Ethiopian Airlines የኢትዮጵያ አየር መንገድ
90.5K subscribers
3.57K photos
134 videos
2 files
398 links
ይህ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።
Download Telegram
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን ኤርባስ A350-1000 አውሮፕላን በፈረንሳይ ቱሉዝ በተካሄደ ስነስርዓት ከኤርባስ ኩባንያ ተረከበ።

በርክክብ ስነስርዐቱ ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ቦርድ ሰብሳቢ ሌተናል ጀነራል ይልማ መርዳሳ ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣ የአየር መንገዳችን ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎችና የኤርባስ ኩባንያ የስራ ሀላፊዎች የተገኙ ሲሆን ይህ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የተረከበው ኤርባስ A350-1000 አውሮፕላን ዛሬ አዲስ አበባ ይገባል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው እና በአፍሪካ በአይነቱ የመጀመሪያው የሆነው ኤርባስ A350-1000 አውሮፕላን ዛሬ አዲስ አበባ ገብቷል። አውሮፕላኑ አቪዬሽን ሳንስ ፍሮንቲርስ ከኤርባስ ኩባንያ ጋር በመተባበር ለኢቲ ፋውንዴሽን ያበረከቱትን ከ100,000 ዩሮ በላይ የሚያወጣ የህክምና ቁሳቁሶች ያጓጓዘ ሲሆን አዲስ አበባ ቦሌ አለም ዓቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ ታላላቅ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች፣ አምባሳደሮች፣ ሚኒስተሮች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ደማቅ የአቀባበል ስነ-ስርአት ተደርጎለታል። ለተጨማሪ ንባብ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ https://rb.gy/wr796e
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ኤርባስA3501000
ማራኪ የጎርጎራ ኢኮ ሎጅ ዕይታ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤርባስ A350-1000
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #መስኮትምልከታ
📸Yonathan Menkir Kassa
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ትኬታቸውን በድረ ገፃችን www.ethiopianairlines.com አሊያም በተንቀሳቃሽ ስልክ መተግበሪያ https://www.ethiopianairlines.com/aa/ethiopian-app ለሚገዙ ደንበኞቹ እስከ 10% የሚደርስ ልዩ ቅናሽ አዘጋጅቷል።
ይህ ልዩ ቅናሽ የተዘጋጀው ወደተለያዩ የአፍሪካ፣ አውሮፓና፣ ኤዥያና መካከለኛው ምስራቅ ሀገራት መዳረሻዎቻችን ሲሆን ትኬትዎን እስከ ሕዳር 6 ቀን 2017 ዓ.ም ገዝተው በረራዎን እስከ ሕዳር 13 ቀን 2017 ዓ.ም ያድርጉ። ይፍጠኑ የዚህ ልዩ ቅናሽ ተጠቃሚ ይሁኑ። ስለ ልዩ ቅናሹ ተጨማሪ መረጃ በድረ ገፅ አድራሻችን https://bit.ly/40tZVL4 ማግኘት ይችላሉ።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤርባስ A350-1000 አውሮፕላን የመጀመሪያ በረራውን ወደ ናይጀሪያ ሌጎስ ያደርጋል። ከእኛ ጋር በምቾት ይብረሩ!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ሌጎስ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን ኤርባስ A350-1000 አውሮፕላን በደመቀ ሁኔታ ተቀብላለች! የናይጄሪያዋ ከተማ ሌጎስ በዚህ ልዩ እና እጅግ ዘመናዊ አውሮፕላን በረራ የጀመርንባት የመጀመሪያዋ መዳረሻ ከተማችንም ሆናለች።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
አፍሪካን እርስ በርስ ብሎም ከተቀረው ዓለም ጋር በአየር ትራንስፖርት በማስተሳሰር አይተኬ ሚና እየተጫወተ የሚገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአለም ግንባር ቀደም ሰማይ ጠቀስ ሕንፃዎች መገኛ እና ተመራጭ ዓለም አቀፍ የመዝናኛ ከተማ ወደሆነችው ዱባይ ምሽቱን በአፍሪካ የመጀመሪያ በሆነው ኤርባስ A350-1000 አውሮፕላን በረራ ያደርጋል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሚያበራቸው የአውሮፕላን አይነቶች ሁሉ የምስለ በረራ ስልጠና የሚሰጥበት ዘመናዊ ክፍል ያለው ሲሆን በምስለ በረራው ውስጥ በትክክለኛው የበረራ ወቅት ሊያጋጥሙ በሚችሉ ክስተቶች ላይ አስተማማኝ ስልጠና ይሰጣል። የዚህን ሳምንት የኢትዮጵያ መርሐ ግብር እንዲከታተሉ በአክብሮት ጋብዘንዎታል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርስቲ 200 የሚደርሱ ጋቦናውያን ተማሪዎችን በደማቅ ስነስርዐት ተቀበለ። ጋቦናውያኑ ተማሪዎች በተለያዩ የአቪዬሽን ዘርፎች በዩኒቨርስቲያችን ትምህርታቸውን የሚከታተሉ ሲሆን በአቀባበል ስነስርዐቱ ላይ በኢትዮጵያ የጋቦን ሪፐብሊክ አምባሳደር ክብርት ሊሊ ስቴላ ንዶንግ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የንግድ ዘርፍ ሓላፊ አቶ ለማ ያዴቻ፣ የአየር መንገዳችን ከፍተኛ የስራ ሓላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #የኢትዮጵያአቪዬሽንዩኒቨርስቲ
ሌላኛዋ የምዕራብ አፍሪካ መዳረሻችን የሆነችው የጋና ዋና ከተማ አክራ በአፍሪካ የመጀመሪያውን ኤርባስ A350-1000 አውሮፕላን በከፍተኛ ድምቀት በኮቶካ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ተቀብላለች።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ