Ethiopian Airlines የኢትዮጵያ አየር መንገድ
90.5K subscribers
3.57K photos
134 videos
2 files
398 links
ይህ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።
Download Telegram
ማሳሰቢያ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለክቡራን መንገደኞቹ የሚሰጣቸው ዓለም አቀፍ የበረራ ቲኬት ሽያጭ አገልግሎቶች በሙሉ በውጪ ምንዛሪ (hard currency) ብቻ እንደሚሆን ተደርጎ በተለያዩ የማህበራዊ መገናኛ አውታሮች ሲዘዋወር ተመልክቶታል።

ይሁን እንጂ የጉዳዩ ትክክለኛ መረጃ በቅርቡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀም መመርያ ማውጣቱን ተከትሎ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዚህ ቀደም ከሀገር ውጪ ተነስተው ወደ ሀገራችን ለሚደረጉ ጉዞዎች በሀገር ውስጥ መገበያያ ገንዘብ ሲሰጥ የነበረውን የበረራ ቲኬት ሽያጭ አሰራር ከሐምሌ 02 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በከፊል የተከለከለ መሆኑን እና በውጪ ምንዛሪ አገልግሎቱን የሚያገኙ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን።

ይኸውም ሀገር ውስጥ በሚንቀሳቀሱ በሁሉም አየር መንገዶች ተግባራዊ እንዲደረግ የወረደ መመርያ መሆኑን እያሳሰብን ኢትዮጵያዊያን እና ህጋዊ ሰነድ ያላቸው (የመኖርያ ፈቃድ፣ ቢጫ ካርድ፣ የሥራ ፈቃድ፣ የዲፕሎማቲክ ፈቃድ ወዘተ) የውጪ ሀገር ዜጎች በሙሉ ከሀገር ውስጥ ወደ ውጪ ሀገራት ለሚደረጉ በረራዎች የቲኬት ሽያጭ አገልግሎታችንን ከዚህ ቀደም በነበረው አሰራር መሰረት ማግኘት የሚችሉ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን። ነገር ግን ትኬታቸውን በኢትዮጵያ የሚገዙ የውጭ ሀገር ዜጎች በውጭ ምንዛሬ መክፈል ይኖርባቸዋል።

ለበለጠ መረጃ
https://www.ethiopianairlines.com/aa/services/help-and-contact/Global-Customer-Interaction-Centre-numbers

የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የስታር አሊያንስ አባል
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሠራተኞች እ.ኤ.አ. በ1977 ዓ.ም. በልዩ የአቪዮኒክስ ሥልጠና ላይ።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ትውስታ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአቪዬሽን ዘርፉ ስኬት ቁልፍ ሚና ካላቸው ባለድርሻ አካላት አንዱ ለሆነው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አቪዬሽን ፖሊስ መምሪያ ያስገነባውን መኖሪያ ካምፕ አስመርቆ ለአገልግሎት አበቃ።
በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ክቡር ደመላሽ ገሚካኤል ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች እና ሌሎች ጥሪ የተደረላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው አየር መንገዱ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ስኬታማ አገልግሎት እንዲሰጥ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አቪዬሽን ፖሊስ መምሪያ አይተኬ ሙያዊ አስተዋፅዖ እያበረከተ እንደሆነ ገልፀዋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ሞምባሳ የ“አንድ ትኬት ይግዙ፤ አንድ በነፃ ይሸለሙ” ልዩ የጉዞ ጥቅል አዘጋጅቶ ይጠብቅዎታል። ትኬትዎን እስከ ሐምሌ 18 ቀን 2016 ዓ. ም በ ET323/324 ላይ ብቻ ይግዙ፤ ጉዞዎን እስከ ነሐሴ 25 ቀን 2016 ዓ. ም ያድርጉ።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከምስረታው ጀምሮ ባካሄዳቸው የተለያዩ የሩጫ መርሓግብሮች የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሰጠው ያልተቋረጠ ድጋፍ እና ለሩጫ መርሐግብሮቹ ስኬታማነት ላበረከተው አስተዋፅዖ ‘የወርቅ ደረጃ’ የዕውቅና ሽልማት ተበረከተለት። ሽልማቱን ያበረከቱት ጀግኖች አትሌቶቻችን ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ እና ገዛኸኝ አበራ ሲሆኑ በሽልማት አሰጣጥ ስነስርዐቱ ላይ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ናሲሴ ጫሊን ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ታላቁሩጫበኢትዮጵያ
አዲስ በረራ በባህር ዳር እና ደሴ ኮምቦልቻ ፤ በመቐለ እና ሽረ መካከል!
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሐምሌ 13 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በሳምንት ሥስት ቀን ማክሰኞ፣ ሐሙስ እና ቅዳሜ ከባህርዳር ወደ ደሴ ኮምቦልቻ እንዲሁም ሰኞ፣ ረቡዕ እና ዓርብ ከመቐለ ወደ ሽረ ቀጥታ በረራ የጀመረ መሆኑን ለክቡራን መንገደኞቹ በደስታ ይገልጻል። ጉዞዎን ያቅዱ በተቀላጠፈ አገልግሎታችን ይረካሉ። በምቾት ይጓዙ!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ዘና ብለው ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ይብረሩ፣ ምርጥ መስተንግዷችንን ያጣጥሙ።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ ብሎም የአፍሪካ ውበት እና ኩራት ጋር ከፍ ብለን እንብረር! #የኢትዮጵያአየርመንገድ
ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ቀጣይ የጉዞ መዳረሻዎን ማቀድ ይጀምሩ።

https://www.ethiopianairlines.com/et
#የኢትዮጵያአየርመንገድ