበታል፡፡
ይህ በአዋጁ አንቀጽ 9 መሠረት የተሰጠ የመድን ምስክር ወረቀት ከተሰጠበት ቀን አንስቶ ከአንድ ዓመት ላላነሰ ጊዜ የሚፀና ነው፡፡ የመድን ሽፋን ውሉ ሲቋረጥ ወይም የውል ዘመኑ ሲያልቅ መድን ገቢው የመድን ምስክር ወረቀቱንና የመድን ተለጣፊውን ወዲያውኑ ለመድን ሰጪው ድርጅት መመለስ አለበት፡፡
የመድን ፈንድ
የመድን ፈንድ ማለት ቋሚ የፋይናንስ ምንጭ ሆኖ በኢትዮጲያ ብሔራዊ ባንክ በሚከፈት ልዩ የባንክ ሂሳብ ውስጥ ተቀማጭ እንዲሆን በአዋጁ የተቋቋመ ቋሚ የገንዘብ ምንጭ ነው፡፡ የፈንዱ የገንዘብ ምንጭ ከፈንዱ ተመን የሚሰበሰብ እና በሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚወሰን ሌላ ተጨማሪ ገቢ ነው፡፡ ይህን ፈንድ የሚስተዳደረው በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ በተቋቋመው የመድን ፈንድ አስተዳደር ኤጀንሲ ሲሆን የፌደራል መንግስት የአስፈፃሚ አካላት ስልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 1263/2014 ስያሜው የመንገድ ደህንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት በሚል ተቀይሯል፡፡
የፈንዱ ዓላማ መድን ባልተገባለት ወይም ባልታወቀ ተሽከርካሪ አደጋ ምክንያት ጉዳት የደረሰበት ሰው አስቸኳይ የህክምና አገልግሎት እንዲያገኝ ማድረግ፣ የአካል ጉዳት ለደረሰበት ሰው ካሳ እንዲከፈለው ማድረግ እና ለሞተ ሰው ቤተሰብ አባላት ካሳ እንዲከፈል ማድረግ ነው፡፡ በአዋጁ አንቀጽ 20(2) ላይ እንደተገለፀው ከፈንዱ ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች የሚከፍለው የካሳ ክፍያ መጠን መድን የተገባለት ተሽከርካሪ አደጋ ባደረሰ ጊዜ በሚከፈለው የካሳ መጠን ልክ እንደሆነ ተደንግጓል፡፡
የመድን ፈንድ አገልግሎቱ ጉዳት ለደረሰባቸው አካላት በሕጉ የተቀመጠውን የጉዳት ካሳ መጠን ከከፈለ በኋላ ይህን የከፈለውን ክፍያ ለጉዳቱ በኃላፊነት ተጠያቂ ከሆነው ሰው ላይ የማስመለስ መብት እንዳለው በአዋጁ አንቀጽ 20(3) ተደንግጎል፡፡
ተጠያቂነት
የተሽከርካሪ የሶስተኛ ወገን ህግን አለማክበር የማስተካከያ አስተዳደራዊ እርምጃዎችን ከማስከተሉም በተጨማሪ ክልከላዎችን ተላልፎ መገኘት ከብር 3 ሺ እስ ብር 5 ሺ በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ወይም ከ1 አመት እስከ 2 አመት በሚደርስ እስራት እንደሚያስቀጣ በአዋጁ አንቀፅ 30 ተደንግጓል፡፡
የተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን ህግ አደጋ የደረሰባቸው ሰዎች ከደረሰባቸው ችግር በተወሰነ መልኩ እንዲቋቋሙ እና አስቸኳይ የህክምና እርዳታ እንዲያገኙ ለማስቻል ተግባራዊ የተደረገ ህግ ነው፡፡ ስለሆነም ሕብረተሰቡም የተሽከርካሪ አደጋ እንዳይደርስ ቅድመ ጥንቃቄ ማድረጉ እንደተጠበቀ ሆኖ አደጋ ከደረሰ ግን በጠቀስናቸው መብቶች መጠቀም የሚችል መሆኑን መገንዘብ እንዳለበት መጠቆም እንወዳለን፡፡
በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
https://t.me/lawsocieties
@lawsocieties
በሦስተኛ ወገን የተሽከርካሪ የመድን ዋስትና የአሽከርካሪውን እድሜ፣ የአካል ወይም የአእምሮ ሁኔታ፣ የተሽከርካሪውን ሁኔታ፣ የፈረስ ጉልበት ወይም የሲሊንደር ችሎታ ወይም ዋጋ፣ የሚይዘው ሰው ብዛት፣ የሚጭነውን እቃ ክብደት፣ አካላዊ ባህሪ ወይም ልዩ መሳሪያ፣ ተሽከርካሪው አገልግሎት ላይ የሚውልበትን ጊዜ ወይም አካባቢ ካሳ እንዳይከፈል ገደብ ሊያስደርጉ አይችሉም።
እንዲሁም እንደ ሌሎች የመድን ዋስትናዎች በመድን ውሉ በተስማማነው መሠረት አይደለም በሚል የመድን ኩባንያው ወይም ሌላ አካል ካሳው እንዳይከፈል መቃወም ወይም መከልከል አይችልም። የመድን ፈንድ ኤጀንሲው ጉዳት አድራሹ ተሽከርካሪ ካልታወቀ ወይም የመድህን ሽፋን ከሌለው በተሽከርካሪው ለደረሰ የሞት ወይም የአካል ጉዳት ከላይ የጠቀስነውን የካሳ መጠን ይከፍላል። የአስቸኳይ ህክምና ወጪንም ይሸፍናል፡፡
አስቸኳይ የህክምና እርዳታ
ማንኛውም ሰው በተሽከርካሪ አደጋ ጉዳት ከደረሰበት ከአደጋው ቦታ፣ ወደ ህክምና በሚጓጓዝበት ወቅትና በድንገተኛ ክፍል እስከ ብር 2 ሺህ አስቸኳይ የህክምና እርዳታ የማግኘት መብት አለው፡፡ ማንኛውም የጤና ተቋም ይህን አስቸኳይ የህክምና እርዳታ ክፍያ ሳይጠይቅ የመስጠት ግዴታ አለበት። ክፍያውን አገልግሎቱን ከሰጠ በኋላ ከመድን ኩባንያው ወይም ከመድህን ፈንድ ኤጀንሲው የሚጠይቅ መሆኑን በአዋጁ አንቀጽ 27(3) እና (4) ላይ ተገልጿል።
የመድን ምስክር ወረቀት እና ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ
የመድን ምስክር ወረቀት ማለት የተሽከርካሪው ባለንብረት ወይም ህጋዊ ግዴታ ያለበት ሰው ተሸከርካሪው በሦስተኛ ወገን ላይ ለሚያደርሰው አደጋ በአዋጁ መሠረት መድን የገባለት መሆኑን የሚያረጋግጥ ሰነድ ነው፡፡ መድን ሰጪ ድርጅት ከመድን ገቢው ጋር የመድን ሽፋን ለመስጠት ከተስማሙ የመድን ፖሊሲውን (የመድን ስምምነት ውላቸውን) ለመድን ገቢው ይሰጠዋል፡፡ ከመድን ፖሊሲው በተጨማሪ በአዋጁ አንቀጽ 9(1) እና 12(1) ላይ እንደተገለፀው የመድን ምስክር ወረቀት እና የመድን ተለጣፊ ምልክት ለመድን ገቢው አብሮ መስጠት እንዳለበት ሕጉ በመድን ድርጅቱ ላይ ግዴታ ጥሎበታል፡፡
ይህ በአዋጁ አንቀጽ 9 መሠረት የተሰጠ የመድን ምስክር ወረቀት ከተሰጠበት ቀን አንስቶ ከአንድ ዓመት ላላነሰ ጊዜ የሚፀና ነው፡፡ የመድን ሽፋን ውሉ ሲቋረጥ ወይም የውል ዘመኑ ሲያልቅ መድን ገቢው የመድን ምስክር ወረቀቱንና የመድን ተለጣፊውን ወዲያውኑ ለመድን ሰጪው ድርጅት መመለስ አለበት፡፡
የመድን ፈንድ
የመድን ፈንድ ማለት ቋሚ የፋይናንስ ምንጭ ሆኖ በኢትዮጲያ ብሔራዊ ባንክ በሚከፈት ልዩ የባንክ ሂሳብ ውስጥ ተቀማጭ እንዲሆን በአዋጁ የተቋቋመ ቋሚ የገንዘብ ምንጭ ነው፡፡ የፈንዱ የገንዘብ ምንጭ ከፈንዱ ተመን የሚሰበሰብ እና በሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚወሰን ሌላ ተጨማሪ ገቢ ነው፡፡ ይህን ፈንድ የሚስተዳደረው በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ በተቋቋመው የመድን ፈንድ አስተዳደር ኤጀንሲ ሲሆን የፌደራል መንግስት የአስፈፃሚ አካላት ስልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 1263/2014 ስያሜው የመንገድ ደህንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት በሚል ተቀይሯል፡፡
የፈንዱ ዓላማ መድን ባልተገባለት ወይም ባልታወቀ ተሽከርካሪ አደጋ ምክንያት ጉዳት የደረሰበት ሰው አስቸኳይ የህክምና አገልግሎት እንዲያገኝ ማድረግ፣ የአካል ጉዳት ለደረሰበት ሰው ካሳ እንዲከፈለው ማድረግ እና ለሞተ ሰው ቤተሰብ አባላት ካሳ እንዲከፈል ማድረግ ነው፡፡ በአዋጁ አንቀጽ 20(2) ላይ እንደተገለፀው ከፈንዱ ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች የሚከፍለው የካሳ ክፍያ መጠን መድን የተገባለት ተሽከርካሪ አደጋ ባደረሰ ጊዜ በሚከፈለው የካሳ መጠን ልክ እንደሆነ ተደንግጓል፡፡
የመድን ፈንድ አገልግሎቱ ጉዳት ለደረሰባቸው አካላት በሕጉ የተቀመጠውን የጉዳት ካሳ መጠን ከከፈለ በኋላ ይህን የከፈለውን ክፍያ ለጉዳቱ በኃላፊነት ተጠያቂ ከሆነው ሰው ላይ የማስመለስ መብት እንዳለው በአዋጁ አንቀጽ 20(3) ተደንግጎል፡፡
ተጠያቂነት
የተሽከርካሪ የሶስተኛ ወገን ህግን አለማክበር የማስተካከያ አስተዳደራዊ እርምጃዎችን ከማስከተሉም በተጨማሪ ክልከላዎችን ተላልፎ መገኘት ከብር 3 ሺ እስ ብር 5 ሺ በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ወይም ከ1 አመት እስከ 2 አመት በሚደርስ እስራት እንደሚያስቀጣ በአዋጁ አንቀፅ 30 ተደንግጓል፡፡
የተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን ህግ አደጋ የደረሰባቸው ሰዎች ከደረሰባቸው ችግር በተወሰነ መልኩ እንዲቋቋሙ እና አስቸኳይ የህክምና እርዳታ እንዲያገኙ ለማስቻል ተግባራዊ የተደረገ ህግ ነው፡፡ ስለሆነም ሕብረተሰቡም የተሽከርካሪ አደጋ እንዳይደርስ ቅድመ ጥንቃቄ ማድረጉ እንደተጠበቀ ሆኖ አደጋ ከደረሰ ግን በጠቀስናቸው መብቶች መጠቀም የሚችል መሆኑን መገንዘብ እንዳለበት መጠቆም እንወዳለን፡፡
በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
https://t.me/lawsocieties
@lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
በቅርቡ ለምንጀምረው አለ ህግ የህግ ጉዳዮች ዩቱብ ቻናል ፕሮግራም ሰብስክራብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ፣
ሼር በማድረግ አድርሱልን።
subscribe our channel
Share
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://youtube.com/@Lawsocieties
ሼር በማድረግ አድርሱልን።
subscribe our channel
Share
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://youtube.com/@Lawsocieties
በቅርቡ አለ ህግ የተሰኘው ፕሮግራም ይጀምራል ሼር እና ሰብስክራብ አድርጉልን።
ሼር በማድረግ አድርሱልን።
#subscribe our YouTube channel
and #Share
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://youtube.com/@Lawsocieties
ሼር በማድረግ አድርሱልን።
#subscribe our YouTube channel
and #Share
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://youtube.com/@Lawsocieties
Forwarded from ሕግ ቤት
Law LLB EE 2015 Result 43.xlsx
11.9 KB
Wolkite university Law LLB Exit Exam Result
ብንዘገይም አልቀረንም #አለ_ህግ የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራብ እና ሼር አድርጉልን በቅርቡ ለሚጀመረው አለ_ህግ ለተሰኘው ፕሮግራም አባል ይሁኑ።
https://youtube.com/@Lawsocieties
subscribe and share Ale_Hig YouTube channel.
Coming soon 🔜🔜🔜🔜🔜
https://youtube.com/@Lawsocieties
https://youtube.com/@Lawsocieties
https://youtube.com/@Lawsocieties
subscribe and share Ale_Hig YouTube channel.
Coming soon 🔜🔜🔜🔜🔜
https://youtube.com/@Lawsocieties
https://youtube.com/@Lawsocieties
አንድ ለአካለ መጠን ያልደረሰ ልጅ የወራሽነት መብቱን ለአካለ መጠን ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ እስከ 15 አመት ባለው ጊዜ ውስጥ ቢጠይቅ በይርጋ ሊታገድ አይገባም፡፡
የፌ.ጠ.ፍ.ሰ.ሰ.ችሎት ቅፅ 20 በመ/ቁ 120841
የፌ.ጠ.ፍ.ሰ.ሰ.ችሎት ቅፅ 20 በመ/ቁ 120841
የፍትሐብሔር ክርክር ሂደት.pdf
694 KB
የፍትሐብሔር ክርክር ሂደት፡- ከክስ አቀራረብ እስከ ፍርድ አሰጣጥ
በዚህ ጽሑፍ የተብራሩ የፍትሐብሔር ክርክር ሂደት ደረጃዎች፡-
👉 የክስ ማመልከቻን መመርመር
👉 ለተከሳሽ መጥሪያ መላክ
👉 የመከላከያ መልስን መመርመር
👉 የጽሑፍ ማስረጃ ስለሚቀርብበት ጊዜና ሁኔታ
👉 የጽሑፍ ክርክር የማቀባበል ሥራን ማጠናቀቅ
👉 ክስን መስማት
👉 የሦስተኛ ወገኖች ጣልቃ ገብነት ወይም ክስ ውስጥ መግባት
👉 ተከራካሪዎችን መመርመር
👉 በመጀመሪያ ደረጃ ክርክር ላይ የሚቀርቡ መቃወሚያዎች
👉 የክርክሩን ጭብጥ መያዝ
👉 ለምስክሮች መጥሪያ መላክ
👉 ምስክሮችን መመርመር
👉 ፍርድ
#EsubalewAmareLawOffice
በዚህ ጽሑፍ የተብራሩ የፍትሐብሔር ክርክር ሂደት ደረጃዎች፡-
👉 የክስ ማመልከቻን መመርመር
👉 ለተከሳሽ መጥሪያ መላክ
👉 የመከላከያ መልስን መመርመር
👉 የጽሑፍ ማስረጃ ስለሚቀርብበት ጊዜና ሁኔታ
👉 የጽሑፍ ክርክር የማቀባበል ሥራን ማጠናቀቅ
👉 ክስን መስማት
👉 የሦስተኛ ወገኖች ጣልቃ ገብነት ወይም ክስ ውስጥ መግባት
👉 ተከራካሪዎችን መመርመር
👉 በመጀመሪያ ደረጃ ክርክር ላይ የሚቀርቡ መቃወሚያዎች
👉 የክርክሩን ጭብጥ መያዝ
👉 ለምስክሮች መጥሪያ መላክ
👉 ምስክሮችን መመርመር
👉 ፍርድ
#EsubalewAmareLawOffice
#ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ( PLC) እና የአክሲዮን ማህበር ተመሳሳይነትና ልዩነት
በኢትዮጵያ ንግድ ህግ ዉስጥ ካሉት የንግድ ማህበራት መካከል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ( PLC ) እና የአክሲዮን ማህበር ይገኙበታል ።
ሁለቱም ማህበራት አክሲዮን ያላቸዉ ወይም ካምፓኒዎች ሲሆኑ ተመሳሳይነትና ልዩነት አላቸዉ።
#ተመሳሳይነታቸዉ
• ህጋዊ ሰዉነት ያላቸዉ መሆኑ ፣
• የራሳቸዉ ንብረት ያላቸዉ መሆኑ፣
• የራሳቸዉን ትርፍና ኪሳራ ተጠያቂነት ያለባቸዉ መሆኑ፣
• ሁለቱም ትንሹ የአባላት ብዛትና የመነሻ ካፒታል ያላቸዉ መሆኑ፣
• ሁለቱም በቦርድና በማናጀር መመራት የሚችሉ መሆኑ ነገር ግን ለ PLC አሰገዳጅ አለመሆኑ፣
• የሁለቱም ተጠያቂ በተዋጣዉ የገንዘብ መጠን (አክሲዮን ) መሆኑ ፣
• ሁለቱም የሙያ መዋጮን የማይቀበሉ መሆኑን (የንግድ ህግ 256 እና 501 )
• በሁለቱም ካፒታል ማሳደግና መቀነስ የሚቻል መሆኑ ፣
• በሁለቱም አክሲዮኖች በመያዣ /በዋስትና / መያዝ ሚችሉ መሆኑ ፣
#ልዩነታቸዉ
አንድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር / PLC/ private Limited Company/ ለማቋቋም የአባላት ብዛት ከሁለት ማነስ የማይችሉ መሆኑ እንዲሁም ከሀምሳ መብለጥ እንደማይችሉ በንግድ ህጉ አንቀጽ 495(4) ላይ ተገልጿል። የአክሲዮን ማህበርን ( share company ) በተመለከተ ለማቋቋም ከ5 አባላት ማነስ የማይችል ሲሆን ብዛት ግን ገደብ የሌለዉ መሆኑን በንግድ ህጉ አንቀጽ 248(3) ላይ ይገኛል።
• ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር መነሻ ካፒታል 15000 ሺህ ብርና ከዚያ በላይ ሲሆን የአንድ አክሲዮን ዋጋም በኢትዮጵያ ብር አንድ በመቶ ማነስ አይችልም (የንግድ ህግ ቁጥር (496)
• አክሲዮን ማህበር መነሻ ካፒታል 50000 ሺህ እና ከዚያ በላይ ሲሆን የአንድ አክሲዮን ዋጋ ከአንድ መቶ ብር በታች መሆን አይችልም (የንግድ ህግ ቁጥር 247)
• ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ካፒታሉ ሙሉ በሙሉ አስቀድሞ የተከፈለ ሲሆን የአክሲዮን ማህበር ግን ሙሉ በሙሉ አስቀድሞ የሚከፈል አይደለም ነገር ግን ከተፈረሙ አክሲዮኖች ቢያንስ 1/4 (25%) መከፈል አለበት የቀረዉ በሂደት የሚከፈል ይሆናል (የንግድ ህግ ቁጥር (495(1)
• ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የአክሲዮኖች ሽያጭ ለህዝብ ክፍት የሚደርግ አይደለም አንቀጽ 495(2) ነገር ግን አክሲዮን ማህበር ለህዝብ ክፍት የሚደረግ ነዉ (የንግድ ህግ ቁጥር248)
• ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ( PLC) ላይ አክሲዮን ማህበር ዉስጥ ያለ ሰዉ አክሲዮኑን ለሶስተኛ ሰዉ ማስተላለፍ አይችልም ምክንያቱም መተዳደሪያ ደንቡ ላይ አባላት ይህን እስካልፈቀዱ ድረስ በህጉ መሰረት sale freely transfrable አይደለም። ነገር ግን አክሲዮን ማህበር ላይ አክሲዮን ማስተላለፍን በተመለከተ አክሲዮን የገዛ ሰዉ አክሲየኑን ለሌላ አባል ላልሆነ ሰዉ በቀላሉ ማስተላለፍ ይችላል ። ስለዚህ አክሲዮን ማስተላለፍ ከተፈለገ በቀላሉ የአክሲዮን ማህበርን መምረጥ ያስፈልጋል ማለት ነዉ።
• አስተዳደራዊ አካል (ቦርድ) ን በተመለከተ አክሲዮን ማህበራት ሁሉ ከ3-12 ሰዉ የሚይዝ ቦርድ ኦፍ ዳይሬክተር ሲቋቋም ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ( plc) ዉስጥ ቦርድ የለም።
#የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ
#ethiolawtips
በኢትዮጵያ ንግድ ህግ ዉስጥ ካሉት የንግድ ማህበራት መካከል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ( PLC ) እና የአክሲዮን ማህበር ይገኙበታል ።
ሁለቱም ማህበራት አክሲዮን ያላቸዉ ወይም ካምፓኒዎች ሲሆኑ ተመሳሳይነትና ልዩነት አላቸዉ።
#ተመሳሳይነታቸዉ
• ህጋዊ ሰዉነት ያላቸዉ መሆኑ ፣
• የራሳቸዉ ንብረት ያላቸዉ መሆኑ፣
• የራሳቸዉን ትርፍና ኪሳራ ተጠያቂነት ያለባቸዉ መሆኑ፣
• ሁለቱም ትንሹ የአባላት ብዛትና የመነሻ ካፒታል ያላቸዉ መሆኑ፣
• ሁለቱም በቦርድና በማናጀር መመራት የሚችሉ መሆኑ ነገር ግን ለ PLC አሰገዳጅ አለመሆኑ፣
• የሁለቱም ተጠያቂ በተዋጣዉ የገንዘብ መጠን (አክሲዮን ) መሆኑ ፣
• ሁለቱም የሙያ መዋጮን የማይቀበሉ መሆኑን (የንግድ ህግ 256 እና 501 )
• በሁለቱም ካፒታል ማሳደግና መቀነስ የሚቻል መሆኑ ፣
• በሁለቱም አክሲዮኖች በመያዣ /በዋስትና / መያዝ ሚችሉ መሆኑ ፣
#ልዩነታቸዉ
አንድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር / PLC/ private Limited Company/ ለማቋቋም የአባላት ብዛት ከሁለት ማነስ የማይችሉ መሆኑ እንዲሁም ከሀምሳ መብለጥ እንደማይችሉ በንግድ ህጉ አንቀጽ 495(4) ላይ ተገልጿል። የአክሲዮን ማህበርን ( share company ) በተመለከተ ለማቋቋም ከ5 አባላት ማነስ የማይችል ሲሆን ብዛት ግን ገደብ የሌለዉ መሆኑን በንግድ ህጉ አንቀጽ 248(3) ላይ ይገኛል።
• ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር መነሻ ካፒታል 15000 ሺህ ብርና ከዚያ በላይ ሲሆን የአንድ አክሲዮን ዋጋም በኢትዮጵያ ብር አንድ በመቶ ማነስ አይችልም (የንግድ ህግ ቁጥር (496)
• አክሲዮን ማህበር መነሻ ካፒታል 50000 ሺህ እና ከዚያ በላይ ሲሆን የአንድ አክሲዮን ዋጋ ከአንድ መቶ ብር በታች መሆን አይችልም (የንግድ ህግ ቁጥር 247)
• ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ካፒታሉ ሙሉ በሙሉ አስቀድሞ የተከፈለ ሲሆን የአክሲዮን ማህበር ግን ሙሉ በሙሉ አስቀድሞ የሚከፈል አይደለም ነገር ግን ከተፈረሙ አክሲዮኖች ቢያንስ 1/4 (25%) መከፈል አለበት የቀረዉ በሂደት የሚከፈል ይሆናል (የንግድ ህግ ቁጥር (495(1)
• ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የአክሲዮኖች ሽያጭ ለህዝብ ክፍት የሚደርግ አይደለም አንቀጽ 495(2) ነገር ግን አክሲዮን ማህበር ለህዝብ ክፍት የሚደረግ ነዉ (የንግድ ህግ ቁጥር248)
• ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ( PLC) ላይ አክሲዮን ማህበር ዉስጥ ያለ ሰዉ አክሲዮኑን ለሶስተኛ ሰዉ ማስተላለፍ አይችልም ምክንያቱም መተዳደሪያ ደንቡ ላይ አባላት ይህን እስካልፈቀዱ ድረስ በህጉ መሰረት sale freely transfrable አይደለም። ነገር ግን አክሲዮን ማህበር ላይ አክሲዮን ማስተላለፍን በተመለከተ አክሲዮን የገዛ ሰዉ አክሲየኑን ለሌላ አባል ላልሆነ ሰዉ በቀላሉ ማስተላለፍ ይችላል ። ስለዚህ አክሲዮን ማስተላለፍ ከተፈለገ በቀላሉ የአክሲዮን ማህበርን መምረጥ ያስፈልጋል ማለት ነዉ።
• አስተዳደራዊ አካል (ቦርድ) ን በተመለከተ አክሲዮን ማህበራት ሁሉ ከ3-12 ሰዉ የሚይዝ ቦርድ ኦፍ ዳይሬክተር ሲቋቋም ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ( plc) ዉስጥ ቦርድ የለም።
#የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ
#ethiolawtips
Forwarded from 🇪🇹የሕግ ጉዳይ
የቤት ሽያጭ ዋጋ ታክስ ይፉ ሆነ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውስጥ ከዚህ ቀደም የቤት ግብይትን ዋጋ በተመለከተ ይቀርብ የነበረው የሽያጭ ውል ወቅቱን እና እውነታውን ያላገናዘበ እንዲሁም የመንግስትን ጥቅም የሚያሳጣ መሆኑ ይታወቃል፡፡
በመሆኑም ይህንን መነሻ በማድረግ የከተማ አስተዳደሩ የጥናት ቡድን በማቋቋም ወቅታዊ የቤት ሽያጭ ዋጋ አስጠንቶ ያጠናቀቀ ስለሆነ ይህንኑ ጥናት ከዚህ ቀደም ባለው መመሪያና አሰራር መሰረት ማለትም የካፒታል ክፍያን፣ የቴንብር ቀረጥ እና አሹራ ክፍያ ከጠቅላላ የቤቱ ዋጋ በፐርሰንት ተሰልቶ በጥናቱ መሰረት ይህ ደብዳቤ ወጪ ከሆነበት ቀን ሰኔ 8/2ዐ15 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንድታርጉ እያሳሰብን የተጠናውን ጥናት 3 ገፅ አባሪ ከዚህ መሽኛ ደብዳቤ ጋር ተልኳል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውስጥ ከዚህ ቀደም የቤት ግብይትን ዋጋ በተመለከተ ይቀርብ የነበረው የሽያጭ ውል ወቅቱን እና እውነታውን ያላገናዘበ እንዲሁም የመንግስትን ጥቅም የሚያሳጣ መሆኑ ይታወቃል፡፡
በመሆኑም ይህንን መነሻ በማድረግ የከተማ አስተዳደሩ የጥናት ቡድን በማቋቋም ወቅታዊ የቤት ሽያጭ ዋጋ አስጠንቶ ያጠናቀቀ ስለሆነ ይህንኑ ጥናት ከዚህ ቀደም ባለው መመሪያና አሰራር መሰረት ማለትም የካፒታል ክፍያን፣ የቴንብር ቀረጥ እና አሹራ ክፍያ ከጠቅላላ የቤቱ ዋጋ በፐርሰንት ተሰልቶ በጥናቱ መሰረት ይህ ደብዳቤ ወጪ ከሆነበት ቀን ሰኔ 8/2ዐ15 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንድታርጉ እያሳሰብን የተጠናውን ጥናት 3 ገፅ አባሪ ከዚህ መሽኛ ደብዳቤ ጋር ተልኳል።
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Lawyer Mike 🔊የህግ ባለሙያ)
ብንዘገይም አልቀረንም #አለ_ህግ የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራብ እና ሼር አድርጉልን በቅርቡ ለሚጀመረው አለ_ህግ ለተሰኘው ፕሮግራም አባል ይሁኑ።
https://youtube.com/@Lawsocieties
subscribe and share Ale_Hig YouTube channel.
Coming soon 🔜🔜🔜🔜🔜
https://youtube.com/@Lawsocieties
https://youtube.com/@Lawsocieties
https://youtube.com/@Lawsocieties
subscribe and share Ale_Hig YouTube channel.
Coming soon 🔜🔜🔜🔜🔜
https://youtube.com/@Lawsocieties
https://youtube.com/@Lawsocieties
ችሎታ (capacity) በህግ እይታ
ሰዎች በማህበራዊ መስተጋብር እርስ በርሳቸው በሚኖራቸው ግንኙነት ህጋዊ ተግባራትን ለመፈፀም፣ መብታቸውን ለማስከበር፣ ግዴታቸውን ለመወጣት እንዲሁም ህጋዊ ሀላፊነት ወይም ተጠያቂነትን ለመውሰድ ችሎታ ሊኖራቸው ይገባል።
በ1960 እ.ኢ.አ በወጣው የኢትዮጵያ ፍሐሀብሔር ህግ እንደተደነገገው ማንኛውም ሰው ችሎታ የሌለው መሆኑ በሕግ ተወስኖ ካልተገለፀ በቀር ማንኛውንም ዓይነት የማህበራዊ ኑሮውን ተግባር ለመፈፀም ችሎታ አለው። ይህም የሚያሳየው ህግ የሚወስደው ግምት ማንኛውም ሰው በመርህ ደረጃ ችሎታ እንዳለው ነው። በዚህ አጭር የንቃተ-ህግ ፅሁፍ የሰዎች ችሎታ ምንነት፣ የችሎታ ጠቀሜታ ወይም አስፈላጊነት እንዲሁም የሰዎች ችሎታ የማይኖርባቸውን ሁኔታዎች ከፍሐሀብሔር ህጉ አንፃር እንዳስሳለን።
የሰዎች ችሎታ ምንነት
የህግ መዝገበ ቃላት በሆነው መሪያም ዌብስተር እንደተሰጠው ትርጉም ህጋዊ ችሎታ ማለት አንድ ሰው በሕግ መሠረት አንድን የተወሰነ ሁኔታ ወይም ግንኙነት ከሌላው ጋር የማድረግ ወይም በአንድ የተወሰነ ሥራ ወይም ግብይት ላይ የመሳተፍ ችሎታ እና ኃይል ነው። በተጨማሪም ችሎታ ውሳኔ ለማድረግ መረጃን የመጠቀም እና የመረዳት ችሎታ እና ማንኛውንም ውሳኔ ማስተላለፍ አቅም ማለት ነው። አንድ ሰው አእምሮው ከተዳከመ ወይም በሆነ መንገድ ጤናው ከተጓደለ አቅም ይጎድለዋል። ይህም ማለት በዚያን ጊዜ ውሳኔ ማድረግ አይችልም ማለት ነው። የሕግ ችሎታ በሕጉ መሠረት በእኩልነት የመስተናገድ መሠረታዊ የሰብአዊ መብት አካል ነው። በመሆኑም ችሎታ ያለው ሰው በፍትሐብሔር ሥነ ስርዓት ህግ ቁጥር 33(1) መሰረት ፍትሐብሔር ክስ ማቅረብ የሚችል ሲሆን የፈፀመው የወንጀል ድርጊትም ካለ የወንጀል ህጉ መሰረት ሀላፊነት ይሆናል ማለት ነው።
• የችሎታ ጠቀሜታ ወይም አስፈላጊነት
ችሎታ ህጋዊ ግንኙነቶችን በራስ ለማከናወን ጠቀሜታ አለው። ለአብነት ያክል አንድ ሰው ውል በራሱ ለመዋዋል ለምሳሌ ሽያጭ ለመፈፀም ችሎታ ሊኖረው ይገባል። ይኸውም እድሜው በህግ በተወሰነው ልክ መሆን ያለበት እንዲሁም የአይምሮው የጤንነት ሁኔታ ጤነኛ መሆን ይኖርበታል። ያለበለዚያ ግን ህጉ በሚያስቀምጠው ሥርዓት ወይም በወኪል በኩል ህጋዊ ግንኙነቶችን ለመፈፀም ይገደዳል። እንዲሁም በወንጀል ጉዳይ የወንጀል ህግን መሰረት በማድረግ ተጠያቂነትን ወይም ተከሳሽነትን ለመወሰን ወይም ሀላፊ እና ኢ-ሀላፊን ለመለየት የአንድ ሰው ችሎታ መኖር ወይም አለመኖር ማወቅ አስፈላጊ ነው።
• ሰዎች ችሎታ የሚያጡበት ሁኔታ
በፍትሐብሄር ህግ ቁጥር 193 ስር እንደተደነገገው ጠቅላላ የችሎታ ማጣት ሁኔታ የሚያስከትሉ ምክንያቶች ዕድሜ ወይም የሰው አእምሮ ሁኔታ ወይም በተሰጠ የፍርድ ቅጣት ናቸው። በተጨማሪም የፍትሐብሔር ህጉ የተለየ የችሎታ ማጣት ሁኔታን የያዘ ሲሆን ይኸውም የተለየ ችሎታ ማጣትን ለመወሰን በግምት ውስጥ ለማስገባት የሚቻለው የሰውዬውን ዜግነት በመመልከት ወይም የሚያከናውነውን ሥራ መሰረት አድርጎ በመያዝ ነው። የችሎታ ማጣት አስረጂን በተመለከተ ሰው ሁሉ ችሎታ እንዳለው የሚገመት ሲሆን ይህ ሰው ችሎታ የሌለው ነው ብሎ ማስረዳት የሚገባው ሰውዬው ችሎታ የለውም ብሎ የሚከራከር ወገን ነው (የፍትሐብሔር ህግ ቁጥር 196)። ከተፈጥሮ ሰዎች በተጨማሪ የሰውነት መብት የተሰጣቸው ድርጅቶችና ለልዩ አገልግሎት የተመደቡ ንብረቶች ችሎታ ያላቸው መሆኑ የሚረጋገጠው እንደ አይነታቸው ለነዚሁ የሰውነት መብት በሚሰጧቸው ድንጋጌዎች መሰረት ነው። ችሎታ የሚያሳጡ ሁኔታዎችን እንደሚከተለው በዝርዝር እንመለከታለን።
• በእድሜ ምክንያት ችሎታ ማጣት (Minors)
በእድሜያቸው ምክንያት ችሎታ የሌላቸው ሰዎች ወይም አካለመጠን ስላልደረሱ ሰዎች ሁኔታ በፍትሐብሔር ህጉ የተደነገጉት ድንጋጌዎች የተሻሻለው የፌደራል የቤተሰብ ህግ ተፈፃሚ በሚሆንባቸው መስተዳድሮች ተፈፃሚ እንደማይሆን በቤተሰብ ህጉ አንቀፅ 319 ስር ተደንግጎ ይገኛል። በመሆኑም በቤተሰብ ህጉ አንቀፅ 215 ስር እንደተደነገገው በእድሜያቸው ምክንያት ችሎታ ያጡ ሰዎች ወይም አካለመጠን ያልደረሰ ሰውን በተመለከተ ትርጉም የሰጠ ሲሆን በትርጉሙ መሰረት አካለመጠን ያልደረሰ ሰው ማለት ፆታ ሳይለይ እድሜው አሥራ ስምንት ዓመት ያልሞላው ልጅ ነው። በእድሜው ምክንያት ችሎታ ያጣ አካለመጠን ያልደረሰ ሰው ህጋዊ ግንኙነቶቸን በራሱ ማከናወን ህጉ ስለማይፈቅድለት ስለመልካም አስተዳደጉና ደህንነቱ ጉዳይ በአሳዳሪው የሚጠበቅ ሲሆን ንብረት ነክ ጥቅሞቹንና በአጠቃላይ የንብረቱን አስተዳደር በሚመለከት በሞግዚት ይወከላል (የቤተሰብ ህግ አንቀፅ 216)። ስለአሳዳሪ እና ሞግዚት አስተዳደር በተሻሻለው የቤተሰብ ህግ ከአንቀፅ 215 እስከ 318 በዝርዝር ተደንግጎ ይገኛል።
• በአእምሮ ሁኔታ ችሎታ ማጣት
አዕምሮዋቸው ስለ ጎደለ ሰዎች፡- የፍትሐብሔር ህጉ ትርጉም የሰጠ ሲሆን አዕምሮው ጎደሎ ነው የሚባለው በተፈጥሮ ዕውቀቱ ያልተስተካከለ በመሆኑ ወይም በአእምሮ መናወጥ ወይም በእርጅና ምክንያት የሚሰራውን ሥራ የሚያደረሰውን ለማወቅ የማይችል ነው። የአእይምሮ ደካሞች ሰካራም ወይም በመጠጥ አፍዛዥ በሆኑ ነገሮች ልማድ የተመረዙና ገንዘብ ያለ አግባብ የሚያባክኑ ሰዎች አእምሮዋቸው እንደጎደለ ሰዎች ይቆጠራሉ (የፍ/ሕ/ቁ. 339)።
በግልፅ ስለታወቀ የአእምሮ ጉድለት ያለበት ሰው፡- የአእምሮ ጉድለት ያለበት ዕብደቱ በግልፅ እንደ ታወቀ ሰው ሆኖ በህግ የሚቆጠረው ይህ የተባለው ሰው በሆስፒታል ውስጥ ወይም በአንድ የአእምሮ ጉድለት ያለባቸው ሰዎች መኖሪያ ቦታ ውስጥ በአእምሮው ሁኔታ ምክንያት በአንድ የጤና ጥበቃ ቤት ውስጥ ተዘግቶበት በዚህ በተዘጋበት ቦታ እስከሚቆይበት ጊዜ ነው (የፍ/ሕ/ቁ. 341)። በግልፅ የታወቀ እብድ የሚሰራቸውን ሥራዎች በተመለከት እብደቱ ግልፅ በሆነበት ጊዜና ቦታ ላይ የሠራቸውን ሥራዎች እርሱ ወይም ወኪሎቹ ወይም ወራሾቹ ሊቃወሟቸው ይችላሉ (የፍ/ሕ/ቁ. 343)። ተቃራኒ የሚሆን አስረጂ ከሌለ በቀር የነዚህ ሰዎች ሥራና ፈቃድ የውለታን ፈራሽነት የሚያስከትል ጉድለት ያለበት ነው ተብሎ ይገመታል። እንዲሁም በስህተት መገኘት ምክንያት የሥራዎችና የውሎች መፍረስ የሚመለከቱት የፍትሐብሔር ህግ ደንቦች በተመሳሳይ ተፈፃሚዎች ይሆናሉ (የፍ/ሕ/ቁ. 344)። ይሁንና የአእምሮ ጉድለት ያለበት ሰው ከእርሱ ጋር የተደረጉት ውሎች በመፍረሳቸው ምክንያት በቅን ልቡና በተዋዋዮች ሦስተኛ ወገኖች ላይ ለሚደርሰው ጉዳት ሀላፊ ይሆናሉ። በሌላ በኩል ከውል ውጪ ሀላፊነትን በተመለከተ ለጤናማ ሰው እንዳለው ሀላፊነት የሚኖርበት ከመሆኑ በተጨማሪ ይህ የአእምሮ ጉድለት ያለበት ያለ አግባብ ካገኘው ብልፅግና የተነሳ ላሉት ግዴታዎች ጤናማ ለሆነ ሰው ያሉበት ግዴታዎች ይኖሩበታል (የፍ/ሕ/ቁ. 350)።
የአእምሮ ጉድለት ያለበቱ በግልፅ ስላልታወቀ ሰው፡- የአእምሮ ጉድለቱ በግልፅ ያልታወቀ ሰው የፈፀማቸው የህግ ሥራዎች ውሎች በዚሁ ሰው የአእምሮ ጉድለት ምክንያት ሊሻሩ አይችሉም። ሆኖም የአእምሮ ጉድለት ያለበት ሰው እነዚህን ውሎች በፈፀመበት ጊዜ ጉድለት የሌለበት ፈቃድ ለመስጠት በማይችልበት ሁኔታ እንደ ነበረ ለማስረዳት ከቻለ ውሎቹን ለማፍረስ ይችላል (የፍ/ሕ/ቁ.
ሰዎች በማህበራዊ መስተጋብር እርስ በርሳቸው በሚኖራቸው ግንኙነት ህጋዊ ተግባራትን ለመፈፀም፣ መብታቸውን ለማስከበር፣ ግዴታቸውን ለመወጣት እንዲሁም ህጋዊ ሀላፊነት ወይም ተጠያቂነትን ለመውሰድ ችሎታ ሊኖራቸው ይገባል።
በ1960 እ.ኢ.አ በወጣው የኢትዮጵያ ፍሐሀብሔር ህግ እንደተደነገገው ማንኛውም ሰው ችሎታ የሌለው መሆኑ በሕግ ተወስኖ ካልተገለፀ በቀር ማንኛውንም ዓይነት የማህበራዊ ኑሮውን ተግባር ለመፈፀም ችሎታ አለው። ይህም የሚያሳየው ህግ የሚወስደው ግምት ማንኛውም ሰው በመርህ ደረጃ ችሎታ እንዳለው ነው። በዚህ አጭር የንቃተ-ህግ ፅሁፍ የሰዎች ችሎታ ምንነት፣ የችሎታ ጠቀሜታ ወይም አስፈላጊነት እንዲሁም የሰዎች ችሎታ የማይኖርባቸውን ሁኔታዎች ከፍሐሀብሔር ህጉ አንፃር እንዳስሳለን።
የሰዎች ችሎታ ምንነት
የህግ መዝገበ ቃላት በሆነው መሪያም ዌብስተር እንደተሰጠው ትርጉም ህጋዊ ችሎታ ማለት አንድ ሰው በሕግ መሠረት አንድን የተወሰነ ሁኔታ ወይም ግንኙነት ከሌላው ጋር የማድረግ ወይም በአንድ የተወሰነ ሥራ ወይም ግብይት ላይ የመሳተፍ ችሎታ እና ኃይል ነው። በተጨማሪም ችሎታ ውሳኔ ለማድረግ መረጃን የመጠቀም እና የመረዳት ችሎታ እና ማንኛውንም ውሳኔ ማስተላለፍ አቅም ማለት ነው። አንድ ሰው አእምሮው ከተዳከመ ወይም በሆነ መንገድ ጤናው ከተጓደለ አቅም ይጎድለዋል። ይህም ማለት በዚያን ጊዜ ውሳኔ ማድረግ አይችልም ማለት ነው። የሕግ ችሎታ በሕጉ መሠረት በእኩልነት የመስተናገድ መሠረታዊ የሰብአዊ መብት አካል ነው። በመሆኑም ችሎታ ያለው ሰው በፍትሐብሔር ሥነ ስርዓት ህግ ቁጥር 33(1) መሰረት ፍትሐብሔር ክስ ማቅረብ የሚችል ሲሆን የፈፀመው የወንጀል ድርጊትም ካለ የወንጀል ህጉ መሰረት ሀላፊነት ይሆናል ማለት ነው።
• የችሎታ ጠቀሜታ ወይም አስፈላጊነት
ችሎታ ህጋዊ ግንኙነቶችን በራስ ለማከናወን ጠቀሜታ አለው። ለአብነት ያክል አንድ ሰው ውል በራሱ ለመዋዋል ለምሳሌ ሽያጭ ለመፈፀም ችሎታ ሊኖረው ይገባል። ይኸውም እድሜው በህግ በተወሰነው ልክ መሆን ያለበት እንዲሁም የአይምሮው የጤንነት ሁኔታ ጤነኛ መሆን ይኖርበታል። ያለበለዚያ ግን ህጉ በሚያስቀምጠው ሥርዓት ወይም በወኪል በኩል ህጋዊ ግንኙነቶችን ለመፈፀም ይገደዳል። እንዲሁም በወንጀል ጉዳይ የወንጀል ህግን መሰረት በማድረግ ተጠያቂነትን ወይም ተከሳሽነትን ለመወሰን ወይም ሀላፊ እና ኢ-ሀላፊን ለመለየት የአንድ ሰው ችሎታ መኖር ወይም አለመኖር ማወቅ አስፈላጊ ነው።
• ሰዎች ችሎታ የሚያጡበት ሁኔታ
በፍትሐብሄር ህግ ቁጥር 193 ስር እንደተደነገገው ጠቅላላ የችሎታ ማጣት ሁኔታ የሚያስከትሉ ምክንያቶች ዕድሜ ወይም የሰው አእምሮ ሁኔታ ወይም በተሰጠ የፍርድ ቅጣት ናቸው። በተጨማሪም የፍትሐብሔር ህጉ የተለየ የችሎታ ማጣት ሁኔታን የያዘ ሲሆን ይኸውም የተለየ ችሎታ ማጣትን ለመወሰን በግምት ውስጥ ለማስገባት የሚቻለው የሰውዬውን ዜግነት በመመልከት ወይም የሚያከናውነውን ሥራ መሰረት አድርጎ በመያዝ ነው። የችሎታ ማጣት አስረጂን በተመለከተ ሰው ሁሉ ችሎታ እንዳለው የሚገመት ሲሆን ይህ ሰው ችሎታ የሌለው ነው ብሎ ማስረዳት የሚገባው ሰውዬው ችሎታ የለውም ብሎ የሚከራከር ወገን ነው (የፍትሐብሔር ህግ ቁጥር 196)። ከተፈጥሮ ሰዎች በተጨማሪ የሰውነት መብት የተሰጣቸው ድርጅቶችና ለልዩ አገልግሎት የተመደቡ ንብረቶች ችሎታ ያላቸው መሆኑ የሚረጋገጠው እንደ አይነታቸው ለነዚሁ የሰውነት መብት በሚሰጧቸው ድንጋጌዎች መሰረት ነው። ችሎታ የሚያሳጡ ሁኔታዎችን እንደሚከተለው በዝርዝር እንመለከታለን።
• በእድሜ ምክንያት ችሎታ ማጣት (Minors)
በእድሜያቸው ምክንያት ችሎታ የሌላቸው ሰዎች ወይም አካለመጠን ስላልደረሱ ሰዎች ሁኔታ በፍትሐብሔር ህጉ የተደነገጉት ድንጋጌዎች የተሻሻለው የፌደራል የቤተሰብ ህግ ተፈፃሚ በሚሆንባቸው መስተዳድሮች ተፈፃሚ እንደማይሆን በቤተሰብ ህጉ አንቀፅ 319 ስር ተደንግጎ ይገኛል። በመሆኑም በቤተሰብ ህጉ አንቀፅ 215 ስር እንደተደነገገው በእድሜያቸው ምክንያት ችሎታ ያጡ ሰዎች ወይም አካለመጠን ያልደረሰ ሰውን በተመለከተ ትርጉም የሰጠ ሲሆን በትርጉሙ መሰረት አካለመጠን ያልደረሰ ሰው ማለት ፆታ ሳይለይ እድሜው አሥራ ስምንት ዓመት ያልሞላው ልጅ ነው። በእድሜው ምክንያት ችሎታ ያጣ አካለመጠን ያልደረሰ ሰው ህጋዊ ግንኙነቶቸን በራሱ ማከናወን ህጉ ስለማይፈቅድለት ስለመልካም አስተዳደጉና ደህንነቱ ጉዳይ በአሳዳሪው የሚጠበቅ ሲሆን ንብረት ነክ ጥቅሞቹንና በአጠቃላይ የንብረቱን አስተዳደር በሚመለከት በሞግዚት ይወከላል (የቤተሰብ ህግ አንቀፅ 216)። ስለአሳዳሪ እና ሞግዚት አስተዳደር በተሻሻለው የቤተሰብ ህግ ከአንቀፅ 215 እስከ 318 በዝርዝር ተደንግጎ ይገኛል።
• በአእምሮ ሁኔታ ችሎታ ማጣት
አዕምሮዋቸው ስለ ጎደለ ሰዎች፡- የፍትሐብሔር ህጉ ትርጉም የሰጠ ሲሆን አዕምሮው ጎደሎ ነው የሚባለው በተፈጥሮ ዕውቀቱ ያልተስተካከለ በመሆኑ ወይም በአእምሮ መናወጥ ወይም በእርጅና ምክንያት የሚሰራውን ሥራ የሚያደረሰውን ለማወቅ የማይችል ነው። የአእይምሮ ደካሞች ሰካራም ወይም በመጠጥ አፍዛዥ በሆኑ ነገሮች ልማድ የተመረዙና ገንዘብ ያለ አግባብ የሚያባክኑ ሰዎች አእምሮዋቸው እንደጎደለ ሰዎች ይቆጠራሉ (የፍ/ሕ/ቁ. 339)።
በግልፅ ስለታወቀ የአእምሮ ጉድለት ያለበት ሰው፡- የአእምሮ ጉድለት ያለበት ዕብደቱ በግልፅ እንደ ታወቀ ሰው ሆኖ በህግ የሚቆጠረው ይህ የተባለው ሰው በሆስፒታል ውስጥ ወይም በአንድ የአእምሮ ጉድለት ያለባቸው ሰዎች መኖሪያ ቦታ ውስጥ በአእምሮው ሁኔታ ምክንያት በአንድ የጤና ጥበቃ ቤት ውስጥ ተዘግቶበት በዚህ በተዘጋበት ቦታ እስከሚቆይበት ጊዜ ነው (የፍ/ሕ/ቁ. 341)። በግልፅ የታወቀ እብድ የሚሰራቸውን ሥራዎች በተመለከት እብደቱ ግልፅ በሆነበት ጊዜና ቦታ ላይ የሠራቸውን ሥራዎች እርሱ ወይም ወኪሎቹ ወይም ወራሾቹ ሊቃወሟቸው ይችላሉ (የፍ/ሕ/ቁ. 343)። ተቃራኒ የሚሆን አስረጂ ከሌለ በቀር የነዚህ ሰዎች ሥራና ፈቃድ የውለታን ፈራሽነት የሚያስከትል ጉድለት ያለበት ነው ተብሎ ይገመታል። እንዲሁም በስህተት መገኘት ምክንያት የሥራዎችና የውሎች መፍረስ የሚመለከቱት የፍትሐብሔር ህግ ደንቦች በተመሳሳይ ተፈፃሚዎች ይሆናሉ (የፍ/ሕ/ቁ. 344)። ይሁንና የአእምሮ ጉድለት ያለበት ሰው ከእርሱ ጋር የተደረጉት ውሎች በመፍረሳቸው ምክንያት በቅን ልቡና በተዋዋዮች ሦስተኛ ወገኖች ላይ ለሚደርሰው ጉዳት ሀላፊ ይሆናሉ። በሌላ በኩል ከውል ውጪ ሀላፊነትን በተመለከተ ለጤናማ ሰው እንዳለው ሀላፊነት የሚኖርበት ከመሆኑ በተጨማሪ ይህ የአእምሮ ጉድለት ያለበት ያለ አግባብ ካገኘው ብልፅግና የተነሳ ላሉት ግዴታዎች ጤናማ ለሆነ ሰው ያሉበት ግዴታዎች ይኖሩበታል (የፍ/ሕ/ቁ. 350)።
የአእምሮ ጉድለት ያለበቱ በግልፅ ስላልታወቀ ሰው፡- የአእምሮ ጉድለቱ በግልፅ ያልታወቀ ሰው የፈፀማቸው የህግ ሥራዎች ውሎች በዚሁ ሰው የአእምሮ ጉድለት ምክንያት ሊሻሩ አይችሉም። ሆኖም የአእምሮ ጉድለት ያለበት ሰው እነዚህን ውሎች በፈፀመበት ጊዜ ጉድለት የሌለበት ፈቃድ ለመስጠት በማይችልበት ሁኔታ እንደ ነበረ ለማስረዳት ከቻለ ውሎቹን ለማፍረስ ይችላል (የፍ/ሕ/ቁ.