#ከትግራይ #ክልል የተመለሱ #የዩኒቨርሲቲ #ተማሪዎች፣
" ተማሪዎቹ በቀጣይ 2 ሳምንታት ውስጥ መፍትሄ ያገኛሉ " - ኢዶሳ ተርፋሳ (ዶ/ር)
ከ150 በላይ ከትግራይ ክልል የተመለሱ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ዛሬ ጠዋት ወደ ትምህርት ሚኒስቴር በማቅናት ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
ይሁን እንጂ "ምንም አይነት ምላሽ ማግኘት እንዳልቻሉ" የተማሪዎቹ ተወካዮች ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ገልጸዋል።
በመቀጠልም በቅርቡ በትምህርት ሚኒስቴር ስር ወደተጠቃለለው የቀድሞው ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በማምራት መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።
የተማሪዎች ጉዳይ ዳይሬክተር የሆኑት ኢዶሳ ተርፋሳ (ዶ/ር) አራት የተማሪዎች እና የወላጆች ተወካዮችን አነጋግረዋል።
"ሚኒስቴሩ ከትግራይ ክልል የተመለሱ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጉዳይ ቀዳሚ አጀንዳ አድርጎ እየሰራበት እንደሚገኝ" ዳይሬክተሩ ለተወካዮቹ ገልጸዋል።
"ተማሪዎቹ በቀጣይ 2 ሳምንታት ውስጥ መፍትሄ እንደሚያገኙም " ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
በትግራይ ክልል ከሚገኙ አራት ዩኒቨርሲቲዎች ከ10 ሺህ በላይ ተማሪዎች በነሐሴ መጀመሪያ ተጠቃለው የወጡ ሲሆን ተማሪዎቹ ትምህርታቸውን ካቋረጡ ሁለት ወር አልፏቸዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጉዳዮች በቲክቫህ ዩኒቨርሲቱ በኩል ተከታተሉ።
በቲክቫህ ኢትዮጵያ
" ተማሪዎቹ በቀጣይ 2 ሳምንታት ውስጥ መፍትሄ ያገኛሉ " - ኢዶሳ ተርፋሳ (ዶ/ር)
ከ150 በላይ ከትግራይ ክልል የተመለሱ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ዛሬ ጠዋት ወደ ትምህርት ሚኒስቴር በማቅናት ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
ይሁን እንጂ "ምንም አይነት ምላሽ ማግኘት እንዳልቻሉ" የተማሪዎቹ ተወካዮች ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ገልጸዋል።
በመቀጠልም በቅርቡ በትምህርት ሚኒስቴር ስር ወደተጠቃለለው የቀድሞው ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በማምራት መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።
የተማሪዎች ጉዳይ ዳይሬክተር የሆኑት ኢዶሳ ተርፋሳ (ዶ/ር) አራት የተማሪዎች እና የወላጆች ተወካዮችን አነጋግረዋል።
"ሚኒስቴሩ ከትግራይ ክልል የተመለሱ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጉዳይ ቀዳሚ አጀንዳ አድርጎ እየሰራበት እንደሚገኝ" ዳይሬክተሩ ለተወካዮቹ ገልጸዋል።
"ተማሪዎቹ በቀጣይ 2 ሳምንታት ውስጥ መፍትሄ እንደሚያገኙም " ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
በትግራይ ክልል ከሚገኙ አራት ዩኒቨርሲቲዎች ከ10 ሺህ በላይ ተማሪዎች በነሐሴ መጀመሪያ ተጠቃለው የወጡ ሲሆን ተማሪዎቹ ትምህርታቸውን ካቋረጡ ሁለት ወር አልፏቸዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጉዳዮች በቲክቫህ ዩኒቨርሲቱ በኩል ተከታተሉ።
በቲክቫህ ኢትዮጵያ
#የዩኒቨርሲቲ_መምህራን !
በዩኒቨርሲቲ መምህራን ማህበራት በኩል የቀረቡ ጥያቄዎች ፦
• መንግሥትን የደመወዝ ጭማሪ እና የዕርከን ዕድገት እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
• ለዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ እና ቴክኒካል ረዳቶች የተሰራውን አዲሱን የስራ ደረጃ ማሻሻያ JEG በተመለከተ ቅሬታ አላቸው።
• የመምህራን የቤት አበልን በተመለከተ በፍጥነት አሁን ያለው የቤት ኪራይ ዋጋ ከግምት አስገብቶ ተሻሽሎ ተግባራዊ እንዲደረገ ጠይቀዋል።
• በመንግስት የተደረገው የደረጃ ማሻሻያ ረጅም ጊዜ በዩንቨርሲቲ ያስተማሩ መምህራንን ልምድ ያላገናዘበ በመሆኑና በመምህራን መካከል በቀጣይ ፍትሀዊ የደምወዝ ልዩነት እንዲኖር ስለማያስችል የደረጃ ማሻሻየው የመምህራንን ልምድ እና ማዕረግ ያገናዘበ እንዲሆን ጠይቀዋል።
• የረዳት ፕሮፌሰር የአካዳሚክ ማዕረግ ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታ የ3ኛ ዲግሪ መደረጉን በተመለከተ ያለን ቅሬታ አላቸው።
• የአካዳሚክ ቴክኒክ ረዳቶች ዝቅተኛው ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ የመጀመሪያ ዲግሪ መሆኑ ላይ አቤቱታ አላቸው።
• የቺፍ ቴክኒካል ረዳት II የትምህርት ደረጃን ፒ ኤችዲ ዲግሪ መሆኑም ላይ አቤቱታ አላቸው።
ጥያቄዎቻችን መልስ ይሰጣቸው እያሉ የሚገኙት መምህራኑ ይህ ካልሆነ እስከ ስራ የማቆም አድማ መምታት ድረስ ዕርምጃ እንደሚወስዱ ገልፀዋል።
👉 ትምህርት ሚኒስቴር ለሪፖርተር ፥ " ጥያቄ እንዳለ እናውቃለን። ነገር ግን አሁን ላይ ለውጦች ለማምጣት ጥናት እየተካሄደ ነው። ከዚህ ባለፈ የምንለው ነገር የለም። የደመወዝ ጉዳይ የትምህርት ሚኒስቴር ብቻ አይደለም የሲቪል ሰርቪስ ጉዳይም ነው "
ያንብቡ : telegra.ph/ETH-08-07-2
via #tikvahethiopia
በዩኒቨርሲቲ መምህራን ማህበራት በኩል የቀረቡ ጥያቄዎች ፦
• መንግሥትን የደመወዝ ጭማሪ እና የዕርከን ዕድገት እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
• ለዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ እና ቴክኒካል ረዳቶች የተሰራውን አዲሱን የስራ ደረጃ ማሻሻያ JEG በተመለከተ ቅሬታ አላቸው።
• የመምህራን የቤት አበልን በተመለከተ በፍጥነት አሁን ያለው የቤት ኪራይ ዋጋ ከግምት አስገብቶ ተሻሽሎ ተግባራዊ እንዲደረገ ጠይቀዋል።
• በመንግስት የተደረገው የደረጃ ማሻሻያ ረጅም ጊዜ በዩንቨርሲቲ ያስተማሩ መምህራንን ልምድ ያላገናዘበ በመሆኑና በመምህራን መካከል በቀጣይ ፍትሀዊ የደምወዝ ልዩነት እንዲኖር ስለማያስችል የደረጃ ማሻሻየው የመምህራንን ልምድ እና ማዕረግ ያገናዘበ እንዲሆን ጠይቀዋል።
• የረዳት ፕሮፌሰር የአካዳሚክ ማዕረግ ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታ የ3ኛ ዲግሪ መደረጉን በተመለከተ ያለን ቅሬታ አላቸው።
• የአካዳሚክ ቴክኒክ ረዳቶች ዝቅተኛው ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ የመጀመሪያ ዲግሪ መሆኑ ላይ አቤቱታ አላቸው።
• የቺፍ ቴክኒካል ረዳት II የትምህርት ደረጃን ፒ ኤችዲ ዲግሪ መሆኑም ላይ አቤቱታ አላቸው።
ጥያቄዎቻችን መልስ ይሰጣቸው እያሉ የሚገኙት መምህራኑ ይህ ካልሆነ እስከ ስራ የማቆም አድማ መምታት ድረስ ዕርምጃ እንደሚወስዱ ገልፀዋል።
👉 ትምህርት ሚኒስቴር ለሪፖርተር ፥ " ጥያቄ እንዳለ እናውቃለን። ነገር ግን አሁን ላይ ለውጦች ለማምጣት ጥናት እየተካሄደ ነው። ከዚህ ባለፈ የምንለው ነገር የለም። የደመወዝ ጉዳይ የትምህርት ሚኒስቴር ብቻ አይደለም የሲቪል ሰርቪስ ጉዳይም ነው "
ያንብቡ : telegra.ph/ETH-08-07-2
via #tikvahethiopia