Ethiopian Airlines የኢትዮጵያ አየር መንገድ
90.5K subscribers
3.55K photos
134 videos
2 files
398 links
ይህ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።
Download Telegram
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጎርጎራ ሪዞርትን በኢትዮጵያ ስካላይት ሆቴል ስር የማስተዳደር ኃላፊነትን ዛሬ በኢትዮጵያ ስካይ ላይት ሆቴል በተደረገ የስምምነት ስነስርዐት ተረከበ። በስነ ስርዐቱ ላይ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ አረጋ ከበደ፣ ከፍተኛ የክልሉ የስራ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የንግድ ሥራ ዋና ኃላፊ አቶ ለማ ያዴቻ እና ሌሎች የኢትዮጵያ አየር መንገድ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በገበታ ለሀገር ፕሮጀክት የተገነቡትን ሀላላ ኬላ ሪዞርት፣ የወንጪ ኢኮ ሎጅ እንዲሁም የጨበራ ጩርጩራ የዝሆን ዳና ሎጅን የማስተዳደር ኃላፊነትን በቅርቡ ወስዶ ወደ ስራ በመግባት ለኢትዮጵያ ቱሪዝም ኢንደስትሪ ዕድገት የራሱን ድርሻ ለመወጣት ያላሰለሰ ጥረት እያደረገ ይገኛል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ #የኢትዮጵያስካይላይትሆቴል #ገበታለሀገር