አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
በፍርድ የማይዳኝ ጉዳይ /Justiciability/---በሰበር ችሎት

ፍቺ--ዳኝነት የተጠየቀበት ጉዳይ በሕግ ለሌላ አካል የተሰጠ

ሰ/መ/ቁ. 51790 ቅጽ 12፣  የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣንን ለማቋቋም የወጣ አዋጅ ቁ. 587/2000 አንቀጽ 19/1/ ለ፣ የፌደራል መንግስት ሠራተኞች አዋጅ ቁ. 515/1999፣ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ሠራተኞች አስተዳደር ለመወሰን የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁ. 155/2000 አንቀጽ 37

ማንኛውም ሰው በፍርድ ሊወሰን የሚገባውን ጉዳይ ለፍርድ ቤት ወይም ለሌላ በሕግ የዳኝነት ስልጣን ለተሰጠው አካል የማቅረብና ውሳኔ ወይም ፍርድ የማግኘት መብት ያለው ስለመሆኑ የኢ.ፌ.ዲ. ሪፐብሊክ ሕገ መንግስት አንቀጽ 37/1/ ድንጋጌ በግልጽ የሚያሳየው ጉዳይ ነው፡፡ ከዚሁ የሕገ መንግስት ድንጋጌ መገንዘብ የሚቻለው ደግሞ ፍርድ ቤቶች አንድን ጉዳይ (አቤቱታ) ተቀብለው ውሳኔ መስጠት የሚችሉት ዳኝነት የተጠየቀበት ጉዳይ በሕግ ለሌላ አካል ያልተሰጠ ጉዳይ በሚሆንበት ጊዜ እንደሆነ መሆኑን ነው፡፡ በሕግ ተለይተው በአስተዳደራዊ ውሳኔ እንዲቋጩ በተባሉ ጉዳዮች ላይ መደበኛ ፍርድ ቤት የመዳኘት የስረ ነገር ስልጣን ስለሌለው በሕጉ መሰረት ለአንድ አስተዳደር አካል ቀርቦ አስተዳደራዊ ውሳኔ የተሰጠበትን ጉዳይ ወይም ለአስተዳደር መቅረብ የሚገባውን ጉዳይ ፍርድ ቤት ሊያስተናግደውም ሆነ አከራክሮ ውሳኔ ሊሰጥበት አይችልም፡፡ ለአንዳንድ የመንግስት አካላት በተወሰኑ ጉዳዮች ላይ የመወሰን ስልጣን የሚሰጡት ሕጎች መጠበቅና መከበር ያለባቸው ሲሆን የዳኝነት አካል ስልጣንም በሕግ የተወሰነ ስለሆነ ሕግ የመተርጎም ስራው በሕጉ በተመለከተው አድማስ የሚመራ ይሆናል፡፡ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 4 ድንጋጌ የሚያሳየውም ፍርድ ቤቶች በሌላ ሕግ በግልጽ በታገዱ ጉዳዮች ላይ አከራክሮ የመወሰን ስልጣን የሌላቸው መሆኑን ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 54697 ቅጽ 12፣  ኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህገ መንግስት አንቀጽ 37፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 4

አንድ ጉዳይ በፍርድ ሊያልቅ የሚችል ነው የሚባለው የክርክሩ መሠረታዊ ባህሪ በፍርድ ለመጨረስ አመች የሆነ ሲሆንና ተከራካሪዎቹ የሚከራከሩበት ጉዳይ ንድፈ ሃሳባዊ ወይም ምናባዊ የፈጠራ ታሪክ ላይ የተመሠረተ ሣይሆን በነባራዊ ዕውነታና ተጨባጭ በሆነ ችግር ወይም ክስተት መሠረት ያደረገ የመብት ወይም የሃላፊነት ጥያቄ ሲሆን እንደሆነ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 42150 ቅጽ 12፣  ኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህገ መንግስት አንቀጽ 37፣ ዓለም አቀፍ የሲቨልና የፖለቲካ መብቶች ቃል ኪዳን ስምምነት አንቀጽ 14 ንዑስ አንቀፅ 1፣ የአፍሪካ የሰዎችና የህዝቦች መብት ቻርተር አንቀጽ 7
(የአንድ ዳኛ የተለየ ሓሳብ)

ግንባታ በጊዜው አለመጠናቀቁን ወይም የገንዘብ አቅም ማነስን አሊያም በሌላ ምክንያት አስተዳደሩ በሚወስዳቸው የኪራይ (lease) ይዞታ ማቋረጥ እርምጃዎች ላይ ባለይዞታው ቅሬታ ሲያድርበት ጉዳዩን ለማየት በሕግ በግልጽ የዳኝነት ስልጣን የተሰጠው ሌላ አካል እስከሌለ ድረስ ጉዳዩ በፍርድ ሊወስን የሚገባው ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 80202 ቅጽ 15 

የንብረት ባለሀብትነት መብት ከአንዱ ወገን ወደ ሌላው እንዴት መተላለፍ እንዳለበት በህጉ የተመለከተውን ደንብና ሥርዓት ሳይከተል ስለሆነ የንብረቱ ባለሀብት ስለመሆኑ የህግ ግምት መውሰጃ የሆነው የባለቤትነት ምስክር ወረቀት ቀሪ ነው፤ ሊሰረዝ ይገባል በማለት የሚቀርብ ጥያቄ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1195፣ 1196 እና በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 33/2/ እና 231/1/ሀ/ በተመለከቱት ድንጋጌዎች መሠረት በፍ/ቤት ሊረጋገጥ የሚችል የዳኝነት ጥያቄ እንጂ ጉዳዩ በፍርድ ሊያልቅ የሚችል ጉዳይ አይደለም ለማለት የሚያበቃ አይደለም፡፡
ሰ/መ/ቁ. 75414 ቅጽ 14፣  ፍ/ህ/ቁ 1195፣ 1196፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 33(2)፣ 231(1) ሀ

የቀበሌ ቤት የተከራይነት መብት ተከራይ ሲሞት ለወራሾቹ ወይም ለቤተሰቦቹ የሚተላለፍ መሆን ያለመሆኑ በፍ/ብ/ሕጉ ስለማይንቀሳቀስ ንብረት የኪራይ ውል የተመለከቱትን ድንጋጌዎች፣ የቀበሌ ቤትን የኪራይ መብትና ግዴታ ለመግዛት በሚመለከተው አካል በወጡት ደንብና መመሪያዎች አንጻር ታይቶ በፍርድ ቤት ዳኝነት የሚሰጥበት እንጂ የቤቱ አስተዳዳሪ የሆነ ቀበሌ ለፈለገው ሰው የሚያከራየው ነው ተብሎ በፍርድ እንዳያልቅ የሚደረግ ጉዳይ አይደለም፡፡
ሰ/መ/ቁ. 97948 ቅጽ 17
#habeshaadvocatesllp
#ethiolawtips
https://t.me/lawsocieties
#የኑዛዜ_አይነቶችና_የኑዛዜ_ማረጋገጫ 
በኢትዮጵያ የውርስ ህግ ሰው ህይወቱ ካለፈ በኋላ በህይወት ዘመኑ ያፈራቸው ንብረቶቹን ለወዳጅ ዘመዶቹ እንዲከፋፈል የሚያደርግበት ሁለት አይነት መንገዶች አሉ፡፡ እነሱም ያለኑዛዜ የሚደረግ ውርስ እና በኑዛዜ የሚደረግ ውርስ ናቸው፡፡ በሁለቱም ዘዴዎች የሚደረግ የንብረት ማስተላለፍ ሂደት በፍትሐ ብሔር ህግ የሚገዛ ሲሆን ለውርሱ ተፈፃሚነት ህጉ ያስቀመጣቸው መስፈርቶች መሟላት ይኖርባቸዋል፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ የኑዛዜ አይነቶች እና የኑዛዜ ማረጋገጫ በዝርዝር ይዳሰሳሉ፡፡
    
የኑዛዜ አይነቶች

በኢትዮጵያ ህግ 3 የኑዛዜ ዓይነቶች አሉ፡፡ ሁሉም የኑዛዜ አይነቶች መከትል ያለባቸው ፎርማሊቲዎች ወይም ቅድመ ሁኔታዎች በ1952 ዓ.ም በወጣው የፍትሐ ብሔር ህጋችን ውስጥ በዝርዝር የተቀመጡ ሲሆን መስፈርቶቹ ያልተሟሉ እንደሆነ ኑዛዜው በህግ ፊት ውድቅ (ፈራሽ) ይሆናል፡፡ ህጉ የመስፈርቶቹን መሟላት በተመለከተ ጥብቅ (strict) ነው፡፡ ይህም የሆነበት ዋና ምክንያት የኑዛዜ ቃል በሚፈፀምበት ወቅት ተናዛዡ በህይወት ስለማይኖር ትክክለኛ ሀሳቡን ማወቅ የሚቻለው ትቶት ከሄደው የኑዛዜ ሰነድ ብቻ ነው፡፡ ስለሆነም ይህ ሰነድ ደግሞ ለአፈፃፀም እንዲያመች መስፈርቶቹን በሙሉ ግልፅ በሆነ ሁኔታ መከተል አለበት፡፡ በፍ/ህ/አ 880 ስር እንደተደነገገው 3ቱ የኑዛዜ አይነቶች

1. በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ (public will)
2. በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜ (holographic will)
3. በቃል የሚደረግ ኑዛዜ (oral will) ናቸው

• በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ ( የፍ/ብ/ህገ/ቁጥር 881-883)

በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ ተናዛዡ እየተናገረ ሌላ ሰው የሚፅፈው ወይም ተናዛዡ ራሱ የሚፅፈው የኑዛዜ አይነት ነው፡፡ ይህ ኑዛዜ በተናዛዡ ወይም በሌላ ሰው ከተፃፈ በኃላ ተናዛዡ እና ምስክሮች ባሉበት መነበብ አለበት፡፡ በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ ተቀባይነት እንዲኖረው ተናዛዡና ምስክሮች ባሉበት መነበቡ ብቻ በቂ አይደለም፡፡ ይልቁንም ይህ መስፈርት (formality) መሟላቱ በኑዛዜው ላይ መስፈር አለበት፡፡ ይኸውም በኑዛዜው ላይ  "ይህ ኑዛዜ ተናዛዡ እና ምስከሮች ባሉበት ተነቧል" ተብሎ መገለጽ አለበት፡፡ በግልፅ በሚደረግ ኑዛዜ ላይ የምስክሮች ብዛት 4(አራት) መሆን ሲኖርበት አራቱም ምስክሮች ኑዛዜው ተነቦላቸው በኑዛዜው ላይ ፊርማቸውን ወዲያውኑ ማስፈር አለባቸው፡፡ በተጨማሪም በኑዛዜው ላይ ኑዛዜው የተደረገበት ቀን ማለትም ቀን፣ ወር፣ ዓመተ ምህረት መፃፍ አለበት፡፡

የምስክሮችን ብዛት በተመለከተ በግልፅ ለሚደረግ ኑዛዜ ከምስክሮቹ መካከል አንዱ ዳኛ ወይም ውል ለማዋዋል ሥልጣን የተሰጠው ሰው ሆኖ ኑዛዜውም የተደረገው ይህ ዳኛ ወይም ለማዋዋል ሥልጣን የተሰጠው ሰው ሥራቸውን በሚያካሄዱበት ክፍል ውስጥ የሆነ እንደሆነ ለኑዛዜው ዋጋ ማግኘት ሁለት ምስክሮች ብቻ በቂ ናቸው፡፡

በአጠቃላይ በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ የሚከተሉትን ፎርማሊቲዎች መከተል አለበት፡፡

 በተናዛዡ በራሱ ወይም እሱ እየተናገረ በሌላ ሰው ሊፃፍ ይችላል
 ተናዘዡና አራት ምስክሮች ባሉበት መነበብ አለበት
 በኑዛዜው ላይ ተናዛዡና ምስክሮቹ ባሉበት መነበቡ በግልፅ መፃፍ አለበት
 ኑዛዜው የተደረገበት ቀን፣ ወር እና ዓ.ም መፃፍ አለበት
 አራት ምስክሮች መኖር አለባቸው፣
 ተናዛዡና ምስክሮች ኑዛዜው እንደ ተነበበላቸው ወዲያውኑ ፊርማቸውን ወይም የጣት አሻራቸውን ማሳረፍ አለባቸው
 በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ ምስክሮች አካለመጠንን የደረሱ (18 ዓመት የሞላቸው) ወይም በህግ ያልተከለከሉ መሆን አለባቸው
 ምስክሮች ኑዛዜው የተፃፈበትን ቋንቋ ለማወቅና የተፃፈውን ለመስማት ወይም ለማንበብ ራሳቸው ችሎታ ያላቸው መሆን አለባቸው፡፡

እነዚህ ከላይ የተመለከቱት መስፈርቶች ካልተሟሉ ኑዛዜው ፈራሽ ይሆናል፡፡ ፍርድ ቤቶችም የኑዛዜ ቃልን ለማስፈፀም መሟላት ያለባቸው መስፈርቶችን በጥብቅ የሚቆጣጠሩ ሲሆን መስፈርቶቹ ካልተሟሉ ኑዛዜውን ውድቅ ያደርጉታል፡፡

• በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜ (የፍ/ብ/ህገ/ቁጥር 883-891)

በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደርግ ኑዛዜ ሙሉ በሙሉ በተናዛዡ የሚፃፍ የኑዛዜ አይነት ነው፡፡ ይህን የኑዛዜ አይነት የሚያደርገው የተማረ ወይም ኑዛዜው የሚፃፍበትን ቋንቋ መፃፍና ማንበብ በሚችል ሰው ሲሆን የምስክሮችን መኖር የሚፈልግ አይደለም፡፡ በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜ በተናዛዡ የእጅ ፅሁፍ ወይም በማሽን (በኮምፒዩተር) ሊፃፍ ይችላል፡፡ ተናዛዡ ኑዛዜውን በኮምፒዩተር የሚፅፈው ከሆነ በእያንዳንዱ ገፅ ላይ እራሱ ስለመፃፉ በእጅ ፅሁፉ ማመልከት አለበት፡፡ ይህም ኑዛዜውን ያደረገው ተናዛዡ እንደሆነ ለማረጋገጥ ይረዳል፡፡ ኑዛዜው በማሽንም ሆነ በእጅ ቢፃፍ ተናዛዡ በእንዳንዱ ገፅ ላይ ቀን ፅፎ ፊርማውን ማስፈር ይኖርበታል፡፡ በተጨማሪም በኑዛዜ ሰነድ ላይ ተናዛዡ ይህ ሰነድ "ኑዛዜ" ነው በማለት በግልፅ መግለፅ አለበት፡፡ እነዚህ መስፈርቶች ካልተሟሉ ኑዛዜው ፈራሽ ነው፡፡ በተጨማሪ በተናዛዡ ፅህፈት የሚደረግ ኑዛዜ ኑዛዜው በተደረገ በሰባት(7) ዓመት ውስጥ ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው ሰው ወይም ፍርድ መዝገብ ቤት መቀመጥ አለበት፡፡

በአጠቃላይ በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜ በህግ ፊት ተቀባይነት እንዲያገኝ እና ተፈፃሚነት እንዲኖረው የሚከተሉት መስፈርቶች በሙሉ መሟላት አለባቸው፡፡

 ሙሉ ለሙሉ በተናዛዡ መፃፍ አለበት
 በኑዛዜው ላይ በግልፅ "ይህ ሰነድ የኑዛዜ ሰነድ ነው "ተብሎ መገለፅ አለበት
 በተናዛዡ በአያንዳንዱ ገፅ ላይ ቀን እና ፊርማ መስፈር አለበት
 ኑዛዜው በተደረገ በሰባት አመት ውስጥ ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ዘንድ መቀመጥ አለበት፣( የፍ/ብ/ህገ/ቁጥር 903)
 ተናዛዡ ግልፅ በሆነ ፊርማው ካላፀደቃቸው በስተቀር የተናዛዡን ፈቃድ ለመለወጥ የሚችል ፍቀት፣ ስርዝ ወይም ድልዝ ያለባቸው ኑዛዜዎች ፈራሽ ናቸው፡፡

ከእነዚህ ከላይ ከተገለፁት መስፈርቶች ውስጥ አንዱ ወይም ከአንድ በላይ ካልተሟላ ኑዛዜው ፈራሽ ይሆናል ወይም ተፈፃሚነት አይኖረውም፡፡ ነገር ግን ኑዛዜ ፈራሽ ሆነ ማለት ወራሾች ንብረት አያገኙም ማለት አይደለም፡፡ ይልቁንም ውርሱ በቁጥር 842 እና ተከታዮቹ መሰረተ ሳይናዘዝ የሞተ ሰው ውርስ በሚተላለፍበት ሂደት የሚተላለፍ ይሆናል፡፡

  
የቃል ኑዛዜ (የፍ/ብ/ህገ/ቁጥር 892-894)

የቃል ኑዛዜ ማለት አንድ ሰው የሞቱ መቃረብ ተሰምቶት የመጨረሻ የፍቃድ ቃሎቹን ለሁለት ምስክሮች የሚሰጥበት የኑዛዜ አይነት ነው፡፡ ከፍ/ህ/ ቁጥር 892 እንደምንረዳው የቃል ኑዛዜ በመደበኛ ሁኔታ (under normal circumstances) የሚደረግ አይደለም፡፡ ተናዛዡ ይህን የኑዛዜ አይነት የሚያደርገው በቅርብ ጊዜ እሞታለው ብሎ ሲያስብ ለምሳሌ አደጋ ደርሶበት ፅኑ ህመም ውስጥ ሆኖ ሊሆን ይችላል፡፡ እንዲህ ባለጊዜ ሌሎቹን የኑዛዜ አይነቶች ማለትም በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜን ወይም በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜን ለማድረግ ሁኔታዎች አይፈቅዱለትም ማለት ነው፡፡ በመሆኑም በቃል የሚደረግ ኑዛዜ ላይ ተናዛዡ የሚናዘዘው በተገደበ ሁኔታ (restricted testamentary disposition) ይሆናል፡፡ በዚህ የኑዛዜ አይነት ተናዛዡ ሙሉ ፍላጎቱን ለማንፀባረቅ አይችልም፡፡ ምክንያቱም ህጉ ገደቦችን አስቀምጧል፡፡

በፍ/ሕ/ቁጥር 893 መሰረት አንድ ሰው የቃል ኑዛዜ ማድረግ የሚችለው በተለይ በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ ነው፡፡
👉የቀብሩን ሥነ-ሥርዓት የሚመለከቱትን ትዕዛዞች ለመስጠት
 እያንዳንዱ ውርስ ከአምስት መቶ የኢትዮጵያ ብር የማይበልጥ የኑዛዜ ስጦታ ለማድረግ፣
 አካለ መጠን ላላደረሱ ልጆቹ አስተዳዳሪን ወይም ሞግዚትን የሚመለከቱ ውሳኔዎችን ለመስጠት ነው፡፡

በቃል የሚደረግ ኑዛዜ ውስጥ ከብር አምስት መቶ በላይ ኑዛዜ ተደርጎ ከሆነ ከአምስት መቶ ብር በላይ ያለው ተቀናሽ ይሆናል፡፡ በቃል የተደረገ ኑዛዜ ከተደረገበት ከሶስት ወር በኋላ ተናዛዡ በህይወት የቆየ እንደሆነ ኑዛዜው ተፈፃሚ አይሆንም ወይም ፈራሽ ይሆናል፡፡ ምክንያቱም ተናዛዡ ያንያህል ጊዜ ሳይሞት ከቆየ በግልጽ የሚደረግ ኑዛዜን ወይም በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜን ለማድረግ እድል አለው ተብሎ ይገመታል፡፡

በሌላ በኩል ብዙ ኑዛዜዎች ካሉ አብሮ ተፈፃሚ ሊሆኑ በሚችሉበት መጠን ልዩ ልዩ ኑዛዜዎች አብረው ተፈጻሚ ይሆናሉ፡፡ ነገር ግን የሁለት ኑዛዜዎች ቃላት ሁለቱም ሊፈፀሙ ያልቻሉ ወይም የተቃረኑ እንደሆነ በኋላ የተደረገው ኑዛዜ ቅድሚያ ይሰጠዋል፡፡

በአጠቃላይ ንብረቱን በኑዛዜ ማስተላለፍ የሚፈልግ ሰው ሶስቱን የኑዛዜ አይነቶች ፎርማሊቲያቸውን በሟሟላት እንደየሁኔታው ሊጠቀምባቸው ይችላል፡፡ ኑዛዜ አድራጊው የኑዛዜ ቃላት ተፈፃሚነት እንዲያገኙ በህጉ የተቀመጡትን መስፈርቶች በጥንቃቄ መከተል አለበት፡፡ ይህ ካልሆነ ኑዛዜው ውድቅ ስለሚሆን የተናዛዡ ፍላጎት ተፈፃሚ አይሆንም ማለት ነው፡፡

 የኑዛዜ ማስረጃ ወይም ማረጋገጫ

በኑዛዜው የሰፈረውን ቃልና ኑዛዜው መኖሩን ማስረዳት ያለበት በዚህ ኑዛዜ ተጠቃሚ ነኝ የሚለው ሰው ነው፡፡ በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ ወይም በተናዛዡ ፅሁፍ የተደረገ ኑዛዜ መኖር የሚረጋገጠው የኑዛዜውን ፅሁፍ ዋናውን በማቅረብ ወይም ለማዋውል ስልጣን በተሰጠው ሰው ዘንድ ወይም ፍርድ መዝገብ ቤት ሹም ተክክለኛ ሆኖ የተመሰከረ አንድ ግልባጭ በማቅረብ ነው፡፡ ኑዛዜዎቹን ለማስፈፀም በማናቸውም ሌላ መንገድ ለማስረዳት አይቻልም፡፡ ነገር ግን በጥፋት ወይም በቸልተኝነት ኑዛዜው እንዲጠፋ ካደረገ ሰው የጉዳት ኪሳራ ለማግኘት ከሆነ በማናቸውም አይነት መንገድ ኑዛዜዎችን ማስረዳት ይቻላል፡፡

በአጠቃላይ በአንድ ኑዛዜ ተጠቃሚ ነኝ የሚል ሰው ሁለት ነገሮችን በመሰረታዊነት ማስረዳት ያለበት ሲሆን እነሱም በተናዛዡ የተደረገውን ኑዛዜ በማቅረብ የኑዛዜን መኖር እና የኑዛዜውን ይዘት በማስረዳት ማለትም እሱ የኑዛዜው ተጠቃሚ (beneficiary) መሆኑን ማስረዳት ናቸው፡፡

በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልተጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
https://t.me/alehig
https://t.me/lawsocieties
#አለሕግ #ህግ  #AleLaw #አለጠበቃ #አለሕግአማካሪ #አለሕግ ነገረፈጅ #አለShare #lawsocieties
ይህ ለጠቅላላ እውቀት ብቻ ነው።
ለበለጠ መረጃ ህግ ባለሙያ ያማክሩ!
#አለሕግ #AleHig
ሼር ለወዳጅ ዘመድ ጓደኛ።
በጌጣጌጥ ላይ የሚከፈል የኤክሳይስ ታክስ

በኤክሳይዝ ታክስ አዋጅ የአፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 67/2013 መሰረት፡-
‹‹
1. የከበሩ ማዕድናትን (አልማዝ፣ ወርቅ፣ ብር እና ወይም ኦፖል ወ.ዘ.ተ) በከፊል የያዙ ጌጣጌጦች የኤክሳይስ ታክስ ይከፈልባቸዋል፡፡

2. በተራ ቁጥር 1 የተገለጸው ቢኖርም በጌጣጌጥነት ያልተሰራ ጥሬ የከበረ ማዕድን (አልማዝ፣ ወርቅ፣ ብር፣ ኦፖል ከእነዚህ ጋር ተመሳሳይ የሆኑት) የኤክሳይዝ ታክስ አይከፈልበትም፡፡

3. በጌጣጌጥ ላይ የኤክሳይስ ታክስ የመክፈል ግዴታ ጌጣጌጡ እንደ ተመረተ ይቋቋማል፡፡

4. ለጌጣጌጥ አምራቾች ጥሬው የከበረ ማዕድን እንደ ጥሬ እቃ ይቆጠራል፡፡

5. የከበሩ ማእድናትን (አልማዝ፣ ወርቅ፣ ብር፣ ኦፖል ከእነዚህ ጋር ተመሳሳይ የሆኑ) የሚያመርቱ የማእድን ኩባንያዎች ለኤክሳይዝ ታክስ የመመዝገብ ግዴታ የለባቸውም፡፡

6. ጌጣጌጥ የሚያመርቱ ድርጅቶች ያመረቱትን ጌጣጌጥ የሸጡበትን የማስረከቢያ እና የሽያጭ ሰነድ መያዝ አለባቸው፡፡

7. የጌጣጌጥ አምራቾች በተፈቀደለት አምራችነት የመመዝገብ እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታ አለባቸው፡፡

ምንጭ፡- ገቢዎች ሚኒስቴር
#EthiopianBusinessDaily
ይህ መንግስታዊ ነውር ነገ በእያንዳንዳችን ላይ የሚደርስ ነው!

" ከደመወዝ የሚያግድ ደብዳቤው በተፃፈ በ13 ቀኑ ዛሬ ማገጃው ደርሶኛል"

"የአዲስ አበባ መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ጥቁር ልብስ ለብሳችሁ ቢሮ አትገቡም ለምን ተባልን በሚል ድምፄን በማሰማቴ ከስራና ደመወዝ የሚያግድ ደብዳቤው በተፃፈ በ13 ቀኑ ዛሬ ማገጃው ደርሶኛል "
Beletu Zeleke Mersha
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ  #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ #አለ_Share #lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
በቆዳ ስፋታቸው 10 ቀዳሚ የአፍሪካ ሀገራት እነማን ናቸው?

ሰሜን አፍሪካዊቷ አልጀሪያ አልጀሪያ ቀዳ ስትሆን፤ ኢትዮጵያም በዝርዝሩ ተካታለች።

በአፍሪካ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ የሆነችው ሰሜን አፍሪካዊቷ አልጀሪያ ስትሆን 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ስኩዬር ኪሎ ሜትር ስፋት አላት።

ከአልጀሪያ በመቀጠልም በመካከለኛው አፍሪካ የምትገኘው እና የበርካታ አምቅ ማዕድናት ባለቤት የሆነችው ዲሞክራቲክ ኮንጎ በ2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ስኩዬር ኪሎ ሜትር ስፋት ሁለተኛዋ ሀገር ተብላለች።

ዝርዝሩን ይመልከቱ፤ https://am.al-ain.com/article/africa-10largest-countries-by-area
የ12 አመት ህፃን ልጅ ላይ የጋብቻ ስነስረዓት በፈፀመ የ28 አመት ዲያቆን ጌታቸው ላይ የ1 ዓመት ከ8 ወር የእስራት ቅጣት ተወሰነበት ።
...
በምስራቅ ጎጃም ዞን በግንደወይን ከተማ አስተዳደር የ12 አመት ህፃን ልጅ ላይ የጋብቻ ስነስረዓት በፈፀመ የ28 አመት ወጣት ላይ የ1ዓመት ከ8ወር የእስራት ቅጣት የተወሰነበት መሆኑን ፋስት መረጃ ከጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

ተከሳሽ ዲያቆን ጌታቸው አለልኝ አግባብ ባለው የቤተሰብ ህግ ከተፈቀደው ውጭ ለአካለ መጠን ያልደረሰች ልጅ ለማግባት በማሰብ ጥር 6 ቀን 2015 ዓ.ም በግምት ከሌሊቱ 11፡0ዐ ሲሆን በግ / ወይን ከተማ አስተዳደር ዐ1ቀበሌ ልዩ ቦታው አርሴማ ቤተክርስቲያን ውስጥ የግል ተበዳይ የ12 ዓመት ህፃንን በተክሊል ጋብቻ ወይም በሀማኖት ስርዓት ያገባት በመሆኑ ተከሳሽ በፈፀመው ለአካለ መጠን ያልደረሰችን ልጅ ማግባት ወንጀል ዓ/ህግ የሰውና ጋብቻው ሲፈፀም የሚያሳይ የፎቶ ማስረጃ በማያያዝ ክስ መስርቶ ተከሳሽም የዓ/ህግ ክስ በችሎት ተሰጥቶት የዓ /ህግ ክስ በችሎት ተነቦለት ክሱን እንዲረዳው ከተደረገ በኋላ ወንጀሉን መፈፀሙን አምኖ ነገር ግን ህፃናትን ማግባት በቤተክርስቲያ ህግ የተፈቀደ ነው ወንጀል አይደለም በማለት ተከራክሮ ፍ/ቤቱም የህግ ምስክሮችን ሰምቶ በወ/መ/ስ/ስ/ህ/ ቁ113/2 / መሠረት ፍ/ቤቱ ወደ ወንጀል ህግ አንቀጽ 648 /ሀ/በመቀየር እንዲከላከል ቢጠይቀውም ተከሳሽ ግን የመከላከያ ምስክር አቅርቦ የአቃቢ ህግን ማስረጃዎች ባለማስተባበሉ በቀን 13/6/2015 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሹን እና ሌላውን የህብረተሰብ ክፍል ያስተምራል ተብሎ የታሰበውን የአንድ ዓመት ከስምንት ወር ቅጣት ውሳኔ ተላልፎበታል ፡፡
#አለ_ህግ  #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ህግ #አለ_Share #lawsocieties
Dear Colleagues, 
Hawassa University Journal of Law (HUJL) is now accepting submissions for its Special Issue (Vol. VII) in the form of peer-reviewed articles, notes/reflections, book reviews and comments for publication in July 2023. 
The journal invites entries in the following categories:
Articles: 4000 – 12000 words
Comments: 1000 – 4000 words
Book Reviews: 1000 – 3000 words
Reflections: 3000 – 5000 words
All entries, except for book reviews,  must be accompanied by an abstract of 200 words and a list of key terms.
Thematic Areas for the Special Issue:
¨ Special Categories of Employees;
¨ Individual Employment Relation: Formation of Labour contract and related Issues;
¨ Legally stipulated minimum working conditions;
¨ Collective bargaining & Collective agreement;
¨ Dispute Settlement under the Labour laws of Ethiopia;
¨ And other related subjects of labour laws.
Submission deadline for this issue: 27 March 2023

https://t.me/lawsocieties
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
SUBMISSION
HUJL is inviting all interested contributors to submit their scholarly work at Hawassa University Journal of Law website (https://journals.hu.edu.et/hu-journals/index.php/hujl). The link can also be used to access previous volumes and download individual contributions.
In order to make the online submission, authors need to first register with the journal. If already registered, authors can simply log in and begin the five-step process. HUJL recommends that you review the About the Journal page for the journal's section policies, as well as the Author Guidelines
before making your online submissions.
Interested contributors can be provided with detailed submission guidance upon request. Please email us your queries at  hu.journaloflaw@hu.edu.et
For further queries please contact
Dr. Beza Dessalegn (editor-in-chief)
+251911472230
   Email: bezadesy4722@gmail.com  
Yirgalem Germu (managing editor)  
+251912014622
Email: yirgalemg45@gmail.com
 Please feel free to circulate this call with your networks as well
 
With Kind Regards
The HUJL Team
#አለ_ህግ  #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ህግ  #አለ_Share #lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
33 ጠበቆች‼️ፓስተር ቢኒያም 👈
ለአንድ እስረኛ አንድ ጠበቃ በቂ ነበር። ነገር ግን 33 ጠበቆች ቆሙለት። ከእነዚህ መካከል አብዛኛዎቹ ለመናገር እድል አያገኙም።  ከሰዓትም ከሌላውም አንፃር ክርክር የሚያደርጉት ጥቂቶች ብቻ ናቸው።


https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ  #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ #አለ_Share #lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
የኛ #ችሎት
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Lawyer Mike 🔊የህግ ባለሙያ)
በጣም ጠቃሚ ሰበሮች ስለ ውል ህጎች

የሰበር መዝገብ ቁጥር 26565
ሊፈጠር ወይም ሊከሰት እንደሚችል ቀድሞ ሊገመት ወይም ሊታሰብና ጥንቃቄ ሊደረግበት የሚቻል ሁኔታ ድንገተኛ ደራሽ ቢሆን እንኳ ከአቅም በላይ የሆነ ሁኔታ (Force majeure) ተብሎ የማይወሰድ ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ ህ/ቁ. 1792(2)

የሰበር መዝገብ ቁጥር 29369
የባለዕዳው ቀጥተኛ የውል ፈፃሚነት ከውሉ ባህሪ አኳያ ማስፈፀም አለመቻል ውሉ እንዲሰረዝ መጠየቅ ሳያስፈልግ ኪሣራ ካለ መጠየቅ ስለመቻሉ ( በውል መሠረት ግዴታውን ያልተወጣ ወገንን አስገድዶ ለማስፈፀም የማይቻል በሆነ ጊዜ በውሉ ግዴታውን የተወጣው ወገን ውሉ ባለመፈፀሙ ምክንያት የደረሰውን ኪሣራ ለመጠየቅ ስለመቻሉ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 1771(1) እና (2)

የሰበር መዝገብ ቁጥር 30947
የስልክ ክፍያ እንዲከፈል ለተገልጋይ የተሰጠ ማስታወቂያ ክፍያው እንዲከፈል ለማድረግ እንጂ ክፍያውን ላለመፈፀም ምክንያት ሊሆን አለመቻሉ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 1901

የሰበር መዝገብ ቁጥር 31480
ለአቅመ አዳም ካልደረሰ ልጅ ጋር የሚደረግ የመያዛ ውል ተፈፃሚ የማይሆን ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 2187/1

የሰበር መዝገብ ቁጥር 12719
በሁለት ወገኖች መካከል የተፈረመ ሰነድን እንደ ህጋዊ ስምምነት ለመውሰድ የፈራሚ ወገኖችን ሃሳብና ፍላጐት መመርመር አስፈላጊ ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ 1734, 1952/1/

የሰበር መዝገብ ቁጥር 20232
የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች የተዋዋይ ወገኖች መብትና ግዴታዎች የሚፈጠሩባቸውና የሚረጋገጡባቸው በመሆናቸው የውል ህግ መሰረታዊ ድንጋጌዎች መሟላታቸው አስፈላጊ ሁኔታ ስለመሆኑ የንግድ ህግ ቁ. 715, የፍ/ብ/ሕ/ቁ. 1706, 1679

የሰበር መዝገብ ቁጥር 22448
ፍርድ እንዲፈፀም ለመጠየቅ ችሎታ ያለው ፍርድ የተፈረደለት ሰው /ወገን/ ብቻ ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ ህ/ቁ. 378/1/

የሰበር መዝገብ ቁጥር 24974
በውል ከተገባ ግዴታ አመዛኙ ክፍል ተፈፀመ ወይም/እና አይነተኛ የሆነ የውል መጣስ ተከስቷል ለማለት ባልተቻለ ጊዜ ውል እንዲሰረዝ ለመወሰን የማይቻል ስለመሆኑየፍ/ብ/ህ/ቁ. 1771,1784, 1785

የሰበር መዝገብ ቁጥር 26996
ውል የተደረገበት ጉዳይ ሊፈፀም የማይችል ሆኖ በተገኘ ጊዜ ተዋዋይ ወገኖችን ወደ ነበሩበት ቦታ የመመለስ ውጤት ያለው ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 1715, 1815

የሰበር መዝገብ ቁጥር 27349
ተዋዋይ ወገኖች በመካከላቸው የሚፈጠርን አለመግባባት በስምምነት ወይም ደግሞ በአስታራቂ አማካኝነት ለመፍታት የተስማሙ ከሆነ ይኼው ስምምነት ተፈፃሚ መሆን ያለበት ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 1765, 1731/1/
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Lawyer and Consultant)
ውል መሰረዝ፤
ማፍረስ እና በስምምነት ማቋረጥ
ውል መሰረዝ

ከተዋዋይ ወገኖች መካከል አንደኛው እንደ ውሉ ባለመፈጸሙና የውሉን ግዴታ በመጣሱ በተዋዋዩ ወይም በፍርድ ቤት ውሉን ወይም በውሉ የተቋቋሙትን ግዴታዎች ቀሪ ማድረግ
ውል የሚሰረዘው ከመሠረቱ ግድፈት ስላለው አይደለም፡፡ ይልቁንም የውል መሠረዝ ምክንያት ከተዋዋይ ወገኖች የውል ግዴታን ከመፈፀምና ካለመፈፀም ጋር ተያይዞ የሚከሠት ነው፡፡ የውል መሠረዝ ሥርዓትም የራሱ የሆነ አካሄድ አለው፡፡ ይኸውም ውሉን የመሠረዝ ፍላጐት ያለውን ወገን የውሉ ግዴታ ባለመፈፀሙ የተነሳ ከህግ ወይም ከውሉ ከራሱ ባገኘው መብት ተጠቅሞ ውሉን ሊሰርዝ ይችላል፡፡ ይህ መብት ተግባራዊ የሚሆንበት አጋጣሚም ግዴታው ባለመፈፀሙ የተነሳ የደረሰውን ጉዳት ከማረጋገጥ ጋር ተያይዞ የሚታይ እንጂ ጥያቄ አቅራቢው ሁል ጊዜ ተቀባይነት የሚያገኝበት አይደለም፡፡ በመሆኑም የውል ይሰረዝልኝና ተያያዥነት ያላቸው ጥያቄዎች በህጉ አግባብ የሚስተናገዱ ስለመሆኑ የፍ/ህ/ቁ. 1784 እና ተከታዮቹ ድንጋጌዎች ያስገነዝባሉ፡፡
ሰ/መ/ቁ. 32299 ቅጽ 8
ውል በተናጠል መሰረዝ
አንደኛው ተዋዋይ ወገን የፍታብሓር ሕግ ቁጥር 1787 ድንጋጌን መሠረት በማድረግ ውልን በተናጠል ለመሠረዝ የሚችለው ከሚከተለት ሶስት ሁኔታዎች አንደኛው የተሟላ መሆኑን ለማስረዳት ሲችል ነው፡፡
• የመጀመሪያው ባለዕዳው በውሉ ላይ በተመለከተው መሠረት የውሉን ግዴታ የሚፈፅምበት ቁርጠኛ ጊዜ በውሉ ላይ በግልፅ ተመልክቶ እንደሆነና በውሉ ላይ የተገለፀው ቁርጥ የሆነ የውል መፈፀሚያ ጊዜ ያለፈ እንደሆነ ነው፡፡ በዚህ ሁኔታ አንደኛው ተዋዋይ ወገን በተናጠል ውሉን ለመሰረዝ የሚችል መሆኑን የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1787 እና የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1775(ለ) ድንጋጌዎች በማገናዘብ ለመረዳት ይቻላል፡፡
• ሁለተኛው ምክንያት ባለዕዳው ውሉን ያልፈፀመበትን ምክንያትና ሌሎች የአካባቢ ሁኔታዎችን በማገናዘብ ዳኞች ባለዕዳው ውሉን የሚፈፅምበት የችሮታ ጊዜ ከሰጡት በኋላ ባለእዳው በዳኛ ውሣኔ በተሰጠው የችሮታ ጊዜ ውስጥ ግዴታውን ሳይፈጽም የቀረ እንደሆነ መሆኑን ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1787 እና ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1770 ድንጋጌዎች ለመረዳት ይቻላል፡፡
ሶስተኛው ባለገንዘቡ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1774 በተደነገገው መሠረት ሌላኛው ተዋዋይ (ባለዕዳው) በውል የገባውን ግዴታ የሚፈፅምበትን ጊዜ በመግለፅ ማስጠንቀቂያ የሰጠ ሲሆንና በማስጠንቀቂያው በተሰጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ሳይፈፅም ሲቀር መሆኑን ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1774 እና ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1787 ድንጋጌ ለመረዳት ይቻላል፡፡ አንደኛው ተዋዋይ ወገን ሌላኛው ተዋዋይ ወገን በውሉ መሠረት እንዲፈፅም ለመጠየቅና ማስጠንቀቂያ ለመስጠት የሚችለው በመጀመሪያ እሱ የበኩሉን ግዴታ የፈፀመ ወይም ለመፈፀም የተዘጋጀ ሲሆን እንደሆነ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1857 በግልፅ ይደነግጋል፡፡
ስለሆነም ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1787 ድንጋጌ መሠረታዊ ዓላማና ግብ እንደዚሁም የድንጋጌውን የተፈፃሚነት ወሰን ለመረዳት የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1787 ድንጋጌ ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1771 ንዑስ አንቀጽ 1 እና ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1757 ድንጋጌዎች ጋር በማጣመር መመርመር ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ አንፃር ስንመዝነው አንደኛው ተዋዋይ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1771 ንዑስ አንቀጽ 1 ሌላኛው ተዋዋይ ውሉን እንዲፈፅምለት ለመጠየቅ፤ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1774 ድንጋጌዎች መሠረት የውል መፈፀሚያ ጊዜ ግልፅ ማስጠንቀቂያ በመስጠትና በፍትሐብሔር ቁጥር 1787 በተደነገገው መሠረት ውሉን በተናጠል ለመሠረዝ በመጀመሪያ በእሱ በኩል በውል የተጣለበትን ግዴታ የፈፀመ ወይም ለመፈፀም ዝግጁ መሆኑ በማስረጃ ለማረጋገጥ የቻለ መሆን እንዳለበት የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1771፣ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1774፣ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1757 እና የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1787 ድንጋጌዎችን ይዘትና መሠረታዊ ግብ በማገናዘብ ለመረዳት ይቻላል፡፡
ሕግ አውጭው በውል ለገባው ግዴታ ተገዥ በመሆን በእሱ በኩል ያለውን ግዴታ ያልፈፀመ ወይም ለመፈፀም ዝግጁ መሆኑን በበቂ ሁኔታ ለማረጋገጥ ያልቻለ አንድ ተዋዋይ ወገን ሌላኛውን ተዋዋይ ወገን ቀድሞ ማስጠንቀቂያ በመስጠት ውሉን በተናጠል እንዲሰርዝ በማሰብ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1787 ድንጋጌን አውጇል ተብሎ አይገመትም፡፡ አንድ ተዋዋይ የውሉን መፈፀሚያ የጊዜ ገደብ በመግለጽ ለሌላኛው ወገን ማስጠንቀቂያ በመስጠት ውል በተናጠል ለመሰረዝ የሚችለው በመጀመሪያ እሱ በውሉ የገባውን ግዴታ የፈፀመ ወይም ለመፈፀም ዝግጁ መሆኑ ሲረጋገጥ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 57280 ቅጽ 13፣ ፍ/ህ/ቁ. 1770፣ 1771፣ 1774፣ 1757፣ 1787
ውል ማፍረስ
በህጉ የተቀመጡት የውል አመሰራረት መስፈርቶችን ያለሟላና ግድፈት ያለበት በመሆኑ የተነሳ የውሉ ወይም በውሉ የተቋቋሙትን ግዴታዎች መቅረት
ውል ማፍረስና ውል መሠረዝ በውል የተቋቋሙት ግዴታዎች ከሚቀሩባቸው መንገዶች ውስጥ የሚካተቱ ቢሆንም ምክንያታቸውና ውጤታቸው የተለያዩ ነው፡፡ የውል ማፍረስ ከውል አመሠራረት ጋር ተያይዞ የሚነሳ ሲሆን ሲሆነ
ውሉ ከአመሰራረቱ በህጉ የተመለከቱትን ሁኔታዎች ባለማሟላቱ ግድፈት ያለበት መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡ በሌላ በኩል የውል መሰረዝ ጉዳይ ከውል አመሰራረት ችግር የሚነሳ ሳይሆን ከተዋዋይ ወገኖች የውል ግዴታውን ካለመወጣት የሚመነጭ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 32299 ቅጽ 8
ውል በስምምነት ማቋረጥ /ቀሪ ማድረግ/
ተዋዋይ ወገኖች በውል አቋቁመውት የነበረውን ግዴታ በፍታሐብሔር ሕግ ቁጥር 1819 ንዑስ አንቀጽ 1 መሠረት በስምምነት ቀሪ ሲያደርጉ የተለየ ፎርም መከተል እንዳለባቸው የሚደነግግ አስገዳጅ ድንጋጌ የለም፡፡ የውለታ በተዋዋዮች ስምምነት መቋረጥ (terminate) መደረግ ከውል መፍረስ ወይም ከውል መሠረዝ የተለየ ባህሪና ውጤት ያለው መሆኑን አግባብነት ያላቸውን የፍታብሔር ድንጋጌዎች ይዘት በማገናዘብ ለመረዳት ይቻላል፡፡ እንደዚሁም ውል በስምምነት ቀሪ ማድረግ (termination of contract) ውልን ከማሻሻል (ውል ከመለወጥ) (variation of contract) እና ውል ከመተካት (Novation of contract) የተለየ ባህሪ፣ ይዘትና ውጤት ያለው መሆኑን፣ የፍታሐብሔር ሕግ ቁጥር 1819 እና ተከታይ ድንጋጌዎችን፣ የፍታብሔር ሕግ ቁጥር 1722 እና የፍታብሔር ሕግ ቁጥር 1826 እና ተከታይ ድንጋጌዎችን ይዘት በማገናዘብ ለመረዳት ይቻላል፡፡
የውሉ በተዋዋዮቹ ፈቃድና ስምምነት መቋረጥ (ቀሪ) መሆን የተዋዋይ ወገኖች የወደፊት የውል የመፈፀም ግዴታ የሚያስቀር መሆኑን የፍታብሔር ሕግ ቁጥር 1819 ንዑስ አንቀጽ 2 ይደነግጋል፡፡ እንደዚሁም የውሉ መቋረጥ /ቀሪ/ መሆን ያለፈውን ሁኔታ የማይነካ መሆኑን የፍታብሔር ሕግ ቁጥር 1819 ንዑስ አንቀጽ 3 ይደነግጋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የውል ቀሪ መሆን (termination of contract) ተዋዋዮቹ በውል አቋቋመውት የነበረውን መብትና ግዴታ ቀሪ የማድረግ ውጤት የሚኖረው መሆኑን ከፍታብሔር ሕግ ቁጥር 1807 /ለ/ ድንጋጌ ይዘት መንፈስና ዓላማ በማገናዘብ ለመረዳት ይቻላል፡፡
ሰ/መ/ቁ. 63063 ቅጽ 14፣ ፍ/ህ/ቁ. 1682-84፣ 1722
በአብላጫ ድምፅ የተሰጠ
#ethiolawtips
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties