አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
ሰ/መ/ቁጥር---228231 የካቲት 30 ቀን 2015 ዓ.ም
የተራ ዋስትና እና የአንድነት ዋስትና ልዩነት
በቅድሚያ ከባለዕዳው ተከራከር የማለት መብት ለመጠቀም መሟላት ያለባቸው ቅድመ ሁኔታዎች የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1935(1) ዋሱ እንደ ተከሰሰ ወዲያውኑ ባለገንዘቡን ከባለዕዳው ጋር ተከራከር ካላለ በቀር ባለገንዘቡ ከዋናው ባለዕዳ ጋር ለመከራከር ግዴታ የለበትም በማለት ሲደነግግ የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1936 ደግሞ በቅድሚያ ከባለዕዳው ተከራከር የሚለውን መብት ለመጠቀም እንደቅድመ ሁኔታ መሟላት ያለባቸው ነገሮች ያስቀመጠ ሲሆን ይኸውም ክርክሩን የሚጠይቀው ዋስ ለባለገንዘቡ የዋናውን ባለዕዳ ንብረቶች መምራትና ለዚሁም ክርክር የሚያስፈልገውን በቂ ወጪ አስቀድሞ ለባለገንዘቡ መስጠት አለበት በማለት አስቀምጧል።
ይህም የሚያስገነዝበን ዋሱ በቅድሚያ ከባለዕዳው ጋር ተከራከር የሚለውን መብት ለመጠቀም፥
አንደኛ ክሱ እንደቀረበበት ወዲያውኑ በቅድሚያ ከባለዕዳው ተከራከር በማለት ማንሳት አለበት፤
ሁለተኛ በደፈናው ባለዕዳው ንብረቶች ማለት ብቻ ሳይሆን ከክርክር ነጻ የሆኑ የባለዕዳው ንብረቶችን ቆጥሮ ወይም መርቶ ማሳየት አለበት፤
ሦስተኛ ለክርክር የሚያስፈልገውን በቂ ወጪ መዴቦ ለባለገንዘቡ መስጠት ይኖርበታል፡፡
ከእነዚህ ሦስት መስፈርቶች ውስጥ አንዱ እንኳ ካልተሟላ ባለገንዘቡን በቅድሚያ ከባለዕዳው ተከራከር የማለት መብቱን እንደሚያጣ በግልጽ ያሳያል፡፡ ይህ ማለት ደግሞ የክፍያው ጊዜ ደርሶ ገንዘቡ ያልተከፈለው ባለገንዘብ ቢፈልግ ባለዕዳውንና ዋሱን በአንድ ሊይ መክሰስ ወይም ባለዕዳውን ትቶ ዋሱን ብቻ መክሰስ የሚችል ሲሆን ተራ የሆነ ዋስትና ግዴታ የገባው ዋስ የአንድነት ዋስትና ከገባው ዋስ የሚለየው ከባለዕዳው ተከራከር የማለት መብቱን ቅድመ ሁኔታዎችን አሟልቶ በአግባቡ መጠቀም ሲችል ብቻ መሆኑን ነው፡፡
ቅድመ ሁኔታዎችን አሟልቶ ከባለዕዳው ጋር በቅድሚያ ተከራከር የማለት መብቱን ያልተጠቀመ ተራ ዋስ በተናጠልም ሆነ ከባለዕዳው ጋር በጋራ የዋስትና ግዴታ የገባውን ዕዳ አልከፍሌም ማለት የሚችልበት የሕግ አግባብ የለም፡፡
#Click Ethiopian Laws

👇👇👇👇👇👇
rights and benfit officals Proclamation 284..pdf
1.7 MB
አዋጅ ቁጥር 284/2014 ዓ.ም
የተሻሻለው ከኃላፊነት የተነሡ የአማራ
ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የምክር ቤት አባላት፣ ዳኞችና ዓቃቤያነ ሕግ መብቶችና ጥቅሞችን መወሰኛ አዋጅ
Proclamation No. 284/2022
The Revised
......
https://t.me/lawsocieties
የመደራጀት መብት

መደራጀት በዓለም ዐቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌዎች ማእቀፍ እንዲሁም በበርካታ ሀገራት ህግጋት ዉስጥ የተፈቀደ መብት ነዉ፡፡ ሰዎች በማህበር በመሆን የግልና የጋራ መብታቸውን ለማስከበር እና የጋራ ግዴታቸውን ለመወጣት፣ የጋራ ጥቅም ለማግኘት ወይም ጥቅሞቻቸውን ለማረጋገጥ፣ የሀገር ሰላምና የህዝብን ደህንነት ለማስጠበቅ ዓላማ ሊደራጁ ይችላሉ፡፡ ይሁን እንጂ የመደራጀት መብት በልዩ ሁኔታ በጠባቡ ሊገደብ የሚችልባቸው ሁኔታዎች አሉ፡፡ በዚህ ፅሑፍ የመደራጀት መብት በዓለም አቀፋዊ የሰብአዊ መብት ሰነዶች እና በሀገራችን ያለውን የህግ ጥበቃ እንመለከታለን፡፡

የመደራጀት መብት የህግ ማዕቀፍ

ማንኛውም ሰው ለማንኛውም ዓላማ በማህበር የመደራጀት መብት እንዳለው በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት አንቀፅ 31 ተመላክቷል፡፡ ሀገራችን አፅድቃ የህጓ አካል ያደረገቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች መግለጫ (UDHR) በአንቀፅ 20 እንዲሁም የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ስምምነት (ICCPR) በአንቀፅ 22 ማንኛዉም ሰው የመደራጀት ነጻነት እንዳለው ደንግገዋል፡፡ በተጨማሪም አለም አቀፍ ሰብዓዊ መብቶች መግለጫ (UDHR) ማንኛዉም ሰው ያለፈቃዱ የማህበር ወይም የድርጅት አባል ያለመሆን መብት ጭምር ያለዉ መሆኑን ደንግጓል፡፡

በዚህም መነሻነት በሀገራችን የመደራጀት መብትን ለማስጠበቅ የሚያስችሉ የተለያዩ ህግጋት በሥራ ላይ ውለዋል፡፡ ለአብነት በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 መሰረት ሠራተኞችና አሠሪዎች እንደ አግባቡ የሠራተኞች ወይም የአሠሪዎች ማኅበር ለማቋቋምና ለመደራጀት፣ የማህበር አባል ለመሆንና በማህበርም ለመሳተፍ መብት አላቸው፡፡ ይህ መብት ሰራተኞች በማህበራት በመደራጀት ከአሰሪዎች እና ጥቅማቸውን ከሚነኩ ሌሎች ድርጅቶች ጋር ደሞዝን፣ በሥራ እድገትን፣ የእረፍት ጊዜን እና ልዩ ልዩ ጥቅማጥቅሞችን በተመለከተ ለመደራደር እና መብታቸውን ለማስከበር የሚያግዛቸው ነው፡፡

በተጨማሪም ዜጎች የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ ቁጥር 1113/2011 መሰረት በሙያ ማህበራት፣ በበጎ አድራጎት ድርጅቶች፣ በብዙሀን ማህበራት፣ በድርጅቶች ህብረቶች እና መሰል ለትርፍ ባልቋቋሙ ድርጅቶች መደራጀት ይችላሉ፡፡ በሌላ በኩል ተደራጅተው በፖለቲካ ውስጥ መሳተፍ የሚፈልጉ ደግሞ በምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ ሥርአት አዋጅ 1162/2011 መሰረት መደራጀት ይችላሉ፡፡

የመደራጀት መብት በህግ ክልከላ የሚደረግበት አግባብ

የመደራጀት መብት በአለም አቀፍ ሰብአዊ መብት ሰነዶች እንዲሁም በሀገራችን ህገ መንግስት የተደነገገ መብት ሲሆን ሳይሻራረፍ እንዲከበር የህግ ጥበቃ ተደርጎለታል፡፡ ይህ መብት ለሀገር ደህንነት፣ ለህዝብ ሰላምና ጸጥታ፣ ለህዝብ ጤና እና ሞራል እንዲሁም የሌሎችን መብትና ነፃነት ለመጠበቅ ሲባል በዲሞክራሲያዊ ማህበረሰብ ውስጥ አስፈላጊ በሆኑ በህግ በተደነገጉ ገደቦች ብቻ በጠባቡ ሊገደብ የሚችል ሲሆን ከዚህ ውጪ ምንም አይነት ገደብ ሊጣልበት እንደማይገባ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ስምምነት (ICCPR) በበግልፅ አመላክቷል፡፡ በተመሳሳይ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት አንቀፅ 31 መሰረት አግባብ ያለውን ህግ በመጣስ ህገወጥ ተግባራት ለመፈፀም መደራጀት የተከለከለ ስለመሆኑ ይደነግጋል፡፡

የመደረጀት መብት ዓለም ዐቀፋዊ ጥበቃ እንዲሁም በሀገራችን የህግ ጥበቃ የተደረገለት መብት በመሆኑ በህግ በልዩ ሁኔታ በግልፅ ከተደነገጉ ገደቦች ውጪ ሊገደብ አይችልም፡፡ በመሆኑም ዜጎች ይህን መብትና ግዴታቸውን አውቀው በመጠቀም ከራሳቸው አልፈው ለማህበረሰባቸው እና ለሀገር ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ይጠበቃል፡፡
በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
ከአለ_ ህግ የፍትሐ "ብሔር ሕግ''
በአጭሩ ይወቁት

አንደኛ(1ኛ): መጽሐፍ
ስለ ' ሰዎች "
ከአንቀጽ 1_549

ሁለተኛ(2ኛ) መጽሐፍ ፡
ስለቤተ ዘመድና ስለ ውርስ ( አወራረስ )
ስለ ሥጋ ዝምድናና ስለ ጋብቻ ዝምድና
ከአንቀጽ 550_1125

ሦስተኛ (3ኛ) መጽሐፍ
ስለ ንብረት
ስለ ንብረት በጠቅላላውና ስለ ይዞታ
ከአንቀጽ 1126_1674

አራተኛ (4ኛ) መጽሐፍ
ስለ ግዴታዎች -
ከአንቀጽ 1675_2265
ስለ ውሎች በጠቅላላው

አምስተኛ (5ኛ) መጽሐፍ "
ስለ ልዩ ውሎች
ከአንቀጽ 2266_3367
መብቶች ማስተላለፍን ስለሚመለከቱ ውሎች

ሼር በማድረግ ወዳጅ ቤተሰብና ጎደኛዎትን በህግ መረጃ ያበልፅጉ።
@lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
የክስ አቤቱታ ቀረበ ስለሚባልበት ጊዜ ሰ/መ/ቁጥር 218519

ክስ ለፍርድ ቤት እንደቀረበ ሊቆጠር የሚገባው ሬጅስትራር ከመራበት ሳይሆን ክሱ ለፋይል ከፋች ቀርቦ የክስ ፋይሉ ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ነው።

በዚህ መዝገብ ክሱ መሰረት ያደረገው ቼክ ሲሆን ጥቅምት 18 ቀን 2009 ዓ.ም ክሱ ከደሀ ደንብ አቤቱታ ጋር ለፍርድ ቤት ቀርቦ በዚሁ ቀን ሬጅስትራር የደሀ ደንብ አቤቱታው ላይ “ለችሎት ይቅረብ” ብሎ ምልክት አድርጎበታል። ሆኖም በሰነድ ማስረጃዎች ላይ የቴምብር ከሳሽ ቀረጥ ያስደረጉት ህዳር 23 ቀን 2009 ዓ/ም ነው። በፋይሉ ላይ የክሱ ቅድመ ሁኔታዎች ተሟልተው እንዲከፈት የተደረገውም በታህሳስ 11 ቀን 2009 ዓ.ም ነው።

የቼኩን የይርጋ ጊዜ ለመወሰን ሲባል ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ክሱ ለፍርድ ቤት እንደቀረበ የሚቆጠረው ህዳር 23 ቀን 2009 ዓ/ም ነው በማለት የይርጋ ጊዜው እንዳለፈ በመቁጠር የስር ፍርድ ቤትን ውሳኔ የሻረው ሲሆን ሰበር ሰሚው ችሎት ደግሞ ይህንን በማጠናከር ክሱ ለፍርድ ቤት ቀረበ የሚባለው ታህሳስ 11 ቀን 2009 ዓ.ም መሆኑን በሀተታው ላይ በመግለጽ የይግባኝ ሰሚውን ውሳኔ አጽንቶታል።
4c5844de2.pdf
1.2 MB
ትውልደ ኢትዮጵያዊ ሆኖ የውጭ ሀገር ዜግነት ያለው ሠው ልዩ መብት የሚደነግግ አዋጅ 270/2002
@lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
Forwarded from PIN NGO
Did you know that access to information is crucial for economic development? When businesses have accurate and up-to-date information, they can make smarter decisions about where to invest and how to grow. #AccessToInformation #EconomicDevelopment
ክስ ይዛወርልኝ
• በመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመታየት ላይ ያለ ጉዳይ የግዛት ስልጣን በሌለው ሌላ ፍርድ ቤት ወይም በዛው ፍርድ ቤት በሌላ ችሎት ተዛውሮ እንዲታይ በመጠየቅ በተከራካሪዎች የሚቀርብ አቤቱታ

በአንድ ወረዳ ፍ/ቤት በመታየት ላይ ያለ ጉዳይ ወደ ሌላ ወረዳ ፍ/ቤት ተዛውሮ እንዲታይ አንደኛው ወገን ሲያመለክት ተገቢ ምክንያቶች መኖራቸው ተረጋግጦ በክስ ይዛወርልኝ አቤቱታው እንደየሁኔታው አግባብነት ያለው ውሳኔ ሊሰጥ የሚችል ስለመሆኑ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 31 ተመልክቷል፡፡ በዚህ ድንጋጌ መሰረት የክስ ይዛወርልኝ አቤቱታ ለማቅረብ ጉዳዩ በክርክር ሂደት ላይ የሚገኝ መሆን ይኖርበታል፡፡ በስር ፍ/ቤት ክስ ተመስርቶ ፋይል ባልተከፈተበት ወይም ቀድሞ የተዘጋ መዝገብ ባልተንቀሳቀሰበት ሁኔታ የሚቀርብ የክስ ይዛወርልኝ አቤቱታ የክስ ምክንያት የለውም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 93171 ቅጽ 16፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 31

የክስ ይዛወርልኝ ጥያቄ /Change of Venue/ የሚስተናገድበትን አግባብ ህጉ የዘረጋው ስርዓት ያለ ሲሆን በ1958ቱ የፍትሐብሔር ስነ ሥርዓት ህግ አንቀጽ 31 ስር የተመለከተው አንዱ ነው፡፡ ከዚህ ህግ በኋላ በፌደራልም ሆነ በክልሎች የወጡት የፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጆች ተመሣሣይ ይዘት ያለውን ድንጋጌ ስራ ላይ አውለው ይገኛል፡፡ አንድ ክስ ወደ ሌላ ስፍራ ሊዛወር የሚችልበትን አግባብ ከሚደነግጉት የስነ ስርዓት ህግ ድንጋጌዎች ይዘትና መንፈስ መገንዘብ የሚቻለው ደግሞ ጥያቄው ከተከራካሪ ወገኖች የሚቀርብ መሆኑና ህጋዊ ምክንያቶች ተብለው በህጉ ከተመለከቱት ሁኔታዎች ውስጥ አንዱ መሟላት ያለበት መሆኑን ነው፡፡

ሰ/መ/ቁ. 66945 ቅጽ 11፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ.31

ኢትዮ-ሕግ🇪🇹⚖️🇪🇹Ethio-Law
  
@lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
በሰዉ_መነገድና_ሰዉን_በህገወጥ_መንገድ_ድንበር_የማሻገር_ወንጀል_ክፍል_1.pptx
309 KB
በሰዉ መነገድና ሰዉን በህገወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀል ሥልጣና ማንዋል ክፍል ሶስት
Forwarded from አለሕግ🔵AleHig
ቤት ኪራይ ዉል .docx
16.2 KB
የቤት ኪራይ ውል ፎርም
ጊዜው ያለፈ ይግባኝ ማሥፈቀጃ.pdf
585.1 KB
ጊዜው ያለፈበት ይግባኝ ማስፈቀጃ ፎርም
https://t.me/lawsocieties
የህግ ጉዳይ መረጃ ከፈለጉ 👈
ስለ ህግ ማብራሪያ ከፈለጉ 👈
አዳዲስ ህግ
መመሪያ፣ ደንብ እና ልዩ ልዩ የህግ ውሳኔዎች👈
ለሌሎች ያጋሩት ይማሩበታል ያተርፉበታል
#አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
#ሼር #Share
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
https://t.me/AleHig
https://t.me/AleHig
የመረጃ ነፃነት
ማንኛውም ሰው ከማንኛውም መንግስታዊ አካል መረጃን የመጠየቅ፣ የማግኘት እና ይህንንም መረጃ የማስተላለፍ መብት ያለው ሲሆን መንግስትም ከጥቂት መረጃዎች በስተቀር ማለትም የሶስተኛ ወገን መረጃ፣ የሀገሪቱን መከላከያ፣ ደህንነት እና አለም አቀፍ ግንኙነት አደጋ ውስጥ ከሚጥሉ መረጃዎች እና አንዳንድ በህግ በሚስጥር እንዲያዙ ከተከለከሉ መረጃዎች ውጪ ያሉ መረጃዎችን በተጠየቀ ጊዜ የማጋራት ሀላፊነት አለበት፡፡
የመገናኛ ብዙሀን እና የመረጃ ነጻነትን ለመደንገግ የወጣ አዋጅ፣ አዋጅ ቁጥር 590/2000፤ አንቀጽ 12፣ 16-29

Access to Information

All persons have the right to seek, obtain and communicate any information held by public bodies, and the government has the responsibility to share information on request, except for a few information, namely third-party information, information that endangers the country's defense, security and international relations, and some information that is required by law to be kept secret.

A PROCLAMATION TO PROVIDE FOR FREEDOM OF THE MASS MEDIA AND ACCESS TO INFORMATION PROCLAMATION NO. 590/2008; Article 12, 16-29)

https://t.me/PublicInformationNoble

https://t.me/PublicInformationNoble

Public Information Noble (PIN) is an CSO/NGO working on the right to access information.
ፐብሊክ ኢንፎርሜሽን ኖብል
Connecting people with information

@PublicInformationNoble
@PublicInformationNoble
በጃፓን ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቹ 4ኛ ክፍል እስኪደርሱ ድረስ ምንም ፈተና አይሰጣቸውም ።

በመጀመሪያዎቹ 2 ዓመታት የትምህርት ቤት ግቡ የተማሪን እውቀት ለመገምገም ሳይሆን መልካም ባህሪን ለመገንባት ነው።

የጃፓን ሊቃውንት ከዕውቀት በፊት ምግባርን ያስተምራሉ።

#atc_news
ለሌሎች  ያጋሩት ይማሩበታል እንዲሁም ያተርፉበታል
#አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
#ሼር #Share
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
የጋብቻ ውል.pdf
75.9 KB
የሰበር (cassation)፣ ይግባኝ (appeal)፣ እና የፍርድ ክለሳ (judicial review) ልዩነት
በመጀመሪያም ከላይ ተጓዳኝ ጭብጦች ናቸዉ ብለን የያዝናቸዉን ጭብጦች መርምረናል፡፡አንድን የመጨረሻ ዉሳኔ በሰበር በማየት (cassation) ፣ በይግባኝ (appeal) በማየት እና በዳኝነት አይቶ በመከለስ (judicial review) መካከል ያለዉ አንድነትና ልዩነት ምንድነዉ የሚለዉን በቅድሚያ መመልኩቱ ተገቢ ይሆናል፡፡ ከመዝገበ ቃላት ትርጓሜ የተነሳን እንደሆነ ሰበር ወይም cassation በሚል የሚታወቀዉ ቃል በታዋቂዉ ብላክስ ሎዉ መዝገበ ቃላት ላይ እንደተመለከተዉ ካሰር (casser) ከሚል የፈረንሳይኛ ቋንቋ ግስ የመጣ ቃል ሆኖ የቃሉ ጥሬ ትርጉምም የአንድን ፍርድ/ዉሳኔ የተፈጻሚነት ኃይል(force) መስበር እና ሕጋዊ ዉጤት እንዳይኖረዉ ማድረግ (invalidate)፣መሻር ወይም ተግባራዊነቱን ማስቀረት ነዉ የሚል ትርጓሜ የተሰጠዉ ነዉ፡፡ (cassation comes from the French verb casser and its literal meaning is to “quash the force and validity of a judgement.(black’s law dictionary 5ኛ እትም ገጽ 197 ይመለከቷል፡፡) የሰበር ሥርዓት ምንጭ የሲቪል ሕግ ሥርዓት ሲሆን እዛን ግራዊች(Ezan Grouich) የተባለ ሰዉ (The Soviet Codes of Law)በሚል ባሳተሙት መጸሀፋቸዉ ላይ እንደገለጹት በራሽያ ፌዴሬሽን የሰበር ስርዓት የመጨረሻ የዳኝነት ሥልጣን ያለዉ ፍርድ ቤት የሕግ ስህተት ያለበትን የመጨረሻ ፍርድ የተፈጻሚነት ኃይል በመስበር በምትኩ ሌላ ፍርድ የሚሰጥበት ሥርዓት ነዉ ሲል ይገልጸዋል፡፡ በሌላ በኩል Peter Herzos እና Martha Weser እንዲሁም Mauro Cappelletti እና Joseph M. Perillo በፌረንሳይና በጣሊያን የፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ላይ እንደቅደም ተከተላቸዉ መጽሐፍት የፃፉ የሕግ ሙሁራን መጽሐፎቻቸዉ ላይ የሰበር ሥርዓት በእነዚህ አገራት አንድ የይግባኝ የሚታይበትን ሂደት የጨረሰ የሕግ ስህተት ያለበት የመጨረሻ ፍርድ የመጨረሻ የዳኝነት አካል በሆነዉ ፍርድ ቤቶቻቸዉ ታይቶ የሚሻርበት ወይም ወደ ሥር ፍርድ ቤት በመመለስ የሚወስኑበት እንጂ የራሳቸዉን አዲስ ዉሳኔ የሚሰጡበት እንዳልሆነ ይገልጻሉ፡፡

ከዚህ የምንገነዘበዉ በሰበር የሚታየዉ በመጨረሻ ፍርድ ቤት እንደሆነ ፣በሰበር የሚታየዉም ፍርድ በበታች ፍርድ ቤቶች የተሰጠ ፍርድ ሆኖ በይግባኝ የሚታየበትን ሂደት የጨረሰ የሕግ ስህተት ያለበት የመጨረሻ ፍርድ እንደሆነ እና ፈረንሳይና ጣሊያን የሰበር ፍርድ ቤቶች የስር ፍርድ ቤትን ዉሳኔ ከመሻር ባለፈ እንደ ራሺያ ፌዴሬሽን ፍርድ ቤት አዲስ ዉሳኔ እንደማይሰጡ ነዉ፡፡

በአገራችን “ስለሰበር” ምንነት ትርጓሜ የሰጠ ሕግ ባይኖርም በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ሕገ መንግስት አንቀጽ 80(3/ሀ) እና በአዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 2(4 እና 5) ስለመሠረታዊ የሕግ ስህተት እና ስለመጨረሻ ዉሳኔ ከተሰጠዉ ትርጓሜ የምንገነዘበዉ በሰበር የሚያየዉ የፌዴራሉ የመጨረሻ ዳኝነት አካል በሆነዉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተደራጀ ሰበር ሰሚ ችሎት መሆኑ፣ የሚያያዉም ዉሳኔ በዚሁ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት እና በበታች መደበኛ ፍርድ ቤቶች ታይቶ የተሰጠ የመጨረሻ ዉሳኔ ላይ የተፈጸመ መሰረታዊ የሕግ ስህተትን ብቻ ሳይሆን በሕግ የመዳኘት ሥልጣን በተሰጠዉ አካል፣በተቋማት ወይም በአማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎች የተሰጠ እና ለጉዳዩ እልባት የሚሰጥ ፍርድ ፣ብይን፣ትእዛዝ፣ዉሳኔ እና/ወይም የይግባኝ ሂደቶችን የጨረሰ ፍርድ ፣ብይን፣ትእዛዝ ወይም ዉሳኔን እንደሚጨምር ተደንግጓል፡፡እንዲሁም በአገራችን እስካሁን በሰበር ችሎቱ ከዳበረዉ ዳኝነታዊ ፍልስፍና(judicial jurisprudence) እንደሚታወቀዉ ሰበር ችሎት ያለዉ ሥልጣን መሰረታዊ የሕግ ስህተት አርሞ ዉሳኔዉን ከመሻር እና ጭብጥ ይዞ ከመመለስ ባለፈ በጉዳዩ ላይ አዲስ ዉሳኔ የመስጠት ሥልጣን ጭምር እንዳለዉ ነዉ፡፡ ይህም የእኛ አገር የሰበር ሥርዓት ከሌሎች ከላይ ከተጠቀሱት ዉሳኔዎችን በሰበር የማየት ሥርዓት ከዘረጉ አገራት ሥርዓት አንጻር ሲነጻጸር መሰረታዊ የሕግ ስህተት ከማረም አኳያ ሰፊ ሥልጣን እንዳለዉ የሚያስገነዝብ ነዉ፡፡ይህም የሆነዉ በሕገ መንግስቱ ይህ ሥርዓት እንዲዘረጋ መነሻ ምክንያት የሆነዉ የሕግ አተረገጓጎም ወጥነት የማምጣትና በዚህም ዜጎች በእኩልነት ተጠቃሚ እንዲሆኑ የማድረግ ዓላማ በተሟላ መልኩ ከግብ እንዲደርስ ለማድረግ እንደሆነ ይታመናል፡፡

በሌላ በኩል ዳኝነታዊ ክለሳ (judicial review) ከላይ በተጠቀሰዉ መዝገበ ቃላት ላይ፡ A court's power to review the actions of other branches or levels of government; esp.,the courts' power to invalidate legislative and executive actions as being unconstitutional. …And a court's review of a lower court's or an administrative body's factual or legal findings.(black’s law dictionary 9ኛ እትም ገጽ 924). የሚል ትርጓሜ የተሰጠዉ ሲሆን ይህም በግርድፉ ሌሎቹ የመንግስት አካላት (ሕግ አዉጭዉ እና ሕግ አስፈጻሚዉ) እንደቅደምተከተላቸዉ የሚያወጡት ሕግ ፣ የሚፈጽሟቸዉ ተግባራት እና የሚያስተላልፋቸዉ ዉሳኔዎች ሕገ መንግስታዊ መሆን አለመሆናቸዉን (constitutionality) እና ሕጋዊነታቸዉን (legality) ፍርድ ቤቶች የሚከልሱበትንና ጉድለት ካለባቸዉም ተግባራዊ እንዳይሆኑ የሚወስኑበትን ሥርዓት የሚመለከት ነዉ የሚል ይዘት ያለዉ ነዉ፡፡

እንዲሁም ከተለያዩ የሕግ ድርሳናት መገንዘብ እንደሚቻለዉ በዳኝነታዊ ክለሳ (judicial review) የሚታዩ ጉዳዮች እንደየአገራት የሕግ ሥርዓት ሊሰፋና ሊጠብ የሚችል መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በሕግ አዉጪዉ የወጣ ሕግ እና የተላለፈ ዉሳኔ ፣የሕግ አስፈጻሚዉ ወይም የአስተዳደር አካላት ተግባራትና ዉሳኔዎች በዳኝነት አካል የሚከለስበት ሥርዓት በሰፊዉ የሚታወቅ ነዉ፡፡አገራት በሕግ አዉጭዉ የወጣ ሕግ ወይም የተላለፈ ዉሳኔ እንደዚሁም በአስፈጻሚዉ/በአስተዳደር አካል የሚፈጸሙ ተግባራት ወይም የሚተላለፉ ዉሳኔዎችን ሕገ መንግስታዊነት እና/ወይም ሕጋዊነት (Constitutionality and legality) በዳኝነት አይተዉ እንዲከልሱ ለመደበኛ ፍርድ ቤት ወይም ለሕገ መንግስታዊ ፍርድ ቤት ሥልጣን ይሰጣሉ፡፡ሕገ መንግስትን መተርጎምን የሚጠይቁ የሕገ መንግስታዊነትና ሕጋዊነትን ጥያቄዎችን ተቀብለዉ ሕገ መንግስትን ተርጉመዉ የሕግ አዉጪዉን ሕግና ዉሳኔ እንዲሁም የሕግ አስፈጻሚዉን ሕግ፣ዉሳኔ ወይም ሌላ ተግባር በዳኝነት አይተዉ እንዲከልሱና የመጨረሻ ዉሳኔ ኢንዲሰጡ አሜሪካ እና ሕንድ የመሰሉ አገራት ለመደበኛ ጠቅላይ ፍርድ ቤቶቻቸዉ ሥልጣን የሚሰጡ ሲሆን እንደ ጀርመን ፣ኦስትሪያ እና ደቡብ አፍሪካ ያሉ አገራት ደግሞ ለሕገ መንግስታዊ ፍርድ ቤቶቻቸዉ ሥልጣን ይሰጣሉ፡፡
እነዚህ ፍርድ ቤቶች አንድ ሕግ ወይም አስተዳደራዊ ዉሳኔ ሕገ መንግስቱን የሚጥስ ወይም የሚቃረን እንዲሁም የሕጋዊነት ጉድለት አለበት የሚል ድምዳሜ ላይ በመድረስ ሕጉን ከሕግነት ተራ በማስወጣት ተፈጻሚ እንዳይሆን ለማድረግ የአስተዳደር ዉሳኔዉም ተግባራዊ እንዳይሆን ለመወሰን የሚከተሉበት

አካሄድም እንደዚሁ የተለያየ ነዉ፡፡ አሜሪካ የዳኝነታዊ ክለሳ የምታደርግበት ሞዴል ያልተማከለ ዳኝነታዊ ክለሳ ሥርዓትን (The decentralized model of judicial review) ሲሆን በዚህ ሞዴል መሰረት የክለሳ ጥያቄዉ ከበታች ፍርድ ቤት ጀምሮ በየደረጃዉ ይግባኝ ሥርዓት በሚመስል አካሄድ ታይቶ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ቀርቦ የመጨረሻ አስገዳጅ ዉሳኔ ተሰጥቶበት እንዲቋጭ ታደርጋለች፡፡ እንደጀርመን ያሉት ደግሞ የክለሳ ጥያቄዉ በቀጥታ ለሕገ መንግስታዊ ፍርድ ቤት እንዲቀርብ የሚያደርግ ሥርዓት(The centralized model of judicial review) የሚከተሉ ሲሆን በዚሁ ፍርድ ቤት ክለሳ ተደርጎ የመጨረሻና አስገዳጅ ዉሳኔ እንዲሰጥበት ያደርጋሉ፡፡በደቡብ አፍሪካ ደግሞ የአንድ ሕግ ሕገ መንግስታዊነትና እና የአንድን የአስተዳደር/የአስፈጻሚ አካል ተግባር/ዉሳኔ ሕገ መንግስታዊነትና ሕጋዊነት በተመለከተ የአገሪቱ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የመጀመሪያ ደረጃ የሕገ መንግስታዊነት ትርጉም (Preliminary Constututional Interpretation) ሕገ መንግስቱን ተርጉሞ እንዲወስን ሥልጣን ትሰጥና የሕገ መንግስታዊነት ጥያቄ የተነሳበት ሕግ እና የሕገ መንግስታዊነትና የሕጋዊነት ጥያቄ የተነሳበት የአስፈጻሚ/የአስተዳደር አካል ተግባር/ዉሳኔ ተፈጻሚነት እንዳይኖራቸዉ የመጨረሻዉን ዉሳኔ የመሰጠት ሥልጣን የሚኖረዉ ሕገ መንግስታዊ ፍርድ ቤት ነዉ የሚል ሥርዓት በሕገ መንግስቷ እንደዘረጋች በዘርፉ የተጻፉ ድርሳናት ያሳያሉ፡፡
የእኛን አገር ስርዓት የተመለከትን እንደሆነ በሦስቱ የመንግሥት አካላት መካከል ማለትም በሕግ አውጭው፣ ሕግ አስፈጻሚው እና በሕግ ተርጓሚው መካከል በፌዴራልና በክልል ሕግጋተ መንግስታት በተመለከተዉ አግባብ የሥልጣን ክፍፍል ያለ ቢሆንም በመካከላቸው የእርስ በእርስ ክትትልና ሚዛኑን ተጠብቆ (check and balance) እየተሰራ መሆኑ የሚረጋገጥበት ሥርዓት ከሌለ ተቋማቱ በሕግ የተጣለባቸውን የዜጎችን ሠብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ማክበርና ማስከበር አይችሉም፡፡ በአንጻሩ የእርስ በእርስ ክትትልና ሚዛኑን ጠብቆ የመስራት መርህ አተገባበር አለአግባብ ጣልቃ መግባትን ካስከተለ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ስለሚያመዝንና የተጣለባቸውን ግዴታ እንዳይወጡ ሊያደርጋቸው ስለሚችል ቁጥጥሩ በሕግ በተዘረጋው ሥርዓት አግባብ መፈጸም አለበት፡፡
አስተዳደራዊ አካላት የሚሠጧቸው ውሳኔዎች በፍ/ሕ/ቁጥር 401/1 እንደተመለከተው ከተሠጣቸው ሥልጣን በማለፍ ከወሰኑ (ultra virus) ወይም በተሠጣቸው ሥልጣን ስር ሆኖ ነገር ግን በሕጉ የተመለከቱትን አስገዳጅ ሁኔታዎችና ፎርም ሳይከተሉ የሚፈጽሙት ተግባር ወይም ውሳኔ ፈራሽ ነው፡፡ በአስተዳደራዊ ውሳኔ ላይ የዳኝነት ክለሳ መኖር ካለበት ዋና ዋና ምክንያቶች አንዱ የመንግሥት አካላት የሥልጣን ክፍፍል መርሕ ነው፡፡ በኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 79/1 መሠረት የዳኝነት ሥልጣን የፍርድ ቤቶች ብቻ ስለመሆኑ ተደንግጓል፡፡ ይህም ከሕገ-መንግሥታዊ ክርክሮች (constitutional disputes) ውጭ ማንኛውም በፍርድ ቤት ታይተው ሊወሰኑ የሚችሉ ጉዳዮች (justiciable matters) ላይ ፍርድ ቤቶች ዳኝነታዊ ክለሳ የማድረግ (judicial review) ተፈጥሮአዊ የሆነ ዳኝነታዊ ሥልጣን (inherent judicial power) እንዳላቸው ያሳያል፡፡ በፍርድ ቤት ታይተው ሊወሰኑ የሚችሉ ጉዳዮች የሚለውም የጉዳዮቹ ባሕሪ በፍርድ ቤት ሥልጣን ሥር ሊወድቁ የማይችሉ፣ አከራክሮ ሊፈጸም የሚችል ውሳኔ ሊሰጥባቸው የማይችሉ ጉዳዮችን የሚመለከት ሲሆን በሌላ በኩል ጉዳዮቹ በፍርድ ሊታይ የሚችሉ እንኳን ቢሆን ሌሎች የመንግሥት አካላት በሕገ- መንግሥት ባለው የሥልጣን ክፍፍል መርሕ መሠረት ሕገ-መንግሥታዊ ሥልጣናቸውን (constitutionally mandated powers) መሠረት አድርገው የሚወስኗቸው ጉዳዮችንም ይጨምራል፡፡ በሌላ በኩል የሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 78/4 እና 37 ላይ የተደነገገዉ አንድ ላይ ሲነበብ በሕግ የተደነገገን የዳኝነት ሥርዓትን የሚከተል የዳኝነት ነክ አካላት በሕግ የመዳኘት ሥልጣን ሊሰጣቸው እንደሚችል ያስገነዝባል፡፡ የእነዚህ አካላት የዳኝነት ሥልጣን በተፈጥሮ የሚገኝ ሳይሆን በግልጽ ሕግ ለመዳኘት ሥልጣን ሲሰጣቸውና የሚሰሩበት የተደነገገ የዳኝነት ሥርዓት ሲኖራቸውና ይህን ተከትለው ሲሰሩ የሚኖራቸው ሥልጣን ነው፡፡ ይህም በዘመናዊው የመንግሥት ሥርዓት መንግሥት ብዙ ጉዳዮች ላይ ሠፊ ሥልጣን ያለው አስፈጻሚዉ አካል በመሆኑ በመሆኑ ለመንግሥት የሕግ አስፈጻሚ አካል የዳኝነት ነክ ሥልጣን አስፈላጊ በመሆኑ፣ የተወሰኑ ጉዳዮች

ደግሞ ፍሬ ነገሮችን ለመመልከት ልዩ ዕውቀት (specialization) የሚጠይቁ በመሆኑ እና ፍርድ ቤቶች ላይ ያለውን የሥራ ጫና ለማቃለል ሥራ ላይ ይውላሉ፡፡

ነገር ግን ጠንካራና አስተማማኝ የዜጎች ሰብዓዊ መብት የሚከበርበት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት የሕግ የበላይነትን ማስፈን ወሳኝ ነው፡፡ በኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት መግቢያ ላይ እንደተመለከተው የሕግ የበላይነትን የተረጋገጠበት አሰራር መዘርጋት የሕገ-መንግሥቱ ዋነኛ ዓላማ ሲሆን አንዱ መስፈርት ደግሞ የዜጎችን በፍርድ ሊታዩ የሚችሉ ጉዳዮች በነፃና ገለልተኛ ፍርድ ቤት እንዲታይ መደረጉ ነው፡፡የሕግ የበላይነት መርሕ ሰፊ ሀሳቦችን የያዘ ቢሆንም በሕግ ሥልጣኑ የተገደበ መንግሥት እንዲኖርና የዜጎች መብት የተከበረበት ሥርዓትን ለመፍጠር የሚረዳ ነው፡፡ በፌዴራሉ ሕገ-መንገሥት መግቢያ ላይ የተመለከተዉ የሕግ የበላይነት ዓላማ ከግብ የሚደርሰዉ የመንግስት አካላት ለሚወስዱት እርምጃ ተጠያቂ መሆንና ኃላፊነት መውሰድ ሲችሉ ነዉ፡፡ይህም ከሚረጋገጥባቸዉ መንገዶች አንዱ በሰጡት አስተዳደራዊ ውሳኔ ላይ መብቱ የተነካበት ሰዉ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት መቅረብ ሲችልና ፍርድ ቤቶችም ተገቢዉን መንገድ ተከትለዉ ጥያቄ የቀረበበት ዉሳኔ ሕጋዊነትን የተከተል መሆን አለመሆኑን በዳኝነት ማየት ሲችሉ ነዉ፡፡ እንዲሁም የአስተዳደር አካላት የሠጡት ውሳኔ በሕጉ የተዘረጋውን ሥርዓት የተከተለና ዜጎች ተገቢው የመሰማት መብት (due process of law) ያገኙ ስለመሆኑ ቁጥጥር ለማድረግ በአስተዳደራዊ ውሳኔ ላይ የዳኝነት ክለሳ ያስፈልጋል፡፡
በኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 79(1) መሠረት የዳኝነት ሥልጣን የፍርድ ቤቶች ብቻ ስለመሆኑ ተደንግጓል፡፡በኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 37 ላይ ሰዎች ፍትሕ የማግኘት መብት ያላቸው በመሆኑ አስተዳደራዊ ውሳኔዎች በፍርድ ሊዳኙ የሚችሉ እስከሆኑ ድረስ ነጻና ገለልተኛ ሆኖ ጉዳዮችን እንዲመለክት በሕገ መንግስቱ አንቀጽ 78 መሰረት ሥልጣን በተሰጠው ፍርድ ቤት ቀርቦ መታየቱ ነጻ የዳኝነት አካል ያስፈለገበት ዓላማ ሊሳካ የሚችልበትና ሰዎች ያላቸውን መብት በሕግ ማስከበር የሚችሉበት ዋነኛ መሣሪያ አስተዳደራዊ ዉሳኔ በዳኝነታዊ ክለሳ ማየት መቻል ነው፡፡ የሰብዓዊ መብቶች ጥበቃም አስተዳደራዊ ውሳኔ ላይ የዳኝነት ክለሳ አስፈላጊ መሆኑን ያሰገነዝባል፡፡ በኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 13(1) ሰብዓዊ መብቶችን የማክበርና ማስከበር ኃላፊነት ከተሰጣቸው አካላት ዋነኛው