አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
Urgent
🔷Vacancy🔷
                                              
1. Driver
2. Junior Cashier and secretary 
3. Guday Asfetsami (ጉዳይ አስፈፃሚ)

          👉 How to Apply 👈
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
consultantentrust@gmail.com
Deadline
February, 10/2023

Share for your friends
     👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
ያለአግባብ የታሰሩ ሰዎች ካሳ የማግኘት መብት አላቸው???         
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ስው የሚታሰረው በምክንያታዊ ጥርጣሬ ላይ ተመስርቶ ለእስሩ አሳማኝ የሆነ ማስረጃ ሲኖር ነው። ይህ ግን ሁልጊዜ እውነት ላይሆን ይችላል ። ምክንያቱ ደግሞ ምክንያታዊ ጥርጣሬ ያጭራል ተብሎ ምርመራ ተደርጎ የሚገኘው ውጤት  ግለሰቡን ለእስር የዳረገው ተግባር ወይም/እና ማስረጃ በፓሊስ፣በአቃቤ ህግ ወይም በፍርድ ቤት ሚዛን ሲታይ ቀሎ ሊገኝ ይችላል። አንዳንዴም በነዚህ የህግ አካላት አይን ሞልቶ ጥፉተኛ አስብሎ በእስራት ያስቀጣ ተግባር እስሩ እየተተገበረ እያለ ወይም እስሩ ከተገባደደና ካለቀም  በኋላ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀመው ሌላ አካልና ሌላ ግለሰብ ሆኖ ይገኝና ሰውየው የተወሰነበት ፣ የታሰረው ሲልም መቀጮ የከፈለው ያለጥፉቱ ፣ያለስህተቱ ፣ ያለአግባብ ይሆናል። በሃገራችንም ብዙ መሰል ጉዳዮችን መዘርዘር ይቻላል።

ለመሆኑ እንዲህ አይነት ያለአግባብ የሆነ እስር ሲያጋጥም አለ አግባብ ነውና የታሰርኩት ከህግ ውጪ  ስለሆነ  ለባከነብኝ ጊዜ ፣ ገንዘብ፣ ለደረሰብኝ የሞራል ጉዳት ወዘተ መንግሥት ካሳ ሊከፍለኝ ይገባል ቢል ይህን ሊያስፈፅምበት የሚችል ህግ ይኖር ይሆን? መልሱ አዎም አይም ነው።

ህግ የለንም የሚለው መከራከሪያ ሃሳብ ግልፅ በሆነ መልኩ የወጣ ሃገራዊ ህግ የለም። ይሄም በዝርዝር ሊቀመጡ የሚችሉ የሃገራችንን ሁኔታ ያገናዘበ ነው፣ አለም አቀፍ ህግ ቢኖርም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ፣ ተተርጉሞ፣ በአዋጅነት እስካልፀደቀና እስካልታተመ ድረስ ሊተገበር(ሩ) አይገባም የሚል መከራከሪያን ያነሳሉ። [2]

በተቃራኒው ወገን የቆሙ ደግሞ ኢትዮጵያ በህገ መንግስቷ አንቀፅ 9(4) እና 13(2) መሰረት አለም አቀፍ መሰረታዊ መብቶችና ነፃነት ህጎችን ተቀብላ እስካፀደቀች ድረስ የሃገሪቱ ህግ አንድ አካል ሆኖ ተግባር ላይ ሊውል ይገባል የሚል መከራከሪያን አስቀድመው ይህ ደግሞ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት እና በየደረጃው ያሉ ፍርድ ቤቶች ሳይቀር በተግባር ያደረጉት እያደረጉትም ያለ ተግባር ነው በሚል የሚከተሉትን የሠበር ውሳኔዎች በምሳሌነት ይጠቅሳሉ [3] ለጥቀውም ከላይ ያለው  መከራከሪያ በተግባር በፍርድ ቤቶችበተዘዋዋሪ ትርጉም ስለተሰጠበት አለም አቀፍ ህግን ጠቅሶ / በተለይ የሰብዓዊ መብቶች አለም አቀፍ ቃል ኪዳኖችን/ ጠቅሶ መወሰን ሊነቀፍ እሚገባ አይደለም ይላሉ።
በካሳ ጉዳዩ ላይ ብዙ አለም አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ህጎች በአለማችን ላይ ተቀባይነት አግኝተው እየተተገበሩ ይገኛል። እንደ አሜሪካ ያሉ ሃገራት ያለአግባብ የታሰረ ሰው በትንሹ ለታሰረበት እያንዳንዱ  አመት 50,000 ዶላር እስሩ ያለአግባብ መሆኑን ላስረዳ ሰው እንደሚከፍሉ በተለያዩ ክልሎቻቸው ባሉ ህጎች ደንግገዋል።
በመሰረታዊነት ለአላግባብ እስር ካስ መከፈል እንደሚገባ የደነገገው አለም አቀፉ የሲቪልና የፓለቲካ መብቶች አለም አቀፍቃል ኪዳን [ 1 ]  ሲሆን ከላይ የተጠቀሱና ሌሎችም የሰበር ሰሚው ውሳኔዎች ህጉን በቀጥታ እየጠቀሱ ውሳኔ በመስጠት ተግባር ላይ ዕንዳዋሉት የታተሙ የሰበር ውሳኔዎች በማስረጃነት ማንሳ ት  ይቻላል።
ሲጠቃለል በሃገራችን ብዙ ህገ ወጥ የሆኑ እስሮች እና አፈናዎች  በስህተት፣ በቸልተኝነትም ይሁን ሆነ ተብሎ ይፈፀማሉ። እነዚህ እስሮች ኢ-ሰብአዊ፣ ኢ-ህገመንግስታዊ እና ኢ-ፍትሃዊ ድርጊት ናቸው። እነዚህን ለመቀነስ ብሎም ለማጥፉት ያላግባብ የታሰሩና የታፈኑ ሰዎች ካሳ የሚጠይቁበትን ህግ በህጎቻችን ላይ በግልፅ ቢካተት ወይም በሁለተኝነት በተነሳው መከራከሪያ መሰረት ጠበቆች እና የህግ ባለሙያዎች አለም አቀፉ ድንጋጌው ተግባር ላይ ሊውል የሚችልበት የህግ መከራከሪያ  ሰፊ ስለሆነ በክርክር ጭብጥ አርጎ መነሳትና መሄድ ያለባቸውን ያክል ሄደው አስገዳጅ ውሳኔ እንዲሰጥ ቢያደርጉ መልካም  ነው።

ማጣቀሻ

[1]የሲቪልና የፓለቲካ መብቶች አለም አቀፍ ቃል ኪዳን
አንቀፅ 14(6) "በአንድ  ሰው   ላይ  ተላልፎ   የነበረው  የመጨረሻ  ፍርድ በማያሻማ  አኳኋን  ኢፍትሃዊ  የነበረ  ስለመሆኑ  አዲስ በተገኘ  ማስረጃ አማካኝነት  የተረጋገጠ  የሆነ  እንደሆነ እና  በዚህም   ምክንያት  ይህ  ሰው   ምህረት  ካገኘ  አልያም  ደግሞ  ተላልፎበት  የነበረው  ውሳኔ  የተሻረ  እንደሆነ   በ እንዲህ  ዓይነቱ   ፍርድ  ምክንያትነት ደርሶበት  ለነበረው  ቅጣት  በህጉ   መሰረት  ሊካስ ይገባል፡፡  "
[2]የፌደራል ነጋሪት ጋዜጣ መቋቋሚያ አዋጅ ቁ. 3/1987
አንቀፅ 3(2)" ማናቸውም የፌዴራል መንግሥት ሕግ የሚወጣው በፌዴራሉ ነጋሪት ጋዜጣ ይሆናል።"
አንቀፅ 3(3) "ማናቸውም የፌዴራል ወይም የክልል ህግ አውጪ፣ አስፈጻሚ እና ተርጓሚ እንዲሁም ማንኛውም የተፈጥሮ ሰው ወይም በህግ የሰውነት መብት የተሰጠው  አካል  በፌዴራል  ነጋሪት  ጋዜጣ  የሚወጣ  ሕግን  የመቀበል  ግዴታ ይኖርበታል።"
[3]   ሠ/መ/ቁ . 95921፣ ሠ/መ/ቁ.100860  / ሁለቱም ቅፅ 18 ላይ ታትመው የወጡ/ አለም አቀፉየሲቪልና የፓለቲካ መብቶች አለም አቀፍቃል ኪዳን  ጠቅሰው ውሳኔ ሰጥተዋል።
//// አለም አቀፍ ህጉን ከሌሎችም መሰረታዊ የሰብዓዊ መብት ቃል ኪዳኖች ጋር  ከስር  ያገኛሉ///👇👇👇
ዳንኤል ፍቃዱ (ጠበቃና የህግ አማካሪ)
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ  #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share #lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች ለዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ የትምህርት ሚኒስቴር አሳሰበ
..................................................
የካቲት 1/2015 ዓም.(የትምህርት ሚኒስቴር) የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና በመጪው ሀምሌ ወር በሁሉም የትምህርት መስኮች እና መርሀግብሮች በግልና በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ይሰጣል።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) በመውጫ ፈተና ዙሪያ ከተማሪዎች ህብረት ተወካዮች ጋር ተወያይተዋል።

በውይይቱም የመውጫ ፈተና በመጪው ሀምሌ ወር በኦንላይን ለሁሉም የመንግስትና የግል ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች እንደሚሰጥ ገልፀዋል።

ለሚሰጠው የመውጫ ፈተና ብቁ ለመሆንም ተማሪዎች በየዩኒቨርስቲዎቹ የሚሰጠውን የመጨረሻውን ሰሚስተር ፈተና መውሰድና ኮርሶችን ማጠናቀቅ እንደሚገባም ሚኒስትር ዴኤታው አስገንዝበዋል፡፡

ለፈተናው በሁሉም የትምህርት መስኮች ላይ የተመረጡ ኮርሶች የብቃት ልየታ ተደርጎላቸው ዩኒቨርስቲዎች እንዲያውቁት መደረጉን የጠቆሙት ዶክተር ሳሙኤል በአሁኑ ወቅትም የፈተና ንድፈ ማሳያና / Blueprint / የፈተና ዝግጅት ስራ በመከናወን ላይ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

በመሆኑም ተማሪዎች በቀሪዎቹ አምስት ወራት ተገቢውን ዝግጅት በማድረግ ራሳቸውን ለፈተናው ብቁ ማድረግ እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡

በመድረኩ የተገኙ የተማሪዎች ህብረት ተወካዮችም ወደ ዩኒቨርስቲዎቻቸው ሲመለሱ ተማሪዎች ለፈተናው በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል፡፡

በውይይቱም ከሁሉም ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ የተማሪዎች ህብረት ፕሬዚዳንቶች ተገኝተዋል፡
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ #አለ_Share #lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር አጠቃቀም

ታክስ ከፋዮችን ለመለየት እንዲቻል እንዲሁም ለታክስ ሕጐች ዓላማ ሲባል ለታክስ ከፋይነት ለተመዘገበ ሰው የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር በሚል የሚታወቅ ቁጥር ይሰጣል:: ታክስ ከፋዩም የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥሩን የታክስ ሕጎች በሚያዙት መሠረት መጠቀም አለበት፡፡
.
ከዚህ አንጻር የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር አጠቃቀምን አስመልክቶ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት የህግ ድንጋጌዎች ተቀምጠዋል፡፡

 የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር የተሰጠው ሰው የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥሩን በማንኛውም የታክስ ማስታወቂያ፣ ማስታወቂያ ወይም ለታክስ ሕግ ዓላማ ሲባል በሚቀርብ ወይም ጥቅም ላይ በሚውል ሰነድ ወይም በታክስ ሕግ መሠረት በሚዘጋጅ ሰነድ ላይ መግለጽ ይኖርበታል፣ እንዲሁም ታክስ ከፋዩ ታክስ ቀንሶ የማስቀረት ግዴታ ባለበት ሰው ክፍያዎች በሚፈጽምለት ጊዜ የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥሩን መስጠት አለበት፡፡
.
 የንግድ ሥራ ለመሥራት ፈቃድ ይሰጠው ዘንድ ማመልከቻ የሚያቀርብ ታክስ ከፋይ ፈቃድ ለሚሰጠው ባለሥልጣን የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥሩን መስጠት አለበት፡፡

 ታክስ ከፋዩ ፈቃዱን በሚያድስበት ጊዜ የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር ማቅረብ የሚጠበቅበት የመጀመሪያው የፈቃድ ማመልከቻ ከቀረበ ወዲህ የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥሩ የተቀየረ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡

 የንግድ ወይም የሥራ ፈቃድ የሚሰጥ የመንግሥት አካል ወይም ተቋም ታክስ ከፋዩ የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥሩን ሳያቀርብ ፈቃድ መስጠት አይችልም፡፡

 የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር ለተሰጠው ሰው ብቻ የሚያገለግል ስለሆነ በሌላ ሰው ጥቅም ላይ ሊውል አይችልም፡፡
.
ገቢዎችን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በድረ ገጽ፦ www.mor.gov.et

https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ  #lawsocieties
አርደህ እንደምትበላት እያወክ በጀርባህ አዝለሀት ትሄዳለህ። የሆድን በጀርባ። ዋው......!
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties
የፌደራል_ፍርድ_ቤቶች_የሠራተኞች_ደንብ_አጭር_ማብራሪያ.pdf
122 KB
የፌደራል ፍርድ ቤቶች የሠራተኞች ረቂቅ ደንብና ማብራሪያ።
የፌደራል_ፍርድ_ቤቶች_የሠራተኞች_ደንብ.pdf
436.8 KB
የፌደራል ፍርድ ቤቶች የሠራተኞች ረቂቅ ደንብና ማብራሪያ።
👉👉👉 Urgent Vacancy 👈👈👈
👉👉👉👉 Junior secretary 
         
Place:👉Addis Ababa

👉Skill
Microsoft word
Microsoft Excel

Deadline
February, 17/2023

👉 How to Apply 👈
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
consultantentrust@gmail.com

Share for your friends
     👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
ሰ/መ/ቁ 35962 (ያልታተመ)
ውል ለማዋዋል ስልጣን ባለው አካል ፊት ያልተደረገ የቤት ሽያጭ ውል መሰረት በማድረግ ገዢ ቤቱን የሚመለከቱ ማንኛውም ሰነዶች እንዲያስረክበው በሻጭ ላይ ክስ አቅርቦ ጉዳዩን የሚያየው ፍርድ ቤት የቤት ሺያጭ ውሉ በፍ/ሕ/ቁ. 1723 መሰረት በዳኛ ወይም ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው ሰው ፊት ባለመደረጉ የህግ ውጤት የለውም የሚል ድምዳሜ ላይ ከደረሰ ሻጭ ሰነዶችን ለማስረከብ እንደማይገደድ ከመወሰን አልፎ የሽያጭ ውሉ እንዲፈርስ ውሳኔ ሊሰጥ አይገባም። ምክንያቱም የቤት ሽያጭ ውሉ እንዲፈርስ የቀረበ የዳኝነት ጥያቄ ባለመኖሩ ፍ/ቤቱ በዝርዝር ባልቀረበ ወይም በግልጽ ባልተጠየቀ ጉዳይ ላይ ውሣኔ መስጠቱ የፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 282/2/ የሚቃረን ነው።
habeshaadvocatellp
#ethiolawtips
ፈቃድ ሳይኖረው ከ18 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ 3.8 ኪሎ ግራም ጥፍጥፍ ወርቅ በህገ-ወጥ መንገድ ከአገር ይዞ ሲወጣ የተያዘው ቻይናዊ ክስ ተመሰረተበት

በኢፌዲሪ ፍትሕ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ የኢኮኖሚ ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ ፈቃድ ሳይኖረው ከ18 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ 3.8 ኪሎ ግራም ጥፍጥፍ ወርቅ እና ኮፐር፣ ዚንክና ሲልቨር የያዘ 2 ኪሎ ግራም የሚመዝን ማዕድን በህገ-ወጥ መንገድ ይዞ ሲወጣ የተያዘው ቻይናዊ ተከሳሽ ላይ የኮንትሮባንድ ወንጀል ክስ ተመሰረተበት፡፡
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ  #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ #አለ_Share #lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
የዐቃቤ ሕግ የክስ መዝገብ እንደሚያስረዳው ሚስተር ፓን ችዋን የተባለው ቻይናዊ ተከሳሽ ገደብ የተደረገበት መሆኑን እያወቀ/ማወቅ ሲገባው የብቃት ማረጋገጫ እና ፈቃድ ሳይኖረው የዋጋ ግምቱ 18 ሚሊዮን 5 ሺ 939 ብር የሚያወጣ ቀረጥና ታክስ 12 ሚሊዮን 824 ሺ 53 ብር የሚከፈልበት 3.8 ኪሎ ግራም ጥፍጥፍ ወርቅ እና 2 ሺ 196 ብር ቀረጥና ታክስ የሚከፈልበት በውስጡ ኮፐር፣ ዚንክና ሲልቨር የያዘ 2 ኪሎ ግራም የሚመዝን ማዕድን የሻንጣ የብረት ዘንግ ውስጥ አድርጎ ከኢትዮጵያ ወደ ቻይና አገር ይዞ ሲወጣ ጥር 16 ቀን 2015 ዓ.ም አዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የወጪ መንገደኞች የደህንነት ኤክስሬይ መፈተሻ ቦታ ላይ ስለተያዘ በፈፀመው ገደብ የተደረገበት ዕቃን በህገ-ወጥ መንገድ ይዞ መውጣት የኮንትሮባንድ ወንጀል የማዕድን ግብይት አዋጅ ቁጥር 1144/2011 አንቀጽ 12/1/፣ 5፣ እና 36/1/ እንዲሁም የጉሙሩክ አዋጅ ቁጥር 859/2006 (በጉሙሩክ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1160/2011 አንቀጽ 2/44/ እንደተሻሻለው) አንቀጽ 168/1/ ስር የተደነገገውን ተላልፎ የኮንትሮባንድ ወንጀል መፈፀም ክስ ቀርቦበታል፡፡

ጉዳዩ የቀረበለት የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 5ኛ ወንጀል ችሎትም ተከሳሹ የተከሰሰበትን ክስ ለመስማት ለየካቲት 28 ቀን 2015 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ  #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ #አለ_Share #lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
የንግድ ምዝገባና ፍቃድ አገልግሎትን እስከ ሀምሌ 1/2015ዓ.ም ድረስ ሙሉ በሙሉ በኦን ላይን ለማድረግ እየተሠራ ነው
==================================
አዲስ አበባ 8/6/2015(ንቀትሚ) በ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያው 6 ወራት ለ781, 843 የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎትን በኦን ላይን ለመስጠት ታቅዶ ለ 898, 284 ተሰጥቷል፡፡
የብልሹ አሰራር ችግሮችን ለመቅረፍ እና የንግድ ስራ አመቺነትን ለማሻሻል አወንታዊ ተፅእኖ ስላለው ተግባራዊ የተደረገው የኦንላይን ንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት በቀጣዮቹ 6 ወራት ሙሉ በሙሉ ይተገበራል፡፡
የንግድ አሠራርን ማዘመን በከፍተኛ ትኩረት እየተሰራበት ሲሆን በቀጣይም አሰራሮችን በቴክኖሎጂ በመታገዝ ማከናወን የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ቀዳሚ ተግባር ነው፡፡
በዘርፉ ያለውን አሠራር ከማዘመን አንፃር የንግድ ምዝገባና ፍቃድ እና ኢንስፔክሽን መመሪያ መመሪያ ቁጥር 935/2015 ተዘጋጅቶ ስራ ላይ እንድውል ተደርጓል፡፡
#ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ( PLC) እና የአክሲዮን ማህበር ተመሳሳይነትና ልዩነት

በኢትዮጵያ ንግድ ህግ  ዉስጥ ካሉት የንግድ ማህበራት መካከል ኃላፊነቱ የተወሰነ  የግል ማህበር ( PLC ) እና የአክሲዮን ማህበር ይገኙበታል ።

ሁለቱም  ማህበራት አክሲዮን ያላቸዉ ወይም  ካምፓኒዎች ሲሆኑ ተመሳሳይነትና ልዩነት አላቸዉ።                       

#ተመሳሳይነታቸዉ

• ህጋዊ ሰዉነት ያላቸዉ መሆኑ ፣
• የራሳቸዉ ንብረት ያላቸዉ መሆኑ፣
• የራሳቸዉን ትርፍና ኪሳራ ተጠያቂነት ያለባቸዉ መሆኑ፣
• ሁለቱም ትንሹ የአባላት ብዛትና የመነሻ ካፒታል ያላቸዉ መሆኑ፣
• ሁለቱም በቦርድና በማናጀር መመራት የሚችሉ መሆኑ ነገር ግን ለ PLC አሰገዳጅ አለመሆኑ፣
• የሁለቱም ተጠያቂ በተዋጣዉ የገንዘብ መጠን (አክሲዮን ) መሆኑ ፣
• ሁለቱም የሙያ መዋጮን የማይቀበሉ መሆኑን (የንግድ ህግ 256 እና 501 )
• በሁለቱም ካፒታል ማሳደግና መቀነስ የሚቻል መሆኑ ፣
• በሁለቱም አክሲዮኖች በመያዣ /በዋስትና / መያዝ ሚችሉ መሆኑ ፣

#ልዩነታቸዉ

አንድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር / PLC/ private Limited Company/ ለማቋቋም የአባላት ብዛት ከሁለት ማነስ የማይችሉ መሆኑ እንዲሁም ከሀምሳ መብለጥ እንደማይችሉ በንግድ ህጉ አንቀጽ 495(4) ላይ ተገልጿል። የአክሲዮን ማህበርን ( share company ) በተመለከተ ለማቋቋም ከ5 አባላት ማነስ የማይችል ሲሆን  ብዛት ግን ገደብ የሌለዉ መሆኑን በንግድ ህጉ አንቀጽ 248(3)  ላይ ይገኛል።

• ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር መነሻ ካፒታል 15000 ሺህ ብርና ከዚያ በላይ ሲሆን የአንድ አክሲዮን ዋጋም በኢትዮጵያ ብር  አንድ በመቶ ማነስ አይችልም (የንግድ ህግ ቁጥር (496)

• አክሲዮን   ማህበር መነሻ ካፒታል 50000 ሺህ እና ከዚያ በላይ ሲሆን የአንድ  አክሲዮን ዋጋ ከአንድ መቶ ብር  በታች መሆን አይችልም (የንግድ ህግ ቁጥር 247)

• ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ካፒታሉ  ሙሉ በሙሉ አስቀድሞ የተከፈለ ሲሆን የአክሲዮን ማህበር  ግን ሙሉ በሙሉ አስቀድሞ የሚከፈል አይደለም ነገር ግን ከተፈረሙ አክሲዮኖች ቢያንስ 1/4  (25%) መከፈል አለበት የቀረዉ በሂደት የሚከፈል ይሆናል (የንግድ ህግ ቁጥር (495(1) 

• ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የአክሲዮኖች ሽያጭ ለህዝብ  ክፍት የሚደርግ አይደለም  አንቀጽ 495(2) ነገር ግን አክሲዮን ማህበር ለህዝብ ክፍት የሚደረግ ነዉ (የንግድ ህግ ቁጥር248)

• ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ( PLC) ላይ አክሲዮን ማህበር ዉስጥ ያለ ሰዉ አክሲዮኑን ለሶስተኛ ሰዉ ማስተላለፍ አይችልም ምክንያቱም መተዳደሪያ ደንቡ  ላይ አባላት ይህን እስካልፈቀዱ ድረስ በህጉ መሰረት sale freely transfrable አይደለም። ነገር ግን አክሲዮን ማህበር ላይ አክሲዮን ማስተላለፍን በተመለከተ አክሲዮን  የገዛ ሰዉ አክሲየኑን ለሌላ አባል ላልሆነ ሰዉ በቀላሉ ማስተላለፍ ይችላል ። ስለዚህ አክሲዮን ማስተላለፍ ከተፈለገ በቀላሉ የአክሲዮን ማህበርን መምረጥ ያስፈልጋል ማለት ነዉ።

• አስተዳደራዊ አካል (ቦርድ) ን በተመለከተ አክሲዮን ማህበራት ሁሉ ከ3-12 ሰዉ የሚይዝ ቦርድ ኦፍ ዳይሬክተር ሲቋቋም  ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ( plc) ዉስጥ ቦርድ የለም።
        
#የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ
የኮ/መ/ቁ 282704/ፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ንግድ ችሎት ውሳኔ /

ቼክ በንግድ ህጋችን እንደ ንግድ ወረቀት ይቆጠራሉ ተብለው በን/ህ/ቁ 732/2/ ስር ከተዘረዘሩት የንግድ ወረቀቶች አንዱ ነው፡፡ ቼክ ከንግድ ወረቀቶች ውስጥ አንዱ ቢሆንም ከሌሎች የንግድ ወረቀቶች የሚለይባቸው ልዩ ባህሪያት ያሉት፣ ገንዘብን ተክቶ በስፋት አገልግሎት እየሠጠ ያለ፣ በንግድ ህጉ እንዲሁም በሌሎች ህጐቻችን ልዩ ጥበቃ የተሠጠው የንግድ ወረቀት ሲሆን ከነዚህ ልዩ ባህሪያት አንዱ ቼክ እንዲቀረበ የሚከፈልበት የንግድ ወረቀት መሆኑ ነው፡፡ ይህም በን/ህ/ቁ 854 ስር ተመልክቷል፡፡ የቼኩ አምጪ / Drawee / ቼኩን ለክፍያ ለከፋዩ ባንክ /Payee/ አቅርቦ ቼኩ ሳይከፈልበት ከተመለሰ የቼኩ አውጪ /Drawer/ ስለ ቼኩ አከፋፈል ዋስ በመሆኑ እና ገንዘቡን የመክፈል ሀላፊነት ያለበት በመሆኑ በቼኩ ላይ የተፃፈውን ገንዘብ የቼኩ አውጪ እንዲከፍለው መጠየቅ ይችላል፡፡ ይህም በን/ህ/ቁ 840 ፣ 868 ፣ 881 /1/ ስር ተመልክቷል፡፡ የቼኩ አውጪም በን/ህ/ቁ 840 መሠረት ገንዘቡን የመክፈል ሀላፊነት አለበት፡፡
የቼኩ አውጪ ከዚህ ኃላፊነት ሊድን የሚችለው ማለትም በቼኩ ላይ የተፃፈውን ገንዘብ ለቼኩ አምጪ የመክፈል ኃላፊነት የማይኖርበት፣ ቼክን መሠረት አድርጐ ለቀረበ ክስ በቼኩ አምጪ ላይ ሊቀርቡ ይችላሉ ተብለው በህጉ ተለይተው እና ተወስነው በን/ህ/ቁ 717 ስር የተቀመጡትን መከላከያ ምክንያቶች ያቀረበ፣ ይህን መከላከያ ምክንያቱንም ያስረዳ ሲሆን ነው፡፡ ይህ መከላከያም በን/ሕ/ቁጥር 717/1//3/፣ 849፣ 850 ስር የተቀመጠውን አይነት ከቼኩ አምጪ ጋር ያለውን የግል ግንኙነት መሠረት ያደረገ /Personal Relation Ship Defence/ ወይም በን/ሕ/ቁጥር 717/1/2/ ስር የተመለከቱት አይነት ከቼኩ አወጣጥ፣ ፎርም፣ የተፃፋ ቃላትና ፊርማ መሠረት ያደረጉ ቼኩን የሚመለከቱ መከላከያዎች /Real Defence/ ያቀረበ እና ይህንም መከለከያውን ያስረዳ ሲሆን ነው፡፡
#Daniel fikadu ዳንኤል ፍቃዱ /ጠበቃና የህግ አማካሪ/