African Leadership Excellence Academy
2.33K subscribers
2.53K photos
96 videos
6 files
119 links
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በንድፈ-ኃ
Download Telegram
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት የሚከተሉትን ሹመቶች ሰጥተዋል
1. ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ - የውጪ ጉዳይ ሚንስቴር ሚኒስትር
2. ወ/ሮ ሰላማዊት ካሳ - የቱርዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር
3. ወ/ሮ ሃና አርአያስላሴ- የፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር
👍17
የምክር ቤት አባላት የሀገር ህልም እንዲሳካ ለማስቻል ከፍተኛ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል-#አቶ_አደም_ፋራህ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ሀገራዊ ህልም እንዲሳካ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ሚናቸውን መወጣት አለባቸው ሲሉ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ በመገኘት ገለፁ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትና ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ጽሕፈት ቤቶች አመራሮች #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡
አቶ አደም ፋራህ በዚህ ወቅት ÷የምክር ቤት አባላት ካለባቸው ሕዝባዊ ኃላፊነት አኳያ የሀገር ህልም እንዲሳካ ከፍተኛ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እንዲሠሩ ያስፈልጋል ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡
ኢትዮጵያ ወደ ተሻለ ከፍታ የሚያደርሳትን እና ለትውልድ የሚሻገር ህልም ተልማለች፤ ይህ ህልም እውን ይሆን ዘንድም ምቹ ነባራዊ ሁኔታዎች አሏት ማለታቸውን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መረጃ አመላክቷል፡፡
“ሀገሪቱ ያላት እምቅ የተፈጥሮ ሀብት፣ ከዓላማው ጎን የሚሰለፍ ሕዝብ እንዲሁም የተገነቡ ተቋማት የሀገራችንን ህልም ዕውን ለማድረግ አስቻይ ሁኔታዎች ከሚባሉት ውስጥ በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው” ብለዋል፡፡
👍18
🌍 AFLEX: Building Bridges for a Prosperous Ethiopia and United Africa 🌍

The African Leadership Excellence Academy (AFLEX) is more than just an institution—it is a bridge that connects various sectors of society to work together towards a prosperous Ethiopia and a united Africa. Here's how:
👍6
🌍 AFLEX: Building Bridges for a Prosperous Ethiopia and United Africa 🌍

The African Leadership Excellence Academy (AFLEX) is more than just an institution—it is a bridge that connects various sectors of society to work together towards a prosperous Ethiopia and a united Africa. Here's how:

🔹 Bridging Government and Civil Organizations, Private Sector, and Academia in Ethiopia
AFLEX will create synergy between the government, civil society, the private sector, and academic communities through leadership development programs, workshops, debates, and collaborative research. Instead of being seen as obstacles or adversaries, these entities will be empowered to collaborate and work hand-in-hand, driving Ethiopia towards prosperity.

🔹 Uniting African Leaders Across the Continent
AFLEX will host continental forums, conferences, and research initiatives that bring together African leaders to collaborate on political, economic, and social development. By fostering cooperation, we can overcome challenges and support one another, building a strong network for African progress.

🔹 Connecting Generations of African Leadership
There are two key generations of leaders in Africa today: the post-independence generation, with its experience and wisdom, and the younger generation, full of energy and technological know-how. Currently, these generations often clash instead of cooperating. AFLEX will bridge this gap through leadership programs, debates, and idea exchanges that foster mutual respect and collaboration—because without both generations working together, Africa's potential will remain untapped.

🔹 Setting Africa’s Own Agenda on the Global Stage
For too long, African leaders have traveled to summits abroad, receiving the agendas of other nations. AFLEX is committed to reversing this trend by establishing state-of-the-art facilities that can host Africa's own summits, such as an African Davos. Africa should be setting its own agenda, with the world coming to us to engage in dialogue. AFLEX will be instrumental in making this vision a reality.

As Ethiopia has always been at the forefront of Africa's fight for unity and progress, AFLEX will continue the legacy of our forefathers, ensuring Africa takes its rightful place in the world. Together, we can create a stronger, more prosperous future for all Africans. 🌍

#AFLEX #LeadershipDevelopment #AfricanUnity #BridgingGenerations #ProsperousAfrica #Ethiopia
👍15
#የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ እና #የኢትዮጵያ_ኤሌክትሪክ_ኃይል #የአመራር_ልማት_ስርዓተ_ስልጠና ዝግጅትን በጋራ ገምግመዋል።
ግምገማው የተካሄደው የአካዳሚው የፕሮግራም ዘርፍ ም/ርዕሰ አካዳሚ ተወካይ #እሸቴ_አበበ /ዶ/ር/ እና የሪፎርም ኮሚቴ ሰብሳቢ #ሞገስ_ሎጋው /ዶ/ር/ እና የካሪኩለም ዝግጅት ቡድን ባሉበት ሲሆን፣ በግምገማውም በአፍሌክስና በኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል በትብብር የተዘጋጀው የአመራር ልማት ስርዓተ ስልጠና ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት የተከናወነ መሆኑ ተጠቅሷል።
#ወንድወሰን_ካሳ ዶ/ር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል #የሰው_ኃይል_ልማት_ዳይሬክተር እንደተናገሩት በአሁኑ ወቅት የስርዓተ ስልጠና ዝግጅቱን በማጠናቀቅ ለቫሊዴሽን ግምገማ /Validation Workshop/ የማዘጋጀት ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፤ በቀጣይ ከቫሊዴሽን/ የሚገኘውን ግብዓት በማካተት ስርዓተ ስልጠናውን በበላይ ሃላፊዎች በማስጸደቅና ሞጁል በማዘጋጀት የአመራር ልማት ፕሮግራም ለማስጀመር የሚያስችል ስራዎች ማጠናቀቅ እንዲሚገባ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡
👍18
🌍 Unlocking Africa's Best Potentials Through AFLEX 🌍

Africa, and Ethiopia in particular, hold vast untapped potential across many areas—politics, economics, culture, intellectual advancements, and natural resources. For far too long, these strengths have been locked away, underutilized and overlooked. But now, it’s time for a change.

AFLEX will play a pivotal role in unleashing Africa’s hidden greatness. Here’s how:
👍2
🔓 Unlocking through Research
AFLEX will conduct cutting-edge research to discover Africa’s most promising strengths and opportunities in politics, economics, and culture. This research will fuel new strategies for growth and development, putting Africa on the path to success.

💡 Generating Ideas
At AFLEX, we’ll bring together thought leaders, scholars, policy makers, and innovators to exchange ideas and generate fresh perspectives. Through collaboration, we will unlock breakthrough solutions to Africa’s challenges and pave the way for a brighter future.

📢 Sharing Knowledge
AFLEX will make sure these ideas and findings are shared and acted upon. By hosting forums, workshops, and continent-wide conferences, we’ll connect African leaders, the private sector, and civil society to collaborate and turn these ideas into reality. These platforms will ensure that Africa’s untapped potential is no longer ignored, but fully leveraged for progress.

It’s time for Africa to step into its full power—AFLEX will lead the way, ensuring our continent’s political, economic, cultural, and intellectual assets are unlocked for a stronger, more united Africa. 🌍

#AFLEX #UnlockingPotential #AfricanExcellence #ResearchAndDevelopment #LeadershipForAfrica #Ethiopia #ContinentalCollaboration
👍16
"ኢትዮጵያን ለማበልፀግ ጠንካራ የተቋማት ግንባታ ወሳኝ ነው"

------ ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሐ -----

(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 09 ቀን፣ 2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ ኢትዮጵያን ለማበልፀግ ጠንካራ የተቋማት ግንባታ ወሳኝ መሆኑን የአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሐ አስገንዝበዋል።

ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሐ ለኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፍተኛ አመሮችና አባላት ዛሬ ለሶስተኛ ቀን በቀጠለው ስልጠና "ተቋማዊ ግንባታ፤ ለሀገር እመርታ" በሚል ርዕስ ገለፃ እያደረጉ ነው።

ክቡር አቶ ዛዲግ በገለፃቸው ሀገራችን ከብዙ አመታት በፊት የዲሞክራሲ መገለጫ የሆነውን የገዳ ስርዓትን እና ወታደራዊ መዋቅሮችን ጨምሮ ሌሎች ተቋማትን የመገንባት ጅምሮ ቢኖራትም እስከመጨረሻው ድረስ ባለመዝለቁ ሀገራችንን ማሳደግ አልቻልንም ብለዋል።

ስለሆነም ይህ ትውልድ ኢትዮጵያን ለማሳደግ ጠንካራ ተቋማትን በመገንባት ረገድ ጀምሮ እስከ ማጠናቀቅ ድረስ ረጅም ርቀትን በቁርጠኝነት ሊሄድ እንደሚገባ አሳስበዋል።
👍15
ስለሆነም በቀጣይ ምክር ቤቱም ሆነ የምክር ቤት አባላት ከስልጠናው የሚገኘውን ዕውቀት፣ ልምድና ተሞክሮ በመቅሰም፣ ከተቋማት ጋር በመቀናጀትና ተናቦ በመስራት፣ እንዲሁም የሚሰጡ ቀጣይ ሀገራዊ አቅጣጫዎችን በአግባቡ በመያዝ ሀገራችንን በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና በፖለቲካዊ ዘርፎች በማጠናከር ወደተሻለ ከፍታና ብልጽግና የማሸጋገር ታላቅ ሀገራዊ ኃላፊነት መወጣት ይጠበቅብናል ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡

የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው ‹‹የህልም ጉልበት ለእመርታዊ እድገት›› የሚለው አለማቀፋዊ፣ አህጉራዊና ሀገራዊ ጥቅል የሆነ ሀሳብን የያዘ በመሆኑ የነበራቸውን ግንዛቤ ይበልጥ እንዳሳደገላቸው ገልጸዋል፡፡

አያይዘውም ዛሬ ላይ አደጉ የሚባሉት ሀገሮች የራሳቸውን ህልም አስቀምጠው እንዳሳኩ ሁሉ ሀገራችንም ወደ ብልፅግና የሚሻግራት ህልም ማስቀመጥ በመቻሏ መደሰታቸውን ገልጸዋል፡፡

በስልጠናው ያገኙት ይህ ህልም ዕውን እንዲሆንም ለመራጭ ህዝባቸው በአግባቡ በማስገንዘብ ሀሳቡ እንዲሰርጽ ማድረግ እና በክትትልና ቁጥጥር ስራቸው ውስጥ በማካተት እንዲሰሩም ሰልጣኝ የምክር ቤት አባላቱ ተናግረዋል፡፡

የተሰጡንን ሀገራዊ ተልዕኮዎችን በአግባቡ በመወጣት፣ ከግጭት እና ከፅንፈኝነት አመላከት በመውጣት፣ ችግሮቻችንን በጋራ በመፍታት እንዲሁም ውስጣዊ አንድነታችንን በማጠናከር ሀገራችንን ወደተሻለ ከፍታ ማሻገር ይጠበቅብናልም ነው ያሉት፡፡

በመጨረሻም ሰልጣኝ የምክር ቤት አባላት #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ በቀጣይም በሚሰጡ የስልጠና ርዕሶች ላይም በአግባቡ እንዲሳተፉና የተሻለ ዕውቀትና ግንዛቤ እንይዛለን ብለው እንደሚጠብቁም ገልጸዋል፡፡

(በኃይለሚካኤል አረጋኸኝ)
👍11
#በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ የሚሰጠው
ስልጠናው ምክር ቤቱ እና የምክር ቤት አባላት የተጣለባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት የሚያስችል ትልቅ አቅምን እንደሚፈጥር ተመላከተ
--------------------
(ዜና ፓርላማ)ጥቅምት 09 ቀን ፣ 2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ለምክር ቤቱ አመራሮችና አባላት እየተሰጠ የሚገኘው ስልጠና ምክር ቤቱ እና የምክር ቤት አባላት የተጣለባቸውን ትልቅ ሀገራዊ ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት የሚያስችል ትልቅ አቅምን እንደሚፈጥር የምክር ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች አመላክተዋል፡፡

ስልጠናው ምክር ቤቱና የምክር ቤት አባላት ሀገራችንን ከወቅታዊ አለምዓቀፋዊ ነባራዊ ሁኔታዎች ጋር በማገናዘብ በህገ-መንግስቱ የተሰጠንን የህግ አወጣጥ፣ የክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የህዝብ ውክልና ስራችንን በሙሉ አቅምና ብቃት ለመወጣት ያስችላል ብለዋል፡፡

የምክር ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች አክለውም ስልጠናው ሀገራችን በተጨባጭ እያስመዘገበች ያለውን እመርታ፣ ያጋጠሟትን ተግዳሮቶችን እና እነዚህን ተግዳሮቶች በአንድነት በመቆምና በትብብር መንፈስ በጋራ በመስራት መወጣት እንደሚቻል ያሳየም ነው ብለዋል፡፡

ከለውጡ ወዲህ በሀገራችን ብዙ ማሻሻያዎች ተደርገዋል፤ ሰፋፊ ስራዎች ተሰርተዋል ያሉት የምክር ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች እኛም እንደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና እንደ ምክር ቤት አባል ተሳትፏችን የጎላ ነበር ሲሉ አብራርተዋል፡፡
👍15