አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.84K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
1. በቂ የወንጀል ጥርጣሬ መኖሩ ተጣርቶ በፓሊስ የወንጀል ምርመራ ይጀመርበታል ፣
2. የምርመራ መዝገቡ ለአቃቤሕግ ከተላከ በሁላ ፣ ለመክሰስ የሚያስችል ማስረጃና የሕግ መሰረት መኖሩ ሲረጋግጥ ክስ የመስረትበታል ፣ ካልሆነ መዝገቡ ይዘጋል ፣
3. ፍ/ቤት ክሱ እንዲደረሰው ትእዛዝ ከስጠ በሁላ ይሄው ደርሶት እራሱን ለመከላከል እድል ይስጠዋል
4. አቃቤሕግ መጀመሪያ ማስረጃውን ያሰማል ፣
5. ፍ/ቤቱ የአቃቤ ሕግን ማስረጃ ከሰማ በሁዋላ ፣ ተከላከል ይለዋል ፣ ወይም መከላከል ሳያስፈልገው በነጻ ያሰናብተዋል ፣
6. ተከላከል ከተባለ ፣ አለኝ የሚለውን መከላከያ አቅርቦ ያሰማል ፣ ይከራከራል ። መከላከል መስረታዊ መብት ነው ፣
7. ተከላከል ከተባለ በሁዋላ ፍ/ቤቱ ጥፋተኛ ሊለው ወይም በነጻ ሊያሰናብተው ይችላል ፣

አንድ ሰው ወንጀል ፈጽሞ ጥፋተኛ ተባለ የሚባለው በዚህ ሂደት ውስጥ አልፎ ነው ። ክስ ከተመሰረተበት በሁዋላ እንኩዋን በሁለት የስነ ስርአት ደረጃዎች ነጻ የመባል እድል አለው ። ማንኛችንም ነገ በሆነ አጋጣሚ በሰውየው ቦታ ልንሆን እንችላለን ። ሕግ የስጠውን መብት እናክብርለት ፣ ቀድሞ ፈራጅ አንሁን ፣ ውጤቱን እንጠብቅ ።

፣ ከማስታወሻዬ ፣ በአንድ ወቅት ...

እነ እገሌ ፣ በቢሊዮን ብር ዘረፉ ተባለ ። ተራገበ ፣ ተጋነነ ፣ ብዙ ተጮህ ። ተጠርጣሪዋቹ ፣ ቤተሰብ ፣ ወዳጅ ዘመዳቸው አፈረ ፣ አንገቱን ደፋ ። ብዙ ሰው በየቤቱ ሰምቶ አዘነባቸው ፣ እነዚህን መግደል እንጂ የምን ክስ ምናምን ነው ተባለ ፣ እኛ ጠበቆቹም ተሰደብን ፣ ሞራል የሌላችው ፣ እንዴት ለነዚህ ይቆማሉ ተባልን ።

ክስ ተመሰረተ ፣ ወሬውና ክሱ አይገናኝም ፣ ክሱና እውነታው አይገናኝም ። እናም ፣ ቆይቶ ፣ ሰዎቹ እንዲከሱ ይፈለግበት የነበረው ፓለቲካ ሲለወጥ ፣ ክሳቸው ተነሳ ።

ዝርዝሩን ሳናውቅ ለመፍረድ አንቸኩል ። ብዙ በተዋራባቸው የወንጀል ጉዳዮች ላይ በጠበቃነት ተሳትፌአለሁ ። በአብዛኛው ግነቱና እውነቱ አይገናኝም ። ሰከን ማለት ፣ ግራ ቀኙን መስማት ፣ ማገናዘብ ፣ ከስሜታዊ ፈራጅነት መቆጠብ ጥሩ ነው ... የወንጀል ምርመራውን ለፓሊስ ፣ የክሱን ጉዳይ ለአቃቤሕግ ፣ ዳኝነቱን ለፍ/ቤት እንተወው ....

መልካም ቀን ። በአበበ አስማረ
Alternative legal enlightenment & Service
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
https://t.me/AleHig
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#አለሕግ #ህግ #ሰበርመዝገብ  #ሕግ_መረጃ #እግድ
ህግ ትምህርት ቤት እያለሁ ስለ መሰማት መብት "right to be heard" ስንማር መምህሬ የነገረን ሁሌም የማስታውሳት አንድ እውነታን ደጋግሞ ይነግረን ነበር።
ሁሉን አዋቂው(Omniscience ) የሆነው እግዚአብሄርም አዳም ፍሬውን እንደበላ እያወቀ እንኳ "...ፍሬውን በላህ ወይ..."በማለት ጠይቆ የአዳምን የመሰማት መብቱን አክብሮለት ነበር ይለናል። እውነት ነው። አምላክ የመሰማትን መብት አልነፈገም። በፍጥረት ጅማሬ ያከበረው መብትም ይሄን መብት ይመስለኛል።ብሄራዊ ጀግናችን ገለቴ ቡርቃ በህይወቷ ስለሆነው ነገር ባዝንም በዛኛው ወገን ያለው ሳልሰማ አስተያየት መስጠት አልፈልግም። ሁሉም ወገን ይሰማ ከማለት ውጪ።ከሁለት ወገን ሳይሰሙ ከውሳኔ መድረስ የደቦ ፍርድ ነው።

- ብስራት መለሰ (ጋዜጠኛ)
Alternative legal enlightenment & Service
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
https://t.me/AleHig
https://linktr.ee/alehig
alehig.com
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_እውቀት #አለሕግ #ህግ #ሰበርመዝገብ #ሕግ_መረጃ #እግድ
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ለፌደራል ጠበቆች ማህበር አባላት በድጋሚ የቀረበ የእርዳታ ጥሪ ፣

የህግ ባለሙያ (ጠበቃ ) አቶ ኤፍሬም ተካ ሀ/የሱስ በፌደራል በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃና የህግ አማካሪ ሆነው እያገለገሉ የሚገኙ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር አባል ናቸው ። ይሁንና ላለፉት 2አመታት ባደረባቸው Rectum Colon የተባለ ህመም በሀገር ውስጥና በህንድ ሀገር ከፍተኛ ወጪ በማውጣት የህክምና ክትትል በማድረግ መቆየታቸው ገልፀው አሁንም በሀኪሞች ውሳኔ የመጨረሻ ዙር ህክምና ማከናወንና ይህንኑ ለመፈፀም 10,000ሺህ የአሜሪካን ዶላር እንደሚያስፈልግ ገልፀው የሚወጣውን ከፍ ያለ ወጪ አቅማቸው መሸፈን የማይችል በመሆኑ በማህበሩ በኩል ድጋፍ እንዲደረግላቸው ጠይቀው ድጋፍ የተሰባሰበላቸው ቢሆንም ህክምናውን ሊሸፍን አልቻለም::

በመሆኑም ከዚህ ቀደም ድጋፍ ይደረጋችሁም ሆነ ያላደረጋችሁ የህግ ባለሙያውን ለማገዝ የምትችሉ የማህበሩ አባላት በስልክ ቁጥር
+251 911- 631118 ደዉላችሁ ማግኘት የምትችሉ ሲሆን እንዲሁም በባንክ አካዉንታቸዉ ገቢ ለማድረግ ለምትፈልጉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካዉንት ቁጥር 1000037330756 ወይም በአዋሽ ባንክ አካውንት ቁጥር - 01320108358200 ላይ ድጋፍ ማድረግ የምትችሉ መሆኑን ማህበሩ ይገልፃል ።

የማህበሩ ጽ/ቤት
ሰኔ 06 ቀን 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
#ትግራይ

የደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ላፕቶፕ ኮምፒተርን " ሰርቀዋል " ተብለው የተጠረጠሩ ግለሰቦች ፍርድ ቤት በዋስ እንዲፈቱ ቢወስንም አልተተገበረም።

6 የVIP የጥበቃ አባላት የህወሓት ሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚከካኤል (ዶ/ር) ላፕቶፕ ኮምፒተርን " ሰርቀዋል " በመባል ተከሰዋል።

የመቐለ ዓዲ ሓቂ ክፍለ ከተማ ፍርድ ቤት ሰኔ 6 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት በሊቀመንበሩ ላፕቶፕ ኮምፒተር ስርቆት የተጠረጠሩት ግለሰቦች በዋስ እንዲፈቱ ወስኗል።

ስድስቱ ተጠርጣሪዎች እያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቁ ፍርድ በሰጠው ውሳኔ መሰረት ቤተሰቦቻቸው ብር ቢያስይዙም " ከላይ የመጣ ትእዛዝ " በሚል ከእስር አልተለቀቁም ብለዋል የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ምንጮች።

ባለፈው የግንቦት ወር 2017 ዓ.ም ሳምንት መጨረሻ የሊቀ-መንበሩ ላፕቶፕ ኮምፒተር " በጠባቂዎቻቸው ተዘርፏል " የሚል መረጃ በማህበራዊ የትስስር ገፆች በስፋት ቢሰራጭም ደጋፊዎቻቸው " መረጃው የፈጠራ ወሬ ነው " በማለት ሲያጣጥሉ ቆይተዋል።

ሊቀ-መንበሩም በቅርቡ ከደጋፊዎቻቸው ጋር በነበራቸው ስብሰባ " አልተሰረቅኩም " የሚል እንደምታ ያለው በሚያሰመስል ሁኔታ ላፕቶፕ ኮምፒዩተር ይዘው ታይተው ነበር።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
በሥር ፍርድ ቤቶች ከረዳት ዳኝነት ጀምረው እስከ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከ20 ዓመታት በላይ የሠሩ፣ የዳበረ ዕውቅትና ልምድ ያላቸው ሦስት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች፣ ሥራቸውን በፈቃዳቸው መልቀቃቸው ታወቀ፡፡