አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.84K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
#ትግራይ

የደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ላፕቶፕ ኮምፒተርን " ሰርቀዋል " ተብለው የተጠረጠሩ ግለሰቦች ፍርድ ቤት በዋስ እንዲፈቱ ቢወስንም አልተተገበረም።

6 የVIP የጥበቃ አባላት የህወሓት ሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚከካኤል (ዶ/ር) ላፕቶፕ ኮምፒተርን " ሰርቀዋል " በመባል ተከሰዋል።

የመቐለ ዓዲ ሓቂ ክፍለ ከተማ ፍርድ ቤት ሰኔ 6 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት በሊቀመንበሩ ላፕቶፕ ኮምፒተር ስርቆት የተጠረጠሩት ግለሰቦች በዋስ እንዲፈቱ ወስኗል።

ስድስቱ ተጠርጣሪዎች እያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቁ ፍርድ በሰጠው ውሳኔ መሰረት ቤተሰቦቻቸው ብር ቢያስይዙም " ከላይ የመጣ ትእዛዝ " በሚል ከእስር አልተለቀቁም ብለዋል የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ምንጮች።

ባለፈው የግንቦት ወር 2017 ዓ.ም ሳምንት መጨረሻ የሊቀ-መንበሩ ላፕቶፕ ኮምፒተር " በጠባቂዎቻቸው ተዘርፏል " የሚል መረጃ በማህበራዊ የትስስር ገፆች በስፋት ቢሰራጭም ደጋፊዎቻቸው " መረጃው የፈጠራ ወሬ ነው " በማለት ሲያጣጥሉ ቆይተዋል።

ሊቀ-መንበሩም በቅርቡ ከደጋፊዎቻቸው ጋር በነበራቸው ስብሰባ " አልተሰረቅኩም " የሚል እንደምታ ያለው በሚያሰመስል ሁኔታ ላፕቶፕ ኮምፒዩተር ይዘው ታይተው ነበር።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia