አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
Regarding Exemption of Motor Vehicles from Customs Duties.jpg
1.5 MB
የተሽከርካሪዎች ከጉምሩክ ቀረጥ ነፃ መሆን በተመለከተ
Regarding Exemption of Motor Vehicles from Customs Duties
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
የተሽከርካሪዎች ከጉምሩክ ቀረጥ ነፃ መሆን በተመለከተ
Regarding Exemption of Motor Vehicles from Customs Duties
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
Exit exam guide line.pdf
393.5 KB
የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና አፈጻጸም መመሪያ*** ከ2015 ጀምሮ በሁሉም ዮኒቨርሰቲዎች ለሁሉም ዲፓርትመንቶች ተግባራዊ የሚደረግ ነው
ፍርድ ቤቱ ሐሰተኛ የቃለ-መሐላ አቤቱታ ያቀረቡ ባለጉዳይን በችሎት መድፈር እንዲቀጡ ወሰነ
*****************************************************************
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሶስተኛ ሰበር ችሎት ሐሰተኛ ቃለ-መሐላ አቤቱታ ያቀረቡ ባለጉዳይን በችሎት መድፈር ጥፋተኛ ናቸው በማለት ሐምሌ 27 ቀን 2014 ዓ.ም በዋለው ችሎት በአንድ ወር ከአስራ አምስት ቀን ቀላል እስራት እንዲቀጡ ወሰነ፡፡
ፍርድ ቤቱ በእስራት እንዲቀጡ የወሰነባቸው አቶ ኃይለማርያም ወዳጆ በደሀ ደንብ መስቀልኛ የሰበር አቤቱታ ለማቅረብ የዳኝነት ለመክፈል ምንም ሀብት እና ንብረት የሌላቸውና በቀበሌ ቤት የሚኖሩ መሆኑን በቃለ-መሐላ በማረጋገጥ አቤቱታቸውን በሀሰተኛ መንገድ በማቅረባቸው ነው፡፡
ሆኖም ግን የግለሰቡ ተከራካሪዎች ለችሎቱ ባቀረቡት አቤቱታ ግለሰቡ በስር ፍርድ ቤት እስከ ክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት ድረስ የዳኝነት ከፍለው ሲከራከሩ የነበረ መሆኑን እና አሏቸው ያላቸውን ሀብትና ንብረት ጠቅሰው በችሎቱ እንዲጣራላቸው በመጠየቃቸው ምክንያት ግራ ቀኙ በችሎት ቀርበው እንዲሰሙ ሲደረግ ግለሰቡ ቀድሞ ባቀረቡት የቃለ-መሐላ አቤቱታ መሠረት በስማቸውም ሆነ በባለቤታቸው ስም የተመዘገበ ምንም ዓይነት ሀብትና ንብረት እንደሌላቸው ለችሎቱ ማረጋገጣቸውን ችሎቱ በግለሰቡ ላይ ከሰጠው የጥፋተኝነት ውሳኔ ለመረዳት ተችሏል፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ስለግለሰቡ ሀብትና ንብረት አጣርቶ እንዲያቀርብ የታዘዘው የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከላይ በተመለከተው አግባብ ግለሰቡ በስማቸው የተመዘገበ መኖሪያ ቤት ያላቸው መሆኑን እና በመጠጥ ችርቻሮ ንግድ ስራ ላይም ተሰማርተው በመስራት ላይ የሚገኙ ስለመሆኑ ለፍ/ቤቱ ማረጋገጡን የችሎቱ ውሳኔ ያስረዳል፡፡
ተጠሪ ሀብትና ንብረት እያላቸው እንዲሁም በንግድ ስራ ላይ ተሰማርተው እያለ ምንም ዓይነት ንብረት እንደሌላቸው በቃለ-መሐላ አቤቱታ ከማረጋገጣቸውም በላይ ስለዚሁ ጉዳይ በችሎት በተጠየቁበት ወቅት በተመሳሳይ ሁኔታ መናገራቸው ሆነ ብለው ሀሰተኛ ፍሬ ነገርን ለችሎት መግለጻቸውን የሚያረጋግጥ መሆኑም በውሳኔው ላይ ተመልክቷል፡፡
ይህ ደግሞ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህግ ቁጥር 481 እና የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 452 መሰረት የወንጀል ክስ ማቅረብ ሳያስፈለግ በቀጥታ በወንጀል ሊያስቀጣ የሚችል ለመልካም ችሎት አመራር ተቃራኒ የሆነ በፍትህ ስራ ላይ ሊደረግ የሚገባው በእውነተኝነት እና በታማኝነት ተግባር ላይ የሚፈፀም የወንጀል ተግባር መሆኑንም ችሎቱ በውሳኔው ላይ ዘርዝሯል፡፡
ግለሰቡ ጥፋተኛ በተባሉበት የወንጀል ህግ አንቀፅ ስር ያለው ቅጣት ከአንድ ዓመት የማይበልጥ ቀላል እስራት ወይም ድርጊቱ የተፈፀመው በወንጀል ክስ ሂደት በሆነ ጊዜ ከሶስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት እንደሚያስቀጣ በመጥቀስም ከተፈፀመው ድርጊት አኳያ ግለሰቡንም ሆነ ሌሎች መሰል ድርጊት ለመፈፀም ሀሳብ ያላቸውን ሰዎች ያስተምራል እንዲሁም ያስጠነቅቃል በማለት ለችሎቱ ሐሰተኛ ቃለ-መሐላ አቤቱታ ያቀረቡት አቶ ኃይለማርያም ወዳጆ በአንድ ወር ከአስራ አምስት ቀን ቀላል እስራት እንዲቀጡ የተወሰነባቸው መሆኑንም ለመረዳት ተችሏል፡፡ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት
የጤና ህግ (Health Law) ትምህርት በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ለመክፈት ምክክር ተካሄደ
***
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ህግ ትምህርት ቤት የ2014ዓ/ም የስራ ዘመን የስራ አፈጻጸም ግምገማ፣ የ2015 ዓ/ምን የስራ እቅድ ትውውቅና በኽልዝ ሎው ስርዓተ ትምህርት (Health Law curriculum) ላይ ያተኮረ ውይይት ዛሬ ሀምሌ 29/2014ዓ/ም በፍሎሪዳ ሆቴል የመሰብሰቢያ አዳራሽ አካሄደ፡፡

በመርሃ ግብሩ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ም/ፕሬዚዳንት ዶ/ር ካሳሁን ተገኘ፣ የአስተዳደር ም/ፕሬዚዳንት ተወካይ አቶ ልጃለም ጋሻው፣ የህግ ትምህርት ቤት ዲን አቶ አለሙ ታዬ፣ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተምረው በህግ መምህርነት ሲያገለግሉ የነበሩና በአሁኑ ሰአት በአሜሪካን ሀገር በሲያትል ዋሽንግተን ጠበቃና የህግ አማካሪ የሆኑት አቶ እዮብ ከበደና ሌሎች የትምህርት ቤቱ መምህራንና የአስተዳደር ሰራተኞች ተገኝተዋል፡፡

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ም/ፕሬዚዳንት ዶ/ር ካሳሁን ተገኘ መርሃ ግብሩን በንግግር የከፈቱ ሲሆን፣ በቅድሚያ አቶ እዮብ በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያ የሆነውን የጤና ህግ (Health Law curriculum) ፕሮግራም በዩኒቨርሲቲው በ2ኛ ዲግሪ ለመክፈትና ከዩኒቨርሲቲው ጋር ለመስራት ያላቸውን ፈቃደኝነትንና ተነሳሽነት በዩኒቨርሲቲው፣ በራሳቸውና በህግ ትምህርት ቤቱ ስም አመስግነዋል፡፡ ዶ/ር ካሳሁን አያይዘውም ፕሮግራሙ በዩኒቨርሲቲው መሰጠቱ የሚኖረውን ፋይዳና ተያያዥ ነጥቦችን በማንሳት ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተው፣ በሚቀርበው የስራ ሪፖርትና እቅድ ላይ ተሳታፊዎች በንቃት እንዲሳተፉ አሳስበዋል፡፡

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የኽልዝ ሎው (Health Law curriculum) ፕሮግራምን በ2ኛ ዲግሪ ለማስጀመር ከፍተኛ ጥረት ሲያደርጉ እንደቆዩ የሚያነሱት አቶ እዮብ የፕሮግራሙን አስፈላጊነት አስመልክቶ፣ፕሮግራሙ ለዩኒቨርሲቲውና እንደ ሀገርም ያለውን ፋይዳ፣ በአጠቃላይ የፕሮግራሙን ጠቀሜታ እንዲሁም ሊያጋጥሙ በሚችሉ ተግዳሮቶች ዙሪያ አጭር ገለፃ አድርገዋል፡፡ ገለፃውን ተከትሎ በርካታ አስተያየቶችና ጥያቄዎች ቀርበው ለጥያቄዎቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡

በመቀጠል የህግ ትምህርት ቤት ዲን በሆኑት በአቶ አለሙ ታዬ የ2014ዓ/ም የስራ ዘመን የስራ አፈጻጸም ሪፖርት የቀረበ ሲሆን፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችንም በዝርዝር አቅርበዋል፡፡ የቀረበውን ሪፖርት ተከትሎ በርካታ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተሰጥተው ለጥያቄዎቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ከዩኒቨርሲቲው ስትራቴጂክ እቅድ በመነሳት የህግ ትምህርት ቤቱ የ2015 ዓ/ም የስራ እቅድ መታቀዱንና በሚቀጥለው የስራ ዘመን ትኩረት ተሰጥቶ የሚከናወኑ ተግባራትንም አቶ አለሙ በዝርዝር አቅርበዋል፡፡

በመጨረሻም በቀረቡት ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተካሂዶ መርሃ ግብሩ ተጠናቋል፡፡
****
ለልህ
ቀት እንተጋለን!
የህዝብና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት
ሀምሌ 29/2014ዓ.ም
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
ኢትዮጵያ በምግብ ዋጋ ንረት ከተመቱ የዓለም ቀዳሚ 10 ሀገራት መካከል አንዷ ኢትዮጵያ ነች።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ኢትዮጵያን ያካተተው የዓለም ባንክ ሪፖርት ይፋ ሆኗል።
በከባድ የምግብ ዋጋ ንረት ተመተዋል በሚል በሪፖርቱ ከተካተቱት ቀዳሚ 10 ሀገራት መካከል አንዷ ኢትዮጵያ ነች።
ኢትዮጵያ ካሳለፍነው ወርሃ መጋቢት ወዲህ እስከ ሰኔ በነበሩት አራት ወራት ከፍተኛ የምግብ ዋጋ ንረት አጋጥሟታል ተብሏል።
ንረቱ 38 በመቶ ሆኖ መመዝገቡም ነው በሪፖርቱ የተጠቀሰው።

በከባድ የብድር ጫና ውስጥ የሚገኙት ኤርትራ፣ ሶማሊያ እና ሱዳን ለከፋ የምግብ ዋስትና ችግር ሊዳረጉ እንደሚችሉም ተገልጿል።

በሪፖርቱ ሊባኖስ በንረቱ ክፉኛ የተጎዳች ሃገር ነች ተብላለች።


https://am.al-ain.com/article/ethiopia-is-among-the-countries-worst-hit-by-the-food-inflation-crisis-wbg-said

#lawsocieties #AleHig
https://t.me/lawsocieties
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
_የኢትዮጵያ_የንግዴ_ስራ_ፈቃዴ_መስጫ_መዯብ_መመሪያ_ቁጥር_17_201.pdf
3.1 MB
በኢትዮጵያ ፌዳራሊዊ ዳሞክራሲያዊ ሪፐብሉክ
የንግድና ኢንደስትሪ ሚኒስቴር


የኢትዮጵያ የንግድ ስራ ፈቃድ መስጫ ደንብ መመሪያ ቁጥር
17/2011

ሰኔ/2011 ዓ.ም
አዲስ አበባ
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
በሽታን ሆን ብሎ ወደሌሎች ማስተላለፍ የሕግ ተጠያቂነት
Via health inovation
#New#Awash Bank#

▪️1 - Administrative Assistant I
▪️2 - Plumber
▪️3- IT Service Management Officer - Core & Interface
▪️4 - Legal Officer
▪️5 - Mobile & Internet Banking Officer I
▪️6 - Digital Channels Technical Support Officer II
▪️7 - Terminal Management Officer II
▪️8 - Agent Banking Officer II
▪️9 - Branch Manager Class II Branch
▪️Posted On - August 07, 2022
▪️🚩Deadline Date: August 13, 2022
▪️Find More Details here
💧💧💧💧💧
https://bit.ly/3P4CMW3
#የዩኒቨርሲቲ_መምህራን !

በዩኒቨርሲቲ መምህራን ማህበራት በኩል የቀረቡ ጥያቄዎች ፦

• መንግሥትን የደመወዝ ጭማሪ እና የዕርከን ዕድገት እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

• ለዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ እና ቴክኒካል ረዳቶች የተሰራውን አዲሱን የስራ ደረጃ ማሻሻያ JEG በተመለከተ ቅሬታ አላቸው።

• የመምህራን የቤት አበልን በተመለከተ በፍጥነት አሁን ያለው የቤት ኪራይ ዋጋ ከግምት አስገብቶ ተሻሽሎ ተግባራዊ እንዲደረገ ጠይቀዋል።

• በመንግስት የተደረገው የደረጃ ማሻሻያ ረጅም ጊዜ በዩንቨርሲቲ ያስተማሩ መምህራንን ልምድ ያላገናዘበ በመሆኑና በመምህራን መካከል በቀጣይ ፍትሀዊ የደምወዝ ልዩነት እንዲኖር ስለማያስችል የደረጃ ማሻሻየው የመምህራንን ልምድ እና ማዕረግ ያገናዘበ እንዲሆን ጠይቀዋል።

• የረዳት ፕሮፌሰር የአካዳሚክ ማዕረግ ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታ የ3ኛ ዲግሪ መደረጉን በተመለከተ ያለን ቅሬታ አላቸው።

• የአካዳሚክ ቴክኒክ ረዳቶች ዝቅተኛው ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ የመጀመሪያ ዲግሪ መሆኑ ላይ አቤቱታ አላቸው።

• የቺፍ ቴክኒካል ረዳት II የትምህርት ደረጃን ፒ ኤችዲ ዲግሪ መሆኑም ላይ አቤቱታ አላቸው።

ጥያቄዎቻችን መልስ ይሰጣቸው እያሉ የሚገኙት መምህራኑ ይህ ካልሆነ እስከ ስራ የማቆም አድማ መምታት ድረስ ዕርምጃ እንደሚወስዱ ገልፀዋል።

👉 ትምህርት ሚኒስቴር ለሪፖርተር ፥ " ጥያቄ እንዳለ እናውቃለን። ነገር ግን አሁን ላይ ለውጦች ለማምጣት ጥናት እየተካሄደ ነው። ከዚህ ባለፈ የምንለው ነገር የለም። የደመወዝ ጉዳይ የትምህርት ሚኒስቴር ብቻ አይደለም የሲቪል ሰርቪስ ጉዳይም ነው "

ያንብቡ : telegra.ph/ETH-08-07-2
via #tikvahethiopia
Draft Registration and Licensing Directive - 01.25.2014.docx
4.2 MB
በአገራችን በ1952 ዓ.ም. ወጥቶ ለረዥም ጊዜ ሥራ ላይ የነበረው የንግድ ሕግ በዘርፉ ካለው ለውጥና ዕድገት ጋር እንዲጣጣም ባለፈው ዓመት በአዲስ መልክ በአዋጅ ቁ 1243/2013 ሆኖ እንዲወጣና ሥራ ላይ እንዲውል ተደርጓል። በሚኒስቴር መ/ቤታችን በኩልም የንግድ ሕጉ ያመጣቸውን ለውጦች ታሳቢ በማድረግ በንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ ቁጥር 980/2008 አንቀጽ 52 ንዑስ አንቀጽ 2 እና በንግድ ሕጉ የመግቢያ ድንጋጌ አንቀጽ 5 መሠረት የተሻሻል የንግድ ምዝገባ፣ ፈቃድ እና ድኅረ ፈቃድ ኢንስፔክሽን መመሪያ ረቂቅ ተዘጋጅቷል።

ረቂቅ መመሪያውን ላይ ያላችሁን አስተያየት በዚህ ቻናል ኮመንት ላይ ወይም በኢምል አድራሻ jiratenemera@yahoo.com ይላኩልን።
#የሊዝ_መብትን_ስለማስተላለፍ_በዋስትና_ስለማስያዝ_እና_መሠረታዊ_የሊዝ_ህግ_ድንጋጌዎች

የፌዴራል የፍትህና የህግ ኢንስቲትዩት/Federal Justice and Law Institute
#የሊዝ_መብትን_ስለማስተላለፍ_በዋስትና_ስለማስያዝ_እና_መሠረታዊ_የሊዝ_ህግ_ድንጋጌዎች
ከሊዝ ሥሪት ውጪ ቦታ መያዝና መፍቀድ ስለመከልከል
ማንኛውም ሰው የከተማ መሬትን በሊዝ አዋጅ 721/2004 ከተደነገገው የሊዝ ሥረዓት ውጪ መያዝ አይችልም፡፡
ማንኛውም ሰው አግባብ ካለው አካል ፈቃድ ሳይገኝ በህጋዊነት ከያዘው ይዞታ ጎን ያለን የከተማ ቦታ አሰፋፍቶ መከለልና መጠቀም አይችልም፡፡
ማኝውም ከልል ወይም የከተማ አስተዳደር በሊዝ አዋጅ 721/2004 ከተደነገገው ውጪ የከተማ መሬትን መፍቀድ ወይም ማስተላለፍ አይችልም፡፡
ነባር ይዞታዎች ወደ ሊዝ ሥሪት ስለሚቀየሩበት ሁኔታ
➠➠➠➠➠➠➠➠➠➠➠➠➠
በነባር ይዞታ ላይ የሰፈረ ንብረት ባለቤትነት ከውርስ በስተቀር በማንኛውም መንገድ ለሌላ ሰው ከተላለፈ ንብረቱ የተላለፈለት ሰው የቦታው ባለይዞታ ሊሆን የሚችለው በሊዝ ሥሪት መሰረት ይሆናል፡፡
ነባር ይዞታና የሊዝ ይዞታ እንዲቀላቀል ጥያቄ ቀርቦ ይዞታው እንዲቀላቀል ከተፈቀደ ጠቅላላ ይዞታው በሊዝ ሥሪት ይተዳደራል፡፡
በሊዝ የተያዘ የከተማ ቦታ አጠቃቀም እና ግንባታ ስለመጀመር
➠➠➠➠➠➠➠➠➠➠
የከተማ ቦታ ሊዝ ባለይዞታ በሊዝ ውሉ ውስጥ በተመለከተው የጊዜ ገደብ ውስጥ ቦታውን ለተፈቀደለት አገልግሎት ጥቅም ላይ ማዋል አለበት፡፡ ነገር ግን ባለይዞታው የቦታውን አጠቃቀም መለወጥ ከፈለገ አግባብ ላለው አስቀድሞ በማመልከት ፈቃድ ሊያገኝ ይገባል፡፡
ማንኛውም የሊዝ ባለይዞታ በሊዝ ውሉ በተመለከተው የጊዜ ገደብ መሠረት ግንባታ መጀመር አለበት ነገር ግን በተወሰነው የጊዜ ገደብ ውስጥ ግንባታውን ካልጀመረ ቦታውን ከተረከበበት ጊዜ ጀምሮ ያለውን የሊዝ ክፍያና የጠቅላላውን የሊዝ ዋጋ ሰባት በመቶ መቀጮ እንዲከፍል ተደርጎ ቦታውን አግባብ ያለው አካል መልሶ ይረከባል፡፡
ግንባታ ስለማጠናቀቅ
➠➠➠➠➠➠➠➠➠➠➠➠
ማንኛውም የሊዝ ባለይዞታ በሊዝ ውሉ ውስጥ በተመለከተው የጊዜ ገደብ መሠረት ግንባውን ማጠናቀቅ አለበት፡፡
የግንባታ ማጠናቀቅያ የጊዜ ገደብ እንደ ሚከተለው ይሆናል፡-
ለአነስተኛ ግንባታ 24 ወራት
ለመካከለኛ ግንባታ 36 ወራት፤
ለከፍተኛ ግንባታ 48 ወራት፡፡
ከላይ የተመለከተው ቢኖርም እንደ ግንባታው ውስብስብነት እየታየ የግንባታ ማጠናቀቅያ ጊዜው ሊራዘም ይችላል፡፡ ሆኖም ለግንባታ ማጠናቀቅያ የሚሰጠው ጠቅላላ ጊዜ በማንኛውም ሁኔታ፡- ለአነስተኛ ግንባታ ከሁለት ዓመት ከስድስት ወር ለመካከለኛ ግንባታ ከአራት ዓመት እና ለከፍተኛ ግንባታ ከአምስት ዓመት መብለጥ አይችልም፡፡ በተጨማሪም የሊዝ ባለይዞታ በተወሰነው የጊዜ ገደብ ግንባታውን ካላጠናቀቀ አግባብ ያለው አካል የሊዝ ውሉን በማቋረጥ ቦታውን መልሶ መረከብ ይችላል፡፡
የሊዝ ውል የተቋረጠበት ሰው በራሱ ወጪ ከስድስት ወር ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ በቦታው ላይ የሠፈረ ንብሩን ማንሳት አለበት፡፡ የሊዝ ባለይዞታው ንብረቱን በወቅቱ ካላነሳ አግባብ ያለው አካል ጀምሮ ግንባታው በፕላኑ መሰረት የተገነባ መሆኑን አረጋግጦ ግንባታውን ማጠናቀቅና መጠቀም ለሚችል ሰው በግልፅ ጨረታ ንብረቱን በመሸጥ ማስተላለፍ ይችላል፡፡
የሊዝ መብትን ስለማስተላለፍና በዋስትና ስለማስያዝ
➠➠➠➠➠➠➠➠➠➠➠➠➠➠
ቦታውን ለተፈቀደለት አገልግት ጥቅም ላይ የማንዋል ግዴታ እንደተጠበቀ ሆኖ ማንኛውም የሊዝ ባለይዞታ መብቱን ለማስተላለፍ ወይም በከፈለው የሊዝ ክፍያ መጠን በዋስያዝ ወይም በካፒታል አስተዋፆነት ለመጠቀም ይችላል፡፡
ማንኛውም የሊዝ ባለይዞታ ባላይዞታ የሊዝ መብቱን ግንባታ ከመጀመሩ ወይም ግንባታውን በግማሽ ከማጠናቀቁ በፊት ከውርስ በስተቀር ማስተላለፍ የሚችለው አግባብ ባለው አካል ቁጥጥር የሚደረግበት ግልጽ የሽያጭ ሥርዓትን በመከተል ይሆናል፡፡
በሌላ አኳኳን ስምምነት ካልተደረገ በስተቀር በመሬት የመጠቀም መብት በዋስትና ሲያዝ ወይም ሲተላለፍ በመሬቱ ላይ የተገነባው ህንፃና ከህንፃው ጋረር የተያያዙ መገልገያዎች መብት አብሮ ይያዛል ወይም ይተላለፋል እንዲሁም ሕንፃና ከሕንፃው ጋር የተያያዙ መገልገያዎች በዋትና ሲያዙ ወይም ሲተላለፉ በመሬት የመጠቀም መብቱም አብሮ ይያዛል ወይም ይተላለፋል፡፡
---------------------
ግንባታ መጀመር ማለት በቦታው ላይ ለመስራት ከተፈቀደው ግንባታ ወይም ሕንፃ ቢያንስ የመሠረት ሥራ መሥራትና የኮለን ግንባታ ለማከናወን የሚያስችሉ የኮለን ብረቶች የማቆም ሥራ ማጠናቀቅ ነው
ግንባታ በግማሽ ማጠናቀቅ ማለት
ሀ/ ቪላ ሲሆን የመሠረቱን የኮለኖችና ለጣሪያ ውቅር የሚስፈልጉ ቢሞችን ሥራ ማጠናቀቅ ፤
ለ/ ፎቅ ሲሆን የመሠረቱንና ከጠቅላላው ወለሎች ውስጥ 50 የሚሆኑትን የስሌት ስራ ማጠናቀቅ ፣
ሐ/ሪል ስቴት ሲሆን የሁሉንም ብሎኮች ግንባታ እንደአግባቡ ማጠናቀቅ ነው፤
ግንባታ ማጠናቀቅ ማለት በሊዝ የተፈቀደ ቦታ ላይ እንዲገነባ የተፈቀደ ቦታ ላይ እንዲገነባ የተፈቀደን ግንባታ በተሰጠው የግንባታ ፈቃድ መሰረት ሙሉ በሙሉ መሥራትና ዋና ዋና አገልግሎቶች ተሟልተውለት ለአገልግሎት ዝግጁ ማድረግ ነው፡፡
ነባር ይዞታ ማለት የከተማ ቦታ በሊዝ ስርዓት መተዳደር ከመጀመሩ በፊት በሕጋዊ መንገድ የተያዘ ወይም ሊዝ ተግባራዊ ከሆነ በኃላ ለነባር ይዞታ ተነሺ በምትክ የተሰጠ ቦታ ነው፡፡
የፌዴራል የፍትህና የህግ ኢንስቲትዩት/Federal Justice and Law Institute
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
#Commercial Bank Of Ethiopia#🚩Call for Written Exam - Legal Attorney Applicants
==================

Dear Applicants,

Thank you for your application for the position of Legal Attorney for Commercial Bank of Ethiopia.

We are pleased to invite you to take a written exam on Saturday August 13, 2022 at 02:00 local time (Morning) at CBE’s Zagwe Building, Lideta, Addis Ababa.

N.B. You are required to provide your ID card or Passport. Using a mobile phone is prohibited.

Please check name lists of applicants to seat for the written exam using the following link:
https://combanketh.et/cbeapi/uploads/Exam_Legal_Attorny_27e81ba84c.pdf