ለኢ-ኮሜርስ ሸቀጦች እንዲሁም ለፖስታ እና ጥቅል መልእክቶች የሎጂስቲክስ አገልግሎትን የሚያቀላጥፈው እና አንድ ደረጃ ከፍ የሚያደርገው ከኢትዮጵያ ካርጎ እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት የሚበረከተው የምስራች ይፋ ሊደረግ ሰዓታት ብቻ ቀሩት፡፡
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #የኢትዮጵያካርጎእናሎጂስቲክስአገልግሎት
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #የኢትዮጵያካርጎእናሎጂስቲክስአገልግሎት
👍36🥰27❤18👏12🎉6
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር የሆኑት ክቡር አምባሳደር ኤርቪን ጆሴ ማሲንጋ እና የልዑክ ቡድናቸው በኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋናው መስሪያ ቤት ተገኝተው ጉብኝት አደረጉ።
ክቡር አምባሳደሩና ልዑካኖቻቸው ከአየር መንገዳችን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው እና የአየር መንገዱ ማኔጅመንት አባላት ጋር ፍሬያማ ውይይት ያደረጉ ሲሆን ስለ አጠቃላይ የአየር መንገዳችን የስራ እንቅስቃሴ እና የዕድገት ጉዞ ገለፃ ተደርጎላቸዋል።
ክቡር አምባሳደር ማሲንጋ ከልዑካኖቻቸው ጋር በመሆን በአቪዬሽን ኢንደስትሪው ዘመናዊ የሆኑትን የተለያዩ የስራ ክፍሎቻችንን ጎብኝተዋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ክቡር አምባሳደሩና ልዑካኖቻቸው ከአየር መንገዳችን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው እና የአየር መንገዱ ማኔጅመንት አባላት ጋር ፍሬያማ ውይይት ያደረጉ ሲሆን ስለ አጠቃላይ የአየር መንገዳችን የስራ እንቅስቃሴ እና የዕድገት ጉዞ ገለፃ ተደርጎላቸዋል።
ክቡር አምባሳደር ማሲንጋ ከልዑካኖቻቸው ጋር በመሆን በአቪዬሽን ኢንደስትሪው ዘመናዊ የሆኑትን የተለያዩ የስራ ክፍሎቻችንን ጎብኝተዋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
❤48👍40🥰6
ዘመናዊ የመንገደኞች መቆያ ስፍራዎች ባልተሟሉባቸው በቀደሙት ግዜያት መንገደቾች በዚህ መልኩ በ DC-3 ሰፋፊ ክንፎች ስር በመሆን የቀትርን ፀሐይ ያሳልፉ ነበር።
#ትውስታ #የኢትዮጵያአየርመንገድ
#ትውስታ #የኢትዮጵያአየርመንገድ
❤75👍24😍19👏3🥰2
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ አዲሱን በአፍሪካ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን እና 55 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር መዋዕለ-ንዋይ ያፈሰሰበትን ዘመናዊ የኢኮሜርስ መሰረተ ልማት በደማቅ ስነ ስርዓት በዛሬው ዕለት አስመረቀ፡፡ የዚህ በልዩ ሁኔታ ለኢኮሜርስ ሸቀጦች እንዲሁም ለፖስታ እና ጥቅል መልእክቶች የሎጂስቲክስ አገልግሎት ለመስጠት ታስቦ ወደ ስራ የሚገባው መሰረተ-ልማት የአፍሪካን የኢኮሜርስ ኢንደስትሪ ዕድገት ከማፋጠኑም ባሻገር አዲስ አበባን በአፍሪካ ብሎም በዓለም የድንብር ተሻጋሪ ኢኮሜርስ ማዕከል የሚያደርግ ነው፡፡
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #የኢትዮጵያካርጎእናሎጂስቲክስአገልግሎት
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #የኢትዮጵያካርጎእናሎጂስቲክስአገልግሎት
👍95❤37🎉13😍2