African Leadership Excellence Academy
2.33K subscribers
2.53K photos
96 videos
6 files
119 links
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በንድፈ-ኃ
Download Telegram
የጋራ ትርክት ሀገራዊ ህልምን ዕውን ለማድረግ አጋዥ መሆኑን አቶ #ዛዲግ_አብርሐ ገለፁ
--------------------------
(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 08 ቀን፣ 2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ የኢትዮጵያን ህልም ዕውን ለማድረግ የጋራ ትርክት መፍጠር አስፈላጊና አጋዥ ነው ሲሉ #የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ_ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሐ ገለፁ።

ክቡር አቶ ዛዲግ ይህን የገለፁት #"የትርክት_እመርታ_ከታሪካዊ_ስብራት_ወደ_ሀገራዊ_ምልአት" በሚል ርዕስ በሙሐዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በተሰጠው የሥልጠና ርዕስ ጉዳይ ላይ ለኢፌድሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትና ከፍተኛ አመራሮች ማጠቃለያ በሰጡበት ወቅት ነው።

ክቡር አቶ ዛዲግ ከተሳታፊዎች ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት #የኢትዮጵያ ታሪክ አጻጻፍ ላይ በሚነሱ አንዳንድ ክፍተቶች ምክንያት የጋራ ታሪክና የወል ትርክቶች መፍጠር አለመቻሉን ገልፀዋል ።

በመሆኑም እነዚህ አሉ የሚባሉ የታሪክ አተራረክ ክፍተቶችን በማረቅ ከነጠላ ትርክት ይልቅ አሰባሳቢና የጋራ የሆነ ትርክት መፍጠር እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
👍16
የታሪክ አለመግባባቶች አሉ ማለት ግን ሁሉንም ታሪኮች አሽቀንጥሮ መጣልና ትክክለኛ ያልሆኑ ታሪኮች መነሻ በማድረግ ወደ ግጭት መግባት ማለት አለመሆኑን የገለፁት ክቡር አቶ ዛዲግ ጥሩ ጥሩ ታሪኮችን መቀበልና ከተዛቡ ታሪኮች ደግሞ ትምህርት መውሰድ ያስፈልጋልም ነው ያሉት።

የታሪክ አለመግባባት በሚኖርበት ሁኔታ #የጋራ_ትርክትን ለመፍጠር እንደችግር የሚታይ እንደሆነ የገለፁት ክቡር አቶ ዛዲግ፤ ዋናው ጉዳይ ግን በእውነት ላይ ያልተመረኮዙና በምናብ በተፈጠሩ ታሪኮች ሳቢያ የሚፈጠሩ አለመግባባቶች ለመከላከል የጋራ እውነት ላይ የተመሠረተ ትርክት መገንባት ይገባል ብለዋል። በታሪክ የተነሳ የሚፈጠሩ አለመግባባቶችንም በቀጣይ ለመቅረፍ እንደ ሀገራዊ የምክክር መድረኮች የመሳሰሉ ዕድሎች መፍትሔ እንደሚሆኑም አመላክተዋል።

በመጨረሻም የኢትዮጵያ ህልም ዕውን ይሆን ዘንድም የጋራ እና አሰባሳቢ የሆነ ትርክትን መፍጠርና በሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት እንዲኖረው ለማድረግ ሁሉም አካል የበኩሉን ጥረት ማድረግ እንዳለበት እና የምክር ቤት አባላት በዚህ ረገድ የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

(በኃይለሚካኤል አረጋኸኝ)
👍15
የሕዝብን ጥያቄዎች ለመመለስ የፖለቲካ እመርታን ማረጋገጥ ይገባል-አቶ አደም ፋራህ
****************
ሕዝብ የሚያነሳቸውን የዲሞክራሲ፣ የፍትህና የመልካም አስተዳደር፣ የኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጥያቄዎች ለመመለስ ወቅቱን የዋጀ ህዝብን ሁለንተናዊ ጥያቄዎችን የሚመልስ የፖለቲካ እመርታን ማረጋገጥ እንደሚገባ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ገለፁ።

አቶ አደም ፋራህ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላት እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮችና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ጽሕፈት ቤቶች አመራሮች " የፖለቲካ እመርታ፤ ከዲሞክራሲ መብት ወደ ሀገራዊ ኃላፊነት" በሚል ርዕስ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ገለፃ አቅርበዋል።

በኢትዮጵያ ቀደም ባሉት ጊዜያት በነበሩ የመንግስት ስርዓቶች የህዝቡ ዲሞክራሲያዊ መብቶች ሙሉ በሙሉ ያልተረጋገጠበት፣ የተለያዩ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጥያቄዎች ምላሽ ያላገኙበት፣ ቁልፍ ፖለቲካዊ ተቃርኖዎችና ችግሮች ያልተፈቱበት እንደነበር አስታውሰዋል። እነዚህን ችግሮች ለመፍታት የፖለቲካ ሪፎርም ማካሄድ ይገባል ብለዋል።

ይህ የፖለቲካ ሪፎርምም ተቃርኖዎችን ሊያስታርቅ የሚችል የመሀል ፖለቲካን የሚከተል፣ የህዝቦችን ሁለንተናዊ ጥያቄዎች የሚመልስ፣ የሀገሪቱን ሰላምና ደህንነት እንዲሁም ብልፅግናዋን ሊያረጋግጥ የሚችል መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል።

ይህ ዕውን እንዲሆን ጠንካራ የዲሞክራሲ ስርዓትንና ተቋማትን መገንባት እንዲሁም ይህን መምራት የሚችል አመራር እንደሚያስፈልግ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ መግለፃቸውን ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተገኘ መረጃ ያመለክታል።

ጥቅምት 10 ቀን 2017 ዓም
👍13
#ኢትዮጵያ በመጪዎቹ ዓመታት #የኢኮኖሚ_እመርታ እንደምታስመዘግብ ተገለፀ።
(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 11ቀን ፣2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ ኢትዮጵያ በመጪዎቹ አራት አስርተ አመታት ከፍተኛ የኢኮኖሚ እመርታ እንደምታስመዘግብ የፕላንና ልማት ሚንስትር ክብርት ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ በሚሰጠው ስልጠና ላይ ገለፁ።
የትንበያ ጥናቱ ከሀገራችን የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ባሻገር የውጭ ሀገራት ባለሙያዎችም ያረጋገጡት ነው ብለዋል።
ክብርት ዶ/ር ፍፁም ይህን የተናገሩት "እመርታ ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ ወደ ተሟላ ብልፅግና" በሚል ርዕስ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ለኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላት እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ጽህፈት ቤቶች አመራሮች እየተሰጠ ባለው ሥልጠና ላይ ባቀረቡት ገለፃ ነው።
ሀገራት ባላቸው የነፍስ ወከፍ ገቢ፣ ከሚያመርቱት ምርትና ከሚጠቀሙት ቴክኖሎጂ አንፃር ከፍተኛ፣ መካከለኛ እና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ሀገራት ተብለው በሶስት እንደሚከፈሉ አብራርተዋል።
ክብርት ዶ/ር ፍፁም ሀገራችን አሁን ላይ በአፍሪካ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ዕድገት ካስመዘገቡ ሀገራት በ5ኛ ደረጃ፣ ከሰሃራ በታች ካሉት ሀገራት በ3ኛ እና ከምስራቅ አፍሪካ ደግም ቀዳሚውን ደረጃ መያዟን አስገንዝበዋል።
በአለም ባንክ በተደረጉ ጥናቶች ኢትዮጵያ በ2021 እና በ2022 ዓ.ም. በአፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ዕድገት ከሚያስመዘግቡ ሀገራት 2ኛ ደረጃን እንደምትይዝ መጠቆሙን አብራርተዋል።
ክብርት ዶ/ር ፍፁም አሁን ላይ ኢትዮጵያ ካላት የተፈጥሮ ሀብት፣ የሰው ሀይል፣ ይሄንን ማስፈፀም የሚችል መንግስት አኳያ ህልሟን እውን የማታደርግበት አንዳች ምክንያት እንደማይኖርም ነው ያስረዱት።
ስልጠናው ዛሬም #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ለ5ኛ ቀን ቀጥሏል።
👍10
🌍 AFLEX #Emerging_Leadership_Development_Program 🌍
@ the African Leadership Excellence Academy (AFLEX), we believe that the future of Ethiopia and Africa is in the hands of its youth.
The Emerging Leaders Program is our flagship initiative, dedicated to empowering and cultivating the next generation of visionary leaders. These future leaders, with their untapped potential and dynamic energy, hold the key to the continent's lasting prosperity and global influence.
👍16
The AFLEX Emerging Leaders Program is a comprehensive leadership development experience that nurtures young minds through transformative, real-world exposure. It is designed to equip aspiring leaders with the knowledge, skills, and mindset necessary to tackle complex challenges and lead with innovation, empathy, and integrity.
Our vision is centered around a future where Africa is led by courageous, ethical, and forward-thinking leaders. The younger generation, filled with boundless potential, will bring transformative change to their communities, countries, and the entire continent.
At AFLEX, we are committed to identifying and shaping these future trailblazers, who will one day lead Ethiopia and Africa to new heights of economic growth, social equity, and sustainable development.
The focus on the younger generation stems from the belief that youth are not only the future but the driving force behind present-day innovation and progress. Without investing in their development, Africa's vision of prosperity, unity, and progress may remain out of reach.
AFLEX is dedicated to ensuring that today’s youth are equipped with the right skills and values to lead the continent toward a brighter future. The leaders who will drive this transformation in politics, business, science, and social activism are being cultivated right here, at AFLEX.
@ AFLEX, we are not just training leaders for Ethiopia but for the entire African continent. This pan-African initiative brings together young talents from across the region, promoting cross-cultural exchange and collaboration. Through the Emerging Leaders Program, AFLEX aims to be the breeding ground for the next great African leaders, who will shape the future of not just one nation but the entire continent.
Are you ready to be part of Africa's leadership transformation? Join the AFLEX Emerging Leaders Program and finance it, partner with us and let us create the future leaders of Africa and Ethiopia.
#EmergingLeadersAFLEX #LeadershipExcellence #FutureOfAfrica #AfricanYouth #AFLEX #LeadershipDevelopment #NextGenLeaders #YouthEmpowerment #Ethiopia
👍13
The Impact of #AI on #leadershipskills
The development of #AI is drastically changing the nature of #leadership in companies, impacting both the talent needed and the dynamics of leadership itself.
👍11
The use of AI presents challenges to traditional leadership models, even though it also presents great opportunities for improved #DataDriven_decision_making, #Emotional_Intelligence (EQ) and #Human_Centric_Leadership, #Innovation_and_Creativity, #Risk_management, Collaborative Leadership and Crossdisciplinarity Expertise, Ethical Governance, Transparency, Strategic Vision and Foresight, etc.
Beyond mere technological know-how, artificial intelligence is completely changing how leadership is perceived.
To effectively traverse the AI-powered business world, future leaders will require a combination of traditional interpersonal abilities, a thorough understanding of technology, and a strong ethical foundation.
Leaders who combine data-driven insights with emotional intelligence, adapt to changing situations and ensure ethical AI applications are most successful in driving their companies forward.
By #Alemu_Gelan
👍19
#የኢኮኖሚ_ሪፎርሙ የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን የምክር ቤቱ ድጋፍ ከፍተኛ መሆን እንዳለበት ተገለፀ::
በኢትዮጵያ የተጀመረው የኢኮኖሚ ሪፎርም የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን የምክር ቤቱ ድጋፍ ከፍተኛ መሆን እንዳለበት የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስትር ክቡር #ካሣሁን_ጎፌ (ዶ/ር) #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ በሚሰጠው ስልጠና ላይ ገለጹ።
ክቡር #ካሣሁን (ዶ/ር) የኢኮኖሚ አምርታ ለማምጣት ሰፊ ሥራዎች በመንግሥት እየተሠሩ መሆኑን የገለፁ ሲሆን ይህንንም ከዳር እንዲደርስ ምክር ቤቱ በሕግ አወጣጥ፣ በክትትልና ቁጥጥር፣ ፖሊሲዎች እንዲወጡና ተፈፃሚ እንዲሆኑ ድጋፍ በማድረግ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑን አመላክተዋል ።
👍10
ክቡር ዶ/ር ካሣሁን ጎፌ ይህን የገለፁት "እመርታ ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ ወደ ተሟላ ብልፅግና" በሚል ርዕስ የፕላንና ልማት ሚንስትር በሆኑት በክብርት #ፍፁም_አሰፋ (ዶ/ር) ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላት እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ጽሕፈት ቤቶች አመራሮች የቀረበ ገለጻን አስመልክቶ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ የአመራር ልማት ማዕከል ውስጥ ከተሳታፊዎች ለቀረቡት ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት መድረክ ላይ ነው።
ክቡር ዶ/ር ካሣሁን ከኢኮኖሚ ዕድገቱ፣ ከዋጋ ግሽበትና ከኑሮ ውድነት እንዲሁም ከንግድ ሥርዓቱ ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች ላይ ማብራሪያ ሲሰጡ ከለውጥ ወዲህ ባሉት ስድስት አመታት ኢትዮጵያ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ዕድገት ማሳየቷ ጥርጥር የሌለው፣ የሚታይና የሚጨበጥ መሆኑን አስገንዝበዋል ።
ይህን የኢኮኖሚ ዕድገት የአለም ባንክና የገንዘብ ተቋማት ሁሉ የመሰከሩለት ነው ያሉት ክቡር ዶ/ር ካሣሁን፤ የዕድገቱ መነሻዎች የለውጡ መንግሥት ያሳየው ቁርጠኝነት እና የፖሊሲ ለውጦች መሆናቸውን በዋናነት ጠቅሰዋል።
አያይዘውም አሁን ላይ የተጀመሩ የኢኮኖሚ፣ የንግድ፣ የሀገር ውስጥ ምርት ዕድገት በተለይ በስንዴ፣ በሩዝና ሌሎች ምርቶች ከፍተኛ የማምረት አቅም፣ የመደበኛና ትይዩ ንግድ ላይ የነበረውን ሰፊ ልዩነት በማጥበብ እና የውጭ ምንዛሪ ማሻሻያዎች በመንግሥት ማድረግ በመቻሉ በአጭር ጊዜ በሀገራችን ኢኮኖሚ ላይ እያሳዩት ያለው ውጤት እጅግ ከፍተኛ በመሆኑ ከዚሁ ጋር ተያይዞ በ2025 ዓ.ም. ኢትዮጵያ በዓለም ኢኮኖሚያቸው በከፍተኛ ደረጃ ካደጉ ሀገራት ዝርዝር ውስጥ ትገባለች፤ ከአፍሪካ ደግሞ በቀዳሚነት ተርታ ትሰለፋለች ሲሉ አብራርተዋል።
የኢኮኖሚ ዕድገቱ እንደተጠበቀ ሆኖ አሁንም ዜጎች የዋጋ ንረትና የኑሮ ውድነት ተፅእኖ እንዳለባቸው ክቡር ዶ/ር ካሣሁን ጠቁመው፤ አነስተኛ ገቢ ላላቸው ደሞዝ ተከፋይ ለሆኑ የመንግሥት ሠራተኞች ያለውን ጫና በመረዳት የደመወዝ ጭማሪ በማድረግ እና በሌሎች ልዩ ልዩ ድጎማዎች እንዲሁም እንደአጠቃላይ የሕዝብን የኑሮ ጫና ለመቀነስ ምርትን በከፍተኛ ደረጃ በማምረት የገበያውን ሁኔታ በማስተካከል ኑሮን ለማቃለል መንግሥት እየሰራ መሆኑንም አስረድተዋል።
በቀጣይም መንግሥት ከሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት ዜጎች በየደረጃው ተጠቃሚ የሚሆኑበትን መንገድ እየቀየሰ እንደሚሰራም ነው የገለፁት።
ከንግድ ሥርዓቱ ጋር በተያያዘ በርካታ ማነቆዎች መኖራቸውን ጠቁመው፤ እነዚህን ችግሮች ለመፍታት መንግሥት ነፃ የንግድ ቀጠናን ጨምሮ በርካታ ማሻሻያዎችን እያደረገ መሆኑንም ክቡር ዶ/ር ካሣሁን አመላክተዋል።
👍10