አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.83K photos
25 videos
1.86K files
3.55K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
Forwarded from 🇪🇹የሕግ ጉዳይ (Alemwaza)
#እናትነት_እና_አባትነት
“እናትነት እውነት ነው ፡ አባትነት እምነት ነው”
#ስለ_እናትነት
የተፈጥሮ ጉዳይ ሆኖ ለሴቶች ልጅን አርግዞ መውለድ በተፈጥሮ የተሰጠ ፀጋ በመሆኑ አንድ ልጅ ተወልዶ ወደዚህች ምድር ሲቀላቀል እናቱ ማናት የሚል ጥያቄ ሊነሳ አይችልም ፡ ምክንያቱም እናቱ አርግዛ የወለደችው ንትና ፡፡ በቤተሰብ ህጉ አንቀፅ 124 መሰረት እናት ፡ ልጁን የወለደችው በመሆኗ ብቻ እናትነቷ ይታወቃል ይላል ፡፡ በመሆኑም በቤተሰብ ህጉ ላይ አባትነትን ወደመቀበል ወይም አባትነትን በፍርድ ቤት ውሳኔ ስለማሳወቅ የሚሉ ጉዳዮች ለአባት ብቻ እንጂ ለእናት የሚሰራ ፅንሰ ሀሳብ አይደለም ፡፡ እናት የወለደችው ልጅ ልጇ በመሆኑ እንድትቀበል ምንም አይነት ፍቃድ የማያስፈልግ ሲሆን ፡ የወለደችውን ልጅ አባት በሚመለከት የእሷ ስምምነት እና እምነት ያስፈልጋል ፡፡ ለዚህም ነው በቤተሰብ ህጉ ውስጥ እናት ልጇን ፈቅዳ የምትቀበልበት ወይም የማትቀበልበት ስርአት የሌለው ማለት ነው ፡፡

#ስለ_አባትነት
አባትነትን በእርግጠኝነት ፡ ማወቅ አስቸጋሪ የሚሆንባቸው ተፈጥሮአዊ አጋጣሚዎች በርካታ በመሆናቸው ፡ አባትነትን ልክ እንደ እናትነት በእርግጠኝነት ማወቅ ሁል ግዜ ቀላል አይሆንም ፡፡ ለዛም ነው ፡ እናትነት እውነት ነው ፡ አባትነት እምነት ነው የሚባለው ፡፡ በቤተሰብ ህጉ አንቀፅ 125 መሰረት የአንድ ልጅ አባት ሊታወቅ የሚችለው በሶስት ምክንያቶች መሆኑን ያስገነዝበናል ፡፡ እነሱም
1, ልጅ በሚፀነስበት ወይም በሚወለድበት ጊዜ በእናትየዋና በአንድ ወንድ መካከል በህግ የታወቀ ግንኙነት መኖሩ በመረጋገጡ ምክንያት አባትነት ይታወቃል (የሕግ ግምት [ከአንቀፅ 126 -130])፡፡
2, አባትየው ልጁን ልጄ ሲል በመቀበሉ ምክንያትም አባትነት ሊታወቅ ይችላል፡፡ (ልጅን መቀበል [ከአንቀፅ 131 -142])
3, በፍርድ ቤት በሚሰጥ ውሳኔም አባትነት እንዲታወቅ ሊደረግ ይችላል፡፡ (የፍርድ ቤት ዉሳኔ ናቸዉ፡፡[ከአንቀፅ 143 -145])

በ ቁጥር አንድ ስር በህግ የታወቀ ግንኙነት ሲባል በባህል ፡ በሀይማኖት ወይም በክብር መዝገብ ሹም ጋብቻቸውን በፈፀሙት ባልና ሚስት አማካኝነት ስለሚፀነሰው ወይም ስለሚወለደው ልጅ የሚመለከት ነወ ፡፡ ይህ ማለት ግን ፡ እንደ ባልና ሚስት ሆነው በሚኖሩት ሰዎች መካከል ስለተፀነሰው ወይም ስለተወለደው ልጅ ህጉ እውቅና አይሰጥም ማለት አይደለም ፡፡ ለሁለቱም አይነት ቤተሰባዊ ግንኙነቶች ፡ አባትነት ሊረጋገጥ ይችላል ፡፡ ቀጥለን አባትነት የሚረጋገጥባቸው መንገዶች እንመለከታለን ፡፡

#አባትነት_የሚረጋገጥባቸው_መንገዶች
ቀጥለው ባሉት ዘዴዎች አባትነት የሚረጋገጠው የልጅ የተፈጥሮ አባት /biological father/ ነው፡፡ ይህም ከልጅ እናት ጋር ፆታዊ ግንኙነት በመፈፀም ልጁ እንዲወለድ ምክንያት የሆነውን አባት ማረጋገጥ ይሆናል፡፡ በትክክለኝነት ለማረጋገጥ አስቸጋር በመሆኑ ይህንን ሁኔታ ለማረጋገጥ ሕጉ የተለያዩ ዘዴዎችን ይጠቀማል፡፡

ሀ. #የሕግ_ግምት
የሕግ ግምት መሠረት የሚያደርገው ልጁ በሚፀነስበት ወይም በሚወለድበት ጊዜ በእናትና በአንድ ወንድ መካከል በሕግ የታወቀ ግንኙነት መኖርን በማረጋገጥ ነዉ፡፡ ይህም ልጁ ሲፀነስ ወይም ሲወለድ ከልጅ እናት ጋር በጋብቻ የነበረ ባል ወይም ጋብቻ ሳይፈጽም አብሯት የነበረው ወንድ የልጅ አባት ነዉ ብሎ ሕጉ ግምት ይወስዳል፡፡ በመሆኑም በልደት ምስክር ወረቀት አባቱ ሌላ ነው ተብሎ ቢፃፍም እንኳን ይህ የሕጉ ግምት አይቀየርም፡፡
ልጅ የተፀነሰው በጋብቻ ወይም አብሮ በኖሩበት ጊዜ ውስጥ ነው የሚባለው ጋብቻው ከተፈጸመበት ወይም አብሮ መኖር ከተጀመረበት ከ180 ቀናት በኋላ ልጅ ሲወለድ መሆኑ በሕጉ በግልጽ ተመልክቷል፡፡ እንዲሁም ጋብቻው ፈርሶ ወይም አብሮ መኖር አብቅቶ ከሆነ ከፈረሰበት ወይም ካበቃበት ቀን ጀምሮ በ300 ቀናት ዉስጥ ልጅ የተወለደ እንደሆነ ነው፡፡ በመሆኑም የልጅ አባት የሚባለዉ በተመለከቱ ጊዜያት ከልጅ እናት ጋር አብሮ ያለው ወይም የነበረ ሰው ነው፡፡ ይህንን የሕጉን ግምት በሌላ ማስረጃ ማስተባበል አይቻልም፡፡,የሕግ ግምት [ከአንቀፅ 126 -130]

ለ. #ልጅነትን_ስለመቀበል
በመቀበል አባትነት የሚረጋገጠዉ አባትየዉ ልጁን ልጄ ነዉ ብሎ በሚሰጠዉ ማረጋገጫ ስያረጋግጥ ነዉ፡፡ የአነባትነት ማረጋገጫ በመስጠት አባትነት የሚረጋገጠዉ የልጅ አባት በሕግ ግምት ለመረጋገጥ የማይቻል ሲሆን ነዉ፡፡ ይህ ሊሆን የሚችለዉ ልጁ የተፀነሰዉ ወይም የተወለደዉ እናት ከአንድ ወንድ ጋር በጋብቻ ወይም ያለጋብቻ በአብሮ መኖር ሥርዓት ሳትመሰርት ልጅ ሲወለድ ነዉ፡፡ በእንዲህ ባለ ሁኔታ አንድ ሰዉ አንድን የተፀነሰ ወይም የተወለደ ልጅ የእርሱ ልጅ መሆኑን አምኖ በመቀበል ቃሉን የሰጠ እንደሆነ የልጁ አባት ይባላል፡፡
መቀበሉን የሚገልጽበት ፎርም ወይም ሥርዓት በክብር መዝገብ ሹም ፊት በመቅረብ በሚሰጠዉ ቃል ወይም በጽሑፍ በሚያደርገዉ ኑዛዜ ወይም በሌላ በማናቸዉም ሥልጣን በተሰጠዉ ባለስልጣን በተረጋገጠ ሠነድ አማካኝነት ነዉ፡፡
በመርህ ደረጃ የመቀበል ቃሉን መስጠት ያለበት አባት ብቻ ነዉ፡፡ አባትየዉ ሞቶ ከሆነ ወይም ፈቃዱን ለመስጠት የማይችል በሆነ ጊዜ ከአባትየዉ ወላጆች አንዱ በእርሱ ስም ልጁን ሊቀበል ይችላል፡፡ አባት ነኝ ባዩ ቃሉን በሚገባዉ ሥርዓት ቢሰጥም እንኳን የልጁ እናት የተቀባዩ አባት እዉነተኝነት ያለዉ መሆኑን ካላመነች የተሰጠዉ ቃል በሕግ ፊት ዉጤት የለዉም፡፡ ይህ ማረጋገጫ ሳትሰጥ እናት ሞታ ወይም ፈቃድ መስጠት የማትችል ከሆነች ከእናት ወላጆች በአንዱ ሊሰጥ ይችላል፡፡ በመርህ ደረጃ አባትነት መቀበል የሚቻለዉ የልጁ በሕይወት እያለ ብቻ ነዉ፡፡ ልጅን መቀበል [ከአንቀፅ 131 -142]

ሐ. #በፍርድ_ቤት_ዉሳኔ_አባትነትን_ማወቅ
በሕግ የታወቀ ግኙኝነት ሳይኖር የሚወለድ ልጅ አባት ባይ ሰዉ በፈቃዱ ካልተቀበለ አባት የሚያጣበት ሁኔታ መኖሩ እሙን ነዉ፡፡ በመሆኑም በመካድ ወይም ባለመቀበል አባትነትን የሚያጡ ልጆች በፍርድ ቤት በሚሠጥ ዉሳኔ አባት እንዲያገኙ ህጉ ይኸንን ሶስተኛዉን ዘዴ አስቀምጧል፡፡

አባትነት በፍ/ቤት በሚሰጥ ዉሳኔ እንዲረጋገጥ: መሟላት ያለባቸዉ ሁኔታዎችም፤
ሀ. ልጁ በተፀነሰበት ጊዜ በእናቲቱ ላይ የመደፈር ወይም የመጠለፍ ተግባር የተፈጸመባት ሲሆን፣
ለ. ሆነ ተብሎ በተደረገ የተንኮል ድርጊት ሥልጣንን ያለ አግባብ በመጠቀም አገባሻለሁ በማለት ተስፋ ቃል በመስጠት ወይም በሌላ ተመሳሳይ መንገድ ልጁ በሚፀነስበት ጊዜ ከእናት ጋር ፆታዊ ግኝኙነት የተፈጸመባት ሲሆን
ሐ. አባት ነዉ በተባለዉ ሰዉ የተጻፈና በማያሻማ ሁኔታ አባትነቱን የሚያረጋግጡ ደብዳቤዎች ወይም ሌሎች ጽሑፎች ሲኖሩ፣
መ. በሕግ የታወቁ ግንኙነት ሳይኖራቸዉ የልጁ እናትና አባት የተባለዉ ሰዉ በሕግ በተመለከተዉ የእርግዝና ጊዜ ቀጣይነት ባለዉ ሁኔታ በግብረ ሥጋ ግንኙነት አብረዉ የኖሩ እንደሆነ ነዉ፡፡
ከእነኝህ ከአምስቱ ሁኔታዎች በአንዱ ምክንያት ልጅ ተፀንሶ ከሆነ በድርጊቱ ላይ የነበረዉ ወንድ አባት ተብሎ በፍርድ ቤት ይወሰናል፡፡ የፍርድ ቤት ዉሳኔ ናቸዉ፡፡[ከአንቀፅ 143 -145]
by

#ሳሙኤል_ግርማ
#የሕግ_አማካሪ_እና_ጠበቃ

https://telegram.me/Ethiopian_Legal_Advocate
ስለወጭና ስለኪሳራ /በክርክሩ ምክንያት የወጡ ወጪዎች የሚመለከተው ወገን/
🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸
#ስለ ፍርድ ቤቱ ሥልጣን
በሌላ አኳኋን እንዲፈጸም በግልጽ ካልተደነገገ በቀር በክስ ምክንያት ስለሚከፈለው ስለማናቸውም ወጭና ኪሳራ፣ የሚከፈለውን ወገን የወጭንና የኪሳራውን ልክ የሚከፈልበትን የሃብት ምንጭ የአከፋፈሉን ሁኔታ ሌላውንም ተገቢ መስሎ የታየውን ውሳኔ ወይም ትእዛዝ ፍርድ ቤቱ ትክክል በስሎ በሚገመተው ሁኔታ ሊሰጥ ይችላል፡፡
#ስለወጭና ስለኪሳራ ዝርዝር
ተረቺው ለረቺው ኪሳራና ማናቸውንም ወጭ እንዲከፍል ፍርድ ቤቱ ሲያዝ፣ ወጭ ያደረገው ወገን የወጭውን ልክ የሚያሳይ ዝርዝር አዘጋጀቶ ማቅረብ አለበት፡፡
ዝርዝር የሚቀርበው ፍርዱን ለፈረደው ፍርድ ቤት ሲሆን አንዱ ግልባጭ ለከፋዩ ወገን ይሰጣል፡፡
#የወጭው ሂሳብ ስለሚመረመርበት ሁኔታ
የወጭው ሂሳብ ዝርዝር ለፍርድ ቤቱ ከቀረበ በኋላ ትክክለኛነቱ የሚመለመርበትን ቀን ቀጠሮ ወስኖ ባለጉዳዮቹ እንዲቀርቡ ያዛል፡፡
ሂሳቡን መርምሮና ተከራካሪዎቹ ወገኖች የሚያቀርቡትን ሃሳብ ተቀብሎ ከዚህ ቀጥሎ የተመለከቱትን ይፈጽማል፡፡
በቀረበው የሂሳብ ዝርዝር ውስጥ በቂ ባልሆነ ምክንያት ከፍ ብሎ የሚታየውን ገንዘብ ይቀንሳል፡፡ ወይም
በዝርዝሩ ውስጥ የክሱን ጉዳይ ለማስፈጽም ወይም አስፈላጊውን ዳኝነት ለመከታተል ተገቢ ያልሆነ ወጭ ተመልክቶበት የተገኘ እንደ ሆነ ፍርድ ቤቱ ሊቀንሰው ወይም ሊያስቀረው ይችላል፡፡
ወጭው ወይም ኪሳራው ሊከፍለው የሚገባው ወገን የሚጠይቀውን የወጭ ዝርዝር ያላቀረበ እንደ ሆነ ፍርድ ቤቱ ይህንኑ መዝግቦ ሌሎች ወገኖች ያደረጉትን ወጭ መርምሮ ያረጋግጥላቸዋል፡፡ ወይም የሂሳቡን ዝርዝር አንዱ ወገን ባለማቅረቡ ምክንያት ሌሎች ወገኖች እንዳይጎዱ ላላቀረበው ወገን ተገቢ ግምት ያለው ኪሳር ይወስንለታል፡፡
ማንኛውም የወጭ ወይም የኪሳራ ገንዘብ በፍርዱ መሰረት እስኪፈጸም ድረስ ዋናው ፍርድ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በሕግ የተወሰነ ወለድ ይታሰብበታል፡፡
ፍርድ ቤቱ በኪሳራና በወጭ አከፋፈል ምክንያት ለተነሳው ክርክር ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊት የፍርድ ቤቱ ሬዢስትራር ወይም የምግብ ቤቱ ሹም የቀረበውን ዝርዝር መርምሮና ተከራካሪዎቹ ወገኖች የሚያቀርቡትን አሳብ ተቀብሎ የተጣራውን ሂሳብ እንዲያቀርብለት ከማዘዝ የዚህ ቁጥር ድንጋጌ አያግደውም፡፡
#ካሳ ስለሚከፈልበት ምክንያት
በማንኛውም ክስ ወይም ክርከር ላይ በክስ ወይም በመከላከያ መልክ ከሳሹ ወይም ተከሳሹ ያቀረበው የመከራከሪያ ወይም የመከላከያ ማስረጃ ወይም ክርክሩ ራሱ ወይም ማስረጃው አሰተኛ ነው ወይም መከራከሪያውንና አሰተኛ ማስረጃ ያቀረበው ወገን በሐሰት የተከራካሪውና አሰተኛ ማስረጃ ያቀረበው ክርክሩን ለማሰናከል፣ ጊዜ ለመፍጀት ወይም አንደኛውን ወገን ለመበደል ወይም ለማጉላላተር ሆነ ብሎ ያደረገው ነው በማለት ወይም የክርክሩንና የማስረጃውን አሰተኛነት እያወቀ ወይም ማወቅ ሲገባው ሆን ብሎ ማቅረቡን ሲያመለክትና ፍርድ ቤቱም ተቃዋሚው ወገን ያቀረበውን ነገር እርግጠኛነት ሲረዳው ይህንኑ በመዝገቡ ላይ አስፍሮ አሰተኛ ማስረጃ ወይም ክስ ወይም መከላከያ ያቀረበው ወገን ላቀረበው ለእያንዳንዱ ሀሰተኛ ማስረጃአንዱን ወገን ለመበደል፣ ለማጉላላት ወይም ጊዜ ለመፍጀት ላቀረበው አሰተኛ ክርክር ከማናቸውም ኪሳራና ከሌላው ወጭ በቀር ከ500 ብር የማይበልጥ ካሳ ለተበዳዩ እንዲከፈል ሊወስንበት ይችላል፡፡
#ይህም በወንጀለኛ መቅጫ ሕግ በቁጥር 446 በተመለከተው መሰረት ሃሰተኛ ማስረጃና ክርክር በማቅረቡ ከመከሰስና ከመቀጣት ነፃ ሊሆን ይችላል፡፡
ካሳ የተወሰነለት ወገን በሀሰት በመከሰሱ ወይም ሃሰተኛ መከላከያ ወይም ክስ የቀረበበት በመሆኑ ካሳና ኪሳራ ይገባኛል ሲል ሌላ ክስ አቅርቦ ካሳ ወይም ኪሳራ የተወሰነለት እንደሆነ በመጀመሪያው ክስ ላይ ከሚወስንለት ኪሳራና ካሳ ላይ ይቀነስበታል፡፡
#ስለ ይግባኝ
ማንኛውም ተከራካሪ ወገን በስረ ነገሩ ላይ ይግባኝ ባያቀርብም፣ በተወሰነበት የወጭ ወይም የኪሳራ አከፋፈል ብይን ላይ ይግባኝ ለማለት ይችላል፡፡ በዚህም ነገር ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት የሚሰጠው ውሳኔ የመጨረሻ ይሆናል፡፡
ስለወጭና ስለኪሳራ /በክርክሩ ምክንያት የወጡ ወጪዎች የሚመለከተው ወገን
#አለ_ህግ
#ስለ ፍርድ ቤቱ ሥልጣን
በሌላ አኳኋን እንዲፈጸም በግልጽ ካልተደነገገ በቀር በክስ ምክንያት ስለሚከፈለው ስለማናቸውም ወጭና ኪሳራ፣ የሚከፈለውን ወገን የወጭንና የኪሳራውን ልክ የሚከፈልበትን የሃብት ምንጭ የአከፋፈሉን ሁኔታ ሌላውንም ተገቢ መስሎ የታየውን ውሳኔ ወይም ትእዛዝ ፍርድ ቤቱ ትክክል በስሎ በሚገመተው ሁኔታ ሊሰጥ ይችላል፡፡
#ስለወጭና ስለኪሳራ ዝርዝር
ተረቺው ለረቺው ኪሳራና ማናቸውንም ወጭ እንዲከፍል ፍርድ ቤቱ ሲያዝ፣ ወጭ ያደረገው ወገን የወጭውን ልክ የሚያሳይ ዝርዝር አዘጋጀቶ ማቅረብ አለበት፡፡
ዝርዝር የሚቀርበው ፍርዱን ለፈረደው ፍርድ ቤት ሲሆን አንዱ ግልባጭ ለከፋዩ ወገን ይሰጣል፡፡
#የወጭው ሂሳብ ስለሚመረመርበት ሁኔታ
የወጭው ሂሳብ ዝርዝር ለፍርድ ቤቱ ከቀረበ በኋላ ትክክለኛነቱ የሚመለመርበትን ቀን ቀጠሮ ወስኖ ባለጉዳዮቹ እንዲቀርቡ ያዛል፡፡
ሂሳቡን መርምሮና ተከራካሪዎቹ ወገኖች የሚያቀርቡትን ሃሳብ ተቀብሎ ከዚህ ቀጥሎ የተመለከቱትን ይፈጽማል፡፡
በቀረበው የሂሳብ ዝርዝር ውስጥ በቂ ባልሆነ ምክንያት ከፍ ብሎ የሚታየውን ገንዘብ ይቀንሳል፡፡ ወይም
በዝርዝሩ ውስጥ የክሱን ጉዳይ ለማስፈጽም ወይም አስፈላጊውን ዳኝነት ለመከታተል ተገቢ ያልሆነ ወጭ ተመልክቶበት የተገኘ እንደ ሆነ ፍርድ ቤቱ ሊቀንሰው ወይም ሊያስቀረው ይችላል፡፡
ወጭው ወይም ኪሳራው ሊከፍለው የሚገባው ወገን የሚጠይቀውን የወጭ ዝርዝር ያላቀረበ እንደ ሆነ ፍርድ ቤቱ ይህንኑ መዝግቦ ሌሎች ወገኖች ያደረጉትን ወጭ መርምሮ ያረጋግጥላቸዋል፡፡ ወይም የሂሳቡን ዝርዝር አንዱ ወገን ባለማቅረቡ ምክንያት ሌሎች ወገኖች እንዳይጎዱ ላላቀረበው ወገን ተገቢ ግምት ያለው ኪሳር ይወስንለታል፡፡
ማንኛውም የወጭ ወይም የኪሳራ ገንዘብ በፍርዱ መሰረት እስኪፈጸም ድረስ ዋናው ፍርድ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በሕግ የተወሰነ ወለድ ይታሰብበታል፡፡
ፍርድ ቤቱ በኪሳራና በወጭ አከፋፈል ምክንያት ለተነሳው ክርክር ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊት የፍርድ ቤቱ ሬዢስትራር ወይም የምግብ ቤቱ ሹም የቀረበውን ዝርዝር መርምሮና ተከራካሪዎቹ ወገኖች የሚያቀርቡትን አሳብ ተቀብሎ የተጣራውን ሂሳብ እንዲያቀርብለት ከማዘዝ የዚህ ቁጥር ድንጋጌ አያግደውም፡፡
#ካሳ ስለሚከፈልበት ምክንያት
በማንኛውም ክስ ወይም ክርከር ላይ በክስ ወይም በመከላከያ መልክ ከሳሹ ወይም ተከሳሹ ያቀረበው የመከራከሪያ ወይም የመከላከያ ማስረጃ ወይም ክርክሩ ራሱ ወይም ማስረጃው አሰተኛ ነው ወይም መከራከሪያውንና አሰተኛ ማስረጃ ያቀረበው ወገን በሐሰት የተከራካሪውና አሰተኛ ማስረጃ ያቀረበው ክርክሩን ለማሰናከል፣ ጊዜ ለመፍጀት ወይም አንደኛውን ወገን ለመበደል ወይም ለማጉላላተር ሆነ ብሎ ያደረገው ነው በማለት ወይም የክርክሩንና የማስረጃውን አሰተኛነት እያወቀ ወይም ማወቅ ሲገባው ሆን ብሎ ማቅረቡን ሲያመለክትና ፍርድ ቤቱም ተቃዋሚው ወገን ያቀረበውን ነገር እርግጠኛነት ሲረዳው ይህንኑ በመዝገቡ ላይ አስፍሮ አሰተኛ ማስረጃ ወይም ክስ ወይም መከላከያ ያቀረበው ወገን ላቀረበው ለእያንዳንዱ ሀሰተኛ ማስረጃአንዱን ወገን ለመበደል፣ ለማጉላላት ወይም ጊዜ ለመፍጀት ላቀረበው አሰተኛ ክርክር ከማናቸውም ኪሳራና ከሌላው ወጭ በቀር ከ500 ብር የማይበልጥ ካሳ ለተበዳዩ እንዲከፈል ሊወስንበት ይችላል፡፡
#ይህም በወንጀለኛ መቅጫ ሕግ በቁጥር 446 በተመለከተው መሰረት ሃሰተኛ ማስረጃና ክርክር በማቅረቡ ከመከሰስና ከመቀጣት ነፃ ሊሆን ይችላል፡፡
ካሳ የተወሰነለት ወገን በሀሰት በመከሰሱ ወይም ሃሰተኛ መከላከያ ወይም ክስ የቀረበበት በመሆኑ ካሳና ኪሳራ ይገባኛል ሲል ሌላ ክስ አቅርቦ ካሳ ወይም ኪሳራ የተወሰነለት እንደሆነ በመጀመሪያው ክስ ላይ ከሚወስንለት ኪሳራና ካሳ ላይ ይቀነስበታል፡፡
#ስለ ይግባኝ
ማንኛውም ተከራካሪ ወገን በስረ ነገሩ ላይ ይግባኝ ባያቀርብም፣ በተወሰነበት የወጭ ወይም የኪሳራ አከፋፈል ብይን ላይ ይግባኝ ለማለት ይችላል፡፡ በዚህም ነገር ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት የሚሰጠው ውሳኔ የመጨረሻ ይሆናል፡፡
ፀጋዬ ደመቀ ሎየር
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
ማስታወቂያ
ሐምሌ 8 ቀን 2014 ዓ/ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ በዝዉዉር ለመመደብ አመልክታችሁ የጽሁፍ ፈተና ተፈትናችሁ ውጤታችሁ ከተገለጸው ውስጥ፡-
ለሴቶች እና ለአካል ጉዳተኞች 55 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያመጣችሁ፣
ለወንዶች 60 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያመጣችሁ፣
ለኢንተርቪው/ቃለ-መጠይቅ የተመረጣችሁ ስለሆነ እራሳችሁን የሚገልጽ መታወቂያ ይዛችሁ ቅዳሜ በ28/12/2014 ዓ/ም ከጠዋቱ 3፡00 ሠዓት ላይ ሜክሲኮ በሚገኘው አ/አ ፍትህ ቢሮ 5 ፎቅ ላይ እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

የዓቃቢያነ ህግ አስተዳደር ጉባዔ
via #ስለ_ህግ