አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.86K photos
25 videos
1.86K files
3.58K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የስራ_ማስታወቂያ_ዕጩ_ዳኛ_እና_ዐቃቤ_ሕግ.pdf
753 KB
ማስታወቂያ

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የፍትሕ ባለሙያዎች ማሠልጠኛና የሕግ ምርምር ኢንስቲትዩት በክልሉ ሥር በሚገኙ ወረዳዎች ዳኛ ወይም ዐቃቤ-ሕግ ሆኖ ለመሥራት ለሚፈልጉ ተወዳዳሪዎች ያወጣው ማስታወቂያ

ብዛት፡- 300
የመመዝገቢያ ጊዜ፡- ከታኅሳስ 30 እስከ ጥር 13 ቀን 2017 ዓ.ም
👍22
Losing a top performer will cost far more than retaining them.
Pay people what they're worth.
👍224👏3🔥1
በሀሰተኛ ዲግሪ ተቀጥሮ በዋና ስራ አስኪያጅነት ሲሰራ የነበረ ግለሰብ በእስራት ተቀጣ!!
 
በሀሰተኛ ዲግሪ ተቀጥሮ በዋና ስራ አስኪያጅነት ሲሰራ የነበረ ግለሰብ በተከሰሰበት የሙስና ወንጀል ድርጊት በእስራት እና በገንዘብ እንዲቀጣ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ወሰነ።

ተከሳሹ የማይገባ ብልፅግና ለራሱ ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ አዲስ ፋና ጠቅላላ ሸቀጣ ሸቀጥና ሆቴሎች ንግድ አክሲዮን ማህበር በሕዳር 6 ቀን 2012 ዓ.ም ባወጣው ክፍት የስራ መደብ ማስታወቂያ ተከሳሽ ለውድድር ሲመዘገብ ተገቢው የትምህርት ዝግጅት እንደሌለው እያወቀና ይህንኑ ሁኔታ በመሰወር ማለትም በሐምሌ 25 ቀን 2001 ዓ.ም በዲግሪ መርሐ-ግብር ከአልፋ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በኢኮኖሚክስ የመጀመሪያ ዲግሪ ያለው በማስመሰል ሰነዱን ለድርጅቱ ማቅረቡ ተጠቅሷል።

ከጥር 18 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ በድርጅቱ የንግድ መምሪያ ስራ አስኪያጅ በመሆን እንዲሁም ከሚያዚያ 28 ቀን 2014 ዓ.ም እስከ ሚያዚያ 29 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ደግሞ የድርጅቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ሆኖ በመስራት በአጠቃላይ የደመወዝና ጥቅማ ጥቅም ክፍያ ብር 715 ሺህ 190 ብር እንዲከፈለው በማድረግ በተጠቀሰው የገንዘብ ልክ ጥቅም ያገኘ መሆኑ ተመላክቶ በከባድ ማታለል የሙስና ወንጀል ተከሷል፡፡ፍርድ ቤቱ ማስረጃዎችን መርምሮና አመዛዝኖ በተከሳሹ ላይ የጥፋተኛ ፍርድ በመስጠት እንዲሁም የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየት ከግምት ውስጥ በማስገባት ተከሳሹን በ5 ዓመት ጽኑ እስራትና በ110 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ተወስኗል።
ኢትዮ-መረጃ

🔽🚨🚨🚨
🔴Attorney and Legal Consultant
ጠበቃና የሕግ አማካሪ

We are delighted to connect with you! You can easily reach us through the following platforms to stay informed and access our legal services:

Website & Social Media
Linktree:📱📱📱📱📱📱📱📱  

              https://linktr.ee/alehig

📱Facebook:
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

📱Telegram Channel:⭐️
https://t.me/AleHig

🌐 📱📱📱📱Website: alehig.com


Direct Contact🔈⬇️✉️

📱WhatsApp: ✉️ +251920666595
📱Telegram:  ✉️ @MikiasMelak


Our Commitment
alehig.com
📊አለሕግ🔽
🔠🔠🔠    🔠🔠🔠
Alternative Legal Enlightenment & Services
🔼⭐️
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት


We provide expert legal advice, support, and resources on various laws, proclamations, regulations, and directives to empower and guide you.

Feel free to reach out anytime‼️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👍274😁2🥰1🤔1
ውሸት ለማናገር ቀላል ነች፣💎
እውነት ግን ለሚናገሩት ሆነ ለሚሰሙት ከባድ ነው
💎📸💎
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👍1
Asset Recovery draft proc. Amharic from COM to HPR.pdf
1.1 MB
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የንብረት ማስመለስ አዋጅ

በወንጀልና በሙስና የተፈራ ንብረት የማስመለስ  አዋጅ ጸደቀ
ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው14ኛ መደበኛ ስብሰባው የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ መርምሮ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል።

አዋጁ በሕገ-ወጥ መንገድ የተፈራን ንብረት ማስመለስ የሚያስችሉና የሕግ-ተጠያቂነትን የሚያስከትሉ ድንጋጌዎችን የያዘ ነው።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ዕጸገነት መንግስቱ በረቂቅ አዋጁ የተደረጉ ማስተካከያዎችና የተጨመሩ አንቀጾችን አስመልክተው ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።

ቋሚ ኮሚቴው በአዋጁ ላይ በአስረጅ፣ በህዝብና የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረኮችን በማዘጋጀት ግብዓት እንደሰበሰበ ገልጸዋል።

የንብረት ማስመለስ አዋጅ የመንግስትና የህዝብ ንብረትን ለማስመለስ የነበረውን የሕግ ክፍተት የሚሞላ እንደሆነ አስረድተዋል።

አዋጁ ዜጎች በላባቸውና በወዛቸው ንብረት እንዲያፈሩ የሚያበረታታ፣ በወንጀል ንብረት የሚያፈሩትን ተጠያቂ የሚያደርግ፣ የአገርን ዕድገት የሚያሳልጥ እንደሆነ አስተያየት የሰጡ የምክር ቤት አባላት አንስተዋል።

ግለሰቦች በወንጀልና በሙስና ያፈሩትን ንብረት የሚያስመልስ በመሆኑ በተፈጻሚነቱ ላይ ጥንቃቄ ማድረግና አስፈጻሚ አካላትን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ እና የዜጎችን ንብረት የማፍራት መብት እንዳይጋፋ መታየት አለባቸው ያሏቸውን ጉዳዮች አንስተዋል።     

የሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዕጸገነት መንግስቱ በአዋጁ ሃብት የማፍራትና የማውረስ ሕገ-መንግስታዊ መብትን የሚቃረን ድንጋጌ አለመካተቱንም አብራርተዋል።

የጸረ-ሙስና ትግል እንዲጠናከር የሚያደርግ፣ በሕገ-ወጥ መንገድ የተገኘና የተመዘበረ የአገር ሃብትን ለማስመለስ የሚያስችልና ሕገ-ወጥነትን የሚያስቆም አዋጅ እንደሆነም ጨምረዋል።

ምክር ቤቱ በአዋጁ አስፈላጊነትና ወቅታዊነት ላይ ዝርዝር ውይይት በማድረግ በ ሶሰት ተቃውሞ እና በአራት  ድምጸ  ታቅቦ  በአብላጫ ድምጽ አጽድቆታል።
https://www.alehig.com/federal-democratic-republic-of-ethiopia-property-recovery-proclamation-approved/
👍179
የሚስትን የልደት ቀን መርሳት ያስቀጣል…
🔥🆕🚨
የዓለም ሀገራት የሚመሩበት እና የሚተዳደሩበት ሕግ አላቸው። አንዳንድ ሕጎች ግን አስገራሚ ናቸው። የሚከተሉት ሀገራት ሕጎች ደግሞ ከተለመደው ወጣ ካሉት መካከል ይጠቀሳሉ።


🚫 የሚስትን የልደት ቀን መርሳት

#ሳሞኣ በምትባል ደሴት ሀገር የሚስትን የልደት ቀን መርሳት ወንጀል ነው። በሀገሪቱ ሕግ ባል የሚስቱን ልደት ከረሳና ሚስትም ለፖሊስ ቅሬታ ካቀረበች ባል ከቅጣት አይድንም። ባል ለመጀመርያ ጊዜ ከሆነ የረሳው ከፖሊስ የቃል ማስጠንቀቂያ ይደርሰዋል። ነገር ግን በድጋሚ ከረሳ በእስራት የሚያስቀጣው ወንጀል ይሆናል።

🚫 ለልጅ በሕግ ያልተፈቀደ ስም ማውጣት

#አይስላንድ ሀገር ልጅ ስድስት ወር ሳይሞላው ስም ሊሰጠው ይገባል። የሚሰጠው ስም በሕግ የተመዘገበ አይስላንዳዊ ስም መሆን ይጠበቅበታል። ይህም በሕግ ይረጋገጣል። ስም መስጠትን በተመለከተ በሀገሪቱ ልዩ የሕግ ድንጋጌ ተፈጻሚ ይሆናል።

ለህጻኑ በብሔራዊ የሰዎች መዝገብ ላይ ያልተዘረዘረ ስም እንዲሰጠው ከተፈለገ፣ ስሙን ለማጽደቅ ለግል ስሞች ኮሚቴ ማመልከቻ ማቅረብ ይጠበቃል። ከዚያ በፊት ያልተመዘገበ አዲስ ስም እንደመሆኑ መጠን ለማስመዝገብም ተገቢውን ክፍያ መፈጸም ግዴታ ነው።

🚫 የቆሸሸ መኪና መንዳት

#ሩሲያ ውስጥ የቆሸሸ መኪና እየነዱ ከተያዙ ፖሊስ እርስዎን ለመቅጣት አያቅማም። ስለዚህ እስከ 2 ሺህ የሩሲያ ሩብል ቅጣት ለመክፈል ዝግጁ መሆን ይጠበቅቦታል። ከማሽከርከርዎ በፊት ማሳጠብ ግድ ነው። ይህ ሕግ በሩሲያ ብቻ ሳይሆን በፊሊፒንስ እና ቤላሩስ ተግባራዊ ይደረጋል።

🚫 ፓርላማ ውስጥ መሞት

#እንግሊዝ ፓርላማ ውስጥ መሞት የተከለከለ ነው፡፡ የፓርላማ አባላትን ጨምሮ በንጉሣዊው ቤተ መንግሥት ውስጥ የሞተ ሰው ብሔራዊ የቀብር ሥነ ሥርዓት የማግኘት መብት አለው የሚል አፈ ታሪክ በመኖሩ በዚያ መሞት ፈጽሞ የተከለከለ ነው። ስለዚህ ወደ እንግሊዝ ፓርላማ የሚገቡበት አጋጣሚ ካለ ስለ ሙሉ ጤንነትዎ እርግጠኛ ይሁኑ። ጥሩ ስሜት ካልተሰማዎት በጭራሽ ወደዛ አይጠጉ።

🚫 ማስቲካ መሸጥ እና ማኘክ

#በሲንጋፖር ለሕክምና ዓላማ ካልሆነ በስተቀር ማስቲካ መሸጥም ሆነ ማኘክ ሕገወጥ ነው። የሲጋራ ቁራጮች፣ የከረሜላ መጠቅለያዎችንም ሆነ ሌሎች መሰል ቆሻሻዎችን መጣልም የሚያሥቀጡ ተግባራት ናቸው። በትንሹ ከ500 ዶላር ያላነሰ ክፍያ ያስቀጣሉ። እንደ ድርጊቱ ተደጋጋሚነትም ቅጣቱ ይጨምራል።

🚫 በምሽት ማፏጨት

#በቱርክ በምሽት ማፏጨት የተከለከለ ነው። ይህም በድሮ ጊዜ በምሽት ማፏጨት ክፉ መንፈስ ይጠራል ተብሎ ስለሚታሰብ የወጣ ሕግ ቢሆንም አሁን ላይ በምሽት የድምጽ ብክለት እንዳይኖር ይረዳል በሚል እስካሁን ጥቅም ላይ ይውላል።
#FANA
🔴Attorney and Legal Consultant
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ

We are delighted to connect with you! You can easily reach us through the following platforms to stay informed and access our legal services:

Website & Social Media
Linktree:📱📱📱📱📱📱📱📱  

              https://linktr.ee/alehig

📱Facebook:
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

📱Telegram Channel:⭐️
https://t.me/AleHig

🌐 📱📱📱📱Website: alehig.com


Direct Contact🔈⬇️✉️

📱WhatsApp: ✉️ +251920666595
📱Telegram:  ✉️ @MikiasMelak


Our Commitment
alehig.com
📊አለሕግ🔽
🔠🔠🔠    🔠🔠🔠
Alternative Legal Enlightenment & Services
🔼⭐️
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት


We provide expert legal advice, support, and resources on various laws, proclamations, regulations, and directives to empower and guide you.

Feel free to reach out anytime‼️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👍26😁113👏1
#እንድታውቁት

ከተሻሻለው የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክን ለመቆጣጠር የወጣው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ

ከፖሊስ በተሽከርካሪ ላይ የደረሰውን የጉዳት አይነት የሚገልጽ የፅሁፍ ማስረጃ ሳይቀበሉ ጥገና የሚያከናውኑ ጋራዦች / የጋራዥ ባለቤቶች / በወንጀል ህግ የሚጠየቁት እንዳለ ሆኑ የ20 ሺህ ብር ቅጣት ይጣልባቸዋል።

አመታዊ የተሽከርካሪ ምርመራ ያላደረገ የተሽከርካሪ ባለንብረት 3,000 ብር ይቀጣል።

የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ሳይኖረው ተሽከርካሪ ያሽከረከረ ማንኛውም ሰው 5,000 ብር ይቀጣል።

  የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ሳይኖረው ተሽከርካሪ በማሽከርከር በንብረት ላይ ጉዳት ያደረሰ ማንኛውም ሰው 7000 ብር ይቀጣል።

ከባለቤትነት ወይም በይዞታው የተያዘውን ተሽከርካሪ የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ለሌላው ሰው አሳልፎ የሰጠ ማንኛውም የተሸከርካሪ ባለንብረት 3,000 ብር ይቀጣል።

🚨የትራፊክ ግጭት ወይም ጉዳት አድርሶ በቦታው ላይ ያልቆመ ወይም ባደረሰው የትራፊክ ጉዳት የተጎዳውን እና ሕክምና የሚያስፈልገውን ሰው ወደ ህክምና በመውሰድ እንዲታከም ያላደረገ 👉 በወንጀል ህጉ መሰረት ይጠየቃል።

ወጣት አሽከርካሪዎች፣ ጀማሪ አሽከርካሪዎች ፣ ሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎች ፣ የንግድ ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎች እና አደገኛ ጭነት የጫኑ አሽከርካሪዎች የአልኮል መጠን በትንፋሽ በየትኛውም መጠን ከተገኘ 2,000 ብር ቅጣት ይጠብቃቸዋል።

የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ታግዶበት ሳለ ያሽከረከረ 3,000 ብር ቅጣት ይጣልበታል።

አልኮል መጠን በትንፋሽ ውስጥ ፦
🍻 0.24 እስከ 0.6 ሚሊግራም/ሊትር 1,500 ብር ያስቀጣል።
🍻 0.61 እስከ 0.8 ሚሊግራም /ሊትር 2,000 ብር ያስቀጣል።
🍻 0.81 እስከ 1.0 ሚሊግራም/ሊትር 2,000 ብር ያስቀጣል።
🍻 1.0 ሚሊግራም/ሊትር በላይ የተገኘበት 3,000 ብር ይቀጣል።

በተሽከርካሪ ላይ ተገቢ ያልሆነ አካል የጨመረ ወይም ከተፈቀደለት ወንበር ውጭ ተጨማሪ ወንበር ወይም መቀመጫ የጨመረ የተሽከርካሪ ባለንብረት 400 ብር ይቀጣል።

የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ሞተር እየሰራና በተሽከርካሪው ውስጥ መንገደኞች እያሉ ነዳጅ መሙላት 1,500 ብር ያስቅጣል።

ቴሌቪዥን ወይም ሌሎች ምስሎችን ተሽከርካሪ ውስጥ እየተመለከተ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

የደህንነት ቀበቶ ሳያስር ወይም ተሳፋሪዎች የደህንነት ቀበቶ ማሰራቸውን ሳያረጋግጥ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

የተንቀሳቃሽ ስልክ በእጁ ይዞ እያነጋገረ፣ ወይም መልዕክት እየጻፈ እየላከ ወይም እያነበበ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

ጫት ቅሞ ወይም እየቃመ ወይም አደንዛዥ ዕፅ ወስዶ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

የተሽከርካሪ የፊት ወይም የኃላ ሰሌዳ ሳይኖረው ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

ለአውቶብስ ብቻ ተብሎ በተለየ መንገድ ላይ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

ቀይ መብራት የጣሰ 1,500 ብር ይቀጣል።

የትራፊክ ተቆጣጣሪ ትዕዛዝ ያልፈጸመ፣ ወይም የተሳሳተ መረጃ የሰጠ ወይም እንዲቆም ሲታዘዝ በእንቢተኝነት ሳይቆም የሄደ 1,000 ብር ይቀጣል።

የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ኖሮት ሳይዝ ያሽከረከረ ወይም የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃዱን ሳያሳድስ ያሽከረከረ 1,000 ብር ይቀጣል።

ከተፈቀደው ፍጥናት በታች ያሽከረከረ ወይም የቀኙን ጠርዝ ሳይዝ በዝግታ ያሽከረከረ 1,000 ብር ይቀጣል።

ከመጠን በላይ ድምጽ እያሰማ ወይም የጆሮ ማዳመጫ እያዳመጠ ያሽከረከረ 1,000 ብር ይቀጣል።

መንገድ ላይ ያለን ውሃ በተሽከርካሪው አማካኝነት እግረኛ ላይ እንዲረጭ ያደረገ 1,000 ብር ይቀጣል።

(ተጨማሪ የጥፋት ዝርዝር እና ቅጣቶቹን ከላይ ያንብቡ)
#tikvahethiopia
🔴Attorney and Legal Consultant
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ

We are delighted to connect with you! You can easily reach us through the following platforms to stay informed and access our legal services:

Website & Social Media
Linktree:📱📱📱📱📱📱📱📱  

              https://linktr.ee/alehig

📱Facebook:
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

📱Telegram Channel:⭐️
https://t.me/AleHig

🌐 📱📱📱📱Website: alehig.com


Direct Contact🔈⬇️✉️

📱WhatsApp: ✉️ +251920666595
📱Telegram:  ✉️ @MikiasMelak


Our Commitment
alehig.com
📊አለሕግ🔽
🔠🔠🔠    🔠🔠🔠
Alternative Legal Enlightenment & Services
🔼⭐️
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት


We provide expert legal advice, support, and resources on various laws, proclamations, regulations, and directives to empower and guide you.

Feel free to reach out anytime‼️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👍243👏1🙏1
ምክር ቤቱ በሙስና የተጠረጠሩ ሁለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞችን አሰናበተ🚫🚫▶️🔴🚨
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 15ኛ መደበኛ ጉባዔው የሁለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች የስንብት ውሳኔን አጽድቋል፡፡

የስንብት ውሳኔውን ሪፖርት እና የውሳኔ ሃሳብ የሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ እጸ-ገነት መንግስቱ አቅርበዋል፡፡

ዳኛ አዱኛ ነጋሳ እና ዳኛ አክሊሉ ዘሪሁን የተጣለባቸውን ሕዝባዊ ኃላፊነት ባለመወጣት ከባድ የዲሲፕሊን ጥፋት መፈጸማቸውን ወ/ሮ እጸ-ገነት አብራርተዋል፡፡

የተሰጣቸውን ሹመት አላግባብ በመጠቀም፣ ዳኛ አዱኛ ነጋሳ ገንዘብ እና ቼክ በመቀበል ፤ ዳኛ አክሊሉ ዘሪሁን የአስር ሚሊዮን ብር ቼክ በመቀበል ከባድ የዲሲፕሊን ቅጣት መፈጸማቸውን ሰብሳቢዋ ጠቅሰዋል፡፡

ጉዳዩን አስመልክቶ ቋሚ ኮሚቴው ከፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ጋር በጥልቀት እንደመከረበት ወ/ሮ እጸ-ገነት ተናግረው ፣ ውሳኔውን ምክር ቤቱ እንዲያጸድቅላቸው ጠይቀዋል፡፡

ውሳኔውን በተመለከተ የምክር ቤት አባላት አስተያየቶችን የሰነዘሩ ሲሆን፣ “ቅጣቱ አስተማሪ አይደለም፤ አስተማሪ የሕግ ተጠያቂነት ሊረጋገጥ ይገባል ፤ ወደ መረጠን ሕዝብ ስንሄድ አገልግሎት እና ፍትህ የምናገኘው በገንዘብ ነው ስለሚሉን ውሳኔው ተገቢ ነው” ብለዋል፡፡

በአንጻሩ፣ “ቋሚ ኮሚቴው ዳኞቹ ከመሰናበታቸው አስቀድሞ የፌዴራሉን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውሳኔ ማዳመጥ ይገባዋል፤ የፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤን ውሳኔ እንደ ምስክር ተጠቅሞ ዳኞችን ከስራ ማሰናበት የዳኞቹን መብት ይጋፋል” የሚሉ አስተያየቶች ቀርበዋል፡፡

በተነሱት ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ምላሽ እና ማብራሪያ ከቀረበ በኋላ ውሳኔው ውሳኔው ውሳኔ ሃሳብ ቁጥር 5/2017 ሆኖ በሁለት ድምጸ-ተኣቅቦ እና በአብላጫ ድምጽ ጸድቋል፡፡(ፓርላማ)
🔴Attorney and Legal Consultant
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ

We are delighted to connect with you! You can easily reach us through the following platforms to stay informed and access our legal services:

Website & Social Media
Linktree:📱📱📱📱📱📱📱📱  

              https://linktr.ee/alehig

📱Facebook:
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

📱Telegram Channel:⭐️
https://t.me/AleHig

🌐 📱📱📱📱Website: alehig.com


Direct Contact🔈⬇️✉️

📱WhatsApp: ✉️ +251920666595
📱Telegram:  ✉️ @MikiasMelak


Our Commitment
alehig.com
📊አለሕግ🔽
🔠🔠🔠    🔠🔠🔠
Alternative Legal Enlightenment & Services
🔼⭐️
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት


We provide expert legal advice, support, and resources on various laws, proclamations, regulations, and directives to empower and guide you.

Feel free to reach out anytime‼️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👍9
አከራካሪ የነበረው የንብረት ታክስ ረቂቅ አዋጅ አጸደቀ📊
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 15ኛ መደበኛ ጉባዔው የንብረት ታክስ ረቂቅ አዋጅን አጽድቋል፡፡
💠
🛎💎
በጉባኤው ላይ የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር)፣ እንደ ሀገር በሪፎርሙ ትኩረት ከተሰጣቸው ዘርፎች መካከል ገቢ መሰብሰብ አንዱ መሆኑን ገልጸው፣ ኢኮኖሚው ከሚመነጨው ሀብት ገቢ ለመሰብሰብ ረቂቅ አዋጁ አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

ታክስ የሚሰበሰብበት መሰረት መስፋት ስላለበት ረቂቅ አዋጁ ታክስ ለመሰብሰብ ወሳኝ መሆኑን ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡

ረቂቅ አዋጁን አስመልክቶ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ደሳለኝ ወዳጄ  የቋሚ ኮቴውን  ሪፖርትና የውሳኔ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል፡፡

በሪፖርታቸውም፣ ረቂቅ አዋጁ ኢኮኖሚው ከሚያመነጨው ሀብት ገቢ በመሰብሰብ ለመሰረተ-ልማቶች እና ልዩ ልዩ አገልግሎቶች ለማዋል ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አቶ ደሳለኝ አብራርተዋል፡፡

አዋጁ በሌሎች አፍሪካ ሀገራት ስራ ላይ ከዋለ ከ 30 ዓመታት በላይ እንደሆነው ያወሱት አቶ ደሳለኝ፤ ረቂቅ አዋጁ አዋጅ ሆኖ ወደ ስራ ሲገባ የሚፈለገውን ገቢ በመሰብሰብ የመሰረተ-ልማት ፍላጎቶችን ለማሟላት ጠቀሜታው ከፍተኛ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡

ይሁን እንጂ፣ ረቂቅ አዋጁን  አስመልክቶ አንዳንድ የምክር ቤት አባላት ሪፖርቱን እና የውሳኔ ሃሳቡን በመቃዎም አስተያየት እና ጥያቄዎችን አቅርበዋል፡፡

ረቂቅ አዋጁ የህዝቡን የኑሮ ደረጃ እና  የገቢ ምንጭን  ያላገናዘበ፣ ለታክስ ከፋዩ ተደራራቢ ጫና የሚፈጥር፣ ቋሚ ኮሚቴው ለታክስ ከፋዩ ሳይሆን ለታክስ አስከፋዩ ውግንና ያሳየበትን የውሳኔ ሀሳብ ማቅረቡን ጠይቀዋል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ በበኩላቸው፣ ረቂቅ አዋጁ በሕዝቡ ላይ የተጋነነ ጫና እንደማይፈጥር እና ከታክስ የሚገኘው ገቢም ተመልሶ ህዝቡን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ነው ያብራሩት፡፡

በመጨረሻም፣ ምክር ቤቱ ረቂቅ አዋጁን አዋጅ ቁጥር 1365/2017 አድርጎ በአራት ተቃውሞ፣ በአስር ድምጸ-ተዓቅቦ እና በአብላጭ ድምጽ አጽድቆታል።
ምክር ቤቱ ( ዜና ፓርላማ ) ጥር 06፣ 2017 ዓ.ም.፤
🔴Attorney and Legal Consultant
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ

We are delighted to connect with you! You can easily reach us through the following platforms to stay informed and access our legal services:

Website & Social Media
Linktree:📱📱📱📱📱📱📱📱  

              https://linktr.ee/alehig

📱Facebook:
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

📱Telegram Channel:⭐️
https://t.me/AleHig

🌐 📱📱📱📱Website: alehig.com


Direct Contact🔈⬇️✉️

📱WhatsApp: ✉️ +251920666595
📱Telegram:  ✉️ @MikiasMelak


Our Commitment
alehig.com
📊አለሕግ🔽
🔠🔠🔠    🔠🔠🔠
Alternative Legal Enlightenment & Services
🔼⭐️
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት


We provide expert legal advice, support, and resources on various laws, proclamations, regulations, and directives to empower and guide you.

Feel free to reach out anytime‼️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👍41