አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.88K photos
25 videos
1.87K files
3.58K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
July 22, 2021
የመፋለም መብትና ክስ
====================
ከህግ ውጪ ወይም በኃይል በሌላ ሰው የተያዘን ንብረት የባለሀብትነት መብት ለማስከበርና ንብረቱን በመከተል ለማስመለስ በንብረቱ ባለቤት የሚቀርብ ክስ
የማይንቀሳቀስ ንብረት የመፋለም ክስ በይርጋ ቀሪ አይሆንም፡፡ ከባለቤትነት መብት ጋር ተያየያዥነት ያላቸው ነገር ግን ከመፋለም መብት ውጪ ያሉ ሌሎች ክሶች እንደሚጠየቀው መፍትሔ እና ለክሱ ምክንያት እንደሆነው ጉዳይ ዓይነት /ጋብቻ፣ ውርስ፣ ሽያጭ፣ ወዘተ…/ በሌሎች ልዩ የይርጋ ህግ ደንቦች የሚተዳደሩ ናቸው፡፡

ሰ/መ/ቁ. 43600 ቅጽ 10፣ ኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህገ-መንግስት አንቀጽ 13/1/፣ 25፣ 37፣ 40፣ 78፣ 79፣ ፍ/ህ/ቁ. 1192፣ 1206፣ 1845፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 280

መፋለም መብት

1 • የንብረት ባለሀብት የሆነ ሰው ንብረቱን ማንም ያልተፈቀደለት ሰው በሕገ ወጥ መንገድ እንዳይነካ፣ በማንኛውም መልኩ ወደ ራሱ ወይም ወደ ሌላ እንዳይዛወር ወይም የንብረቱን ህልውናና ደህንነት እንዳያውክ በሀይል ተጠቅሞ የማስወገድ መብት
2 • ያለባለቤቱ ፈቃድ ወይም ከህግ ውጪ ንብረቱ ተወስዶ ከሆነ ባለቤቱ ይህን ንብረት የመከተልና እንዲመለስለት ዳኝነት የመጠየቅ መብት
ሰ/መ/ቁ. 43600 ቅጽ 10፣ ፍ/ህ/ቁ.1845፣ 1184፣ 1168/1/፣ 1186፣ 1189፣ 1190፣ 1192፣ 1153-1646፣ 1206፣ ኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህገ-መንግስት አንቀጽ 40/1/
Via legal consulting limited
#Join #Join #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
July 22, 2021
Senior Legal Supervisor - Addis Ababa

Abeba Giday Business Group (Abeba Giday Trading House, Abeba Transport, Addis Spare Parts, and Bazen Agricultural and Industrial PLC…) are looking for the following vacancies.

Main purpose of the job

To supervise the provision of legal support to managers and staff so that the organization meets its legal obligations, and to protect its interests

Main responsibilities

Supervise legal staff to ensure that they carry out their responsibilities to the required standards and receive all necessary training and development

Supervise legal staff to ensure that they carry out their responsibilities to the required standards and receive all necessary training and development

Assist in the preparation of all legal documents required by managers and staff to ensure that these are accurate and legally sound

Provide legal advice to managers and staff on the interpretation of statutes and legal documents to ensure that the actions they take are legally sound

Represent the organization at courts and tribunals on routine matters to ensure that the organization’s interests are safeguarded

Draft, review, and amend legal documents drafted by, or sent to, the organization

Monitor the progress of legal transactions to ensure that the correct actions are taken at the appropriate times

Instruct counsel where necessary

Maintain an awareness of developments in all legal fields relevant to the organization

Required Number:1

Job Requirements:

Knowledge, skills, and experience required

BSc degree with at least 5 years supervisory experience in business firms

Considerable experience of advocacy

Good supervisory and legal matters handling experience

Good negotiating and interpersonal skills

Excellent presentation skills

Excellent knowledge of the organization’s work and functions

Accuracy and an eye for detail

How To Apply:

Interested and qualified applicants can apply through www.ethiojobs.net 

Posted: 07.21.2021

Deadline: 07.31.2021

Job Category: Legal

Employment: Location: Addis Ababa

Abeba Gidey Trading House P.L.C

#join #join #Share #Share #Share

🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
July 22, 2021
Head of Legal Services - Addis Ababa

Job Description:

Abeba Giday Business Group (Abeba Giday Trading House, Abeba Transport, Addis Spare Parts, and Bazen Agricultural and Industrial PLC…) are looking for the following vacancies.

Main purpose of the job

To direct and control the provision of effective legal services to the company and to provide legal advice to managers and staff

Main responsibilities

Direct and control the staff of the legal services department to ensure that they are appropriately motivated and trained and that they carry out their responsibilities to the required standards

Provide accurate legal advice to managers and staff to ensure that decisions taken are legally correct and that the company’s interests are protected

Develop and monitor an annual budget for the department to ensure that all financial targets are met and appropriate financial controls are in place

Represent the company at court hearings and tribunals to ensure that the company’s interests are effectively safeguarded and so that it carries out its legal obligations effectively

Negotiate, and draft and implement, complex legal agreements relating to the work of the company

Represent the company at meetings with external bodies to ensure that the legal aspects of any decisions are fully considered

Maintain an awareness of developments in the legal field which might affect the company and prepare reports on relevant matters for consideration by management

Required Number: 1

Job Requirements:
Knowledge, skills, and experience required

BSc degree and above qualified solicitor with at least 10 years post-qualification experience in business firms

Considerable experience of advocacy

Good managerial and legal matter handling experience

Highly developed negotiating and interpersonal skills

Excellent representational skills

Excellent knowledge of the organization’s work and functions

How To Apply:

Interested and qualified applicants can apply through www.ethiojobs.net 

Posted: 07.21.2021

Deadline: 07.31.2021

 

Job Category:

Legal: Employment:

Location: Addis Ababa
Abeba Gidey Trading House P.L.C

#join #join #Share #Share #Share

🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
July 22, 2021
Attorney at Lion International Bank S.C

Company: Lion International Bank S.C

Location: Ethiopia

State: Addis Ababa Jobs

Job type: Full-Time

Job category: Legal Jobs
Job Description

Job Title: Attorney

– Place of Assignment: Head Office, Legal Services Department
– Salary: As per the Bank’s salary scale
– Deadline: July 24, 2021 until noon 6 pm (Local Time)

Qualifications/Skills
• Educational Qualification: LLB Degree in Law
• Work Experience: 2 years of experience in Legal Service


Method of Application

Interested applicants should present in person application letter along CV & photocopies of Credentials at:-

Lion International Bank S.C
Human Capital Management Dep’t
22 Mazoria, Lex Plaza Building 7th Floor
Addis Ababa

Closing Date : July 24, 2021
#join #join #Share #Share #Share

🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
July 22, 2021
July 22, 2021
 ታማሚው ወይም የቅርብ ቤተሰቡ በግልጽ ፈቃዱን ሳይሰጥ በታማሚው ላይ ልዩ ልዩ አገልግሎቶችን መፈጸም፣
 የህክምና ስነ-ስርዓት ወቅት ስህተት መፈፀም ለምሳሌ በቀዶ ጥገና ወቅት ወይም ልጅ በማዋለድ ጊዜ ስህተት መፈፀም እና ሌሎችን ያካትታል፡፡
2. ሕክምና ተቋማት እና የጤና ባለሙያዎች የአስተዳደርና የፍትሐብሔር ኃላፊነት፤

2.1 አስተዳደራዊ እርምጃዎች፤

አስተዳደራዊ እርምጃ ማለት አንድ ሠራተኛ በሚሰራዉ ጥፋት መሰረት በዲስፕሊን የሚጠየቅበት ሥርዓት ማለት ነዉ፡፡ የአስተዳደራዊ እርምጃ ዓላማ ሠራተኛዉ ከፈጸመዉ ጥፋት እንዲታረምና ብቁ ሠራተኛ እንዲሆን ለማስቻል ወይም የማይታረም ሆኖ ሲገኝ ከስራዉ በማሰናበት የሚወሰድ የመፍትሔ እርምጃ ነዉ፡፡ የዲሰፕሊን ጉድለት የፈፀመ ሠራተኛ እንደጥፋቱ ክብደት የቃል ማስጠንቀቂያ፣ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ፣ ከስራ ደረጃና ደመወዝ ዝቅ ማድረግ እንዲሁም ከስራ ማሰናበትን ሊያጠቃልል ይችላል፡፡ የሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ ስንመለከት መንግስት ደረጃዉን ባልጠበቀ የጤና አገልግሎት እንዲሁም ብቃትና የሙያ ሥነ-ምግባር በጎደለዉ የጤና ባለሙያ ምክንያት በዜጎች ላይ ሊደርስ የሚችለዉን የጤና ችግር ለመከላከል ይቻል ዘንድ የጤና አገልግሎቱን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ የተለያዩ ሕጎችን በማዉጣትና በተግባር ላይ በማዋል የቁጥጥር ሥርዓት ዘርግቷል፡፡ አዋጅ ቁጥር 1112/2011 በአንቀጽ 48 አግባብ ባለዉ አካል የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ወይም የህክምና ሙያ ሥራ ፈቃድ የተሰጠዉ ማንኛዉንም ሰዉ ጤናን በተመለከተ አዋጆችን፣ ደንቦችን ወይም መመሪያዎችን በመተላለፍ ሲሰራ የተገኘ እንደሆነ የተሰጠዉ የህክምና ምስክር ወረቀት ወይም ፈቃድ ሊታገድ ወይም ሊሰረዝ እንደሚችል በአዋጁ አንቀጽ 41 እና 90 ላይ ተደንግጎ ይገኛል፡፡

አንድ የጤና ባለሙያ የጤና አገልግሎት ለመስጠት አስቀድሞ በሙያው እውቅና ካለው ተቋም የሰለጠነ መሆኑ ተረጋግጦ እና ቃለ መሀላ እንዲፈፅም ይደረጋል፡፡ ይህን ተላልፎ የአሰራር ስርዓቱን ወይም የሥነ-ምግባር መመሪያዎችን ሲጥስ እርምጃ የሚወሰደዉ የጤና ስነ-ምግባር ኮሚቴ ለኢትዮጵያ የምግብና የመድሀኒት ቁጥጥር ባለስልጣን በሚያቀርበዉ የዉሰኔ ሀሳብ አማካኝነት ነዉ፡፡

የምግብ የመድሀኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 299/2006 አንቀጽ 71 ንዑስ አንቀጽ 1 መሰረት የጤና ስነ-ምግባር ኮሚቴ የሚቋቋመዉ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አማካኝነት ሲሆን የስራ ድርሻዉም የሚቀርቡለትን ጉዳዮች አጣርቶ ጥፋት በፈፀሙ የጤና ባለሙያዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ ለባለስልጣኑ መስሪያ ቤት የዉሰኔ ሀሳብ የሚያቀርብ ነዉ፡፡

የጤና ሙያ ሰነ-ምግባር ኮሚቴ አንድ የጤና ባለሙያ ከሕክምና ስነ-ምግባር ዉጪ በመስራት በተገልጋዩ ላይ ጉዳት ያደረሰ ከሆነ ወይም ጉዳት ባያደርስም የስነ ምግባር መርሆችን ተላልፎ ከተገኘ ጉዳዩን አስመልክቶ ተገቢዉን ማጣራት በማድረግ በባለሙያዉ ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ ያደርጋል፡፡ ከእነዚህ ዉስጥም የሙያ ፈቃድ ማገድ ወይም እንደ ጥፈቱ ክብደት የሙያ ፈቃድ መሰረዝ፣ የገንዘብ ቅጣት መጣል፣ ከደረጃ ዝቅ ማድረግ፣ የቃል ወይም የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ መስጠት፣ የደመወዝ ቅጣት መጣል እንዲሁም ሌሎች እርምጃዎችን ሊያካትት ይችላል፡፡

2.2 የጤና ባለሙያዎች የፍትሐብሔር ኃላፊነት፣

ማንኛዉም የጤና ባለሙያ ከምንም ነገር በላይ ለታካሚዉ ጤንነት ቅድሚያ ሊሰጥ ይገባዋል፡፡ የጤና ባለሙያዉ በሚሰጠዉ አገልግሎትም ሆነ በሚወስነዉ ወሳኔ ምክንያት ለሚከሰት ስህተት ወይም ጉዳት በሕግ አግባብ ተጠያቂነት አለበት፡፡ አንድ የጤና ባለሙያ የህክምና ሙያዉ በሚፈቅደዉ መልኩ ታካሚዉን ማገልገል ይጠበቅበታል፡፡

የፍትሐብሔር ኃላፊነት ሲባል አንድ የጤና ባለሙያ ከተገልጋዩ ወይም ከታካሚው ጋር በሚያደርገዉ የዉል ስምምነት የሚፈጠር ወይም ከዉል ዉጪ በሆነ እና በሕግ በተደነገገ ጊዜ የሚመነጪ ኃላፊነት ነዉ፡፡ ይህ ዓይነት ኃላፊነት አጥፊዉ በገንዘብ ወይም ዋጋ ባለዉ ዕቃ ወይም ንብረት የሚቀጣበት ሥርዓት ነዉ፡፡ አንድ ሐኪም የሕክምናዉ ጥበብ ከሚፈቅደዉ ዉጪ የሕክምና አገልግሎት በመስጠት በተገልጋይ ላይ ጉዳት ካደረሰ እንደነገሩ ሁኔታ ማለትም ከዉል ዉጪ ወይም ከዉል በሚመነጭ ኃላፊነት ጉዳት የደረሰበትን ተገልጋይ የመካስ ነዉ፡፡

3.3 የሕክምና ተቋማት የፍትሐብሔር ኃላፊነት፤

የሕክምና ተቋማት ባለሙያዎቻቸዉ ለታካሚዎች የሕክምና አገልግሎት በሚሰጡበት ወቅት በታከሚዉ ላይ አካላዊ ብሎም ለሞት የሚዳርግ ጉዳት ሊያደርሱ ይቻላሉ፡፡ በዚህ ወቅት የሕክምና ተቋማት ለሚደርሰዉ ጉዳት ከህክምና በለሙያው ጋር በአንድነት በፍትሐብሔር ተጠያቂ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ከላይ እንዳየነዉ የፍትሐብሔር ኃላፊነት ስንል አንድ ሰዉ በዉል ወይም ከዉል ዉጪ ከሚመነጭ የሚኖርበት ኃላፊነትን የሚመለከት ሲሆን የሕክምና ተቋማትም ከታካሚዎቻቸዉ ጋር በሚያደርጉት የዉል ስምምነት ወይም ከዉል ዉጪ በሚያደርሱት ጉዳት የፍትሐብሔር ኃላፊነት ይኖርባቸዋል፡፡

3.3.1 የመንግስት የጤና የሕክምና ተቋማት ኃላፊነት፣

የመንግስት የጤና የሕክምና ተቋማት ሠራተኞቻቸዉ በተቋሙ ዉስጥ የሕክምና አገልግሎት በሚያገኙ ታካሚዎች ላይ ለሚያደርሱት ጉዳት ከዉል ወጪ ኃላፊነት አለባቸዉ፡፡ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2126 መሰረት የመንግስት ሹም ወይም ሠራተኛ በራሱ ጥፋት በሌላ ሰዉ ላይ ጉዳት የደረሰ እንደሆነ በማናቸዉም ምክንያት ቢሆን ኪሳራዉን ለመክፈል ይገደዳል፡፡ ነገር ግን የተደረገዉ ጥፋት የመንግስቱን ስራ ሲሰራ የደረሰ የስራ ጥፋት የሆነ እንደሆነ የተጎዳዉ ሰዉ ኪሳራ ከመንግስት ላይ ለመጠየቅ ይችላል፡፡ ሠራተኛዉ ያደረገዉ ጥፋት የግል ጥፋቱ የሆነ እንደሆነ ግን መንግስት ኃላፊነት አይኖርበትም፡፡ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2127 የሥራ ጥፋት ምን ማለት እንደሆነ ያስቀመጠ ሲሆን ጥፋቱ እንደ ሥራ ጥፋት ሆኖ የሚቆጠረዉ ጥፋት አድራጊዉ በዚሁ ጥፋት ላይ የወደቀዉ በቅን ልቦና በስልጣኑና በሥራዉ ክፍል መልካም ያደረገ መስሎት የፈፀመ ሲሆን ነዉ፡፡ በቅን ልቦና ያልተሰራ ለመሆኑ ተቃራኒ ማስረጃ ያልቀረበ እንደሆነ የሹሙ ወይም የሰራዉ አሰራር በቅን ልቦና እንደተሰራ ይገመታል በማለት አስቀምጧል፡፡ በአንድ የመንግስት የጤና የሕክምና ተቋም ተቀጥሮ የሚሰራ የሕክምና ባለሙያ በተቋሙ ዉስጥ ሆኖ ታካሚዎችን በሚያክምበት ወቅት ጥፋት ከፈፀመ ኃላፊ ሊሆን የሚገባዉ የህክምና ተቋሙ ነዉ፡፡

ይኸዉም ጥፋቱ የተፈፀመዉ ከላይ በተገለፀዉ መሰረት በቅን ልቦና በስልጣኑና ለስራዉ ክፍል መልካም ያደረገ መስሎት የተፈፀመ ሲሆን ነዉ፡፡ የሕክምና ጥፋት ተፈጽሟል አልተፈጸመም የሚለዉን ጉዳይ አጣርቶ ትክክለኛ መረጃ ለፍርድ ቤት ወይም አግባብ ላለዉ አካል ሊሰጥ የሚችለዉ በሙያዉ በቂ ዕዉቀት፣ልምድ እና ክህሎት ያለዉ ባለሙያ መሆን ይገባዋል፡፡ በሌላ በኩል ግን ጥፋቱ የሐኪሙ ወይም የሰራተኛዉ ከሆነ የጤና የሕክምና ተቋሙ ኃላፊነት አይኖርበትም፡፡ ታካሚዉ ከተቋሙ የጉዳት ካሳ ተቀብሎ ከከሆነም መንግስት ጥፋት ከፈፀመዉ ሐኪም ወይም ሠራተኛ ላይ ለመጠየቅ መብት ይኖረዋል (የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2126(2)፡፡የመንግስት የሕክምና ተቋማት ስለ ሠራተኞቻቸዉ ያለባቸዉ ኃላፊነት የሚመሰረተዉ ተቋሙ ከሠራተኛዉ ጋር የሥራ ቅጥር ዉል ስምምነት ፈጽሞ ከሆነብቻ መሆኑን
July 22, 2021
ከላይ የተጠቀሱት የሕግ ድንጋጌዎች ያስረዳሉ፡፡ ነገርግን በሕክምና ተቋሙ የሥራ ቅጥር ዉል ሳይፈጽሙ የሕክምና አገልግሎት የሚሰጡ ሠራተኞች የሚኖሩበት አጋጣሚ ስለሚኖር እነዚህ ሠራተኞች ( የሕክምና ባለሙያዎች) በታካሚዎች ላይ ለሚያደርሱት ጉዳት እራሳቸዉ ተጠያቂ ናቸዉ፡፡ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2134 መሰረት አንድ ሰዉ የተጠየቀዉን ሥራ በሚሰራበት ጊዜ ለሥራዉ ጥፋት ጥፋተኛዉ በሥራ ሰጪዉ ሥልጣን ስር ያልሆነ እንደሆነ ነፃነቱንም እንደያዘ መሆኑ ከታወቀ አሰሪዉ በኃላፊነት እንደማይጠየቅ አስቀምጧል፡፡ ስለሆነም በዚህ ወቅት ለሚደርሰዉ ጉዳት ኃላፊነት የሚወስደዉ በራሱ ሥልጣን የሚሰራዉ ሠራተኛ / Indepenent Contactor / ይሆናል፡፡ በራሱ ስልጣን የሚሰራዉ ሠራተኛ በታካሚዉ ላይ ለሚያደርሰዉ ጉዳት የሚጠየቀዉ በራስ ጥፋት በሌላሰዉ መብትና ጥቅም ላይ የሚደርስ ጉዳት (የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2027(1) እና 2031 (1) በሚለዉ ሕግ ነዉ፡፡

3.3.2 የግል የሕክምና ተቋማት ኃላፊነት፣

የሕግ ሰዉነት የተሰጣቸዉ የግል የጤና የሕክምና ተቋማት ሠራተኞች በታካሚ ላይ በሚያደርሱት ጉዳት ልክ እንደ መንግስት የጤና የሕክምና ተቋማት ሁሉ በፍትሐብሔር ተጠያቂ ናቸዉ፡፡ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2129 መሰረት የሰዉነት መብት የተሰጣቸዉ ድርጅቶች ሠራተኞቻቸዉ፣እንደራሴዎች፣ ወኪሎች ወ.ዘ.ተ የተሰጣቸዉን ስራ በሚያከናዉኑበት ጊዜ ኃላፊነትን የሚያስከትል ስራ የፈፀሙ እንደሆነ የፍትሐብሔር ኃላፊነት ያለባቸዉ መሆኑን ያስገነዝበናል፡፡ አንድ የሕክምና ሠራተኛ ስራዉን በሚሰራበት ጊዜ ኃላፊነትን የሚያስከትል ጥፋት የሰራ እንደሆነ በፍትሐብሔር በኃላፊነት የሚጠየቀዉ አሰሪዉ ሲሆን ይህም የሚሆነዉ ጥፋቱ የደረሰዉ በመስራት ወይም ባለመስራት ሆኖ ስራን በመስራት ተፈፅሞ የሆነ እንደሆነ ነዉ፡፡ በመስራት ወይም ባለመስራት የደረሰዉ ጥፋት ሥልጣን በመተላለፍ ሆኖ ሰሪዉ እንዳይሰራ በግልጽ ተከልክሎ ቢገኝ እንኳ ጉዳት የደረሰበት ሰዉ ምክንያቱን ካላወቀ ወይም ሊዉቀዉ ይገባዉ ነበር የሚል ካልሆነ በስተቀር በፍትሐብሔር ኃላፊነት የሚጠየቀዉን ክልከላዉ ምክንያት ሆኖ ከኃላፊነት አያድነዉም (የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2131 (1) እና (2) ይመለከቷል፡፡ ስለሆነም የግል የጤና የሕክምና ተቋማት ከላይ በተገለጸዉ አግባብ ሠራተኞቻቸዉ በታካሚዎች ላይ ለሚያደርሱት ጉዳት ከዉል ወጪ ኃላፊ ይሆናሉ ማለት ነዉ፡፡ የተቋሙ የቅጥር ሠራተኞች ያልሆኑ ብዙ የጤና ባለሙያዎች በአንድ የጤና ተቋም ዉስጥ በተለይ ደግሞ በግል የጤና ተቋማት ዉስጥ የሕክምና አገልግሎት የሚሰጡበት ሁኔታ አለ፡፡ ለትርፍ ተቋቋሙ የግል የጤና ተቋማት አንዳንድ የሕክምና አገልግሎቶችን ለተገልጋዩ ኅብረተሰብ የሚሰጡት በራሱ ስልጣን በሚሰራ ሠራተኛ አማካኝነት ነዉ፡፡ በዚህ መንገድ የሚሰጡ የሕክምና አገልግሎቶች በቂ የሕክምና ባለሙያና የሕክምና መሣሪያ በሀገሪቱ ዉስጥ በሌለባቸዉ ሲሆን ለአብነት ያህልም የፊዚዮትራፒስት፣ የራዲዮሎጂስት እና የኒሮሎጂስት ባለሙያዎች የሚሰጧቸዉን የሕክምና አገልግሎቶች መጥቀስ ይቻላል፡፡ በዚህ ወቅት በግላቸዉ የሕክምና አገልግሎት በተቋሙ የሚሰጡ ሠራተኞች በታካሚዉ ላይ ለሚያደርሱት ጉዳት የጤና ተቋሙ የፍትሐብሔር ኃላፊነት የለበትም፡፡ ምክንያቱም በሠራተኛዉ እና በጤና ተቋሙ መካከል የስራ ዉል ወይም የቅጥር ዉል ስምምነት የሌለ በመሆኑ ነዉ፡፡ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2134 መሰረት አንደሰዉ የተጠቀሰዉን ሥራ በሚሰራበት ጊዜ ለሰራዉ ጥፋት ጥፋተኛዉ በስራ ሰጪዉ ሥልጣን ስር ያልሆነ እንደሆነ ነፃነቱንም እንደያዘ መሆኑ ከታወቀ አሠሪዉ በኃላፊነት አይጠየቅም በማለት ይደነግጋል፡፡ ይህ አንቀጽ የሚደነግገዉ ስለ / Indepenent Contactors / በራሱ ሥልጣን ስለሚሰራ ሠራተኛ ሲሆን የጤና ተቋማት በዚሁ ሠራተኛ ጥፋት ምክንያት በተቋሙ ዉስጥ የሕክምና አገልግሎት በሚያገኙ ተገልጋዮች ላይ ለሚደርስ ጉዳት ኃላፊነት አይኖርባቸዉም ፡፡ የጤና ተቋማት በራሱ ሥልጣን በሚሰራ ሠራተኛ በጤና ተቋሙ ተገልጋዮች ላይ ለሚደርስ ጉዳት የጤና ተቋማት ከዉል ዉጪ ኃላፊነት የለባቸዉም ሲባል ጉዳት የደረሰባቸዉ ተገልጋዮች የሕግ መፍትሔ የላቸዉም ማለት እንዳል ሆነ መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡.ምክንያቱም ጉዳቱ የደረሰባቸዉ የሕክምና አገልግሎት ተጠቃሚዎች ጉዳቱ የደረሰባቸዉ በራሱ ስልጣን በሚሰራ ሠራተኛ ከሆነ የጤና ተቋማቱን መጠየቅ የማይችሉ ቢሆንም አገልግሎቱን የሰጠዉን ሠራተኛ ግን በፍትሐብሔርም ሆነ በወንጀል ከመጠየቅ የሚከለክል ሕግ የሌለ በመሆኑ ነዉ፡፡ ይኸዉም በራሱ ሥልጣን በሚሰራ የሕክምና ባለሙያ በታካሚዉ ላይ ለሚደርሰዉ ጉዳት ከታካሚዉ ጋር የዉል ስምምነት ያለዉ ከሆነ በዉሉ መሰረት ተጠያቂ የሚሆን ሲሆን በሁለቱ መካከል የዉል ስምምነት ከሌለ ደግሞ ከዉል ዉጪ ኃላፊነት በራስ ጥፋት በሌላ ሰዉ መብትና ጥቅም ላይ የሚደርስ ጉዳት በሚለዉ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2031(1) መሰረት ኃላፊ ይሆናል፡፡
ኢፌዴሪ ጠቅላይ አቃቤ ህግ
#Join #Join #Share
🟩 @Alehig
🟨 @Alehig 💯
🟥 አለሕግ 💯

🔴Attorney and Legal Consultant
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ

We are delighted to connect with you! You can easily reach us through the following platforms to stay informed and access our legal services:

Website & Social Media
Linktree:📱📱📱📱📱📱📱📱  

              https://linktr.ee/alehig

📱Facebook:
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

📱Telegram Channel:⭐️
https://t.me/AleHig

🌐 📱📱📱📱Website: alehig.com


Direct Contact🔈⬇️✉️

📱WhatsApp: ✉️ +251920666595
📱Telegram:  ✉️ @MikiasMelak


Our Commitment
alehig.com
📊አለሕግ🔽
🔠🔠🔠    🔠🔠🔠
Alternative Legal Enlightenment & Services
🔼⭐️
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት


We provide expert legal advice, support, and resources on various laws, proclamations, regulations, and directives to empower and guide you.

Feel free to reach out anytime‼️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
July 22, 2021
ውል እንዲፈርስ ለመጠየቅ መብት ስላለው ሰው፣ ስለሚጠየቅበት ጊዜ እና ስለውል መፍረስ ውጤት
=========================
1. ውል እንዲፈርስ ለመጠየቅ መብት ስላለው ሰው እና ስለሚጠየቅበት ጊዜ

ለአንድ ውል ውጤት ማግኘት የሚያስፈልጉት ሁኔታዎች የተሟሉ እንደሆነ ይፈፀማሉ፡፡ የተጓደሉ እንደሆነ ግን ውሉ እንዲፈርስ ይደረጋል፡፡ ጥያቄውን ለማቅረብ የሚችለውም በፈቃዱ ጉድለት ወይም በችሎታው ማጣት ሰበብ በውሉ የተጎዳው ወገን ብቻ ነው፡፡ ሌላ ሰው ጥቅም ኖሮት ቢሆን እንኳ ለመጠየቅ አይፈቀድም፡፡ ውሉ ከህግ ውጪ ነው፣ ለህሊና ይቃረናል ወይም የተደነገገውን የአፃፃፍ ሥርዓት አልተከተለም በሚል ውሉ እንዲፈርስ ለመጠየቅ ሥልጣን የተሰጠው ግን ለተዋዋዮችና በጉዳዩ ላይ ጥቅም አለኝ ለሚል ማንኛውም ሰው ነው፡፡ ይህ ልዩነት የኋለኞቹ ምክንያቶች ጉዳቱ ከተዋዋዮች ማሕበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ደህንነትም በላይ ጠቅላላውን ህዝብ የበለጠ የሚጎዱ ቀውስን የሚፈጥሩ ናቸው በሚል ትኩረት የተደረገባቸው መሆኑን የሚጠቁም ነው፡፡
ከዚህ በተረፈ ጥያቄዎቹ የሚቀርቡበት ሁኔታ በጊዜ የተገደበ ስለመሆኑ ከፍ.ብ.ህ.ቁ.1810 (2) መረዳት ይቻላል፡፡ ውል የማይረጋበት ምክንያት ከቀረበት ጊዜ ጀምሮ በሁለት አመት ውስጥ ውል እንዲፈርስ መጠየቅ አለበት፡፡ ውል የማይረጋበት ምክንያት ከቀረበት ማለቱ ውሉ የማይረጋበት ምክንያት የሚቀርባቸውን እንደችሎታ ማጣት፣ አቅመ-አዳም አለመድረስ ወይም መገደድ ያሉትን አጋጣሚዎች ለመግለጽ የታለመ ነው፡፡ ሌላው የጊዜ ገደብ የተቀመጠው በጉዳት ምክንያት unconscionable contracts የተደረጉ እና አካለ መጠን ያደረሰ ሰው ያደረጓቸውን ውሎች የሚመለከቱ ናቸው፡፡ ውሉ ከተደረገበት ጊዜ ጀምሮ በሚቆጠር በሁለት ዓመት ውስጥ እንዲፈርሱ ካልተጠየቁ ይፀናሉ፡፡

2. የውል መፍረስ ውጤት

አንድ ውል የማይረጋ በመሆኑ ምክንያት እንዲፈርስ የተደረገ እንደሆነ በተቻለ መጠን ተዋዋዮች ወደነበሩበት ቦታ እንደመለሱ ማድረግ ይገባል፡፡ ውሉ የፀና ነው በሚል ዕምነት ውሉን በመፈፀም ረገድ የተደረጉ ስራዎች ካሉ ቀሪ ይሆናሉ፡፡ ውጤት ያሌላቸው ወይም የማያስገኙ ይሆናሉ፡፡ ይህ ማለት ስለውሉ አፈፃጸም የተደረጉትን አንዱ ለሌላው መመለስ ይኖርበታል ማለት ነው፡፡
ይህ የውል ማፍረስ ውጤት አንዱ ገጽታ ሲሆን ሌላው ደግሞ ተዋዋዮችን በተለያየ ምክንያት እነበሩበት ቦታ መመለስ የማይቻል፣ አስቸጋሪ ወይም ከፍ ያለ መሰናከል የሚያመጣ ሲሆን ህጉ የሚያስቀምጠው አማራጭ ነው፡፡ ስለውሉ አፈጻጸም የተሰሩ ሥራዎች ሁሉ እንደረጉ እንዲቀሩ ያዛል፡፡
ሁልጊዜም ማለት በሚቻል ደረጃ ውል ከፈረሰ በኋላ የመጀመሪያውን አማራጭ በመጠቀም ተዋዋዮች ወደነበሩበት እንዲመለሱ በማድረግ ውሳኔ የሚሰጥ ስለመሆኑ በርካታ የፍርድ ቤት ውሳኔዎችን በማየት መረዳት ይቻላል፡፡ ፍርድ ቤቶች ሁለተኛውን አማራጭ ሲጠቀሙ አይታይም፡፡ መመላለስ የሚቻልበት ሁኔታ ሁልጊዜም ስላለ ነው ብሎ መደምደም ያስቸግራል፡፡ በቅርብ ጊዜያት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በነ ወ/ሮ ጎርፌ ላይ የሰጠውን ውሳኔ ተከትሎ በየፍርድ ቤቱ የሚቀርቡ ጉዳዮች መብዛት ይህንን ክፍተት ለመጠቀም ከመሻት የሚነሱ ናቸው ብሎ በድፍረት ለመናገር ብዙ የሚያሳቅቅ አይደለም፡፡
Via Legal consulting limited
#join #join #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
July 23, 2021
የመሰየም ምንነትና ሕጋዊ ውጤቱ
====================
ቀድሞ ወንጀለኛ የነበረ ሰው ወደ ንፁህነት የሚመለስበት ወይም ስሙ እንደገና የሚታደስበት ሁኔታ መሰየም ተብሎ ይጠራል፡፡ አንድ ወንጀለኛ ቅጣቱን ከፈፀመና ወደ ሕበረተሰቡ ተመልሶ በሕጉ የተመለከተውን የፈተና ጊዜ በብቃት ካለፈ የወንጀል ሪኮርዱ ሊፋቅለት ይገባል እንጅ ወንጀሉ በሄደበት ቦታ ሁሉ እንደ ጥላ ሊከተለው አይገባም፡፡ ሕብረተሰቡ ውስጥ ገብቶ መልካም ኗሪነቱን በተግባር ያረጋገጠው የቀድሞ ወንጀለኛ እንደ ማንኛወም የሕብረተሰብ አባል መታየት የሚጀምርበት ሁኔታ መፈጠር አለበት፡፡ የፈፀመው ወንጀል አሉታዊ ውጤት እስከ ሕይወት ፍጻሜው እንዲከተለው መደረጉ ለሕብረተሰቡም ምንም ዓይነት ገንቢ አገልግሎት የለውም፡፡

ለመሰየም በጥፋተኛው ላይ የተጣለው ቅጣት በተለያዩ ምክንያቶች ቀሪ ከሆኑ በኋላ የተወሰነ ጊዜ ማለፍ አለበት፡፡ ቅጣቱ ቀሪ ከሆነ በኋላ ምን ያህል ጊዜ ቆይቶ ነው የቀድሞው ወንጀለኛ ለመሰየም ጥያቄ ማቅረብ የሚችለው የሚለውን በተመለከተ ተወስኖበት በነበረው የቅጣት ዓይነት ይወሰናል፡፡ በወንጀለኛው ላይ ተወስኖበት የነበረው ቅጣት ፅኑ እስራት፣ ከአገር እንዲወጣ ወይም ንብረቱ እንዲወረስ ከሆነ ቅጣቱ ቀሪ ከተደረገበት ጊዜ ጀምሮ አምስት ዓመት (የቀድሞው ሕግ አስር ዓመት ይል ነበር) ማለፍ ያለበት ሲሆን አጥፊው ተወስኖበት የነበረው ቅጣት ከነዚህ ዝርዝሮች ውጭ ከሆነ ግን ሁለት ዓመት (የቀድሞው ሕግ አምስት ዓመት ይል ነበር) ማለፍ አለበት፡፡ ይህ አጠቃላይ የጊዜ ወሰን በመርህ ደረጃ የተደነገገ ቢሆንም የመሰየም ጥያቄ የሚያቀርበው ተቀጪ በሕዝባዊ፣ በወታደራዊ ወይም በማህበራዊ አገልግሎት መስክ ተሰማርቶ በግልፅ የሚታይ የሚያስመሰግን ሥራ ለሕብረተሰቡ አበርክቶ ከተገኘ በሕግ የተወሰነው አነስተኛ የጊዜ ገደብ ከመድረሱ በፊት መሰየሙ ሊፈቀድለት ይችላል(አንቀጽ 234(2))፡፡ እንዲሁም ለመሠየም የሚያበቃው አነስተኛ ጊዜ ተፈፃሚነት የሚኖረው ስለደጋጋሚነት የተደነገገውን የጊዜ ገደብ እስካልነካ ድረስ ነው፡፡ ይህም ማለት አንድ ሰው ቅጣቱ ቀሪ ከሆነለት ጊዜ ጀምሮ ሁለት ዓመት ካለፈ በፍርድ ቤት ውሳኔ ሊሰየም የሚችል ቢሆንም ስለ ደጋጋሚነት በተቀመጠው መስፈረት መሰረት ደግሞ ቅጣቱ ቀሪ ከሆነለት ጊዜ ጀምሮ በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ወንጀል ከፈፀመ በደጋጋሚ ወንጀለኛት ሊፈረጅ የሚችል በመሆኑ መሰየሙ እንደ ደጋጋሚ ወንጀለኛ ከመቆጠር አያድነውም ማለት ነው፡፡ ይህ ልዩ ሁኔታ በወንጀለኛ መቅጫ ሕጉ ላይ ያልነበረ በወንጀል ሕጉ ውስጥ እንዲካተት የተደረገ አዲስ መመዘኛ ነው፡፡

ቅጣቱ ቀሪ ከሆነ በኋላ ከዚህ በላይ የተጠቀሰው አነስተኛ የጊዜ ገደብ ማለፉ ብቻ ወድያውኑ መሰየምን አያስከትልም፡፡ እንዲሁም በወንጀል ሕጉ ላይ በግልፅ እንደሰፈረው “መሰየም የሚገኘው በመልካም ሥራ ነው እንጂ በይገባኛል አይደለም” (አንቀጽ 232(1))፡፡ ለመሰየም ቅጣቱ ቀሪ ከሆነ በኋላ በሕግ የተወሰነው ጊዜ ማለፍ ያለበት መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ሌሎች ለመሰየም የሚያበቁ ቅድመ ሁኔታዎችም ተሟልተው መገኘት አለባቸው፡፡ እነርሱም፡-

1. ለመሰየም ብቁ እንዲሆን በሕግ በተወሰነው ከላይ በተጠቀሰው አነስተኛ የጊዜ ገደብ ወስጥ በመልካም ጠባይ ተመርቶ እንደሆነና በእስራት ቅጣት የሚያስቀጣ ወንጀል ፈጽሞ ጥፋተኛ ሳይሆን ቆይቶ ከሆነ፤ በወንጀለኛ መቅጫ ሕጉ ይህ ቅድመ ሁኔታ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ በማናቸውም ጥፋት ሳይከሰስ እንዲሁም አቤቱታ ሳይቀርብበት ቆይቶ እንደሆነ በሚል ነበር ተመልክቶ የነበረው (ቁጥር 243(ለ))፡፡

2. ከዋናው ቅጣት ጋር ተጨማሪ ቅጣት በአጥፊው ላይ ተወስኖ የነበረ ከሆነ ይኸው ቅጣት ተፈጽሞ እንደሆነ፤ በዚህም መሰረት አጥፊው ለምሳሌ የወንጀሉን ተጎጂ ይቅርታ እንዲጠይቅ ተጨማሪ ቅጣት ተወስኖበት የነበረ ከሆነ ይህንኑ መፈፀሙ ካልተረጋገጠ በቀር ለፍርድ ቤት ያቀረበው የመሰየም ጥያቄ ተቀባይነት ሊያገኝ አይችልም፡፡
3. የተለቀቀው ተቀጪ አቅሙ በፈቀደ መጠንና ራሱም ሊፈፅመው ይገባዋል ብሎ በሚገመትበት ሁኔታ በፍርድ የተወሰነበትን ካሳ፣ የዳኝነትና ማናቸውንም ሌላ ኪሣራ በሚገባ አጠናቅቆ ከፍሎ እንደሆነ፣
የሚሉት ናቸው፡፡

በወንጀለኛ መቅጫ ሕጉ ቁጥር 247 መሠረት አንድ ጥፋተኛ በተሰየመ በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ማናቸውም ዓይነት ነፃነትን የሚያሳጣ ወይም የሞት ቅጣት የሚያስቀጣ አዲስ ወንጀል የፈፀመ እንደሆነ የመሰየም ውሳኔው ይሻራል፡፡ በዚህም መሰረት ተቀጪው የፈፀመው አዲስ ወንጀል ቀላል እስራትም ሆነ ፅኑ እስራት የሚያስቀጣው ቢሆን የመሰየም ውሳኔውን የማሻር ውጤት ይኖረዋል፡፡ በአዲሱ የወንጀል ሕግ ላይ ግን በዚህ መመዘኛ ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ይኸውም ተቀጪው የፈፀመው አዲስ ወንጀል በፅኑ እስራት ወይም በሞት ቅጣት የሚያስቀጣ ካልሆነ በቀር የመሰየም ውሳኔውን የማሻር ውጤት አይኖረውም፡፡ ስለሆነም በአዲሱ ሕግ መሰረት ተቀጪው እንዲሰየም ከረፈቀደለት በኋላ በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ አዲስ ወንጀል ፈፅሞ በሞት ወይም በፅኑ እስራት ከተቀጣ (ፅኑ እስራት ከተወሰነበት) የተፈቀደለት መሰየም ይሰረዛል፣እንዲሁም ዳግመኛ እንዲሰየም ሊፈቀድለት አይችልም (አንቀጽ 237)፡፡

በቀድሞው ሕግ ላይ ጥፋተኛው በገደብ የተለቀቀ በሚሆንበት ጊዜ ስለሚሰየምበት ሁኔታ አልተመለከተም ነበር፡፡ ከዚህ በፊት ለመግለፅ እንደተሞከረው አንድ ወንጀል አድራጊ በፍርድ ቤት ተከስሶ ጥፋተኛ ሆኖ ከተገኘ በኋላ የሚጣልበት ቅጣት የተወሰነ ፈተና ጊዜ ተሰጥቶት ሳይፈፀምበት ሊቀር የሚችልበት ያለ ሲሆን በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ አጥፊው በገደብ በሚለቀቅበት ጊዜ ለመሠየም የሚያበቃው አነስተኛ ጊዜ የሚሰላው ቅጣቱ ከታገደበት ጊዜ ጀምሮ ስለመሆኑ በአዲሱ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 233(ሀ) ላይ በግልፅ ሰፍሯል፡፡

የመሰየም ውሳኔ ቀደም ሲል በተቀጪው ላይ ተወስኖ የነበረውን ፍርድ ሙሉ በሙሉ የሚሰርዘው በመሆኑ የመሰየም ውሳኔውን የሚያሽር ወንጀል ካልተፈፀመ በስተቀር ተቀጥቶ የነበረው ሰው ከቅጣቱ የተነሳ እንዳይጠቀምባቸው ተከልክሎ የነበሩትን መብቶች ሁሉ እንደገና ይዞ የመስራት ችሎታ ይኖረዋል፡፡ ፍርዱ የሚሰረዝለት በመሆኑ ከወንጀለኞች መዝገብ ላይ ተፍቆለት ወደፊት እንዳልተፈረበት ይቆጠራል፡፡

የሕጉ ዓላማ የወንጀለኛው ወደ መልካም ሰውነት መመለስ ይቃና ዘንድ ለዚህ ብቁ የሆነን የቀድሞ ወንጀለኛ ምንም ዓይነት የወንጀለኛንነት ምልክት እንዳይኖር ማድረግ ነው፡፡ በመሆኑም ጥፋተኛነቱና ቅጣቱ እንዳልነበሩ ሆነው ሊቆጠሩ ይገባል፡፡ በተግባር ቀደም ሲል መፈፀሙ በፍርድ ቤት ጭምር በማስረጃ ተረጋግጦ የነበረውን እውነታ (የወንጀል ድርጊት) ሕጉ ለግለሰቡና ለሕብረተሰቡ ጥቅም ሲል እንዳልነበረ (እንዳልተፈጠረ) የሚቆጥረው በመሆኑ ከመሰየሙ በፊት የነበረውን ጥፋት እያነሳ የተሰየመውን ሰው መውቀስ በስም ማጥፋት ወንጀል የሚያስጠይቅ አድርጎታል፡፡ ስለ ጥፋቱ የተነሳው ለመልካም ዓላማ እንደሆነ አድርጎ በማቅረብ ከተጠያቂነት መዳንም አይቻልም፡፡ በዚህ መሰረትም የመሰየም ውሳኔው ተሰያሚውን ከቀድሞ የወንጀለኛነት ሪከርዱ ፍፁም ንፁህ ያደርገዋል ማለት ነው፡፡
Via Legal consulting limited
#join #join #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
July 24, 2021
July 24, 2021
the person charged with crime.” በማለት ይገልፃሉ፡፡ በመሆኑም የወንጀል ምርመራ የወንጀል የምርመራ መዝገቡን እስከ ማጠናቀቅ ድረስ ያለውን ሂደት ብቻ የሚመለከት አድርገው የሚያስቡና ተከሣሹንና በምርመራ ሂደት የተሰበሰቡትን ማስረጃዎች ለፍርድ ቤት በማቅረቡ ሂደት ምንም አይነት እገዛ ማድረግ እንደሌለባቸው የሚያስቡ መርማሪ ፖሊሶች “ የወንጀል ምርመራን እንደ መሠረታዊ ግብ ማሣኪያ ሂደት ሣይሆን ምርመራ ማጣራቱ በራሱ ግብ አድርገው የሚመለከቱ በመሆናቸው የአመለካከት ለውጥ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡

6. #የወንጀል ምርመራ ልዩ ባህሪ ያላቸውና የወንጃል ሰለባ የሆኑ ሰዎች በመያዣነት የታገቱባቸው ወንጀሎች ተፈፅመው በሆነ ጊዜ ከላይ ከተገለፁት ተግባራት በተጨማሪ የወንጀል ሰለባ የሆኑትን ሰዎች ከተጋረጠባቸው አደጋ ለመታደግና አስፈላጊውን እርዳታ እንዲያገኙ የሚከናወነውን ተግባር ያጠቃልላል፡፡ የተፈፀመው ወንጀል ሰውን አስገድዶ መሰወር፣ ጠልፉ፣ ንፁሐን ዜጎችን ማገትና መደራደሪያ ማድረግ የመሳሰሉት በሆነ ጊዜ ከላይ ከተገለፁት በተጨማሪ የወንጀሉን ሰለባ ለማስለቀቅ የሚከናወኑ ተግባራትን ያጠቃልላል፡፡
ከፀጋዬ ደመቀ ገፅ
#join #join #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
July 24, 2021
Tips of the Day Wisdom
Be mindful. Be grateful. Be positive. Be true. Be kind. So Let us be grateful to the people who make us happy; they are the charming gardeners who make our souls blossom.
Note.
When a new day begins, dare to smile gratefully. When there is darkness, dare to be the first to shine a light. When there is injustice, dare to be the first to condemn it. When something seems difficult, dare to do it anyway. When life seems to beat you down, dare to fight back. When there seems to be no hope, dare to find some. When you’re feeling tired, dare to keep going. When times are tough, dare to be tougher. When love hurts you, dare to love again. When someone is hurting, dare to help them heal. When another is lost, dare to help them find the way. When a friend falls, dare to be the first to extend a hand. When you cross paths with another, dare to make them smile. Always Dare to Be. Good morning. Danrabi
#join #join #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
July 25, 2021
በሰብአዊ መብቶች ጥበቃ የዐቃቤ ሕግ ሚና‼️‼️🔴
=========================
ዐቃቤ ሕግ በሕግ ጠባቂነቱ መንግስት የሚያወጣቸውን የተወሰኑ ሕጐች መከበራቸውን የሚያረጋግጥ የመንግስት አካል ነው፡፡ ሕግን የተላለፉ ሰዎችን ለሕግ በማቅረብ ሕግና ስርዓት በሕብረተሰቡ ውስጥ እንዲሰፍን ማድረግ ዋነኛ የዐቃቤ ሕግ ተግባር ነው፡፡ ይህ የመንግስት አካል እንደሌሎች የመንግስት ተቋማት ሁሉ የእለት ተዕለት ስራውን ሲያከናውን በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግስት የተረጋገጡ የዜጐች ሰብአዊ መብቶችና መሠረታዊ ነፃነቶች የማክበርና የማስከበር ኃላፊነት አለበት፡፡

በመሆኑም በመንግስት ተቋምነቱ ከሌሎች የመንግስት አካላት ጋር ያለው ህገ መንግስቱን የማክበርና የማስከበር የወል ኃላፊነት እንደተጠበቀ ሆኖ ዐቃቤ ሕግ በሕግ አስከባሪነቱ እና ጠባቂነቱ ለሕግ የበላይነት እና ለሰብአዊ መብቶች ጥበቃ በወንጀል ፍትህ አስተዳደር ውስጥ ከፍተኛ ሚና መጫወት ይኖርበታል፡፡

የተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባኤ እኤአ ሴፕቴምበር 1990 ባወጣው የዐቃብያነ ሕግ ሚናን በሚመለከት መመሪያ(UN Guidelines on the Role of prosecutors) በወንጀል ፍትህ ሂደት ያላቸውን ከፍተኛ ሓላፊነት በተመለከተ በአንቀጽ 12 ስር አቃብያነ ህግ በህጉ መሰረት ግዴታቸውን ፍትሃዊ በሆነ ሁኔታ መወጣት እንዳለባቸው ከማስቀመጡ በተጨማሪ ሰብዓዊ ክብርን የመጠበቅ፣ ሰብአዊ መብቶችን የማክበርና እንከን የሌለው የወንጀል የፍትህ ስርአት እንዲኖር አስተዋጽኦ ማድረግ እንደሚኖርባቸው አስቀምጧል፡፡

ከተጠቀሰው የተባበሩት መንግስታት መመሪያ በሚቀራረብ ሁኔታ ዐቃቤ ሕግ ሰብአዊ መብቶች እንዲከበሩ በፍትህ ስርዓቱ ውስጥ የሚያደርገው አስተዋፅጾ ከምርመራ አንስቶ የተጠርጣሪው ጥፋተኝነት ተረጋግጦ ቅጣት እስኪጣልበት ወይም ንፁህ መሆኑ እስኪረጋገጥ ድረስ ሊዘልቅ እንደሚችል በብሄራዊ ህጎችም ተደንግጎ ይገኛል፡፡ ይህንንም እንደሚከተለው በዝርዝር እናያለን፡፡

1. #ዐቃብያነ ሕግ ከፖሊስ ምርመራ ጋር በተያያዘ ስላለባቸው ኃላፊነት

በሕብረተሰብ ውስጥ ሰላምን የሚያደፈርስ እንቅስቃሴ ወይም ሕገወጥ ተግባር ተፈጽሞ ሲገኝ አጥፊዎችን ለፍርድ ለማቅረብ የወንጀል ምርመራ ስራ በዋነኛነት በፖሊስ አካላት እንደሚካሄድ የታወቀ ነው፡፡ የወንጀል ምርመራ ስራ ሂደት በባህሪው የዜጐችን መብት የመገደብ ወይም የመንካት ሁኔታ የሚያስከትል በመሆኑ ከዜጐች የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ አንፃር በጥንቃቄ ሊከናወን የሚገባው ተግባር ነው፡፡

የወ/መ/ሕ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 8/2/ ዐቃቤ ሕግ ተግባሩን በሚያከናውንበት ጊዜ አስፈላጊ የሆነውን ትዕዛዝና መመሪያ ለፖሊስ የመስጠትና ፖሊስ በሕጉ መሠረት ግዴታውን መወጣቱን ማረጋገጥ እንዳለበት መደንገጉ ፖሊስ የምርመራ ስራውን ሲያከናውን የግለሰቦችን ሰብአዊ መብቶች ባከበረና በሕግ በተወሰኑ ስርዓቶች መሰረት ኃላፊነቱን መወጣቱን ዐቃቤ ሕግ እንዲቆጣጠር የታለመ እንደሆነ ይታመናል፡፡

በቅርብ አመታት ወጥተው በፌዴራል መንግስት ተፈፃሚ ከሆኑ ሕጐች መካከልም የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አዋጅ ቁጥር 313/95 እና የኢፌዲሪ አስፈፃሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጣው አዋጅ ቁጥር 471/98 ዐቃቤ ሕግ የፖሊስን ተግባር ሕጋዊነት የሚቆጣጠርበት ድንጋጌ አካተዋል፡፡ በፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አዋጅ ቁጥር 313/95 አንቀፅ 7/9/ ፌዴራል ፖሊስ “የወንጀል ምርመራን በተመለከተ ከፌዴራል ዐቃቤ ሕግ የሚሰጠውን ትዕዛዝ” እንደሚፈፅም የተደነገገ ሲሆን በአዋጅ ቁጥር 471/98 አንቀፅ 23/3/ ስር ደግሞ ፍትህ ሚኒስቴር (ፌዴራል ዐቃቤ ሕግ)

“በፌዴራል ፍርድ ቤቶች ስልጣን ስር የሚወድቁ ወንጀል ተፈፅሟል ብሎ ሲያምን ምርመራ እንዲደረግ ያዛል፣ በቂ ምክንያት ሲኖር የተጀመረ ምርመራ እንዲቆም ወይም ተጨማሪ ምርመራ
እንዲከናወን ያደርጋል...”

በማለት ደንግጓል፡፡ በዚህ ድንጋጌ መሰረት የፌዴራል ዐቃቤ ሕግ ከተለያዩ አካላት ወንጀል ስለመፈፀሙ ጥቆማ ሲደርሰው፣ ፖሊስ አላግባብ ምርመራ አላጣራም አለኝ የሚል አቤቱታ ሲቀርብለት ወዘተ ምርመራ እንዲጀመር ለፖሊስ ትዕዛዝ የሚሰጥ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ከሕግ ውጪ ምርመራ እየተጣራብኝ ነው የሚል አቤቱታ ሲቀርብለት እና በሌሎች ምክንያቶች አላግባብ በፖሊስ የተጀመሩ ምርመራዎች መኖራቸውን ካረጋገጠ የተጀመረ ምርመራ እንዲቋረጥ ትዕዛዝ ሊሰጥ ይችላል፡፡ የክልል ዐቃቤ ሕግ ተቋማትም የክልል ፖሊሶች ከሚፈፅሙት የምርመራ ተግባር ጋር በተያያዘ ተመሳሳይ ስልጣን እንዳላቸው ይታመናል፡፡

ከላይ ከቀረቡት ዝርዝር ድንጋጌዎች ዐቃቤ ህግ በራሱ ህግ አስፈጻሚ ብቻ ሳይሆን የፖሊስ አባላትም የዜጐችን ሰብአዊ መብቶች የሚመለከቱ ሕግጋት በትክክል ማክበራቸውን የማረጋገጥ ኃላፊነት እንዳለበት እና በሰብአዊ መብቶች ጥበቃ ቁልፍ የሆነ ድርሻ እንዳለው ለመረዳት ይቻላል፡፡

2. #ዐቃብያነ ህግ ከክስ ጋር በተያያዘ ስላለባቸው ኃላፊነት ዐቃቤ ሕግ በፖሊስ ተጣርቶ የቀረበለትን የምርመራ መዝገብ በማየት
የዜጐችን የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት መብት ግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ፡-

ተጨማሪ ደጋፊ ማስረጃ ሊገኝ ይችላል ብሎ ካመነ ተጨማሪ ምርመራ እንዲደረግ በወ/መ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 38/ሐ/ መሠረት ለፖሊስ ትዕዛዝ የማስተላለፍ፣
ተጠርጣሪን ጥፋተኛ ለማድረግ የሚያስችል በቂ ማስረጃ የለም ብሎ ካመነ ደግሞ በወ/መ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 42/1/ሀ/ መሠረት ክስ ያለማቅረብ ወይም
ክስ ለመመስረት እና ተከሳሽን ለማስቀጣት የሚያስችል በቂ ማስረጃ አለ ብሎ ካመነ ደግሞ ክስ በማዘጋጀት ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት በማቅረብ ተገቢውን ክርክር የማድረግ ግዴታ አለበት፡፡

ዐቃቤ ሕግ በተከሳሽ ላይ ክስ የሚያቀርበው ሕዝብን በመወከል ስለሆነ፣ የሕዝብ ጥቅም የሚጠበቀው ጥፋተኞች ሲቀጡ እና ንፁህ የሆኑ ሰዎች ከክስ ነፃ ሲሆኑ በመሆኑ በመጀመርያ ክስ ለመመስረት በቂ ማስረጃ መኖሩን የማረጋገጥ፣ በክሱ መሰማት ሂደት የተከሳሽን ንፁህ መሆን የሚያረጋግጡ ማስረጃዎች ካገኘ ወይም ጥፋተኛ ሊያስደርጉ የሚችሉ ማስረጃዎች በሂደት የጠፉ ከሆነ ወዘተ ደግሞ ክሱን ማንሳት ይጠበቅበታል፡፡ፀጋዬ ደመቀ ሎየር ገፅ ተገኘ
#join #join #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
July 25, 2021
July 26, 2021
July 26, 2021
Explanatory_Note_for_the_Provisions_of_Federal_Administrative_Procedure.pdf
2 MB
July 26, 2021
July 26, 2021