አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
በሰባት ዳኞች የተለወጡ የሰበር ውሳኔዎች
≈≈≈
በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 26 ስር እንደተደነገገው አምስት ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት የተሰጠን ትርጉም በተለያዩ ምክንያቶች ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ከሰባት ያላነሱ ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት እንዲታይ እንደሚደረግ እና በዚህ መልኩ የሚሰጠው የህግ ትርጉም ውሳኔው ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በማናቸውም ደረጃ ለሚገኝ የፌደራል ወይም የክልል ፍርድ ቤት አስገዳጅ እንደሚሆን ተመልክቷል፡፡

በዚህ መሰረት ባሳለፍነው በጀት አመት ከሰባት ያላነሱ ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት ውሳኔ የተሰጠባቸውን ጉዳዮች አጭር መግለጫ እንደሚከተለው አቅርበናል፡፡ የውሳኔዎቹን ሙሉ ግልባጭ በፍርድ ቤቱ ዌብሳይት https://www.fsc.gov.et/ ላይ ማግኘት ይችላሉ፡፡

መልካም ንባብ
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ኮሚዩኒኬሽንና ስትራቴጂያዊ አጋርነት ዳይሬክቶሬት
https://www.alehig.com
ዋቢን እናስተዋውቅዎ!

ዋቢ የህግ ሙያን ለማዘመን፣የዜጎችን የህግ ግንዛቤ ለማሳደግ እንዲሁም የህግ አገልግሎቶችን ለማመቻቸት ቁልፍ ሚና የሚጫወት ድህረ ገፅ ነው።


ዋቢ የሚሰጣቸዉ አገልግሎቶች

- የሰበር ውሳኔዎች፣ አዋጆች፣ መመሪያዎች፣ ስምምነቶች እና የመሳሰሉትን የህግ ሰነዶች ያካተተ ሰፊ የህግ ላይብረሪ
- ⁠የተረጋገጡ ጠበቆችን በነጻ ተደራሽ የሚያደርግ የጠበቆች ዝርዝር
- ⁠የተለያዩ የህግ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ብሎጎች
- ⁠የህግ ትርጓሜዎችን የያዘ የህግ መዝገበ ቃላት
- ⁠ኦንላይን የህግ ምክር

ዋቢን ይጎብኙ!
Wabilaws.com

ስለ ዋቢ የበለጠ ለማወቅ የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችን ይከታተሉ!

Facebook:
https://www.facebook.com/profile.php?id=61562959684020
Instagram:
https://www.instagram.com/wabi_laws?igsh=aWR0M3ZqMWZnemcx&utm_source=qr
LinkedIn:
https://www.linkedin.com/company/wabilaws/
Telegram:
https://t.me/WABI_laws
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ቼክና ዋስትና
በ፦ዮሴፍ አእምሮ (ጠበቃና የሕግ አማካሪ)

በኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች ቼክን በተመለከተ በሚደረጉ ክርክሮችም፣ ቼክ ለባንክ እንደቀረበ የሚከፈልበት የንግድ ወረቀት እንደሆነ እና ለሌላ አገልግሎት እንደማይውል መግባባት አለ፡፡ ይህ አቋም ግን አስገዳጅ የህግ ትርጉም የመስጠት ሥልጣን ባለው የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የተለወጠ ይመስላል፡፡ የዚህ ፅሑፍ ዓላማም በቼክ ባህሪ እና በፍርድ ቤቱ ውሳኔ ላይ ምልከታ ለማድረግ ነው።

ጸሐፊው በጽሑፉ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በቼክ ላይ የሰጠውን ውሳኔ ይተቻል።

#cheque #abyssinialawblog

https://www.abyssinialaw.com/blog/cheque-and-guarantee-in-ethiopia
የፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት የኦሎምፒክ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴን አገደ

መስከረም 8 2017 ዓ.ም በመዝገብ ቁጥር 333122 የዋለው ችሎት በይግባኝ ባዮች በእነ አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገ/ስላሴ (4 ሰዎች) እና መልስ ሰጪ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ (5 ሰዎች) ጉዳይ የተመለከተው ፍርድ ቤቱ ይግባኝ ባዮች በዋናነት ያነሱት

- ግንቦት 5 2016 እና ሰኔ 4 2016 የተከናወኑ ህገወጥ የጠቅላላ ጉባኤ እና የስራ አስፈፃሚ ምርጫ እንዲታገድ

- የህዝብ እና የሀገር ሀብት እንዳይባክን ከደመወዝ ክፍያ ውጪ የባንክ አካውንት እንዲታገድ ጠይቀዋል

የይግባኝ መነሻቸውን ፍርድ ቤቱ የመረመረ ሲሆን አመልካቾችና ጠበቆች በሰጡት ምልሽ በዋናነት ህግና ስርዓት ተከብሮ ተቋሙን የመታደግ አላማና ወደነበረበት ከፍታ ለመመለስ ከመሻት የመነጨ ፍላጎት እና ቁጭት እንጂ የጥቅምም ሆነ የስልጣን ፍላጎት እንደሌላቸው ለፍርድ ቤት አስረድተዋል፡፡

ከስራ አስፈፃሚዎች ነውጠኝነትና ለስርዓትና ለህግ ያለመገዛት አዝማሚያ በስራ ማስኬጃ ሰበብ ብክነት እንዳይኖር እንዲሁም በሪፎርም በሚል ምክንያት የታቀዱ ብክነቶች ስለመኖራቸው መረጃ ስላለን ፍርድ ቤቱ አካውንቱን እንዲያግድ ያቀረቡትን ጥያቄ ተቀብሎ ትእዛዝ ለባንኮችና ለዋና መስሪያ ቤቱ የእግድ ትዕዛዝ ተላልፏል፡፡

ሌላኛው ትእዛዝ ለኢ.ፌ.ድ.ሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በቀን 04/10/2016 ዓ.ም የተደረገው ምርጫ የታገደ መሆኑን እንዲያውቁና እግዱን እንዲፈፅሙም ታዟል፡፡
የመልስ ሰጪዎችን ምላሽ ለመስማት ለመስከረም20 ፍርድቤቱ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
ኢትዮ-መረ
👉Telegram👈
https://t.me/AleHig

👉Telegram_Group👈
https://t.me/AleHig_Group


official website
https://www.alehig.com
ቅፅ_26_የፌ_ጠ_ፍ_ቤት_ሠበር_ሰሚ_ችሎት_ውሳኔዎች.pdf
5.2 MB
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎች ቅጽ 26 ታትሞ ወጥቷል፡፡
*
መጻሐፉን
አራት ኪሎ በሚገኘው የብርሃንና ሰላም ዋና መ/ቤት፣ ፒያሳ ከቅዱስ ጊዬርጊስ ቤተክርስቲያን ወደ አፍንጮ በር በሚወስደው መንገድ፣ በልደታ ከፍተኛ ፍ/ቤት በሚገኙት የብርሃንና ሰላም የሽያጭ መደብሮች እንዲሁም በሌሎች መጻሕፍት መደብሮች ያገኛሉ፡፡

https://www.alehig.com/%e1%8b%a8%e1%8d%8c%e1%8b%b0%e1%88%ab%e1%88%8d-%e1%8c%a0%e1%89%85%e1%88%8b%e1%8b%ad-%e1%8d%8d%e1%88%ad%e1%8b%b5-%e1%89%a4%e1%89%b5-%e1%88%b0%e1%89%a0%e1%88%ad-%e1%88%b0%e1%88%9a-%e1%89%bd%e1%88%8e/
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎች ቅጽ 26 ታትሞ ወጣ::

https://t.me/AleHig