Ethiopian Airlines የኢትዮጵያ አየር መንገድ
90.5K subscribers
3.55K photos
134 videos
2 files
398 links
ይህ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።
Download Telegram
በቀደሙት ግዜያት ስንከተለው የነበረው “አፍሪካውያንን እርስ በርስ ማስተሳሰር” የተሰኘው መርሀችን ዛሬም በድምቀት ቀጥሎ ለ37ኛው የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ በአፍሪካዋ መዲና አዲስ አበባ የተገኙ 20 የአፍሪካ አገራት መሪዎችን በግዙፉ እና ዘመናዊው የኢትዮጵያ ስካይ ላይት ሆቴል በክብር ተቀብለን አስተናግደናል። የኢትዮጵያ ስካይ ላይት ሆቴል በአፍሪካ ከሚገኙ ትላልቅ ሆቴሎች አንዱ ሲሆን በውስጡም 1024 ክፍሎች አሉት። የኢትዮጵያ ስካይ ላይት ሆቴል እንደ አህጉራችን አፍሪካ ሁሉ በህብረ ቀለማት አሸብርቆ እንግዶቹን በክብር አስተናግዶ ሸኝቷል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #የኢትዮጵያስካይላይትሆቴል #ፓንአፍሪካዊ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአፍሪካ አየር መንገዶች ማህበር (AFRAA) ጋር በጥምረት ያዘጋጀው 12ኛው የአፍሪካ አየር መንገዶች ማህበር ጉባዔ በኢትዮጵያ ስካይላይት ሆቴል በድምቀት በመካሄድ ላይ ይገኛል። ይህ የሶስት ቀናት ጉባዔ 'የአፍሪካን አቪዬሽን ከማገናኘት ባሻገር' በሚል መሪ ቃል የኢንዱስትሪውን ቁልፍ ተዋናዮች ያሰባሰበ ነው። #12ኛውየአፍሪካአየርመንገዶችማህበር #የአፍሪካንአቪዬሽንከማገናኘትባሻገር #የኢትዮጵያስካይላይትሆቴል #የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጎርጎራ ሪዞርትን በኢትዮጵያ ስካላይት ሆቴል ስር የማስተዳደር ኃላፊነትን ዛሬ በኢትዮጵያ ስካይ ላይት ሆቴል በተደረገ የስምምነት ስነስርዐት ተረከበ። በስነ ስርዐቱ ላይ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ አረጋ ከበደ፣ ከፍተኛ የክልሉ የስራ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የንግድ ሥራ ዋና ኃላፊ አቶ ለማ ያዴቻ እና ሌሎች የኢትዮጵያ አየር መንገድ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በገበታ ለሀገር ፕሮጀክት የተገነቡትን ሀላላ ኬላ ሪዞርት፣ የወንጪ ኢኮ ሎጅ እንዲሁም የጨበራ ጩርጩራ የዝሆን ዳና ሎጅን የማስተዳደር ኃላፊነትን በቅርቡ ወስዶ ወደ ስራ በመግባት ለኢትዮጵያ ቱሪዝም ኢንደስትሪ ዕድገት የራሱን ድርሻ ለመወጣት ያላሰለሰ ጥረት እያደረገ ይገኛል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ #የኢትዮጵያስካይላይትሆቴል #ገበታለሀገር
በዘንድሮው የ “World Travelers Award” ለሽልማት ከታጨንባቸው ስድስት ዘርፎች አንዱ በአፍሪካ ምርጡ የኮንፈረንስ ሆቴል ሲሆን በዚህ ዘርፍም የኢትዮጵያ ስካይ ላይት ሆቴል ዕጩ ሆኗል። ከታች በተቀመጠው ሊንክ ለዚህ ዘርፍ የታጨውን የኢትዮጵያ ስካይ ላይት ሆቴል ይምረጡ!
https://www.worldtravelawards.com/vote-r3#votenow
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #የኢትዮጵያስካይላይትሆቴል