በጅቡቲ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ህጋዊ መኖሪያ ማግኘት ያልቻሉበት ምክንያት ምንድነው ?
የጅቡቲ መንግስት ሰነድ አልባ ስደተኞች በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በፈቃዳቸው ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ ካወጀ ሰነባብቷል፡፡ የተሰጠው ቀነገደብ በመጠናቀቁም መጠነ ሰፊ አፈሳ እንደሚጀምር አውጇል፡፡
በዚያች ሀገር የሚኖሩ ሰነድ አልባ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በበኩላቸው፣ ሀብት ንብረታችንን ሸጠን የምንወጣበት ጊዜ ይስጠን እያሉ ይማፀናሉ፡፡ ለዚህም ቀነገደቡ እንዲራመዝላቸው ይፈልጋሉ፡፡
ለመሆኑ እነዚህ ሰነድ አልባ ኢትዮጵያውያን (ቁጥራቸው በትንሹ ከ200 ሺህ በላይ ይገመታል) ለምን እስካሁን ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ መያዝ አልቻሉም፡፡
ይህን ጥያቄ ያነሳንላቸው ስማችን አይጠቀስ ያሉ ሶስት ስደተኞች፣ ሕጋዊ ለመሆን ስላለው ሁኔታ የሚከተለውን ሀሳብ ሰጥተዋል፡፡
ሕጋዊ ለመሆን ያለው ችግር ምንድነው ?
" ሁሉም ሰው ህጋዊ መሆን ይፈልጋል፡፡ ችግሩ የገንዘቡ መብዛት ነው፡፡ ሒደቱም ረጅም የድለላ ሰንሰለትን የሚያልፍ እና በእጅጉ ረዥም፣ አድካሚና ውስብስብ ነው፡፡ የአንድ ሰው የአመት ገቢ እንኳ አይበቃም፡፡
ህጋዊ ለመሆን ለጅቡቲ መንግስት የሚከፈለው ገንዘብ አንድ አመት ሙሉ ሰርቶ ማጠራቀም አይቻልም፡፡ የዚህ ሀገር ህጋዊ መሆኛ አሰራር ለድሀና ለስደተኛ የሚመጥን አይደለም፡፡ እንኳን ግለሰብ ቀርቶ፣ ድርጅቶችም አይችሉትም፡፡
የንግድ ድርጅቶች ለሰራተኞቻቸው ህጋዊ የስራ ፈቃድ ለማውጣት፣ እስከ 200 ሺህ ፍራንክ (160 ሺህ ብር ገደማ) ይጠየቃሉ፤ ለአንድ ሰራተኛ፡፡ ለግለሰብ ደግሞ እስከ 70 ሺህ ፍራንክ ይደርሳል በህጋዊው መንገድ፡፡ ግን አብዛኛውን ጊዜ ህጋዊው አካሔድ ስለማይገኝ በደላሎች በኩል እስከ 120 ሺህ ፍራንክ ትጠየቃለህ፡፡ አሁን በቅርቡ 120 ሺህ ፍራንክ ከፍለው ያወጡ ሰዎች አሉ፡፡ አንዳንዴም ከ150 ሺህ እስከ 200 ሺህ ብር ያስወጣሀል፡፡ ይህን ያህል ከፍለህ የምታገኘው የመኖሪያ ፈቃድ፣ ተሰጠህ ሳይሆን ገዛህ ነው ሊባል የሚችለው፡፡ አንዴ ከፍለህ የሚያበቃ ነገር ደግሞ አይደለም፡፡ በየአመቱ ከ 20 ሺህ እስከ 30 ሺህ ፍራንክ እየከፈልክ ታሳድሳለህ ፈቃድህን፡፡
እንደ ሌሎች ሀገራት ብዙ አመት ከቆየህ በኋላ ህጋዊ ነዋሪ አትሆንም፡፡ ሁሌም ጊዜያዊ ነዋሪ እየተባልክ በየአመቱ ፈቃድህን እያደስክ ትኖራለህ፡፡ የቋሚ ነዋሪነት መታወቂያ አይሰጡህም፡፡ ይህ ችግር አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ስደተኛ፣ ሰነድ አልባ ሆኖ በስጋት ውስጥ እንዲኖር አስገድዶታል፡፡
ህጋዊ ሰነድ ለማግኘት ደግሞ ፓስፖርትህ ላይ ቪዛ መመታት አለበት ይሉሀል፡፡ ይህን ቪዛ ለማስመታት ከጅቡቲ ትወጣና እንደገና መግባት አለብህ፣ ቪዛ ለማግኘት የግድ ከጅቡቲ መውጣት አለብህ በየአመቱ፡፡ ተመልሰህ ስትገባ ኤርፖርት ቪዛ ይሰጠሀል፡፡ አዲስ አበባ እና ድሬዳዋም ይመታልሀል፡፡ ግን ቅድመ ሁኔታው በጣም ብዙ ነው፣ አሰልቺም ጭምር፡፡ በዚህ መልኩ፣ ህጋዊ የመሆኛው ሒደት ውድና አድካሚ ነው፡፡ ምንም አይነት ግልፅ የሆነ ህጋዊ አሰራር የላቸውም፡፡
ይህን የምታደርገው ደግሞ ፓስፖርት ካለህ ነው፡፡ ፓስፖርት ይዘን ነው፣ ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የምትጠይቀው፡፡ የእኛ ኤምባሲ ፓስፖርት ለመስጠት 200 ዶላር ይጠይቃል፡፡ በጅቡቲ ፍራንክ ሳይሆን፣ በዶላር ክፈል ነው የምትባለው፡፡ ይህ ራሱ በጣም ብዙ ነው፡፡
ከአንድ አመት በፊት የኢትዮጵያ ፓስፖርት ለመውሰድ ክፍያው ዝቅተኛ ነበር፡፡ 100 ዶላር፣ 150 ዶላር የነበረበት ወቅት ነበር፡፡ አሁን በጣም ነው የጨመረው፡፡ አዲስ ፓስፖርት ተቀይሯል ተብሎ ነው የጨመረው፡፡ አንድ የጥበቃ ሰራተኛና አንዲት የቤት ሰራተኛ የሆኑ ስደተኞች የአንድ ወር ሙሉ ደመወዛቸው ለፓስፖርት ማውጫ አይበቃቸውም፡፡ ሙሉ ደመወዝ ለዚህ ብቻ ልታውለው አትችልም፡፡ መብላት መጠጣት መልበስ የሚባሉ ነገሮች አሉ፡፡ 200 ዶላር ለመቆጠብ ጊዜ ይፈጃል፡፡ ሰዉ ደግሞ የተወሰነ አመት ሰርቶ፣ ገንዘብ አጠራቅሞ ወደ ሀገሩ መመለስ ነው እንጂ፣ ያገኛትን ገንዘብ ለመኖሪያ ፈቃድና ለፓስፖርት መጨረስ አይፈልግም፡፡
ስለዚህ በኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል ያለው የፓስፖርት ክፍያ ቢቀንስ ጥሩ ነበር፡፡ እንደው 100 ዶላር እንኳን ቢያደርግልን፡፡ በሁሉም አቅጣጫ፣ ህጋዊ ሰነድ ማግኘት የምትችልበት ሁኔታ ነው መፈጠር ያለበት፡፡ ኤምባሲያችን ይህ ጉዳይ እንዲቀረፍ መስራት አለበት፡፡
የጅቡቲ መንግስት የመኖሪያ ፈቃዱ ቀለል ባለ መንገድ እንዲገኝ ማድረግ አለበት፡፡ የኢትዮጵያ ኤምባሲም ለዚህ ጫና ማድረግና የመኖሪያ ፈቃድ ለማግኘት በደላሎች እየተበዘበዘ ያለውን ህዝብ ችግር ከግምት አስገብቶ መስራት አለበት፡፡ ሁሉም ሰው ህጋዊ መሆን ይፈልጋል፡፡ ስርዓቱ ለዚህ መመቸት አለበት ነው የምንለው፡፡ "
ስደተኞቹ ህጋዊ ሰነድ ለመያዝ ይገጥሙናል ስላሉዋቸው ችግሮች እንዲሁም የኢትዮጵያን ፓስፖርት ለማውጣት እስከ 200 ዶላር መክፈል አግባብ አይደለም በማለት ላቀረቡት ቅሬታ፣ በጅቡቲ ካለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ማብራሪያ ካገኘን እናቀርባለን፡፡ ሆኖም የፓስፖርት የአገልግሎት ክፍያን በተመለከተ በህገደንብ የተወሰነ መሆኑን ማረጋገጥ ችለናል፡፡
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ለሚሰጣቸው አገልግሎቶች የሚከፈል የአገልግሎት ክፍያን ለመወሰን የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 520/2016 ላይ እንደተገለፀው፣ በውጭ ሀገራት በኤምባሲ በኩል የሚሰጥ ባለ 32 ገፅ መደበኛ ፓስፖርት የአገልግሎት ክፍያው 200 ዶላር መሆኑን ተመልክተናል፡፡ በኦንላይንና በእድሳት ደግሞ 250 ዶላር እንደሚያስከፍል ይጠቅሳል ደንቡ፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
" የተሽከርካሪ ታርጋ አይፈታም ክልክል ነው ፤ ደንቡም ላይ ተቀምጧል " - የመንገድ ደኅንነት እና መድን ፈንድ
➡️ " ተሳፋሪን ለማውረድ ክልክል የነበሩ ቦታዎች እየተፈቀዱ ነው ተጨማሪ ቦታዎችም እየታዩ ቅሬታ የሚነሳባቸው ቦታዎች ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተነጋገርን ነው ! "
ከነሐሴ 13 ቀን 2016 ዓም ጀምሮ በስራ ላይ የዋለው " የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ ደንብ ቁጥር 557/2016 " ተግባራዊ ከሆነ ስምንት ወራት ተሻግሯል።
ነባሩ ደንብን በመተካት ተሻሽሎ የወጣው ደንብ የጥፋት እርከንን በሦስት በመክፈል የትራፊክ ቅጣቱንም ከ500 ብር እስከ 1,500 ብር ከፍ አድርጓል።
ደንቡ የከተማ የፍጥነት ወሰንን በ 50 ኪሜ በሰዓት ከመወሰኑ በተጨማሪ ፣ የራዳር መቆጣጠሪያ የሚያውኩ መሳሪያዎችን ይዞ መንቀሳቀስን ይከለክላል።
በተጨማሪም አደጋ አድርሰው በአደጋው ህይወታቸው ያለፈ አሽከርካሪዎች የአደጋውን ምክንያት ለመመርመር ህይወታቸው ካለፈ በኋላም የደም ናሙና እንዲወሰድ የሚፈቅዱ አዳዲስ ጉዳዮችን አካቷል።
ደንቡ ተግባራዊ ከሆነ ጀምሮ " የቅጣት ገንዘቡ የተጋነነ ነው " የሚሉ ቅሬታዎችን ጨምሮ " ያለ አግባብ እየተቀጣን ነው " የሚሉ ቅሬታዎች በአሽከርካሪዎች ዘንድ ይሰማል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ደንቡ ተግባራዊ ከሆነ ጀምሮ ውጤታማነቱ ተገምግሟል ወይ ? ስለሚነሱት ቅሬታዎችን ምን ምላሽ አላቹ ? ሲል የሚመለከተውን አካል ጠይቋል።
የመንገድ ደኅንነት እና መድን ፈንድ ህግ ትግበራ ዴስክ ሃላፊ ወ/ሮ ብርክቲ ባህሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?
" ደንቡ ከወጣ ጊዜ ጀምሮ ሁሉም ክልሎች እንዲደርሳቸው ተደርጓል ከደረሳቸውም በኋላ የማስተዋወቅ እና ምን ምን ተሻሻለ የሚለውን ነገር የማሳወቅ ስራ ሰርተናል።
ጀምረዋል አልጀመሩም የሚለውን አንድ ዙር ተገምግሟል አብዛኛው ክልል ጀምሯል ማለት ይቻላል አጀማመራቸው እኩል ባይሆንም።
' ቅጣቱ ተጋኗል ' የሚል ቅሬታ በሚመለከት ከዚህ በፊት የነበረው ቅጣት አስተማሪ አልነበረም በጣም አነስተኛ ነበር።
ዋናው አላማችን አደጋን መቀነስ ነው ቅጣቶቹ የተቀመጡት ከአደጋ አንጻር ነው።
ቢያንስ ግንዛቤ እየኖረው ነው ' ቅጣቱ ይሄን ያህል ነው ' የማለት የመጠንቀቅ ነገር አለ ለውጥ አለ።
ደረጃ አንድ፣ ሁለት ፣ ሦስት እና ልዩ ጥፋት እርከን ተብሎ ነው የተቀመጠው።
አሽከርካሪዎች ደጋግመው ሊያጠፏቸው ይችላሉ የተባሉትን ጥፋቶች ከመጠናቸውም አንጻር ታይቶ በአንደኛ ደረጃ የጥፋት እርከን ነው የተቀመጡት።
ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጡት ከበድ ያለ አደጋ ሊያደርሱ ይችላሉ ተብለው የተለዩ ጥፋቶች ናቸው ቅጣታቸውም 1,500 ብር ነው።
' ተጋኗል ' የሚል ካለ የማያጠፋን አይመለከትውም ቅጣት የሚመለከተው አጥፊውን ብቻ ነው።
ስፒድ ሊሚተር የሚገጠምላቸው አሽከርካሪዎች አሉ ይህንን ሲፒድ ሊሚተር በትክክል እንዳያሳይ የሚያበላሽ አለ እንደዚህ አይነት ቴክኖሎጂዎችን የሚያሰናክሉ ካሉ የገጠሙት ነገር ይወረሳል ፣በወንጀልም ይጠየቃሉ ቅጣትም አለው።
ይህን አይነቱን ጥፋት የሚያጠፉ አሽከርካሪዎች እንዳሉ ከዚህ ቀደም በተሰሩ ጥናቶች በመታወቁ በደንቡ ላይ እንዲካተቱ ሆኗል።
ከዚህ ቀደም በነበረው ድንብ ላይ ጠጥቶ ወይም አደንዛዥ እጽ ተጠቅሞ አደጋ ያደረሰ እና ህይወቱ ያለፈ አሽከርካሪ ላይ ጠጥቶ ይሁን አይሁን ለማረጋገጥ የሚቻልበት መንገድ አያስቀምጥም ነበር።
በአሁኑ ደንብ አሽከርካሪው በህይወት ባይኖርም የደም ናሙና እንዲወሰድ ይፈቅዳል አተገባበሩ ላይ መመሪያ እየተዘጋጀ ነው።
ተሳፋሪን ለማውረድ ክልክል የነበሩ ቦታዎች እየተፈቀዱ ነው ተጨማሪ ቦታዎችም እየታዩ ቅሬታ የሚነሳባቸው ቦታዎች ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተነጋገርን ነው።
ህጉ ገና መውጣቱ ነው ረዥም ጊዜው አይደለም መሬት ላይ ያለው ሁኔታ ምን ላይ ነው ያለው ? የሚለውን ከሁሉም ክፍል የተወጣጣ ቡድን በስራ ላይ ነው።
ከዚህ ቀደም አሽከርካሪዎች ተደጋጋሚ ጥፋት ስለሚያጠፉ የትራፊክ ፖሊሶች ታርጋ ይፈቱ ነበር መንጃ ፈቃድም ይወስዱ ነበር።
አሁን ላይ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ይህንን የሚያስቀር መተግበሪያ አበልጽጓል።
ከዚህ በኋላ ሰሌዳ መፍታትም ሆነ መንጃ ፈቃድ መውሰድ ሳያስፈልግ አሽከርካሪን የሚቀጣበት አሰራር ነው።
ከዚህ በኋላ ታርጋ አይፈታም ክልክል ነው ደንቡም ላይ ተቀምጧል።
ሲስተሙ ይፋ ተደርጓል ወደ ተግባር እየገቡበት ነው ተሞክሮው ተወስዶ ወደ ክልሎችም የማስተዋወቅ ስራ ይሰራል።
በህጉ መሰረት እንደማይፈቀድ ሁሉም ግንዛቤ እስከሚኖረው ድረስ ጊዜ ይጠይቃል ነገር ግን ታርጋ መፍታት አይፈቀድም " ብለዋል።
ከዚህ ቀደም " የተሽከርካሪን ሰሌዳን መፍታት ክልክል ነው " የሚለው ህግ በተጨባጭ ለምን ተግባራዊ አልሆነም ? የሚል ጥያቄ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን አቶ ክበበው ሚደቅሳ አቀርቦላቸው ነበር።
አቶ ክበበው " ሰሌዳ ቁጥሩ የሚፈታበት አጋጣሚ ይኖራል፣ እሱም የሚሆነው የቅጣት እግድ የደረሱ ከሆነ፣ መንጃ ፍቃዳቸው ላይ ያለው ስልክ ቁጥራቸው የማይሰራ ወይም የክፍለ ሀገር ከሆነ ይፈታል፣ ምክንያቱም አስገዳጅ ምክንያቶች ስለሆኑ በሂደት ግን የሁሉም ሰው አንዳይፈታ እናደርጋለን " ሲሉ መልሰው ነበር።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
➡️ " ተሳፋሪን ለማውረድ ክልክል የነበሩ ቦታዎች እየተፈቀዱ ነው ተጨማሪ ቦታዎችም እየታዩ ቅሬታ የሚነሳባቸው ቦታዎች ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተነጋገርን ነው ! "
ከነሐሴ 13 ቀን 2016 ዓም ጀምሮ በስራ ላይ የዋለው " የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ ደንብ ቁጥር 557/2016 " ተግባራዊ ከሆነ ስምንት ወራት ተሻግሯል።
ነባሩ ደንብን በመተካት ተሻሽሎ የወጣው ደንብ የጥፋት እርከንን በሦስት በመክፈል የትራፊክ ቅጣቱንም ከ500 ብር እስከ 1,500 ብር ከፍ አድርጓል።
ደንቡ የከተማ የፍጥነት ወሰንን በ 50 ኪሜ በሰዓት ከመወሰኑ በተጨማሪ ፣ የራዳር መቆጣጠሪያ የሚያውኩ መሳሪያዎችን ይዞ መንቀሳቀስን ይከለክላል።
በተጨማሪም አደጋ አድርሰው በአደጋው ህይወታቸው ያለፈ አሽከርካሪዎች የአደጋውን ምክንያት ለመመርመር ህይወታቸው ካለፈ በኋላም የደም ናሙና እንዲወሰድ የሚፈቅዱ አዳዲስ ጉዳዮችን አካቷል።
ደንቡ ተግባራዊ ከሆነ ጀምሮ " የቅጣት ገንዘቡ የተጋነነ ነው " የሚሉ ቅሬታዎችን ጨምሮ " ያለ አግባብ እየተቀጣን ነው " የሚሉ ቅሬታዎች በአሽከርካሪዎች ዘንድ ይሰማል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ደንቡ ተግባራዊ ከሆነ ጀምሮ ውጤታማነቱ ተገምግሟል ወይ ? ስለሚነሱት ቅሬታዎችን ምን ምላሽ አላቹ ? ሲል የሚመለከተውን አካል ጠይቋል።
የመንገድ ደኅንነት እና መድን ፈንድ ህግ ትግበራ ዴስክ ሃላፊ ወ/ሮ ብርክቲ ባህሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?
" ደንቡ ከወጣ ጊዜ ጀምሮ ሁሉም ክልሎች እንዲደርሳቸው ተደርጓል ከደረሳቸውም በኋላ የማስተዋወቅ እና ምን ምን ተሻሻለ የሚለውን ነገር የማሳወቅ ስራ ሰርተናል።
ጀምረዋል አልጀመሩም የሚለውን አንድ ዙር ተገምግሟል አብዛኛው ክልል ጀምሯል ማለት ይቻላል አጀማመራቸው እኩል ባይሆንም።
' ቅጣቱ ተጋኗል ' የሚል ቅሬታ በሚመለከት ከዚህ በፊት የነበረው ቅጣት አስተማሪ አልነበረም በጣም አነስተኛ ነበር።
ዋናው አላማችን አደጋን መቀነስ ነው ቅጣቶቹ የተቀመጡት ከአደጋ አንጻር ነው።
ቢያንስ ግንዛቤ እየኖረው ነው ' ቅጣቱ ይሄን ያህል ነው ' የማለት የመጠንቀቅ ነገር አለ ለውጥ አለ።
ደረጃ አንድ፣ ሁለት ፣ ሦስት እና ልዩ ጥፋት እርከን ተብሎ ነው የተቀመጠው።
አሽከርካሪዎች ደጋግመው ሊያጠፏቸው ይችላሉ የተባሉትን ጥፋቶች ከመጠናቸውም አንጻር ታይቶ በአንደኛ ደረጃ የጥፋት እርከን ነው የተቀመጡት።
ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጡት ከበድ ያለ አደጋ ሊያደርሱ ይችላሉ ተብለው የተለዩ ጥፋቶች ናቸው ቅጣታቸውም 1,500 ብር ነው።
' ተጋኗል ' የሚል ካለ የማያጠፋን አይመለከትውም ቅጣት የሚመለከተው አጥፊውን ብቻ ነው።
ስፒድ ሊሚተር የሚገጠምላቸው አሽከርካሪዎች አሉ ይህንን ሲፒድ ሊሚተር በትክክል እንዳያሳይ የሚያበላሽ አለ እንደዚህ አይነት ቴክኖሎጂዎችን የሚያሰናክሉ ካሉ የገጠሙት ነገር ይወረሳል ፣በወንጀልም ይጠየቃሉ ቅጣትም አለው።
ይህን አይነቱን ጥፋት የሚያጠፉ አሽከርካሪዎች እንዳሉ ከዚህ ቀደም በተሰሩ ጥናቶች በመታወቁ በደንቡ ላይ እንዲካተቱ ሆኗል።
ከዚህ ቀደም በነበረው ድንብ ላይ ጠጥቶ ወይም አደንዛዥ እጽ ተጠቅሞ አደጋ ያደረሰ እና ህይወቱ ያለፈ አሽከርካሪ ላይ ጠጥቶ ይሁን አይሁን ለማረጋገጥ የሚቻልበት መንገድ አያስቀምጥም ነበር።
በአሁኑ ደንብ አሽከርካሪው በህይወት ባይኖርም የደም ናሙና እንዲወሰድ ይፈቅዳል አተገባበሩ ላይ መመሪያ እየተዘጋጀ ነው።
ተሳፋሪን ለማውረድ ክልክል የነበሩ ቦታዎች እየተፈቀዱ ነው ተጨማሪ ቦታዎችም እየታዩ ቅሬታ የሚነሳባቸው ቦታዎች ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተነጋገርን ነው።
ህጉ ገና መውጣቱ ነው ረዥም ጊዜው አይደለም መሬት ላይ ያለው ሁኔታ ምን ላይ ነው ያለው ? የሚለውን ከሁሉም ክፍል የተወጣጣ ቡድን በስራ ላይ ነው።
ከዚህ ቀደም አሽከርካሪዎች ተደጋጋሚ ጥፋት ስለሚያጠፉ የትራፊክ ፖሊሶች ታርጋ ይፈቱ ነበር መንጃ ፈቃድም ይወስዱ ነበር።
አሁን ላይ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ይህንን የሚያስቀር መተግበሪያ አበልጽጓል።
ከዚህ በኋላ ሰሌዳ መፍታትም ሆነ መንጃ ፈቃድ መውሰድ ሳያስፈልግ አሽከርካሪን የሚቀጣበት አሰራር ነው።
ከዚህ በኋላ ታርጋ አይፈታም ክልክል ነው ደንቡም ላይ ተቀምጧል።
ሲስተሙ ይፋ ተደርጓል ወደ ተግባር እየገቡበት ነው ተሞክሮው ተወስዶ ወደ ክልሎችም የማስተዋወቅ ስራ ይሰራል።
በህጉ መሰረት እንደማይፈቀድ ሁሉም ግንዛቤ እስከሚኖረው ድረስ ጊዜ ይጠይቃል ነገር ግን ታርጋ መፍታት አይፈቀድም " ብለዋል።
ከዚህ ቀደም " የተሽከርካሪን ሰሌዳን መፍታት ክልክል ነው " የሚለው ህግ በተጨባጭ ለምን ተግባራዊ አልሆነም ? የሚል ጥያቄ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን አቶ ክበበው ሚደቅሳ አቀርቦላቸው ነበር።
አቶ ክበበው " ሰሌዳ ቁጥሩ የሚፈታበት አጋጣሚ ይኖራል፣ እሱም የሚሆነው የቅጣት እግድ የደረሱ ከሆነ፣ መንጃ ፍቃዳቸው ላይ ያለው ስልክ ቁጥራቸው የማይሰራ ወይም የክፍለ ሀገር ከሆነ ይፈታል፣ ምክንያቱም አስገዳጅ ምክንያቶች ስለሆኑ በሂደት ግን የሁሉም ሰው አንዳይፈታ እናደርጋለን " ሲሉ መልሰው ነበር።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#Tigray
ዛሬ በመቐለ ማእከላይ ፍርድ ቤት ምንድን ነው የተከሰተው ?
እንስት ዘውዱ ሃፍቱ ከሁለት ዓመት በፊት በግፍ ከተገደሉት ሴቶች አንድዋ ናት።
የሟችዋ ጉዳይ በፓሊስ ተጣርቶ መዝገቡ ወደ ፍርድ ደርሶ ለሁለት ዓመት ያህል ውሳኔ ሳያገኝ በይዋል ይደር ረጅም ጊዜ መውሰዱ የተበዳይዋ ቤተሰብና የፍትህ ፈላጊዎች ሁሉ መነጋገሪያ ሆኖ ቆይቷል።
ይህ በእንዲህ አንዳለ የመቐለ ማእከላይ ፍርድ ግንቦት 8 ቀን 2017 ዓ/ም ከሰዓት በፊት የመጨረሻው ውሳኔ ለመስጠት ችሎት ይቀመጣል።
ፍርድ ቤቱ በግድያ ወንጀሉ በተጠረጠሩት ላይ የመጨረሻ ያለውን የጥፋተኝነት የቅጣት ውሳኔ ይሰጣል።
ይህንን ተከትሎ ችሎቱ በሚከናወንበት አዳራሽ የነበሩት ብዛት ያላቸው የተጠርጣሪ ወገኖች ጠረጴዛ በመደብደብና የተለያዩ ድምፆች በማሰማት ረብሻ ይጀምራሉ።
ከረብሻ በዘለለ ዳኞቹን " እናንተም እንደመስሳቹሃለን ፤ ቀናችሁን ጠብቁ " የሚሉ የስድብ ናዳና ዛቻ ያወርዳሉ።
በችሎት አዳራሹ በቂ የሆነ ስርዓት አስከባሪ ባለመኖሩና ዳኞቹ ሁኔታው ከአቅማቸው በላይ እና አስፈሪ በመሆኑ ምክንያት ውሳኔውን ሳይቋጩ ለግንቦት 18/2017 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ስጥተዋል።
የችሎት መድፈር ተግባሩ የማህበራዊ የትስስር ገፅ ሰፊ መነጋገሪ ሆኖዋል።
ጠበቃ ሚኪኤለ ፍስሃ የተባሉ የሟች ጠበቃ " በፍርሃት ስራዬን አላቋርጥም፤ የተበዳይን እንባ ለማበስ ነገም ዛሬም እሰራለሁ " ሲሉ በማህበራዊ ሚድያ የትሰስር ገጻቸው ላይ ሀሳባቸውን አስፍረዋል።
በርካቶች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የህግ ልዕልና እንዲከበር አገልግሎት በሚሰጠው ፍርድ ቤትና ዳኞች ላይ የተፈፀመ ድፍረት በምሬትና በቁጣ ሲያወግዙት ተስተውለዋል።
የመቐለ ማእከላይ ፍ/ቤት በያዝነው ሳምንት ብቻ የእንስት ዘውዱን ጨምሮ 4 በግፍ የተበደሉ ሴቶችን ጉዳይ መመልከቱን የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ከቦታው መረጃውን አድርሷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ዛሬ በመቐለ ማእከላይ ፍርድ ቤት ምንድን ነው የተከሰተው ?
እንስት ዘውዱ ሃፍቱ ከሁለት ዓመት በፊት በግፍ ከተገደሉት ሴቶች አንድዋ ናት።
የሟችዋ ጉዳይ በፓሊስ ተጣርቶ መዝገቡ ወደ ፍርድ ደርሶ ለሁለት ዓመት ያህል ውሳኔ ሳያገኝ በይዋል ይደር ረጅም ጊዜ መውሰዱ የተበዳይዋ ቤተሰብና የፍትህ ፈላጊዎች ሁሉ መነጋገሪያ ሆኖ ቆይቷል።
ይህ በእንዲህ አንዳለ የመቐለ ማእከላይ ፍርድ ግንቦት 8 ቀን 2017 ዓ/ም ከሰዓት በፊት የመጨረሻው ውሳኔ ለመስጠት ችሎት ይቀመጣል።
ፍርድ ቤቱ በግድያ ወንጀሉ በተጠረጠሩት ላይ የመጨረሻ ያለውን የጥፋተኝነት የቅጣት ውሳኔ ይሰጣል።
ይህንን ተከትሎ ችሎቱ በሚከናወንበት አዳራሽ የነበሩት ብዛት ያላቸው የተጠርጣሪ ወገኖች ጠረጴዛ በመደብደብና የተለያዩ ድምፆች በማሰማት ረብሻ ይጀምራሉ።
ከረብሻ በዘለለ ዳኞቹን " እናንተም እንደመስሳቹሃለን ፤ ቀናችሁን ጠብቁ " የሚሉ የስድብ ናዳና ዛቻ ያወርዳሉ።
በችሎት አዳራሹ በቂ የሆነ ስርዓት አስከባሪ ባለመኖሩና ዳኞቹ ሁኔታው ከአቅማቸው በላይ እና አስፈሪ በመሆኑ ምክንያት ውሳኔውን ሳይቋጩ ለግንቦት 18/2017 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ስጥተዋል።
የችሎት መድፈር ተግባሩ የማህበራዊ የትስስር ገፅ ሰፊ መነጋገሪ ሆኖዋል።
ጠበቃ ሚኪኤለ ፍስሃ የተባሉ የሟች ጠበቃ " በፍርሃት ስራዬን አላቋርጥም፤ የተበዳይን እንባ ለማበስ ነገም ዛሬም እሰራለሁ " ሲሉ በማህበራዊ ሚድያ የትሰስር ገጻቸው ላይ ሀሳባቸውን አስፍረዋል።
በርካቶች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የህግ ልዕልና እንዲከበር አገልግሎት በሚሰጠው ፍርድ ቤትና ዳኞች ላይ የተፈፀመ ድፍረት በምሬትና በቁጣ ሲያወግዙት ተስተውለዋል።
የመቐለ ማእከላይ ፍ/ቤት በያዝነው ሳምንት ብቻ የእንስት ዘውዱን ጨምሮ 4 በግፍ የተበደሉ ሴቶችን ጉዳይ መመልከቱን የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ከቦታው መረጃውን አድርሷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" ከነገ ግንቦት 21 ጀምሮ ወደ ስራ ገበታ ይመለሳሉ " - ፅ/ቤቱ
ላለፉት 12 ቀናት በስራ ማቆም አድማ የቆዩት የመቐለ ዳኞች ስራ ለመጀመር መግባባት ላይ መደረሳቸው ተነግሯል።
ዳኞቹ ያቀረቡት የደህንነት ስጋት ጥያቄ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚከታተለው በተደረሰው ስምምነት ምክንያት ነው ወደ ስራ ገበታቸው ለመመለስ የወሰኑት።
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት " ዳኞቹ ያለባቸው የድህንነት ስጋት በማስመልከት ከፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) እና ከፍትህ አካላት አመራሮች ጋር ተወያይተዋል " ብሏል።
" በውይይቱ በዳኞቹ ላይ ያንዣበበው የደህንነት ስጋት በጥልቀት ተዳሷል ፤ ችግሩን ከስሩ በመረዳት ለመፍትሄው ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል " ሲል ገልጿል።
" የደህንነት ስጋቱ በዘላቂነት ለመፍታት የአጭርና የረጅም ጊዜ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል። በተደረሰው መግባባት መሰረት የመቐለ ሰባቱ ክፍለ ከተማ ፍርድ ቤቶች ከነገ ግንቦት 21/2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ስራ ገበታ ይመለሳሉ " ብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ላለፉት 12 ቀናት በስራ ማቆም አድማ የቆዩት የመቐለ ዳኞች ስራ ለመጀመር መግባባት ላይ መደረሳቸው ተነግሯል።
ዳኞቹ ያቀረቡት የደህንነት ስጋት ጥያቄ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚከታተለው በተደረሰው ስምምነት ምክንያት ነው ወደ ስራ ገበታቸው ለመመለስ የወሰኑት።
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት " ዳኞቹ ያለባቸው የድህንነት ስጋት በማስመልከት ከፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) እና ከፍትህ አካላት አመራሮች ጋር ተወያይተዋል " ብሏል።
" በውይይቱ በዳኞቹ ላይ ያንዣበበው የደህንነት ስጋት በጥልቀት ተዳሷል ፤ ችግሩን ከስሩ በመረዳት ለመፍትሄው ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል " ሲል ገልጿል።
" የደህንነት ስጋቱ በዘላቂነት ለመፍታት የአጭርና የረጅም ጊዜ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል። በተደረሰው መግባባት መሰረት የመቐለ ሰባቱ ክፍለ ከተማ ፍርድ ቤቶች ከነገ ግንቦት 21/2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ስራ ገበታ ይመለሳሉ " ብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" የተርሚናል አገልግሎት ክፍያው የሚፈጸመው ማህበራቱ በስኬት ባንክ በከፈቷቸው አካውንቶች በቴሌብር አማካኝነት ነው " - ማህበራቱ
ነባር ተራ እስከባሪዎችን በመተካት የተርሚናል አስተዳደር እና ቁጥጥር ስልጠና የወሰዱ ከ 80 በላይ በሚሆኑ ማህበራት(ኢንተርፕራይዝ) የተደራጁ ተራ አስከባሪ ወጣቶች ዛሬ ከሰአት ስራ ጀምረዋል።
ዛሬ ጠዋት የአዲስ አበባ ከተማ ስራ እና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አቶ ጥራቱ በየነ ፣የአዲስ አበባ የሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ እና የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ያብባል አዲስ በተገኙበት የተመረቁት 996 የታክሲ ተራ አስከባሪ ወጣቶች ከሰአት በኋላ ስራ መጀመራቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተዘዋውሮ ተመልክቷል።
ነባሮቹን ተራ አስከባሪ ወጣቶች በመተካት ከዛሬ ጀምሮ ወደ ስራ የገቡት ወጣቶች በየወረዳው የተደራጁ ሲሆን በከተማዋ በሚገኙ 87 ተርሚናሎች ወደ ስራ ገብተዋል።
የተርሚናል አገልግሎት ክፍያው የሚፈጸመው ማህበራቱ በስኬት ባንክ በከፈቷቸው አካውንቶች በቴሌብር አማካኝነት መሆኑን ቲክቫህ ያነጋገራቸው የማህበራቱ አባላት ገልጸዋል።
ለትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ግንዛቤ ማስጨበጫ በሚል ከትላንት ጀምሮ የተበተነው እና ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው በራሪ ወረቀት የተቀመጠው የአገልግሎት ክፍያ በየትኛውም መነሻ እና መድረሻ ላይ 10 ብር መሆኑን በመግለጽ ክፍያውንም በዲጂታል መንገድ ብቻ እንዲፈጸም ይጠይቃል።
በተጨማሪም ከተቀመጠው የአገልግሎት ክፍያ በላይ የከፈለ አሽከርካሪም ሆነ ረዳት 4000 ብር እንደሚቀጡ ይገልጻል።
ነባር ተራ አስከባሪዎች በመረጡት የስራ ዘርፍ እንዲሰማሩ አስፈላጊው ድጋፍ ይደረግላቸዋል ተብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ነባር ተራ እስከባሪዎችን በመተካት የተርሚናል አስተዳደር እና ቁጥጥር ስልጠና የወሰዱ ከ 80 በላይ በሚሆኑ ማህበራት(ኢንተርፕራይዝ) የተደራጁ ተራ አስከባሪ ወጣቶች ዛሬ ከሰአት ስራ ጀምረዋል።
ዛሬ ጠዋት የአዲስ አበባ ከተማ ስራ እና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አቶ ጥራቱ በየነ ፣የአዲስ አበባ የሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ እና የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ያብባል አዲስ በተገኙበት የተመረቁት 996 የታክሲ ተራ አስከባሪ ወጣቶች ከሰአት በኋላ ስራ መጀመራቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተዘዋውሮ ተመልክቷል።
ነባሮቹን ተራ አስከባሪ ወጣቶች በመተካት ከዛሬ ጀምሮ ወደ ስራ የገቡት ወጣቶች በየወረዳው የተደራጁ ሲሆን በከተማዋ በሚገኙ 87 ተርሚናሎች ወደ ስራ ገብተዋል።
የተርሚናል አገልግሎት ክፍያው የሚፈጸመው ማህበራቱ በስኬት ባንክ በከፈቷቸው አካውንቶች በቴሌብር አማካኝነት መሆኑን ቲክቫህ ያነጋገራቸው የማህበራቱ አባላት ገልጸዋል።
ለትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ግንዛቤ ማስጨበጫ በሚል ከትላንት ጀምሮ የተበተነው እና ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው በራሪ ወረቀት የተቀመጠው የአገልግሎት ክፍያ በየትኛውም መነሻ እና መድረሻ ላይ 10 ብር መሆኑን በመግለጽ ክፍያውንም በዲጂታል መንገድ ብቻ እንዲፈጸም ይጠይቃል።
በተጨማሪም ከተቀመጠው የአገልግሎት ክፍያ በላይ የከፈለ አሽከርካሪም ሆነ ረዳት 4000 ብር እንደሚቀጡ ይገልጻል።
ነባር ተራ አስከባሪዎች በመረጡት የስራ ዘርፍ እንዲሰማሩ አስፈላጊው ድጋፍ ይደረግላቸዋል ተብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia