አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የፌዴራል የጠበቆች ማኅበር አስተዳደር ቦርድ ተመሠረተ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
ሐምሌ 22 ቀን 2014(ኢዜአ) በኢትዮጵያ የፍትሕና የጥብቅና ስርዓትን ያዘምናል ተብሎ የታመነበት የፌደራል የጠበቆች ማህበር አስተዳደር ቦርድ ተመሠረተ።

በመሆኑም በህግ እና በሕግ ብቻ የሚመራ የጠበቆች ቦርድ ማቋቋም አስፈልጓል።
#አለህግ
በዚህም በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የሆነው የፌደራል የጠበቆች ማህበር አስተዳደር ቦርድ ተመስርቷል ብለዋል።

ቦርዱ ተጠሪነቱ ለፍትህ ሚኒስቴር እንደሆነም ነው የገለጹት፡፡

ቦርዱ በዋናነት የፍትህና የጥብቅና ስርዓትን ለማዘመን አላማው አድርጎ የተቋቋመ መሆኑንም አብራርተዋል።

የቦርዱ ስራ አስፈፃሚ አባላት ዛሬ የመጀመሪያውን ውይይት ከሚኒስቴሩ አመራሮች ጋር ያካሄዱ ሲሆን ከነገ ጀምሮ ቦርዱ በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ የሚገባ ይሆናል።

በኢትዮጵያ ሁለት የጠበቆች የሙያ ማህበራት ቢኖሩም በቦርድ ደረጃ ሲቋቋም ይህ የመጀመሪያ ነው ።

የኢትዮጵያ የፌደራል ጠበቆች ማህበር በጥር ወር 2014 ዓ.ም ሲሆን ማህበሩ በወቅቱ የምስረታ እና የመጀመሪያ ጠቅላላ ጉባኤውን ማድረጉ ይታወሳል።

በሐምሌ ወር 2013 ዓ.ም በጸደቀው የፌደራል ጥብቅና አገልግሎት ፍቃድ አሰጣጥ እና አስተዳደር አዋጅ አማካኝነት ነው ማህበሩ የተቋቋመው።

ማህበሩ በፌደራል ደረጃ በጥብቅና ሙያ ላይ የተሰማሩ ባለሙያዎች አባል የሚሆኑበት ነው።

#Share #ሼር #አለ_ህግ #Alehig
#lawsocieties #AleHig
https://t.me/lawsocieties
የቦርዱ ስራ አስፈፃሚ አባላት ዛሬ የመጀመሪያውን ውይይት ከሚኒስቴሩ አመራሮች ጋር ያካሄዱ ሲሆን ከነገ ጀምሮ ቦርዱ በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ የሚገባ ይሆናል።
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
ሥራና_ሠራተኛ_አገናኝ_ኤጀንሲዎች_የሥራ_ስምሪት_መመሪያ.pdf
5.2 MB
የግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች በሀገር ውስጥ የሥራ ስምሪት አገልግሎት ስለሚሰጡበት ሁኔታ ለመወሰን የወጣ መመሪያ

የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መመሪያ

የግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ሕግና አሠራርን በመከተል ፍትሃዊ ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው የሥራ ስምሪት አገልግሎት በሀገር ውስጥ የሚሰጡበትን ሁኔታ መወሰን በማስፈለጉ

በኤጀንሲ, አማካኝነት ለሥራ የተሰማራውን ሠራተኛ መብትና ደህንነት በማስጠበቅ ረገድ ኤጀንሲው እና የአገልግሎት ተጠቃሚው ድርጅት ሊኖራቸው የሚገባውን የጋራና የተናጠል

ኃላፊነት ለይቶ የማመልከቱ ተገቢነት ስለታመነበት፣

መንግሥት በሀገር ውስጥ በግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች የሚሰጠውን የሥራ ስምሪት አገልግሎት በብቃትና በተገቢው በመከታተል፣ በመቆጣጠርና በመደገፍ፤ በሥራ ላይ የሚሠማሩ ሠራተኞች መብት፣ ደህንነትና ጥቅም የሚጠበቅበትን ሁኔታ መፍጠር እና የኢንዱስትሪ ሠላምን ማስፈን አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ!

በመንግሥት እና በግሉ ዘርፍ የሚሰጡ የሥራ ስምሪት አገልግሎቶች በተቀናጀ አግባብ የሚፈጸሙበትን ሁኔታ በመፍጠር ለሀገሪቱ የሥራ ገበያ እድገትና ውጤታማነት ተገቢውን አስተዋጽኦ ማበርከት በማስፈለጉ፤

የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 በአንቀጽ 171/1/ተ እና በአንቀጽ 174 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ይህንን መመሪያ አውጥቷል፡፡
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
Contract/ውል
Period of limitation/የይርጋ ጊዜ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ውል እንዲፈፀም፤ ውል ባለመፈፀሙ ለደረሰ ጉዳት መፍትሄ ወይም ውል እንዲፈርስ ለመጠየቅ (ውስ የሚሰጠው መብት ከተሰራበት ቀን ወይም ግዴታውን ለመጠየቅ ተገቢ ከነበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር)10 አመት ነው።

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆

actions for the performance of a contract, actions based on the non-performance and actions for the invalidation of a contract (counted from the date when the obligation is due or the rights under the contract could be exercised) 10 years.
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
የጤና_ባለሙያዎች_ምዝገባና_የሙያ_ሥራ_ፈቃድ_አሰጣጥ፣_አስተዳደርና_ቁጥጥር_መመሪያ_770.pdf
817.4 KB
የጤና ባለሙያዎች ምዝገባና የሙያ ሥራ ፈቃድ አሰጣጥ፣ አስተዳደርና ቁጥጥር መመሪያ ቁ. 770-2013
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
Succession/ውርስ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ኑዛዜው እንዳይፀና ወይም በአጣሪው የቀረበው የሀብት ክፍፍል ሀሳብ እንዳይፀና ለመቃወም ኑዛዜው - ከተነበበበት ቀን ጀምሮ ወይም አጣሪው ስለክፍፍል ሀሳቡ ካሳወቃቸው ቀን ጀምሮ የሚቆጠር 15 ቀናት
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆

to apply for the nullity of a will or to impugn the order of partition proposed (counted from the opening of the will or from the day the person was told about the proposed partition) 15 days.
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
ለመንግሥት ሠራተኞች የሚሰጥ የወሊድ ፈቃድ፣
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
https://t.me/lawsocieties

ለአንድ የመንግስት ሰራተኛ የተለያዩ ዕረፍት ዓይነቶች ያሉ ስሆን በፌደራል መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1064/2010” አንቀጽ 43 ላይ የተደነገገው የወሊድ ፈቃድ ነው።
ነፍሰጡር የሆነች የመንግሥት ሠራተኛ፣ ከእርግዝናዋ ጋር የተያያዘ ምርመራ ለማድረግ ሐኪም በሚያዘው መሠረት ደመወዝ የሚከፈልበት ፈቃድ ይሰጣታል፤

👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆

1. ከመውለዷ በፊት ዕረፍት እንድታደርግ ሐኪም ካዘዘ ደመወዝ የሚከፈልበት ዕረፍት ይሰጣታል፡፡
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) የተመለከተው ፈቃድ እንደ ህመም ፈቃድ አይቆጠርም፡፡
3. ነፍሰጡር የሆነች የመንግሥት ሠራተኛ መውለጃዋ ሲደርስ እወልዳለሁ ብላ ከገመተችበት ቀን በፊት 30 ተከታታይ ቀናት የቅድመ ወሊድ ፈቃድ፣ እንዲሁም ስትወልድ ከወለደችበት ቀን ጀምሮ 90 ተከታታይ ቀናት፣ በአጠቃላይ 120 ተከታታይ ቀናት ደመወዝ የሚከፈልበት የወሊድ ፈቃድ ይሰጣታል፡፡
4. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (3) መሠረት ሠራተኛዋ የተሰጣት የቅድመ ወሊድ ፈቃድ ከማለቁ በፊት ከወለደች ያልተጠቀመችበትን ቀሪ የቅድመ ወሊድ ፈቃድ ከወለደች በኋላ እንድትጠቀምበት ይደረጋል፡፡
5. ሠራተኛዋ የወሰደችው የቅድመ ወሊድ ፈቃድ ሲያልቅ ያልወለደች እንደሆነ እስከምትወልድበት ቀን ድረስ ባሉት የሥራ ቀናት የምትቆይበት ዕረፍት በበጀት ዓመቱ ካላት የዓመት ዕረፍት ፈቃድ ወይም በበጀት ዓመቱ የዓመት ፈቃድ የሌላት እንደሆነ ከሚቀጥለው የበጀት ዓመት የዕረፍት ፈቃዷ ይተካል፡፡
6. ሠራተኛዋ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (3) የተወሰነውን የወሊድ ፈቃድ ከጨረሰች በኋላ ብትታመምና ተጨማሪ ፈቃድ የሚያስፈልጋት መሆኑ በሀኪም ከተረጋገጠ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 43(1) በተደነገገው መሠረት የሕመም ፈቃድ መውሰድ ትችላለች፡፡
7. ማንኛዋም ስድስት ወር የሞላት ነፍሰጡር የሆነች የመንግስት ሠራተኛ የቅድመ ወሊድ ፈቃድ ከመውሰዷ በፊት ጽንሱ የተቋረጠባት ከሆነ ይህንኑ የሚያረጋግጥ የህክምና ማስረጃ ስታቀርብ የ60 ቀን የድህረ ወሊድ ፈቃድ ይሰጣታል፡፡
8. የቅድመ ወሊድ ፈቃድ ከወሰደች በኋላ የጽንስ መቋረጥ ካጋጠማት የወሰደችው የቅድመ ወሊድ ፈቃዷ ተቋርጦ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (3) የተመለከተው የ90 ቀን የድህረ ወሊድ ፈቃድ ይሰጣታል፡፡
9. ከሦስት እስከ ስድስት ወር ባለው የእርግዝና ጊዜ ውስጥ የፅንስ መቋረጥ ያጋጠማት የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ የሚከፈልበት 30 ተከታታይ ቀን ፈቃድ ይሰጣታል፡፡
10. ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ የትዳር ጓደኛው ስትወልድ ደመወዝ የሚከፈልበት 10 የሥራ ቀን ፈቃድ ይሰጠዋል፡፡

ምንጭ: Tsegaye Demeke - Lawyer
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
ህግን አለማወቅ እና የህግ ስህተት ከተጠያቂነት የማያድን መሆኑ ያውቃሉ ?
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
የህግ ምንነት
ህግ የሚለው ቃል በማህበረሰቡ ዘንድ በስፋት የሚታወቅ ቃል ነው፡፡
በተለይ ህግ አስገዳጅ መሆኑን የሚረዳው ለመሆኑ ቀደም ባለው ጊዜ በየዕለት ኑሮ ፀብ ሲገጥመው እንኳን “በህግ አምላክ” ብሎ ፀብ የማብረድ ልምድ የነበረው መሆኑ ማሳያ ነው፡፡ ሆኖም ማህበረሰቡ ህግን የሚረዳው በተለምዶአዊው አረዳድ እንጂ የዘርፉ ባለሞያዎች በሚረዱበት መልኩ አይደለም፡፡

በመሰረቱ ህግ ለሚለው ቃል ትርጓሜ መስጠት ቀላል አይደለም፡፡ ምክንያቱም የተለያዩ ምሁራን ቃሉን በተለያየ መንገድ የሚገልፁት በመሆኑ ነው፡፡ እንዲሁም የቃሉ ፍቺ ሊደረስባቸው በሚፈለጉት የተለያዩ ዓላማዎች ምክንያት ሊለያይ ይችላል።
ለህግ ቃላት ትርጉም በመስጠት የሚታወቀው ብላክስ ሎው የህግ መዝገበ ቃላት በተሻሻለው ስድስተኛ እትሙ (Black’s Law Dictionary, 6th ed.,) ለህግ ትርጉም ሲሰጥ law is “a body of rules of action or conduct prescribed by controlling authority, and having binding legal force, which must be obeyed and followed by citizens subject to sanctions or legal consequence is a law.” ወደ አማርኛ በግርድፉ ሲመለስ ስልጣን ባለው አካል የተደነገገ የተግባር ወይም የምግባር ደንብ እና አስገዳጅ የህግ ኃይል ያለው አካል ነው። ይህንንም ዜጎች ሊታዘዙት እና ሊከተሉት የሚገባ ሆኖ ማዕቀብ ወይም ህጋዊ ውጤት የሚጥል ህግ መሆኑን መረዳት ይቻላል።

በመሆኑም የአንድ ሀገር ሕግ፡- ሰላምን ለማስጠበቅ፣ ነባራዊ ሁኔታውን ለማስጠበቅ (maintain the status quo)፣ የግለሰብ መብቶችን ለማስጠበቅ፣ አናሳዎችን ከብዙኃን ለመከላከል ( protect minorities against majorities)፣ ማኅበራዊ ፍትህን ለማስፈን( promote social justice) እና ሥርዓት ያለው ማህበራዊ ለውጥ እንዲኖር ለማድረግ( provide for orderly social change) ያገለግላል።

• የህግ መሰረታዊ ባህሪያት
የህጎችን የተለመዱ ባህሪያት እና ተፈጥሮ መፈተሽ የህግ ጽንሰ-ሀሳብን ለመገንዘብ የሚረዳ ሲሆን ከእነዚህ ባህሪያት እና ተፈጥሮዎች መካከል እንደ ወሰኝ ወይም አስፈላጊ የሚታሰቡት አጠቃላይነት(ህግ በሁሉም ሰው ላይ በተመሳሳይነት (uniformity) እና እኩልነትን (Equality) የሚፈፀም መሆኑ)፣ መደበኛነት (ህግ ማህበራዊ ባህሪን በመፍቀድ፣ በማዘዝ ወይም በመከልከል ልማዶችን የሚፈጥር መሆኑ) እና ማዕቀብ ወይም ቅጣትን (ህግን ያላከበረ ቅጣት የሚጠብቀው መሆኑን) ያካትታሉ፡፡

• ህግን አለማወቅ እና የህግ ስህተት ከተጠያቂነት የማያድን መሆኑ
በወንጀልም ሆነ በፍትሐ ብሄር ጉዳይ ህጎቹ ስልጣን ባለው የህግ አውጪ አካል ወጥተው ከፀደቁበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንደሚውሉ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ዜጎች የህጎቹን መኖር ወይም መውጣት የማወቅ ግዴታ አለባቸው፡፡ ይኸውም ህግን አለማወቅ ከተጠያቂነት አያድንም የሚለው የህግ መርህ በላቲን Ignorantia juris non excusat ወይም በእንግሊዘኛ "ignorance of the law excuses not" ከሮማውያን ህግ የተወሰደ ሲሆን ህግን የማያውቅ ሰው ይዘቱን ባለማወቅ ብቻ ህጉን በመተላለፍ ከተጠያቂነት ሊያመልጥ እንደማይችል የሚገልጽ የህግ መርህ ነው። እንዲሁም የህግ ስህተት (mistake of law) ሰዎች በአንድ ጉዳይ ላይ ተፈጻሚነት ያለው ሕግ እንዴት እንደሚተገበር የሚይዙትን የአረዳድ ስህተቶችን የሚያመለክት የሕግ መርህ ነው። ‘ህግን አለማወቅ’ እና ‘የህግ ስህተት’ የሚሉት ቃላቶች በህጋዊ እይታ ውስጥ ተመሳሳይ ትርጉም የማይሰጡ ሲሆን አለማወቅ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ አጠቃላይ የእውቀት ያለመኖርን ያመለክታል። ማሳሳት ግን እውቀትን ተቀብሎ ወይም እውቀት እንዳለ አምኖ ነገር ግን የተሳሳተ መደምደሚያን ላይ መድረስን ያሳያል። ይሁንና ህግን አለማወቅም ሆነ የህግ ስህተት ከተጠያቂነት እንደማያድን እንደ አንድ የህግ መርህ ይወሰዳል፡፡

• ህግን አለማወቅ እና የህግ ስህተት ከተጠያቂነት የማያድን መሆኑ መርህ ምክንያት (rationale for "ignorance of the law excuses not" principle)
በመሠረቱ አንድ ሰው ህግን ከጣሰ ህጉን ስለመጣሱ ምንም እውቀት ባይኖረውም ተጠያቂ ይሆናል ማለት ነው፡፡ ይህ ማለት ሰዎች ህጉን አላውቀውም በማለት ድርጊታቸውን ሊከላከሉ እንደማይችሉ ያመለክታል፡፡ የዚህ ህግ መርህ ምክንያት( rationale) አለማወቅ ሰበብ ቢሆን ኖሮ ምንም እንኳን ያ ሰው ህጉ መኖሩን ቢያውቅም በወንጀል ህግ ወይም በፍትሐ ብሄር ጉዳይ ቢከሰስ ህጉን አላወኩም በማለት ከተጠያቂነት ማምለጫ እንዳይሆን በሚል ነው፡፡ በመሆኑም ከመርህ በስተጀርባ ያለው ምክንያት አለማወቅ ሰበብ ከሆነ ማንኛውም በወንጀል ወይም በፍትሐ ብሄር የተከሰሰ ሰው ተጠያቂነትን ለማስወገድ አላዋቂ ነኝ ሊል ይችላል የሚል ነው። ስለዚህ ህጉ የቱንም ያህል አጭር ጊዜ ቢቆይ ሁሉም ህጎች በስልጣኑ ውስጥ ላለ ለእያንዳንዱ ሰው ተፈፃሚ ይሆናሉ ማለት ነው፡፡

በኢትዮጵያም ህግን አለማወቅ ወይም የህግ ስህተት ከተጠያቂነት እንደማያድን በወንጀል ህጉ አንቀፅ 81 ስር ተደንግጓል፡፡ በዚሁ መሰረት ሕግን አለማወቅ ወይም በህግ ላይ መሳሳት መከላከያ ሊሆን እንደማይችል ያስቀምጣል፡፡ በሌላ በኩል በፍትሐ ብሄር ህግ አንቀፅ 2035/1 እና 2 ስር አንድ ሰው በህግ ላይ በትክክል የተገለፀውን ድንጋጌ፣ ልዩ ደንብና ሥርዓት የጣሰ እንደሆነ ጥፋተኛ እንደሆነ እና ህግን አለማወቅ ይቅርታ ሊያስገኝ የማይችል መሆኑ ተደንግጎ ይገኛል፡፡

• የህግ መኖር ማወቅ የሚቻልበት መንገድ
ህግን አለማወቅ ከተጠያቂነት አያድንም የሚል የህግ መርህ ተቀባይነት አለው ማለት ሁሉም ሰው ህግ የማወቅ ግዴታ እንዳለበት እና የህግን መኖር ያውቃል የሚል ግምት እንደሚወሰድ ያመለክታል፡፡ ታዲያ ሁሉም ሰው ህግን የተማረ ሊሆን የማይችል በመሆኑ እንዲሁም ህግን ቢማር እንኳ ሁሉን ህግ በተገቢው ሁኔታ ያውቃል ማለት ተጨባጭ (realistic) የማይመስል በመሆኑ የህግን መኖር እንዴት ማወቅ ይቻላል የሚለው ወሳኝ ጥያቄ ነው፡፡

የህግን መኖር በተለያዩ መንገዶች ማወቅ ይቻላል፡፡ ይኸም በዋናነት ህጎች የሚፀኑበትን ጊዜ ከሚገነግጉ ድንጋጌዎች ሲሆን ህግ የሚፀናበት ጊዜ በተለያዩ ህጎች ላይ በተለያየ ሁኔታ ተገልፆ ይገኛል፡፡ በዚሁ መሰረት ህጉ ወይም አዋጁ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከሚወጣበት ቀን ጀምሮ የሚፀና ይሆናል፣ ህጉ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፀደቀበት ቀን ጀምሮ ተፈፃሚ ይሆናል እና የተወሰነ ቀን በማስቀመጥ ከዛ ቀን ጀምሮ ተፈጻሚ እንደሚሆን ሊደነገግ ይችላል፡፡ ለምሳሌ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገ መንግስት በህዳር 29/1987 የፀደቀ ሲሆን ከነሐሴ 15/1987 ጀምሮ በሥራ ላይ እንደሚውል እና የፀና እንደሚሆን በመደንገግ ህጉ የሚፀናበትን ጊዜ በዚህ መልኩ አውጇል ፡፡ በመሆኑም ህጎቹ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ታውጀው ከፀደቁበት ቀን ጀምሮ ወይም በነጋሪት ጋዜጣ ታትመው ከወጡበት ጊዜ ጀምሮ በህብረተሰቡ ይታወቃሉ ተብሎ ይገመታል፡፡
ህግን አለማወቅ እና የህግ ስህተት ከተጠያቂነት የማያድን መሆኑ መርህ የማይፈፀምበት ልዩ ሁኔታ
ህግን አለማወቅ እና የህግ ስህተት ከተጠያቂነት የማያድን መሆኑ መርህ የማይፈፀምበት ልዩ ሁኔታ የተፈጠረው በዓለም አቀፍ ደረጃ በፍርድ ቤቶች በአንዳንድ ሁኔታዎች ላይ ነው።
ፍርድ ቤቶች የህግ አለማወቅ እንደ ሰበብ የተቀበሉት የህግ ጥሰት ሆን ተብሎ ያልተፈፀመ ወይም ያለጥፋት ሲጣስ ሆኖ በዚህ ጊዜ ቅጣት ለመጣል ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡ ስለሆነም የሕግ ስህተት እንደ መከላከያ የሚሠራው የሕግ ስህተቱ ሐቀኛ ሆኖ በቅን ልቦና ሲሠራ ነው። እንዲሁም የተከሳሽ ህግን አለማወቅና ስህተት ምክንያታዊ በሆነ ጊዜ አጠቃላይ ህግን አለማወቅ እና የህግ ስህተት ከተጠያቂነት አያድንም የሚለው መርህ ተፈፃሚ አይሆንም ማለት ነው፡፡

በተመሳሳይ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ወንጀል ህግ አንቀፅ 81/2 ስር እንደተደነገገው ድርጊቱን ለመፈፀም መብት ያለው መሆኑን በቅን ልቦና ለማመንና እንደዚህ ባለ የተሳሳተ እምነት ላይ ለመገኘት በቂና እርግጠኛ ምክንያት ያለው ሆኖ ለተገኘ ወንጀለኛ ፍርድ ቤቱ ቅጣቱን ሊያቀልለት እንደሚችል ያስቀምጣል፡፡ ፍርድ ቤቱ ቅጣቱን የሚወስነው ከስህተት የደረሰበትን ምክንያት በተለይም የስህተትና የነገሩን ሁኔታ በመገመት ነው፡፡ በተጨማሪ ምክንያት ሊገኝበት በሚችልና ፍፁም በሆነ አለማወቅና ቅን ልቦና እንዲሁም ወንጀሉን የማድረግ አሳብ መኖሩን በግልፅ በማይታይባቸው የተለዩ ሁኔታዎች ፍርድ ቤት ከቅጣት ነፃ ለማድረግ እንደሚችል የወንጀል ህጉ ይደነግጋል፡፡

በአጠቃላይ ህግ የሰዎችን የእለት ተዕለት ተግባር በመግዛት ሰላማዊ ኖሮ እንዲኖሩ የሚያስችል አንዱ መሳሪያ በመሆኑ ሰዎች ህግን አለማወቅ ከተጠያቂነት እንደማያድን እና መከላከያ ሊሆን እንደማይችል በማወቅ በተቻለ መጠን ህገ ወጥ ከሆኑ ተግባራት እራሳቸውን በማረቅ ይኖርባቸዋል፡፡
በእፁብ ደጀኔ
በንቃተ ህግ፣ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
የፌዴራል ፍርድ ቤቶች በነሐሴ ወር መደበኛ ሥራቸውን ይቀጥላሉ

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ከነሐሴ 1 እስከ 30 ቀን 2014 ዓ.ም ባለው ጊዜ መደበኛውን የዳኝነት አገልግሎት መስጠታቸውን የሚቀጥሉ እንደሚቀጥሉ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስታውቋል።

ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ በመግለጫው ወደ 2015 ዓ.ም የሚያልፉ መዝገቦችን ቁጥር ለመቀነስ፣ የበሰሉ መዝገቦችን እልባት ለመስጠት፣ እስረኛ ያለባቸውን መዝገቦች ቅድሚያ ሰጥቶ ለመስራት እንዲያስችል በዳኞች ፈቃደኝነት ላይ በመመስረት የፌዴራል ፍርድ ቤቶቹ ከነሐሴ 1-30/2014 ዓ.ም ባለው ጊዜ መደበኛውን የዳኝነት አገልግሎት መስጠታቸውን የሚቀጥሉ ይሆናል ሲል አስታውቋል።
(የፌ/ጠ/ፍርድቤት)
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
#New#Cooperative Bank Of Oromia#

▪️1 - Digital Banking Officer
▪️2 - Attorney
▪️3 - Legal Aid
▪️4 - Corporate Strategy Management Officer
▪️5 - Corporate Strategy Management Expert
▪️Find More Details here
💧💧💧💧💧
https://bit.ly/3d0PAiX

▪️Deadline - August 08/2022
ጉባዔው በ26 የሕገ መንግሥት ትርጉም ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ።
------------------------------------------------------------------------------------------------------
የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ረቡእ ሚያዝያ 05 ቀን 2014 ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ 26 ጉዳዮች ላይ በመወያየት 25ቱ የሕገ መንግሥት ትርጉም አያስፈልጋቸውም በማለት እንዲዘጉ የወሰነ ሲሆን፤ በአንድ ጉዳይ ላይ በሰፊው በመወያየት ጉዳዩ ተጨማሪ ጥናት እንዲደረግበት በይደር እንዲያልፍ ወስኗል።
ሰፊ ውይይት የተደረገበትና ተጨማሪ ጥናት እንዲደረግበት የተወሰነው ጉዳይ የንብረት ክርክር ጉዳይ ሲሆን ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቤት የስምንት ሰዎች ይዞታ የተመዘገበ ሆኖ እያለ ፍ/ቤቱ ከስምንቱ አመልካች አንዱ ሆነው የቀረቡትን የተከሳሽ ሚስትንና ተከሳሽ ሆነው የቀረቡትን ባል በማከራከር የከሣሽ እና ተከሣሽ የጋራ ሀብት ነው በማለት ይወስናል፡፡ የተቀሩት ሰባቱ ባለይዞታዎችም ውሳኔውን በፍ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 358 በመቃወም ጣልቃ ገብ አመልካች ሆነው ወደ ክርክሩ ቢገቡም ፍ/ቤቱ በክርክሩ ሂደት ወቅት ግማሾቹ በምስክርነት የቀረቡ ሌሎቹ ደግሞ ችሎት እየገቡ ሲከታተሉ የነበሩ በመሆኑ መብታቸውን ለማስከበር ጣልቃ በመግባት መከራከር እየቻሉ የክርክሩን ውጤት ጠብቀው መብታቸውን የሚነካ ውሣኔ ሲሰጥ በፍ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 358 መሠረት ያቀረቡት ተቃውሞ ተቀባይነት የለውም በማለት ብይን ይሰጣል፡፡ የይግባኝ አቤቱታቸውን ለፌ/ከ/ፍ/ቤት ቢያቀርቡም ፍ/ቤቱ አስቀርቦ በማከራከር የስር ፍ/ቤት ውሣኔን አፅንቷል፡፡ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎትም አያስቀርብም በማለት ጉዳዩን በመዝጋቱ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰበር መ.ቁ. 201187 እና 187023 የሰጣቸው ውሣኔዎች በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 40/1፣ 2፣ 7 እና 81 ስር የተደነገጉትን የንብረት መብቶች እና በአንቀጽ 9/1/ የተደነገገውን የሕገ መንግሥት የበላይነት ድንጋጌን ስለሚቃረን የሕገ መንግሥት ትርጉም ይሰጠን በማለት ጠይቀዋል፡፡
ጉባዔውም በጉዳዩ ላይ በስፋት የተከራከረ ሲሆን በአንድ በኩል ከላይ ፀንተው ያሉት ሁለቱ ውሣኔዎች ለሕገ መንግሥት ትርጉም አቤቱታ የቀረቡ ቢሆንም ሁለቱም የፍ/ቤቶቹ ውሣኔዎች ማስረጃን በመመዘን እና ሕግን በመተርጎም የተወሰኑ በመሆናቸው የአመልካቾችን የትኛውንም ሕገ መንግሥታዊ መብት የሚፃረሩ አይደሉም የሚል ሀሳብ ቀርቧል፡፡
በሌላ በኩል የፍ/ስ/ስ/ህጉ ቁ. 358 ድንጋጌ ይዘት ሲመረመር በዋና ክርክር ወቅት ተካፋይ መሆን ሲገባው በክርክሩ ተካፋይ ያልሆነና ወይም በክርክሩ መብት ያለው እና ተካፋይ ባልሆነበት ክርክር የተሰጠው ፍርድ መብቱ የተነካበት ሰው ፍርዱ ከመፈጸሙ በፊት የመቃወም አቤቱታ አቅርቦ መከራከር እንደሚችል በግልጽ ስለሚገነግግ የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰበር መዝገብ ቁጥር 56795 ላይ አንድ ክርክር መጀመሩን ያወቀ ወገን የክርክሩን ውጤት ጠብቆ መብቱን የሚነካበት ሆኖ ባገኘው ጊዜ ከውሳኔው በኋላ የሚያቀርበው አቤቱታ በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 358 መሰረት ተቀባይነት የለውም ብሎ የሰጠው አስገዳጅ የህግ ትርጉም ህግን ከመተርጎም ስልጣኑ ያለፈና የአመልካቾችን ንብረት የማፍራት መብት የሚጻረረር በመሆኑ ውሳኔው የሕገ መንግስቱን አንቀጽ 37፣ 40 እና 79(1) ድንጋጌ ስለሚቃረን የሕገ መንግሥት ትርጉም ያስፈልገዋል የሚል ሀሳብ ቀርቧል፡፡ ጉባዔውም በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ጥናት እንዲደረግበትና ለቀጣይ ውይይት እንዲቀርብ ወስኗል፡፡
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር የተጠናቀቀውን የበጀት አመት የግብር አከፋፈል ጋር የተፈጠሩ የአሰራር ችግሮች ጋር በተያያዘ መፍትሄ ለማምጣት እና ዘላቂ የአሰራር ስርአት እንዲኖር ከሀምሌ 01 ቀን 2014ዓ.ም ጀምሮ የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ መሆኑ ይታወቃል:: የዚሁ አካል በሆነው 11 አባላት ያሉት ግብረ ሀይል (Task force) አቋቁሞ በርካታ ተግባራትን በየእለቱ ሲያከናውን ቆይቷል::

በዚሁ መሰረት ለአጭርና ለረጅም ጊዜ ስራዎች እቅድ በማውጣት ለአጭር ጊዜ መፍትሄው ቅድሚያ በመስጠት ሲሰራ ቆይቷል::

በዚህም የጠበቆች ማህበሩ በጉዳዩ ላይ ያለውን አቋም ከነማብራሪያው በይፋ ለሚመለከታቸው አካላት በፅሁፍ ከማሳወቅ ጀምሮ አማራጭ መፍትሄዎችን አቅርቧል:: በተመሳሳይ ከሚመለከታቸው የፍትህ ሚ/ር; የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የገቢዎች ቢሮ እና ሌሎች ተቋማት የበላይ ሀላፊዎች ተከታታይ ውይይቶች ሲደረጉ ቆይተዋል:: በዚህም የአጭር ግዜ መፍትሄው በመልካም ውጤት ተጠናቋል::

በመሆኑም ግብር ከፋይ ጠበቆች;
1. ሂሳብ መዝገብ የያዙ ጠበቆች ካሉ በዛው መሰረት እንዲስተናገዱ;
2. በአማራጭ ደረሰኝ የሚስተናገዱ በቆረጡት ደረሰኝ መሰረት ታክሳቸውን አሳውቀው እንዲስተናገዱ;
3. ሁለቱምን ያልያዙ ወይም የሌላቸው ጠበቆች ደግሞ እንደከዚ ቀደሙ በቁርጥ ግብር/ወጪ እንዲስተናገዱ ለሁሉም የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ቅርንጫፎች መመሪያ ተላልፏል::
4. በመሆኑም ከዛሬ ጀምሮ ጠበቆች በየግብር መክፈያ ቅርንጫፋቸው እየተገኙ ታክሳቸውን መክፈል መቀጠል የሚችሉ ይሆናል::

በዚህ ሂደት አስተዋፅኦ እና ቀና ትብብር ላሳያችሁ ለፍትህ ሚ/ር; የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የበላይ አመራሮችና የስራ ባልደረቦች እንዲሁም በሂደቱ ላይ በቀጥታ ለተሳተፋችሁ ግዜ እና እውቀታችሁን ጭምር አስተዋፅኦ ያደረጋችሁ የማህበሩን የአመራር አባላት እና የግብረሀይሉ አባላት ማህበሩ ምስጋናውን ያቀርባል::

ዘላቂ መፍትሄውን በተመለከተም ከኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር; ከገንዘብ ሚኒስቴር; ከገቢዎች ሚ/ር እና ከአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የተውጣጣ የጥናትና መፍትሄ አመንጪ ቡድን በማህበሩ አስተባባሪነት ተቋቁሞ ስራውን የሚጀምር መሆኑን እና የሚደረስባቸውን ውጤቶችም የሚያሳውቅ መሆኑን ማህበሩ ይገልፃል::

ከላይ ከተገለፀው በተቃራኒ እክል የሚፈጠርባችሁ ጠበቆች በማህበሩ አድራሻ ስማችሁን; ቅርንጫፍ ፅ/ቤቱንና tin no በማስመዝገብ መፍትሄ እንድታገኙ የሚደረግ መሆኑን ማህበሩ ያሳስባል::


የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር
ሀምሌ 27 ቀን 2014 ዓ.ም
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
አዲሱ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል እኩል ደረጃ ያላቸው አራት ዋና ከተሞች እንደሚኖሩት የክልሉ ምክር ቤት አስታውቋል።

1. ቦንጋ ከተማ የፖለቲካ እና የርዕሰ መስተዳደሩ መቀመጫ፣
2. ተርጫ የክልሉ ምክር ቤት መቀመጫ፣
3. ሚዛን አማን የዳኝነት አካል መቀመጫ
4. ቴፒ የብሔረሰቦች ምክር ቤት መቀመጫ እንደሚሆኑም በረቂቅ አዋጁ ላይ ተቀምጧል።

የክልሉ ዋና ከተሞች አራት እንዲሆኑ የተደረገው ፍትሐዊ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማረጋገጥ እንደሆነም የብዝኃ ከተሞች ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጁ ይጠቅሳል።

ረቂቅ አዋጁ በቀጣይ በክልሉ ምክር ቤት ፀድቆ የሚተገበር ከሆነ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል እኩል ደረጃ ያላቸው አራት ዋና ከተሞች ያሉት የመጀመሪያው ክልል ይሆናል።
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
New_Investment Incentives Regulation_No 517_2022.pdf
4 MB
አዲሱ_የኢንቨስትመንት ማበረታቻ ደንብ ቁጥር 517_2014

New _ Investment Incentive Regulation No.517_2022
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆