Ethiopian Airlines የኢትዮጵያ አየር መንገድ
90.5K subscribers
3.75K photos
141 videos
2 files
411 links
ይህ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።
Download Telegram
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና አርቸር አቪዬሽን በኤሌክትሪክ የሚሰሩ አውሮፕላኖችን በአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ ለማዋል የሚያስችል የጋራ ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱ ዘመኑ የደረሰበትን የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት ከማስቻሉም በላይ ለአየር ንብረት መጠበቅ የራሱ አስተዋፅዖም ያበረክታል።
ለተጨማሪ ንባብ ሊንኩን ይጫኑ። https://corporate.ethiopianairlines.com/Press-release-open-page/ethiopian-airlines-africa-s-largest-carrdier-and-archer-sign-an-agreement-to-deploy-midnight-under-the-launch-edition-program
የኢትዮጵያአየርመንገድ
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኞች መንደር (ET Village) ህፃናት እና ታዳጊዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ ተገኝተው ያደረጉትን ጉብኝት በዛሬው የኢትዮጵያ መርሐግብር ይዘንላችሁ ቀርበናል። ተከታተሉን!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1446ኛው ዒድ አልፈጥር በዓል አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሰላም፣ የጤና እና የፍቅር እንዲሆንላችሁ ምኞቱን ይገልፃል።
ዒድ ሙባረክ!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ምርጫዎን የኢትዮጵያ አየር መንገድን ያድርጉ። ትኬትዎን በድረገፃችን www.ethiopianairlines.com አሊያም በተንቀሳቃሽ ስልክ መተግበሪያችን https://www.ethiopianairlines.com/aa/ethiopian-app ገዝተው ባመችዎ የበረራ አማራጭ እና በልዩ ኢትዮጵያዊ መስተንግዶ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ይብረሩ።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
አለም ዓቀፍ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት ከምርጥ ኢትዮጵያዊ መስተንግዶ ጋር!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የዛሬውን #የመስኮትምልከታ ያጋሩን @ Yalemsew Birhanu ናቸው፤ እናመሰግናለን! #የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከትናንት እስከ ዛሬ!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ትውስታ
ተፈጥሮአዊ ዉበትን ከዉብ ባህል ጋር አጣምራ ወደያዘችዉ ጋምቤላ ከተማ የማይረሳ ጉዞ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ያድርጉ!

#ኢትዮጵያአየርመንገድ #ጋምቤላ
ከምርጥ መስተንግዶ ጋር በክብር ልናገለግልዎ ተዘጋጅተናል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ከ140 በላይ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎቻችን በምቾት እና ከልዩ ኢትዮጵያዊ መስተንግዶ ጋር ይብረሩ።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ምርጫዎን የኢትዮጵያ አየር መንገድን ያድርጉ።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር አስደሳች በረራ በማድረግ ሳምንትዎን ይጀምሩ!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ሻርጃ ከተማ ከግንቦት 24 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ አዲስ የበረራ አገልግሎት የሚጀምር መሆኑን ሲያበስር ደስታ ይሰማዋል። ይህ አዲስ የበረራ አገልግሎት በሳምንት አራት ቀናት የሚደረግ ሲሆን መንገደኞች በተቀላጠፈ የበረራ አማራጭ የደማቅ ባህል እና ሰፊ ኢኮኖሚያዊ እድሎች ባለቤት ወደሆነችው ሻርጃ ከተማ በቀላሉ እንዲጓዙ ያስችላል። ለተጨማሪ ንባብ ሊንኩን ይጫኑ። https://corporate.ethiopianairlines.com/Press-release-open-page/ethiopian-airlines-prepares-to-launch-passenger-flight-service-to-sharjah-the-uae
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
አፍሪካን እርስ በእርስ እንዲሁም ከተቀረው ዓለም ጋር በማገናኘት ለ79 ዓመታት የዘለቀ ስኬታማ ጉዞ!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ማሳሰቢያ
አዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፍያ ዛሬ ሐሙስ ሚያዝያ 2 ቀን 2017 ዓ.ም ከስምንት እስከ ዘጠኝ ሰዓት ለአንድ ሰዓት የሚቆይ የድንገተኛ አደጋ ምላሽ አሰጣጥ የሙሉ አቅም ልምምድ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
ይህ ልምምድ የድንገተኛ አደጋ ምላሽ አሰጣጥ እና የእርዳታ መስጫ ቁሳቁሶች ብቁነትን፣ በአደጋ ጊዜ የሚኖር የመልዕክት ልውውጥ ፍሰትን እንዲሁም በእርዳታ ሰጪዎች መካከል የሚኖረውን ቅንጅት እና ጥምረት ለመፈተሸ ይረዳል፡፡
በተጨማሪም ልምምዱ ከአየር ማረፍያው ውጪ የሚገኙ እርዳታ ሰጪዎች ከአየር ማረፍያው አቀማመጥ እና በውስጡ ከሚገኙ የእርዳታ መስጫ ቁሳቁሶች ጋር እንዲተዋወቁ በማድረግ በእውነተኛ ድንገተኛ አደጋ ወቅት የእርዳታ አሰጣጥ ሂደቱ የተፋጠነ እንዲሆን በማስቻል ረገድ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል፡፡
ይህንንም ለመፈተሽ በወቅቱ በከተማው ሆስፒታሎች እና በአየር ማረፍያው መካከል የእርዳታ መስጫ ተሸከርካሪዎች እንቅስቃሴ የሚኖር መሆኑን እያሳወቅን ይህ እንቅስቃሴ የልምምዱ አካል መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች እንዲረዱልን በታላቅ አክብሮት እንገልፃለን።
አዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፍያ መሰል ልምምዶችን በእየሁለት አመት አንዴ ያከናውናል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የስታር አልያንስ አባል!
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የዛሬው የኢትዮጵያ የተሰኝው ፕሮግራማችን በተለያዩ የአቪዬሽን ሙያ ላይ የተሰማሩ ሴት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሠራተኞች ጋር ቆይታ አድርጓል ተከታተሉን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)