🔴በኮሮና እዳንያዝ የሚከላከል ባህላዊ መዳኒት🔴
2ፍንካች ነጭ ሽንኩርት 2ዝንጅብል
1/4 ቀይ ሽንኩርት መውቀጥ
8ፍሬ ጥቁር አዝሙድ ሳይፈጭ
8ፍሬ ድንብላል ሳይፈጭ
1የሾርባ ማንኪያ ነጭ አዝሙድ ሳይፈጭ
1ሎሚ ጭማቂ በማደባለቅ በ አንድ ሊትር ውሃ መበጥበጥ እና 🔴ለ1ቀን ማሣደር ከዚያም አንድ ሊትሩን በአንድ ቀን መጠጣት
ለሚቀጥለውም ቀን በዚሁ መልክ ማዘጋጀት 🔴ለ3ቀን መጠጣት ህመሙ እንዳይዘን ይከላከላል።
ብለው በውስጥ መስመር ላኩልን ያገሬ ሰዎች እባካችሁ እንሞክረው እና እራሳችንን እንከላከል።🔴
@lawsocieties
https://telegram.me/lawsocieties
2ፍንካች ነጭ ሽንኩርት 2ዝንጅብል
1/4 ቀይ ሽንኩርት መውቀጥ
8ፍሬ ጥቁር አዝሙድ ሳይፈጭ
8ፍሬ ድንብላል ሳይፈጭ
1የሾርባ ማንኪያ ነጭ አዝሙድ ሳይፈጭ
1ሎሚ ጭማቂ በማደባለቅ በ አንድ ሊትር ውሃ መበጥበጥ እና 🔴ለ1ቀን ማሣደር ከዚያም አንድ ሊትሩን በአንድ ቀን መጠጣት
ለሚቀጥለውም ቀን በዚሁ መልክ ማዘጋጀት 🔴ለ3ቀን መጠጣት ህመሙ እንዳይዘን ይከላከላል።
ብለው በውስጥ መስመር ላኩልን ያገሬ ሰዎች እባካችሁ እንሞክረው እና እራሳችንን እንከላከል።🔴
@lawsocieties
https://telegram.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
የትግራይ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ
* ማሳሰቢያ: ይህ ፅሁፍ ከሳምንት በፊት የተፃፈ ነው። ለመስተዳድሩ Benefit of doubt ለመስጠት 15 ቀኗ ትለፍ በሚል ሳይለጠፍ ቆይቷል።
መሪ ድርጅቱ እንደሆነ ሁሌም ፖሊስ ስቴት (police-state) ለመፍጠር የተቀባበለ ይመስለኛል። በተለይ ግራ የተጋባ ሰሞን፣ የግለሰብ ፖለቲካ የነገሰ ሰሞን እና የሐሳብ ድርቅ ሲመታው አይጣል ነው። ሁሌም የታየ ነው። ፍርሃት እና ሥጋት ያፋፋዋል፣ መዳኛውም ነው። ስለዚህ እሷን መጀን ብሎ ያለችዋን ፍርሃት ማጉላት እና ማለብ አቋራጩ መንገድ ይመስለዋል። ልንወረር ነው ከሰመች እና ኮሮና መጣልን። የሚያሳዝነው አሁን አሁን መድህን ከርዕዮተ–አለም ይልቅ ከስቴድየም ማግኘት ጀምሯል።
የሚገርመኝ አክቲቭ/ንቁ ነኝ የሚለው ልሂቅ ነው፤ ለመጠየቅ ሳይሆን ለማመን የተቀባበለው ማለቴ ነው። የማይናቅ ቁጥር ያለው ዝም ያለ ልሂቅ እንዳለ ሳይረሳ። ሶሻል ሚዲያም ከድሮው የስብሰባ አገዛዝ የተለየ አይደለም። በሆነ አክቲቪስት/ምሁር በኩል ሃሳቡን ያሰርጋል ድርጅቱ፣ ልሂቁ የራሱ ሃሳብ እንዲመስለው ይደረጋል፣ ከዛ ደግፎ ይከራከራል። በዛ ላይ ቀድሞ በደንብ የተሰራው የፌደራል V. ትግራይ "ግብግብ" ለአስቸኳይ አዋጅ ተቀባይነት ጠቅሟል። ፌደራሉ የማይረባ እና ሃላፊነት የጎደለው ነው የሚለውን (አይሆንም ማለቴ አይደለም) ለማስረገጥ ትግራይ ቀድማ እርምጃ መውሰድ አለባት ይልሃል። በዛ ላይ ኮሮና ነው፣ አስበው። (አለምን ያንቀጠቀጠ፣ ያውም ጂ7ቶችን፣ ስለዚህ እኛን ካገኘንማ ይጨርሰናል 😊 አዎን አውስትራሊያ እሳት ቃጠሎ ጎድቷታል፣ ውይ እኛ ጋር ቢመጣ ደግሞ አለቀልን፣ የእሳት አደጋ መኪና አለን? 😃 ) ሆይ ሆይ ሆይ ሆይ ...
እስኪ ጉዳዩ የአመፅና ብጥብጥ ነው እንበል። መቼ ነው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሚታወጀው? ሶስት፣ አራት አመት በፊት ስንሰልቀው ስንወቅጠው ነበር እና አላሰለችህም። ብጥብጡ ከተለመደው የፖሊስ እና ፀጥታ ኃይል እና አሰራር በላይ ሲሆን ነው። አለቀ። ታድያ ኮሮና በአገራችን ብሎም በትግራይ እንደዛ አይነት ደረጃ ላይ ደርሷል ወይ ብለን መጠየቅ ነው። ስንት ቆሰለ፣ ሞተ፣ ፖሊስን ጨምሮ ትላለህ ለብጥብጥ። ኮሮናም የራሱ አውድ/ኮንቴክስት አለው። መንግስት ቴስት አድርጎ ያመጣው ማስረጃ አለ? እሱን የምታረጋግጥበት ገለልተኛ መንገድ መፈለጉን እንርሳው። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጅ ካለበት ደግሞ ከላይ በጠየቅነው ማስረጃ ላይ የተመሰረተ ሆኖ ምን ምን ስልጣንን ያካተተ ይሁን? በአገርም በክልልም ስርጭቱ ምን ያህል ነው? በእግዜር በአገር 29 ሆኖ 2 ተርፈዋል። (አንተ ዱቅ ብለህ በኮሮና ቻናል፣ ማለትም ሲኤንኤን ኒውዮርክ የአስቸኳይ ጊዜ ይታወጅ አይታወጅ የሚል ክርክር ታያለህ፣ የኛ ሚዲያም ራሱ ሲኤንኤን ሆኗል) የተያዙ ሰዎች ቁጥር፣ የሞቱ ሰዎች ቁጥር፣ መተላለፊያ መንገድ ወዘተ ታይቶ መንግሥት ለዛ ሲባል ይሄ ይሄ ስልጣን ይኑረው ይባላል። ይሄ ይሄ አያስፈልግም ምክንያቱም ከመረጃው ጋር ወይ ከቁጥሮች ጋር አይሄድም ይባላል። ለምሳሌ አንድም የተያዘ ሰው መኖሩን አልሰማንም አላየንም። ምርመራ ትናንት ተጀመረ ተባለ፣ ለምን ከዚያ በኋላ ስለ አዋጅ አንነጋገርም ነበር? ራንደም ምርመራ ማድረግ ይቻላልኮ፣ ሳምፕል ፖፑሌሽን ሳይዝ ወስደህ። ከዛ ባለው ስጋት መሰረት አስቸኳይ ጊዜ ይወራል፣ ከተስማማህበት ደግሞ ስለሚገባው ስልጣን ይወራል። ስልጣኑም በዛው በስጋቱ መሰረት ይወሰናል። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የክልሉ ድንበር (entry point) ላይ ብቻ ሊያተኩር ይችላል፣ በኔ እምነት ከዛ ማለፍ የለበትም ነበር። ወይ "እንደ አሁኑ" ከተማ ገጠር ሊሆን ይችላል፣ ክላስተር ለይተን ማድረግም ይቻላል፣ ሙሉ በሙሉ ቤት ቅር ሊሆንም ይችላል (አሁን እራሱ እየፎከረ ነው ሊቀመንበሩ)። የትኛው ደረጃ እንደ ታወጀ እየው እስኪ በትግራይ? ሱቅህ ውስጥ ገብቶ ፍሪጅ ያሽግልሃል። በየቀኑም ስልጣኑም እየጨመረ ነው። እንዴት? በምን መሰረት? እንደ ህፃን ሓንጉጉ ስለተባለ ፈርተን እናውጃለን? እርምጃችን ከቻይና ጋር ተመሳስሎ፣ በበሽታ የተያዘ ሰው እንኳን የለንም።
እንበልና የአብይ መንግስት ሲዳማ ላይ ወይ ሶማሌ ላይ አስቸኳይ ጊዜ ቢያውጅ እንዴት ነበር የምትከራከረው? የኢፌዴሪ ህገመንግስት ምነው ተረሳ፣ ከአድማስ ባሻገር ብቻ ነው የሚታየን? አሁን ደሞ ሌሎች ክልሎች (ማለቴ ገዥ ፓርቲዎች) የትግራይን ፈለግ እየተከተሉ ነው 😔 በነበረው ትርክት ከሄድን ይሄን እድል ተጠቅሞ አስቸኳይ ጊዜ ያውጃል ብለን ምንጠብቀው ዶር አብይ ነበር እኮ 😃
ወደ መሬት ስንወርድ ደሞ እዚ ሰፈር ይታወጅ የሚለው፣ የሚያውጀው፣ የሚፈፅመው ሁሉም ደሞዝተኛ ነው። እሱ ምን አለበት? ቤት ተዘግቶብህ፣ ቢዝነስ ቆሞብህ፣ መኪና ቆሞብህ፣ ሥራ ከነደሞዙ ቆሞብህ አላየህም። ያውም የኪራይ ስራ። በዛ ኪራይ–ቤት ሰርቶ ባገኘው የመኖርያ ቤቱን ኪራይ ከፍሎ ስንት ቤተሰብ የሚያስተዳድረው ስንት ነው? አውቶቡስ፣ ሚኒባስ ስንት ነው? ደግሞ ያንን የደደቢት ብድር የሚከፍለውስ? የባንክ ብድር ያለበት? የንግድ ፈቃድ ልዩነት (ቁርስ ቤት ብሎ ቡና አብሮ የሚሸጡ፣ ቁርስና ኮፊ ሐውስ የሚል፣ ኮፊ ሐውስ ብሎ ቁርስም ሲሸጡ የነበሩ) አስገራሚ የኑሮ ደረጃ ልዩነት ፈጥሯል። የገጠሩን ህዝብ ተወው፣ ድሮስ ሁሉም ለራሱ ፖለቲካ ሲል ያነሳዋል እንጂ ማን ትዝ ብሎት? ህዝብ እዬዬ እያለ ነው። ከማማህ ላይ ውረድ እና እየው፣ ስማው። ተከራከርለት። ልክ የፌዴራሉን መንግስት እና ፓርቲ እንደምትጠይቀው እና እንደምትሞግተው የራስህንም ክልል መንግስት እና ፓርቲ ጠይቅ። ሞግት።
* ይህ ፅሁፍ ኮሮናን "ዝም ብሎ በሽታ ነው፣ አያሰጋም እያለ ነው" ብለህ አትውሰደው። አታምታታ። ይህ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጉዳይ ነው።
* ኮሮናን ለመከላከል እጃችንን ቶሎ ቶሎ እንታጠብ፣ ንክኪ እናስወግድ። ሰው በዛ ባለበት ቦታ አፍና አፍንጫችን ላይ መሸፈኛ እናድርግ።
via ሀሰን ሙሀመድ
https://telegram.me/lawsocieties
* ማሳሰቢያ: ይህ ፅሁፍ ከሳምንት በፊት የተፃፈ ነው። ለመስተዳድሩ Benefit of doubt ለመስጠት 15 ቀኗ ትለፍ በሚል ሳይለጠፍ ቆይቷል።
መሪ ድርጅቱ እንደሆነ ሁሌም ፖሊስ ስቴት (police-state) ለመፍጠር የተቀባበለ ይመስለኛል። በተለይ ግራ የተጋባ ሰሞን፣ የግለሰብ ፖለቲካ የነገሰ ሰሞን እና የሐሳብ ድርቅ ሲመታው አይጣል ነው። ሁሌም የታየ ነው። ፍርሃት እና ሥጋት ያፋፋዋል፣ መዳኛውም ነው። ስለዚህ እሷን መጀን ብሎ ያለችዋን ፍርሃት ማጉላት እና ማለብ አቋራጩ መንገድ ይመስለዋል። ልንወረር ነው ከሰመች እና ኮሮና መጣልን። የሚያሳዝነው አሁን አሁን መድህን ከርዕዮተ–አለም ይልቅ ከስቴድየም ማግኘት ጀምሯል።
የሚገርመኝ አክቲቭ/ንቁ ነኝ የሚለው ልሂቅ ነው፤ ለመጠየቅ ሳይሆን ለማመን የተቀባበለው ማለቴ ነው። የማይናቅ ቁጥር ያለው ዝም ያለ ልሂቅ እንዳለ ሳይረሳ። ሶሻል ሚዲያም ከድሮው የስብሰባ አገዛዝ የተለየ አይደለም። በሆነ አክቲቪስት/ምሁር በኩል ሃሳቡን ያሰርጋል ድርጅቱ፣ ልሂቁ የራሱ ሃሳብ እንዲመስለው ይደረጋል፣ ከዛ ደግፎ ይከራከራል። በዛ ላይ ቀድሞ በደንብ የተሰራው የፌደራል V. ትግራይ "ግብግብ" ለአስቸኳይ አዋጅ ተቀባይነት ጠቅሟል። ፌደራሉ የማይረባ እና ሃላፊነት የጎደለው ነው የሚለውን (አይሆንም ማለቴ አይደለም) ለማስረገጥ ትግራይ ቀድማ እርምጃ መውሰድ አለባት ይልሃል። በዛ ላይ ኮሮና ነው፣ አስበው። (አለምን ያንቀጠቀጠ፣ ያውም ጂ7ቶችን፣ ስለዚህ እኛን ካገኘንማ ይጨርሰናል 😊 አዎን አውስትራሊያ እሳት ቃጠሎ ጎድቷታል፣ ውይ እኛ ጋር ቢመጣ ደግሞ አለቀልን፣ የእሳት አደጋ መኪና አለን? 😃 ) ሆይ ሆይ ሆይ ሆይ ...
እስኪ ጉዳዩ የአመፅና ብጥብጥ ነው እንበል። መቼ ነው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሚታወጀው? ሶስት፣ አራት አመት በፊት ስንሰልቀው ስንወቅጠው ነበር እና አላሰለችህም። ብጥብጡ ከተለመደው የፖሊስ እና ፀጥታ ኃይል እና አሰራር በላይ ሲሆን ነው። አለቀ። ታድያ ኮሮና በአገራችን ብሎም በትግራይ እንደዛ አይነት ደረጃ ላይ ደርሷል ወይ ብለን መጠየቅ ነው። ስንት ቆሰለ፣ ሞተ፣ ፖሊስን ጨምሮ ትላለህ ለብጥብጥ። ኮሮናም የራሱ አውድ/ኮንቴክስት አለው። መንግስት ቴስት አድርጎ ያመጣው ማስረጃ አለ? እሱን የምታረጋግጥበት ገለልተኛ መንገድ መፈለጉን እንርሳው። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጅ ካለበት ደግሞ ከላይ በጠየቅነው ማስረጃ ላይ የተመሰረተ ሆኖ ምን ምን ስልጣንን ያካተተ ይሁን? በአገርም በክልልም ስርጭቱ ምን ያህል ነው? በእግዜር በአገር 29 ሆኖ 2 ተርፈዋል። (አንተ ዱቅ ብለህ በኮሮና ቻናል፣ ማለትም ሲኤንኤን ኒውዮርክ የአስቸኳይ ጊዜ ይታወጅ አይታወጅ የሚል ክርክር ታያለህ፣ የኛ ሚዲያም ራሱ ሲኤንኤን ሆኗል) የተያዙ ሰዎች ቁጥር፣ የሞቱ ሰዎች ቁጥር፣ መተላለፊያ መንገድ ወዘተ ታይቶ መንግሥት ለዛ ሲባል ይሄ ይሄ ስልጣን ይኑረው ይባላል። ይሄ ይሄ አያስፈልግም ምክንያቱም ከመረጃው ጋር ወይ ከቁጥሮች ጋር አይሄድም ይባላል። ለምሳሌ አንድም የተያዘ ሰው መኖሩን አልሰማንም አላየንም። ምርመራ ትናንት ተጀመረ ተባለ፣ ለምን ከዚያ በኋላ ስለ አዋጅ አንነጋገርም ነበር? ራንደም ምርመራ ማድረግ ይቻላልኮ፣ ሳምፕል ፖፑሌሽን ሳይዝ ወስደህ። ከዛ ባለው ስጋት መሰረት አስቸኳይ ጊዜ ይወራል፣ ከተስማማህበት ደግሞ ስለሚገባው ስልጣን ይወራል። ስልጣኑም በዛው በስጋቱ መሰረት ይወሰናል። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የክልሉ ድንበር (entry point) ላይ ብቻ ሊያተኩር ይችላል፣ በኔ እምነት ከዛ ማለፍ የለበትም ነበር። ወይ "እንደ አሁኑ" ከተማ ገጠር ሊሆን ይችላል፣ ክላስተር ለይተን ማድረግም ይቻላል፣ ሙሉ በሙሉ ቤት ቅር ሊሆንም ይችላል (አሁን እራሱ እየፎከረ ነው ሊቀመንበሩ)። የትኛው ደረጃ እንደ ታወጀ እየው እስኪ በትግራይ? ሱቅህ ውስጥ ገብቶ ፍሪጅ ያሽግልሃል። በየቀኑም ስልጣኑም እየጨመረ ነው። እንዴት? በምን መሰረት? እንደ ህፃን ሓንጉጉ ስለተባለ ፈርተን እናውጃለን? እርምጃችን ከቻይና ጋር ተመሳስሎ፣ በበሽታ የተያዘ ሰው እንኳን የለንም።
እንበልና የአብይ መንግስት ሲዳማ ላይ ወይ ሶማሌ ላይ አስቸኳይ ጊዜ ቢያውጅ እንዴት ነበር የምትከራከረው? የኢፌዴሪ ህገመንግስት ምነው ተረሳ፣ ከአድማስ ባሻገር ብቻ ነው የሚታየን? አሁን ደሞ ሌሎች ክልሎች (ማለቴ ገዥ ፓርቲዎች) የትግራይን ፈለግ እየተከተሉ ነው 😔 በነበረው ትርክት ከሄድን ይሄን እድል ተጠቅሞ አስቸኳይ ጊዜ ያውጃል ብለን ምንጠብቀው ዶር አብይ ነበር እኮ 😃
ወደ መሬት ስንወርድ ደሞ እዚ ሰፈር ይታወጅ የሚለው፣ የሚያውጀው፣ የሚፈፅመው ሁሉም ደሞዝተኛ ነው። እሱ ምን አለበት? ቤት ተዘግቶብህ፣ ቢዝነስ ቆሞብህ፣ መኪና ቆሞብህ፣ ሥራ ከነደሞዙ ቆሞብህ አላየህም። ያውም የኪራይ ስራ። በዛ ኪራይ–ቤት ሰርቶ ባገኘው የመኖርያ ቤቱን ኪራይ ከፍሎ ስንት ቤተሰብ የሚያስተዳድረው ስንት ነው? አውቶቡስ፣ ሚኒባስ ስንት ነው? ደግሞ ያንን የደደቢት ብድር የሚከፍለውስ? የባንክ ብድር ያለበት? የንግድ ፈቃድ ልዩነት (ቁርስ ቤት ብሎ ቡና አብሮ የሚሸጡ፣ ቁርስና ኮፊ ሐውስ የሚል፣ ኮፊ ሐውስ ብሎ ቁርስም ሲሸጡ የነበሩ) አስገራሚ የኑሮ ደረጃ ልዩነት ፈጥሯል። የገጠሩን ህዝብ ተወው፣ ድሮስ ሁሉም ለራሱ ፖለቲካ ሲል ያነሳዋል እንጂ ማን ትዝ ብሎት? ህዝብ እዬዬ እያለ ነው። ከማማህ ላይ ውረድ እና እየው፣ ስማው። ተከራከርለት። ልክ የፌዴራሉን መንግስት እና ፓርቲ እንደምትጠይቀው እና እንደምትሞግተው የራስህንም ክልል መንግስት እና ፓርቲ ጠይቅ። ሞግት።
* ይህ ፅሁፍ ኮሮናን "ዝም ብሎ በሽታ ነው፣ አያሰጋም እያለ ነው" ብለህ አትውሰደው። አታምታታ። ይህ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጉዳይ ነው።
* ኮሮናን ለመከላከል እጃችንን ቶሎ ቶሎ እንታጠብ፣ ንክኪ እናስወግድ። ሰው በዛ ባለበት ቦታ አፍና አፍንጫችን ላይ መሸፈኛ እናድርግ።
via ሀሰን ሙሀመድ
https://telegram.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
Mathias:
Hyyy ale.. do u have info about exit exam of zis year.. pleas share if any
Hyyy ale.. do u have info about exit exam of zis year.. pleas share if any
አለሕግAleHig ️
የትግራይ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ * ማሳሰቢያ: ይህ ፅሁፍ ከሳምንት በፊት የተፃፈ ነው። ለመስተዳድሩ Benefit of doubt ለመስጠት 15 ቀኗ ትለፍ በሚል ሳይለጠፍ ቆይቷል። መሪ ድርጅቱ እንደሆነ ሁሌም ፖሊስ ስቴት (police-state) ለመፍጠር የተቀባበለ ይመስለኛል። በተለይ ግራ የተጋባ ሰሞን፣ የግለሰብ ፖለቲካ የነገሰ ሰሞን እና የሐሳብ ድርቅ ሲመታው አይጣል ነው። ሁሌም የታየ ነው። ፍርሃት…
Ansaredin Juwhar:
Ye tgray weys ye ager new miyaweraw gra yegebaw glxinet yegodelew werea iko teposto yalew wstu sle ager new gn titlu gn sle tgray emergency declaration new mnamn ylalu eski negeru mndnew
Ye tgray weys ye ager new miyaweraw gra yegebaw glxinet yegodelew werea iko teposto yalew wstu sle ager new gn titlu gn sle tgray emergency declaration new mnamn ylalu eski negeru mndnew
FSC decided files.pdf
5 MB
የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል በከፊል ዝግ ሆነው በቆዩባቸው ጊዜያት የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ከመጋቢት 11- 30 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ በተለያዩ ችሎቶች በቀረቡ መዝገቦች ላይ የተሰጡ ውሳኔዎች የሚገልጽ መረጃ እንዲህ ቀርቧል፡፡
የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
በችሎቶች የተሰጡ ውሳኔዎች Table.pdf
160.7 KB
የፌደራል ፍርድ ቤቶች የኮሮና ቫይረስ ወረርሽንን ለመከላከል በከፊል ዝግ ሆነው በቆዩባቸው ጊዜያት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከመጋቢት 11 - 28/2012 ዓ.ም ድረስ በተለያዩ ችሎቶች በቀረቡ መዝገቦች ላይ የተሰጡ ውሳኔዎች እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡
Emanuel T Future Lawyer:
Hello Ale Family
I am Eskendir From Gambela University School of Law.
I am in need of Sound Lecture on Law of Person, Family law and on Succession. Please send me.
Stay Home Stay Safe!
Thank You!
Please if u have ,dont post it , just send me through my chat.. because time is not for seeking such kinda help.
Hello Ale Family
I am Eskendir From Gambela University School of Law.
I am in need of Sound Lecture on Law of Person, Family law and on Succession. Please send me.
Stay Home Stay Safe!
Thank You!
Please if u have ,dont post it , just send me through my chat.. because time is not for seeking such kinda help.
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ማስፈፀሚያ ደንብ ይፋ ሆነ
https://telegram.me/lawsocieties
https://telegram.me/lawsocieties
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ማስፈፀሚያ ደንብ ይፋ ሆነ
አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 3 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ስርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠርና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ የወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማስፈፀሚያ ደንብን የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ይፋ አደረገ።
በሚኒስትሮች ምክር ቤት የወጣው አዋጅ ትናንት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መፅጽደቁ ይታወቃል።
የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ የአዋጁን ማስፈፀሚያ ደንብ አጠቃላይ ይዘት በሚመለከት ዛሬ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በህገ መንግስቱ አንቀፅ 93 ንኡስ ቁጥር 4 መሰረት የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማስፈፀሚያ ደንብ ማውጣት እንዳለበት ይደነግጋል።
በዚህም መሰረት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ያወጣውን ማስፈፀሚያ ደንብ አጠቃላይ ዝርዝር በሚመለከት ወይዘሮ አዳነች አብራርትዋል።
ማስፈፀሚያ ደንቡ አጠቃላይ አራት ዋና ዋና ከፍሎች ያሉት ሲሆን ይሄውም ክልከላን የሚያስቀምጥ፣ ግደታዎችን የሚጥል፣ የአስፈፃሚ አካላትን ክንውን እንዲሁም ልዩ ለዩ ድንጋጌዎችን የያዘ ነው።
ክልከላን በሚመለከት ማንኛውም ሃይማኖታዊ ይሁን ፖለቲካዊ ስብሰባዎች፣ እድር፣ ደቦ፣ እቁብና ሌሎችም ከ4 ሰው በላይ ስብሰባዎች ክልክል ናቸው።
ከአራት ሰዎችም ቢሆኑ ሁለት የአዋቂ ሰው እርምጃ የጠበቀ መሆን እንዳለበት አቃቤ ህጓ አብራርተዋል።
ቀብርና ሌሎች አስፈላጊ ጉዳዮች ሲኖሩ ግን እየታዩ ሊፈቀዱ የሚችሉበት አሰራር መኖሩን ጠቁመዋል።
ታራሚዎች ከጠበቆቻቸው ጋር አስፈላጊው ጥንቃቄ ተደርጎ እንዲገናኙ የሚፈቀድ ቢሆንም ጥየቃ ለሚሄዱ ሰዎች የማይፈቀድ መሆኑ ተገልጿል።
በፖሊስ የተያዙ እስረኞችንም ስንቅ ከማቀበል በስተቀር መገናኘት የተከለከለ መሆኑን አስረድትዋል።
በድንበር አካባቢ ከካርጎ፣ የደረቅና ፈሳሽ ጭነት አገልግሎቶች በስተቀር ሌሎች እንቅስቃሴዎች ዝግ ተደርገዋል።
የቤት ተከራዮች በራሳቸው ፍላጎት ካልወጡ በስተቀር ማስውጣትና ኪራይም መጨመር በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተከልክሏል።
ሰራተኞችን መቀነስና የስራ ቅጥር ውል ማቋረጥም መከልከሉን ወይዘሮ አዳነች አብራርትዋል።
በዚህ ደንብ መሰረት ተማሪዎችና መምህራን በኦን ላይን ካልሆነ በአካል እንዲገናኙ አይፈቀድም።
ስፖርታዊ ጨዋታዎች፣ የህፃናትም ይሁን የሌሎች መጫወቻ ስፍራዎች እንዲሁም የእጅ መጨባበጥ ሰላምታ የተከለከለ መሆኑን ከኢዜአ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
በትራንስፖርት ዘርፍም አገር አቋራጭ ካለው ወንበር ከ50 በመቶ በላይ ተሳፋሪ መጫን የተከለከለ ነው፡፡
https://telegram.me/lawsocieties
አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 3 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ስርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠርና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ የወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማስፈፀሚያ ደንብን የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ይፋ አደረገ።
በሚኒስትሮች ምክር ቤት የወጣው አዋጅ ትናንት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መፅጽደቁ ይታወቃል።
የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ የአዋጁን ማስፈፀሚያ ደንብ አጠቃላይ ይዘት በሚመለከት ዛሬ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በህገ መንግስቱ አንቀፅ 93 ንኡስ ቁጥር 4 መሰረት የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማስፈፀሚያ ደንብ ማውጣት እንዳለበት ይደነግጋል።
በዚህም መሰረት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ያወጣውን ማስፈፀሚያ ደንብ አጠቃላይ ዝርዝር በሚመለከት ወይዘሮ አዳነች አብራርትዋል።
ማስፈፀሚያ ደንቡ አጠቃላይ አራት ዋና ዋና ከፍሎች ያሉት ሲሆን ይሄውም ክልከላን የሚያስቀምጥ፣ ግደታዎችን የሚጥል፣ የአስፈፃሚ አካላትን ክንውን እንዲሁም ልዩ ለዩ ድንጋጌዎችን የያዘ ነው።
ክልከላን በሚመለከት ማንኛውም ሃይማኖታዊ ይሁን ፖለቲካዊ ስብሰባዎች፣ እድር፣ ደቦ፣ እቁብና ሌሎችም ከ4 ሰው በላይ ስብሰባዎች ክልክል ናቸው።
ከአራት ሰዎችም ቢሆኑ ሁለት የአዋቂ ሰው እርምጃ የጠበቀ መሆን እንዳለበት አቃቤ ህጓ አብራርተዋል።
ቀብርና ሌሎች አስፈላጊ ጉዳዮች ሲኖሩ ግን እየታዩ ሊፈቀዱ የሚችሉበት አሰራር መኖሩን ጠቁመዋል።
ታራሚዎች ከጠበቆቻቸው ጋር አስፈላጊው ጥንቃቄ ተደርጎ እንዲገናኙ የሚፈቀድ ቢሆንም ጥየቃ ለሚሄዱ ሰዎች የማይፈቀድ መሆኑ ተገልጿል።
በፖሊስ የተያዙ እስረኞችንም ስንቅ ከማቀበል በስተቀር መገናኘት የተከለከለ መሆኑን አስረድትዋል።
በድንበር አካባቢ ከካርጎ፣ የደረቅና ፈሳሽ ጭነት አገልግሎቶች በስተቀር ሌሎች እንቅስቃሴዎች ዝግ ተደርገዋል።
የቤት ተከራዮች በራሳቸው ፍላጎት ካልወጡ በስተቀር ማስውጣትና ኪራይም መጨመር በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተከልክሏል።
ሰራተኞችን መቀነስና የስራ ቅጥር ውል ማቋረጥም መከልከሉን ወይዘሮ አዳነች አብራርትዋል።
በዚህ ደንብ መሰረት ተማሪዎችና መምህራን በኦን ላይን ካልሆነ በአካል እንዲገናኙ አይፈቀድም።
ስፖርታዊ ጨዋታዎች፣ የህፃናትም ይሁን የሌሎች መጫወቻ ስፍራዎች እንዲሁም የእጅ መጨባበጥ ሰላምታ የተከለከለ መሆኑን ከኢዜአ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
በትራንስፖርት ዘርፍም አገር አቋራጭ ካለው ወንበር ከ50 በመቶ በላይ ተሳፋሪ መጫን የተከለከለ ነው፡፡
https://telegram.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
#DrAbiyAhemed
April 11, 2020
በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መሰረት የተጣሉ ግዴታዎች ይፋ ሆነዋል!
የኮሮናቫይረስ ቨወረርሽኝ ሥርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠር እና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ የወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 3/2012 ማስፈፀሚያ ደንብ ዛሬ የሚኒስትሮች ምክር ቤት አጽድቋል። በዚሁ ደንብ መሰረትም የተጣሉ ግዴታዎች ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ናቸው።
1. ማንኛውም ኮቪድ-19 እንዳለበት የተጠረጠረ ሰው ወይም ወደ ሀገር የሚገባ አለማቀፍ መንገደኛ ኳራንታይን የመደረግና የኮቪድ-19 ምርመራ የማድረግ ግዴታ አለበት፤
2. ወደ ሀገር የገባ አለማቀፍ መንገደኛ ኳራንታይን በሚደረግበት ጊዜ የራሱን ወጪ የመሸፈን ሀላፊነት ያለበት ሲሆን፣ መንገደኛው የመክፈል አቅም የሌለው ከሆነ መንግስት ለዚሁ አላማ ባዘጋጀው ቦታ እንዲቆይ ይደረጋል፣
3. በኮቪድ-19 መያዙ የተረጋገጠ ማንኛውም ሰው መንግስት በሚያዘጋጀው ለይቶ ማቆያ ክፍል የመቆየት ግዴታ አለበት፤
4. በጉዞ ወቅት ኮቪድ-19 አለበት ተብሎ የሚጠረጠር መንገደኛ ሲኖር የማጓጓዣ አንቀሳቃሹ በአቅራቢያው ላለው ወይም ለሚያርፍበት የመግቢያና መውጫ ኬላ ሀላፊ ወይም የኮቪድ19 ምርመራ ለሚያደርግ ቡድን የማሳወቅ ሀላፊነት አለበት፤
5. የኮቪድ-19 ያለበት ወይም አለበት ተብሎ የሚጠረጠር ሰው ሰለመኖሩ የሚያውቅ ማንኛውም ሰው ለጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ወይም ለፖሊስ የማሳወቅ ግዴታ አለበት፣
6. የባንክ አገልግሎት በሚሰጥባቸው አካባቢዎች፣ በገበያዎች፣ በትራንስፖርት መሳፈሪያ ቦታዎች፣ በትራንስፖርት ውስጥ፣ በሱቆች፣ በመድሀኒት መሸጫ አካባቢዎች፣ ህዝባዊ አገልግሎት በሚሰጥባቸው ቦታዎችና ሌሎች ህዝብ በሚበዛባቸው መሰል አካባቢዎች የሚገኝ ማንኛውም ሰው አፍና አፍንጫው ላይ መሸፈኛ የማድረግ ግዴታ አለበት፤
7 በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 6 የተመለከተው የአፍና አፍንጫ መሸፈን ግዴታ ለዚሁ አላማ ተብሎ በፋብሪካ በተሰራ፣ በቤት ውስጥ ከተለያዩ ጨርቃጨርቆች በተዘጋጀ ወይም በማናቸውም አይነት ልብሶች ሊፈጸም ይችላል፡፡
8. ማንኛውም አገልግሎት የመንግስትም ሆነ የግል አገልግሎት ሰጪ ተቋም አገልግሎቱን ለማግኘት ወደ ተቋሙ ለሚመጡ ተገልጋዮች ቫይረሱን ለመከላከል የሚያስችሉ የንፅህና መጠበቂያ ቁሶችን ማዘጋጀትና ተገልጋዮች አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረጋቸውን የማረጋገጥ ሀላፊነት አለበት፣
9. ማናቸውም አገልግሎት የሚሰጡ የመንግስትም ሆነ የግል ተቋማት አገልግሎት ለማግኘት ወደ ተቋማቱ የሚሄዱ ተገልጋዮች ሁለት የአዋቂ እርምጃ ተራርቀው የሚቆሙበትን ቦታ ምልክት የማድረግ ሀላፊነት አለባቸው፤
10.የመንግስት የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎችና የግል የሚዲያ ተቋማት ኮቪድ-19ኝና ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተ የሚያስተላልፏቸው መረጃዎች፣ የዜና ትንተናዎች ወይም ፕሮግራሞች ሳይጋነኑ ወይም ሳይቃለሉ ተገቢው መረጃ ወደ ሕዝቡ የማድረስ እና አላግባብ የሆነ ድንጋጤና ሽብርን የማይፈጥሩ መሆን አለባቸው፣
11.ማንኛውም በፌዴራልም ሆነ በክልል የሚገኙ የመንግሥትም ሆነ የግል ተቋማት በተቋሙ ስር ለሚገኙ ሰራተኞች ስለቫይረሱ አስፈላጊውን መረጃ የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም የማድረስ፣ በመግቢያና መውጫ በሮችና ሌሎች አስፈላጊ ቦታዎች ላይ ቢያንስ እጅ ለመታጠብ የሚያስችል ውሃና ሳሙና ማዘጋጀት ፣ በተቻለ መጠን ሌሎች የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት የሚረዱ የጥንቃቄ ቁሳቁሶችን ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤
12.ማንኛውም በፌዴራልም ሆነ በክልል የሚገኙ የመንግሥትም ሆነ የግል ተቋማት በተቋሙ ስር የሚገኙ ሰራተኞች በአንድ ክፍል ውስጥ፣ በአንድ መስሪያ ቦታ ወይም በአንድ ትራንስፖርት ውስጥ ተጨናንቀውና አካላዊ ርቀትን ለመጠበቅ በማያስችል መልኩ እንዳይሰሩ ለማድረግ አስፈላጊውን ፈረቃ ማመቻቸት፤ ሰራተኞቹ ቤታቸው ሆነው የሚሰሩበትን ሁኔታ ወይም እረፍት በመውሰድ ስራ ቦታ እንዳይመጡ የማመቻቸት ሀላፊነት አለበት፤
13.ማንኘውም የፌዴራልም ሆነ የክልል የመንግስት ተቋምና በአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 መሰረት የሚተዳደሩ ሰራተኞችን የሚስተዳድር የግል ድርጅት ሰራተኞቹ ወደ ስራ ቦታ ለመሄድ ትራንስፖርት መጠቀም አስፈላጊ ከሆነ በስራ ላይ ለሚገኙ ሰራተኞች የትራንስፖርት አገልግሎት የማመቻቸት ሀላፊነት አለበት፤
14.ፖሊስ ኮሚሽን ወይም ማረሚያ ቤት ተጠርጣሪዎች ከጠበቆቻቸው ጋር የሚገናኙበትን ሁኔታ የማመቻቸት ሀላፊነት አለበት፤
15 ማንኛውም የቤት፣ የሆቴል፣ የአፓርታማ፣ የተሽከርካሪ፣ የአዳራሽ ወይም የማንኛውም ንብረት ባለቤት መንግስት የኮቪድ-19 ሥርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠር እና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ ለሚያደርገው ጥረት አስፈላጊ የሆነ ንብረቱን ለዚህ አላማ አገልግሎት ላይ እንዲውል በሚኒስትሮች ኮሚቴ ወይም ኮሚቴው ውክልና በሰጠው የመንግስት አካል ሲወሰንና ሲጠየቅ ንብረቱን ለእለት ከእለት ፍጆታው የሚጠቀምበት ካልሆነ በሰተቀር ውሳኔውን ተግባራዊ የማድረግ ግዴታ አለበት፤
16.ማንኛውም አምራች ወይም አገልግሎት ሰጪ ድርጅት፣ የኮቪድ-19 ሥርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠር እና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ ለሚያደርገው ጥረት አስፈላጊ የሆነ አግለግሎት እንዲሰጥ፣ አገልግሎቱን እንዲያሰፋ፣ ምርት እንዲያመርት፣ የሚያመርተውን ምርት መጠን እንዲጨምር፣ አዲስ ምርት አይነት እንዲያመርት ወይም ምርቱን መንግስት በሚወስነው ተመጣጣኝ ዋጋ ለመንግስት፣ ለሾማቾች ወይም ለህብረት ስራ ማህበራት እንዲሸጥ በሚኒስትሮች ኮሚቴ ወይም ኮሚቴው ውክልና በሰጠው የመንግስት አካል የሚሰጠውን ትዕዛዝ ተግባራዊ ማድረግ አለበት።
17.ሆቴሎች ለደንበኞቻቸው አገልግሎት በሚሰጡበት ጊዜ የእጅ መታጠቢያ ውሀና ሳሙና የማቅረብ ሀላፊነት ያለባቸው ሲሆን፣ የሆቴሉ ተጠቃሚዎችም እጃቸውን መታጠባቸውንና አስፈላጊውን ንፅህና አጠባበቅ ስርአት ተግባራዊ ማድረጋቸውን የማረጋገጥ እንዲሁም ደንበኞች ከተጠቀሙ በኋላ የተገለገሉባቸውን ጠረጴዛዎች፣ ወንበሮችና ሌሎች እቃዎች የማከም ግዴታ አለባቸው፣
18.ማንኛውም በስራ ላይ ያለ፣ ጡረታ የወጣ ወይም በትምህርት ላይ ያለ የጤና ወይም የሌላ ሙያ ባለቤት ወይም ማንኛውም ዜጋ የኮቪድ-19 ሥርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠር እና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ በሚደረገው ጥረት አስተዋፅዖ እንዲያደርግ በመንግስት ጥሪ ሲደረግለት የመተባበር ግዴታ አለበት፡፡
https://telegram.me/lawsocieties
April 11, 2020
በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መሰረት የተጣሉ ግዴታዎች ይፋ ሆነዋል!
የኮሮናቫይረስ ቨወረርሽኝ ሥርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠር እና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ የወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 3/2012 ማስፈፀሚያ ደንብ ዛሬ የሚኒስትሮች ምክር ቤት አጽድቋል። በዚሁ ደንብ መሰረትም የተጣሉ ግዴታዎች ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ናቸው።
1. ማንኛውም ኮቪድ-19 እንዳለበት የተጠረጠረ ሰው ወይም ወደ ሀገር የሚገባ አለማቀፍ መንገደኛ ኳራንታይን የመደረግና የኮቪድ-19 ምርመራ የማድረግ ግዴታ አለበት፤
2. ወደ ሀገር የገባ አለማቀፍ መንገደኛ ኳራንታይን በሚደረግበት ጊዜ የራሱን ወጪ የመሸፈን ሀላፊነት ያለበት ሲሆን፣ መንገደኛው የመክፈል አቅም የሌለው ከሆነ መንግስት ለዚሁ አላማ ባዘጋጀው ቦታ እንዲቆይ ይደረጋል፣
3. በኮቪድ-19 መያዙ የተረጋገጠ ማንኛውም ሰው መንግስት በሚያዘጋጀው ለይቶ ማቆያ ክፍል የመቆየት ግዴታ አለበት፤
4. በጉዞ ወቅት ኮቪድ-19 አለበት ተብሎ የሚጠረጠር መንገደኛ ሲኖር የማጓጓዣ አንቀሳቃሹ በአቅራቢያው ላለው ወይም ለሚያርፍበት የመግቢያና መውጫ ኬላ ሀላፊ ወይም የኮቪድ19 ምርመራ ለሚያደርግ ቡድን የማሳወቅ ሀላፊነት አለበት፤
5. የኮቪድ-19 ያለበት ወይም አለበት ተብሎ የሚጠረጠር ሰው ሰለመኖሩ የሚያውቅ ማንኛውም ሰው ለጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ወይም ለፖሊስ የማሳወቅ ግዴታ አለበት፣
6. የባንክ አገልግሎት በሚሰጥባቸው አካባቢዎች፣ በገበያዎች፣ በትራንስፖርት መሳፈሪያ ቦታዎች፣ በትራንስፖርት ውስጥ፣ በሱቆች፣ በመድሀኒት መሸጫ አካባቢዎች፣ ህዝባዊ አገልግሎት በሚሰጥባቸው ቦታዎችና ሌሎች ህዝብ በሚበዛባቸው መሰል አካባቢዎች የሚገኝ ማንኛውም ሰው አፍና አፍንጫው ላይ መሸፈኛ የማድረግ ግዴታ አለበት፤
7 በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 6 የተመለከተው የአፍና አፍንጫ መሸፈን ግዴታ ለዚሁ አላማ ተብሎ በፋብሪካ በተሰራ፣ በቤት ውስጥ ከተለያዩ ጨርቃጨርቆች በተዘጋጀ ወይም በማናቸውም አይነት ልብሶች ሊፈጸም ይችላል፡፡
8. ማንኛውም አገልግሎት የመንግስትም ሆነ የግል አገልግሎት ሰጪ ተቋም አገልግሎቱን ለማግኘት ወደ ተቋሙ ለሚመጡ ተገልጋዮች ቫይረሱን ለመከላከል የሚያስችሉ የንፅህና መጠበቂያ ቁሶችን ማዘጋጀትና ተገልጋዮች አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረጋቸውን የማረጋገጥ ሀላፊነት አለበት፣
9. ማናቸውም አገልግሎት የሚሰጡ የመንግስትም ሆነ የግል ተቋማት አገልግሎት ለማግኘት ወደ ተቋማቱ የሚሄዱ ተገልጋዮች ሁለት የአዋቂ እርምጃ ተራርቀው የሚቆሙበትን ቦታ ምልክት የማድረግ ሀላፊነት አለባቸው፤
10.የመንግስት የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎችና የግል የሚዲያ ተቋማት ኮቪድ-19ኝና ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተ የሚያስተላልፏቸው መረጃዎች፣ የዜና ትንተናዎች ወይም ፕሮግራሞች ሳይጋነኑ ወይም ሳይቃለሉ ተገቢው መረጃ ወደ ሕዝቡ የማድረስ እና አላግባብ የሆነ ድንጋጤና ሽብርን የማይፈጥሩ መሆን አለባቸው፣
11.ማንኛውም በፌዴራልም ሆነ በክልል የሚገኙ የመንግሥትም ሆነ የግል ተቋማት በተቋሙ ስር ለሚገኙ ሰራተኞች ስለቫይረሱ አስፈላጊውን መረጃ የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም የማድረስ፣ በመግቢያና መውጫ በሮችና ሌሎች አስፈላጊ ቦታዎች ላይ ቢያንስ እጅ ለመታጠብ የሚያስችል ውሃና ሳሙና ማዘጋጀት ፣ በተቻለ መጠን ሌሎች የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት የሚረዱ የጥንቃቄ ቁሳቁሶችን ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤
12.ማንኛውም በፌዴራልም ሆነ በክልል የሚገኙ የመንግሥትም ሆነ የግል ተቋማት በተቋሙ ስር የሚገኙ ሰራተኞች በአንድ ክፍል ውስጥ፣ በአንድ መስሪያ ቦታ ወይም በአንድ ትራንስፖርት ውስጥ ተጨናንቀውና አካላዊ ርቀትን ለመጠበቅ በማያስችል መልኩ እንዳይሰሩ ለማድረግ አስፈላጊውን ፈረቃ ማመቻቸት፤ ሰራተኞቹ ቤታቸው ሆነው የሚሰሩበትን ሁኔታ ወይም እረፍት በመውሰድ ስራ ቦታ እንዳይመጡ የማመቻቸት ሀላፊነት አለበት፤
13.ማንኘውም የፌዴራልም ሆነ የክልል የመንግስት ተቋምና በአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 መሰረት የሚተዳደሩ ሰራተኞችን የሚስተዳድር የግል ድርጅት ሰራተኞቹ ወደ ስራ ቦታ ለመሄድ ትራንስፖርት መጠቀም አስፈላጊ ከሆነ በስራ ላይ ለሚገኙ ሰራተኞች የትራንስፖርት አገልግሎት የማመቻቸት ሀላፊነት አለበት፤
14.ፖሊስ ኮሚሽን ወይም ማረሚያ ቤት ተጠርጣሪዎች ከጠበቆቻቸው ጋር የሚገናኙበትን ሁኔታ የማመቻቸት ሀላፊነት አለበት፤
15 ማንኛውም የቤት፣ የሆቴል፣ የአፓርታማ፣ የተሽከርካሪ፣ የአዳራሽ ወይም የማንኛውም ንብረት ባለቤት መንግስት የኮቪድ-19 ሥርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠር እና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ ለሚያደርገው ጥረት አስፈላጊ የሆነ ንብረቱን ለዚህ አላማ አገልግሎት ላይ እንዲውል በሚኒስትሮች ኮሚቴ ወይም ኮሚቴው ውክልና በሰጠው የመንግስት አካል ሲወሰንና ሲጠየቅ ንብረቱን ለእለት ከእለት ፍጆታው የሚጠቀምበት ካልሆነ በሰተቀር ውሳኔውን ተግባራዊ የማድረግ ግዴታ አለበት፤
16.ማንኛውም አምራች ወይም አገልግሎት ሰጪ ድርጅት፣ የኮቪድ-19 ሥርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠር እና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ ለሚያደርገው ጥረት አስፈላጊ የሆነ አግለግሎት እንዲሰጥ፣ አገልግሎቱን እንዲያሰፋ፣ ምርት እንዲያመርት፣ የሚያመርተውን ምርት መጠን እንዲጨምር፣ አዲስ ምርት አይነት እንዲያመርት ወይም ምርቱን መንግስት በሚወስነው ተመጣጣኝ ዋጋ ለመንግስት፣ ለሾማቾች ወይም ለህብረት ስራ ማህበራት እንዲሸጥ በሚኒስትሮች ኮሚቴ ወይም ኮሚቴው ውክልና በሰጠው የመንግስት አካል የሚሰጠውን ትዕዛዝ ተግባራዊ ማድረግ አለበት።
17.ሆቴሎች ለደንበኞቻቸው አገልግሎት በሚሰጡበት ጊዜ የእጅ መታጠቢያ ውሀና ሳሙና የማቅረብ ሀላፊነት ያለባቸው ሲሆን፣ የሆቴሉ ተጠቃሚዎችም እጃቸውን መታጠባቸውንና አስፈላጊውን ንፅህና አጠባበቅ ስርአት ተግባራዊ ማድረጋቸውን የማረጋገጥ እንዲሁም ደንበኞች ከተጠቀሙ በኋላ የተገለገሉባቸውን ጠረጴዛዎች፣ ወንበሮችና ሌሎች እቃዎች የማከም ግዴታ አለባቸው፣
18.ማንኛውም በስራ ላይ ያለ፣ ጡረታ የወጣ ወይም በትምህርት ላይ ያለ የጤና ወይም የሌላ ሙያ ባለቤት ወይም ማንኛውም ዜጋ የኮቪድ-19 ሥርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠር እና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ በሚደረገው ጥረት አስተዋፅዖ እንዲያደርግ በመንግስት ጥሪ ሲደረግለት የመተባበር ግዴታ አለበት፡፡
https://telegram.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
This is valid all year round but, especially in times of crisis like #Covid19 one, we need to rely only on accurate, up-to-date information. Avoid spreading rumors and when in doubt, check the source you are getting the information from.
Follow accurate public health advice from the World Health Organization (WHO) or your local health authority.
https://telegram.me/TransparencyEthiopia
Follow accurate public health advice from the World Health Organization (WHO) or your local health authority.
https://telegram.me/TransparencyEthiopia
Telegram
Transparency International Ethiopia (TIE)
Ethical and corruption free society that upholds integrity and accountability
Contact Us via
@Transparency_Ethiopia_Bot
and
ethiopiatransparency@gmail.com
Contact Us via
@Transparency_Ethiopia_Bot
and
ethiopiatransparency@gmail.com
YES I CAN:
ሰላም ውድ የ ኣለ ቤተሰቦች ከ ጉንበት 3-6 እንዲሰጥ ተይዞለት የነበረው ሃገር ኣቀፍ የ ሕግ ተማሪዎች መውጫ ፈተና ከ ከፍተኛ ኣመራር አንዳ ኣረጋገጥኩት ላልተወሰነ ግዜ ተራዝማል በምሆንም ኣሁንም ማለትም ቡሃላ ሚሰጠን ግዜ ስለ ማይታወቅ አንደ ለመድነው ግዜ ሰጠን አንድናነብ ያው ለ ፊልም ግዜ ካለን ለ ሶሻል ሚድያ ግዜ ካለን ለ ማንበብም ግዜ አንስጠው ዝም ከማለት ይሻላል ስለዚ አንደ ወትሮ በደንብ እናንብብ #ኣሁን ነው ቤታችን ቁጭብለን የ ሰው ልጅ ምናተርፈው በታችን እንቀመጥ #ፈጣሪ የ ኣለም ህዝብ ማርልን # via ክብሮም ስዩም ባህርዳር ዪንቨርስቲ
ሰላም ውድ የ ኣለ ቤተሰቦች ከ ጉንበት 3-6 እንዲሰጥ ተይዞለት የነበረው ሃገር ኣቀፍ የ ሕግ ተማሪዎች መውጫ ፈተና ከ ከፍተኛ ኣመራር አንዳ ኣረጋገጥኩት ላልተወሰነ ግዜ ተራዝማል በምሆንም ኣሁንም ማለትም ቡሃላ ሚሰጠን ግዜ ስለ ማይታወቅ አንደ ለመድነው ግዜ ሰጠን አንድናነብ ያው ለ ፊልም ግዜ ካለን ለ ሶሻል ሚድያ ግዜ ካለን ለ ማንበብም ግዜ አንስጠው ዝም ከማለት ይሻላል ስለዚ አንደ ወትሮ በደንብ እናንብብ #ኣሁን ነው ቤታችን ቁጭብለን የ ሰው ልጅ ምናተርፈው በታችን እንቀመጥ #ፈጣሪ የ ኣለም ህዝብ ማርልን # via ክብሮም ስዩም ባህርዳር ዪንቨርስቲ
COVID 19.docx
67 KB
የኮቪድ 19 የሥራ ቦታ ምላሽ (workplace Response) የሶስትዮሽ ፕሮቶኮል