African Leadership Excellence Academy
2.33K subscribers
2.53K photos
96 videos
6 files
119 links
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በንድፈ-ኃ
Download Telegram
የታሪክ አለመግባባቶች አሉ ማለት ግን ሁሉንም ታሪኮች አሽቀንጥሮ መጣልና ትክክለኛ ያልሆኑ ታሪኮች መነሻ በማድረግ ወደ ግጭት መግባት ማለት አለመሆኑን የገለፁት ክቡር አቶ ዛዲግ ጥሩ ጥሩ ታሪኮችን መቀበልና ከተዛቡ ታሪኮች ደግሞ ትምህርት መውሰድ ያስፈልጋልም ነው ያሉት።

የታሪክ አለመግባባት በሚኖርበት ሁኔታ #የጋራ_ትርክትን ለመፍጠር እንደችግር የሚታይ እንደሆነ የገለፁት ክቡር አቶ ዛዲግ፤ ዋናው ጉዳይ ግን በእውነት ላይ ያልተመረኮዙና በምናብ በተፈጠሩ ታሪኮች ሳቢያ የሚፈጠሩ አለመግባባቶች ለመከላከል የጋራ እውነት ላይ የተመሠረተ ትርክት መገንባት ይገባል ብለዋል። በታሪክ የተነሳ የሚፈጠሩ አለመግባባቶችንም በቀጣይ ለመቅረፍ እንደ ሀገራዊ የምክክር መድረኮች የመሳሰሉ ዕድሎች መፍትሔ እንደሚሆኑም አመላክተዋል።

በመጨረሻም የኢትዮጵያ ህልም ዕውን ይሆን ዘንድም የጋራ እና አሰባሳቢ የሆነ ትርክትን መፍጠርና በሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት እንዲኖረው ለማድረግ ሁሉም አካል የበኩሉን ጥረት ማድረግ እንዳለበት እና የምክር ቤት አባላት በዚህ ረገድ የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

(በኃይለሚካኤል አረጋኸኝ)
👍15