አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
ጥቅምት 30 ቀን 2015 ዓ.ም
ሰ/መ/ቁ. 226596
የኢንሹራንስ ዉልን መነሻ ያደረገ ክርክር ሲሆን ከሳሻ በምርጫዉ የኢንሹራንስ ኩባኒያዉ በሚገኝበት ዋና መስሪያ አካባቢ ስልጣን ላለዉ ፍ/ቤት ክስ ማቅረብ የሚችል በመሆኑ ምንም እንኳ ለክሱ መነሻ የሆነዉ አደጋ የተከሰተዉ ከአዲስ አበባ ውጭ በሌላ ክልል ዉስጥ ቢሆንም፣ የተክሳሽ ድርጅት ዋና መስሪያ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች በሚያስችሉበት በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኝ ከመሆኑ አንፃር ሲታይ ከሳሽ በእራሱ ምርጫ ክሱን ለፌዴራል ፍርድ ቤት ሊያቀርብ ይችላል። ፌዴራል ፍርድ ቤቶችም ክሱን ሰምቶ ለመወሰን የአካባቢ የዳኝነት ስልጣን አለው።
26 ክሶችን ያልተረታው ዳኛ በ27ኛው  ራሱ ተከሰሰ 😳
         
በኬንያ ምንም አይነት የህግ ትምህርተ ሳይወስድ  በሐሰተኛ ትምህርት ማስረጃ  ጠበቃ ሆኖ ሲሰራ የነበረ አንድ ግለሰብ በፖሊስ መያዙ ተዘግቧል።

ግለሰቡ ለ26 ክሶች ጠበቃ ሆኖ ቀርቦ ሁሉንም በአሸናፊነት ፋይል አዘግቷል።ነገር ግን የህግ ትምህርት  በዲፕሎማም ሆነ በዲግሪ ደረጃ አለመማሩን  የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ሰሞኑን ዘግበዋል። አሁን ላይ 27ኛው  ክስ  የራሱ ሆኖ ቀርቦለታል😳

Via: DW

Ephrem H. From woldia university school of law

ለሌሎች  ሼር ያድርጉት፣ ያጋሩት ይማሩበታል ያተርፉበታል
#አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
#ሼር #Share

#Telegram #channel:
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties

#Telegram #Group:
https://t.me/AleHig
https://t.me/AleHig
https://t.me/AleHig
ችግርን_በሰነድ
አንድ የህግ ባለሙያ በባቡር እየተጓዘ ሳለ
አንድ በጣም ቆንጆ የሆነች ልጅ መጥታ ፊት ለፊቱ ከሚገኘው ወንበር ላይ ተቀመጠች።
በዚህም የህግ ባለሙያው ደስ አለው። ቀና ብሎ ሲመለከታት አይን ለአይን ተያዩ ከዛም ፈገግ አለች።
አሁን ደግሞ በይበልጥ ደስ አለው። ትንሽ ቆይታ አጠገቡ ሄዳ ተቀመጠች። በዚህን ጊዜ እጅግ በጣም ደስ አለው።
ትንሽ ቆየችና ወደ ጆሮው ጠጋ ብላ በሹክሹክታ "ያለህን ገንዘብ; የATM ካርድህን ከነፓስ ዎርዱ እና የሞባይል ቀፎህን አሁኑኑ ካልሰጠኸኝ ስትጎነትለኝ እንደ ነበረና ፆታዊ ትንኮሳ እንደደረሰብኝ እዚህ ባቡር ውስጥ ላሉት ሁሉ በመንገር እጮኃለሁ።" አለችው።
የህግ ባለሙያው በቸልተኝነት ቀና ብሎ ተመለከታትና ከቦርሳው ውስጥ ወረቀትና እስክሪብቶ አውጥቶ እንዲህ ብሎ ፃፈላት "ይቅርታ መናገርና መስማት የተሳነኝ ነኝ። እባክሽን ማለት የፈለግሽውን ሁሉ እዚህ ወረቀት ላይ ፃፊልኝ።"
ልጅቷም ቀደም ብላ ስትነግረው የነበረውን ሁሉ ጽፋ ሰጠችው።
የህግ ባለሙያው ወረቀቱን ተቀብሏት በጥሩ ሁኔታ አጥፎ ኪሱ ከከተተው በኋላ ከተቀመጠበት ተነስቶ ጎርነን ባለ ድምጽ ምን ቢላት ጥሩ ነው "አሁን እንደፈለግሽ መጮህ ትቺያለሽ።"

የታሪኩ ምግባር: ሰነድን በአግባቡ መያዝ ምን ግዜም አስፈላጊ ነው።
ለሌሎች  ሼር ያድርጉት፣ ያጋሩት ይማሩበታል ያተርፉበታል

("ዮኒ እንደተረጎመው"]
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
#አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
#ሼር #Share

#Telegram #channel:

https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties

#Telegram #Group:
https://t.me/AleHig
https://t.me/AleHig
https://t.me/
ማስታወቂያ
።።።።።።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ በዕጩ ዓቃቤ ሕግነት አወዳድሮ ለመቅጠር በአዲስ ዘመን ጋዜጣ እሁድ ጥቅምት 4 ቀን 2016 ዓ.ም እትም ማውጣት ይታወቃል።
በመሆኑም ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ከጥቅምት 5 ቀን ጀምሮ ባሉ 15 የስራ ቀናት ውስጥ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
#ሼር #Share

#Telegram #channel:

https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties

#Telegram #Group:
https://t.me/AleHig
https://t.me/AleHig
https://t.me/
#United Insurance Company S.C#

▪️1- Underwriting Officer II
▪️2 - Senior Attorney
▪️3  - Documentation/Filing Clerk
▪️4 - Junior Attorney
▪️5 - Attorney II
▪️6 -  Head-Legal Service
▪️Find More Details here
          💧💧💧💧💧
https://elelanajobs.com/job/united-insurance-s-c-oct-16-23/

▪️Deadline: October 20/2023
ስልጣን ባለው አካል ፊት መረጋገጥና መመዝገብ ስላለባቸው ውሎች

ሰዎች በማኅበራዊ ህይወት ውስጥ ሲኖሩ በግብይ መልክ ያላቸውን ይሰጣሉ የሌላቸውን ይቀበላሉ፡፡ በዚህም የተለያዩ ህጋዊ ልውውጦችን ያካሂዳሉ፡፡ በመሆኑም ሂደቱ አስተማማኝ እንዲሆን፣ በሀብትና ንብረቶቻቸው ላይ ያሏቸው መብቶች ዋስትና እንዲያገኙ የልውውጡን ሥርዓት የሚገዛ ሕግ ያስፈልጋል፡፡ ከነዚህም ውስጥ ውል አንዱ ነው፡፡ ውሎች በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1731 መሠረት በሕጉ አግባብ የተቋቋሙ ውሎች ባቋቋሟቸው ሰዎች ላይ ሕግ ናቸው፡፡ ይህም ለሕግና ለሞራል እስካልተቃረነ ድረስ በተዋዋይ ወገኖች መካከል ጸንቶ የሚቆይ መሆኑን ያሳየናል፡፡ ከነዚህ ውሎች መካከል ሕግ ባለ ጊዜ እና ተዋዋይ ወገኖች ሲፍቀዱ በጽሁፍ እና ሥልጣን ባለው አካል ፊት መደረግ ያለባቸውና መመዝገብ ያለባቸው ውሎች ብዙ ናቸው፡፡ በዚህ አጭር ጽሁፍ የውሎች ምዝገባ ሥርዓት አሥፈላጊነትና ጠቀሜታ፣ መረጋገጥና መመዝገብ ስለሚገባቸው ሰነዶች፣ ውሎችን የመመዝገብ ሥልጣን የተሰጣቸው የመንግስት አካላት እና የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን የሚመለከቱ ውሎችን አረጋግጦ ስለ መመዝገብ የሚሉትን እንመለከታለን፡፡

የውሎች ምዝገባ ሥርዓት አሥፈላጊነትና ጠቀሜታ
የውሎች ምዝገባ አስፈላገነት ከማየታችን በፊት ስለ ውል (ሰነድ) ትርጉም ማየቱ ተገቢ ነው፡፡ "ሰነድ መመዝገብ" ማለት አንድን ሰነድ ለዚሁ በተዘጋጀ መዝገብ መለያ ቁጥር በመስጠት መመዝገብና ማስቀመጥ ወይም በሕግ መሠረት በሰነድ አረጋጋጭና መዝጋቢ ተቋም ዘንድ እንዲቀመጥ የተባለ ሰነድን ተቀብሎ መመዝገብና ማስቀመጥ ነው በማለት የሰነዶች ማረጋገጥና ምዝገባን ለመደንገግ የወጣው አዋጅ ቁጥር 922/2008 አንቀጽ (2) ንዑስ አንቀጽ (3) ደንግጎት እናገኘዋለን፡፡

ውሎች በጽሁፍ የሚደረጉት አንድም አንዳንድ በባህሪያቸው ለየት ያሉ የውል ዓይነቶች የግድ በጽሁፍ መደረግ አለባቸው የሚሉ አዛዥ ደንቦች በሚኖሩበት ጊዜ አለያም ተዋዋዮቹ ራሳቸው ውላቸውን በጽሁፍ ለማድረግ በሚስማሙበት ጊዜ ነው፡፡ አንዳንድ ልዩነቶች እንዳሉ ሆነው ሁሉም ዓይነት የጽሁፍ ሰነዶች የሚጋሩት የውል ባህርይ በፍትሐብሔር ህግ ቁጥር 2005 የተመለከተውና የጽሁፍ ሰነዶች በላያቸው ላይ ስለ ሰፈረው ፍሬ ነገር በተዋዋዮቹ መሀከል ሙሉ እምነት የሚጣልባቸው በቂ ማስረጃዎች ናቸው ይላል፡፡ የዚህ ደንብ ዝርዝር የአፈጻጸም ሥርዓቶችና ልዩ ሁኔታዎች በዚሁ ሕግ ከቁጥር 2006 እስከ 2019 በተመለከቱት ደንቦች ውስጥ የሚገኙ ናቸው፡፡ ሌላው ልብ ሊባል የሚገባው ጉዳይ ውል ለማዋዋል ሥልጣን ባለው አካል ፊት (በባለሥልጣን ፊት) የተደረገ (authentic deed) በግል ከተደረጉ ጽሁፎች (non-authentic deeds or private acts) በይዘት፤ በቅርጽ፤ ይልቁንም ተአማኒነቱና ህጋዊነቱ የበለጠ አስተማማኝ ነው፡፡ መንግስት በአንድ በኩል በእርሱና በዜጎቹ መካከል ያለውን ግንኙነት በሌላ በኩል ደግሞ ዜጎች የግለሰቦችን እርስ በእርሳቸው የሚያደርጓቸው ግንኙነቶች የህግ አግባብ የተከተለና ሥርዓት ባለው መልኩ እንዲመሩ፣ ለእነዚህ ግኑኝነቶች ህጋዊ ጥበቃና ዋስትና መስጠት ካለው ሀላፊነት አንፃር የሚመነጭ በተለይም ለፍትህ ሥርዓቱ አስተዳደር እና ለሕግ የበላይነት መረጋገጥ የበኩሉን እገዛ ያደርጋል፡፡

የውሎች ምዝገባ ሥርዓት ወንጀል ከመከላከልና የማጭበርበር ተግበራትን በመከላከል ረገድም አይነተኛ አስተዋጽኦ አለው፡፡ የውሎች ምዝገባ የሚካሄዱት የንግድም ሆነ ሌሎች ተግባራትን (transactions) ሥርዓት ባለው መልኩ እንዲካሄድ የተዋዋይ ወገኖች ማንነት በማረጋገጥ ተዋዋዮች በሚዋዋሉት ተግባር የተሟላ ግንዘቤ እንዲኖራቸውና ውጤቱን አውቀውና ፈቅደው እንዲገቡ በማስቻል፣ ሲፈርሙ እርግጠኛ ሁነው እንዲፈርሙ በማድረግ አመኔታ ያለው የንግድና ሌላም ህጋዊ ተግባራት እንዲካሄዱ ያግዛል፡፡ ስለዚህ የውሎች ሥልጣን ባለው አካል በመመዝገብ ሂደት ማጭበርበር (forgery)፣ የማይመለከተው በማሳሳት (misrepresentation)፣ ማስገደድን ለማስወገድ እና ግድፈቶችን (omission) ለመከላከል ውጤታማ እገዛ አለው፡፡ ስለዚህ የውሎች ምዝገባ ሥርዓት በሚከተሉት ሁኔታዎች የንብረት ማጭበርበርን የመመዝገብ ሥልጣን ባለው አካል ፊት በመገኘትና በመፈፀም ዜጋው ያልሆኑ ተግባራትን እንዳይፈጽም ይከላከላል፡፡ በዚህም እጅግ ወሳኝ የሆኑ ቀጣይ ዋስትናዎችንም በንብረት ማስተላለፉ ሂደት ያካሄዳል፡፡

1. በአካል መቅረብን (personal appearance) ህጎችና አሰራሮች ተዋዋይ ወገኖች ንብረትን ሲያስተላልፉ በአዋዋዩ ፊት ቀርበው ፈቃዳቸውን ማረጋገጥ አለባቸው፡፡
አረጋጋጩ ፊት ያልቀረበና ያልተፈረመ ፊርማ ተቀባይነት የለውም፡፡ በስሚስሚ (Hearsay) ማረጋገጥ የለበትም፡፡ ቀደም ሲል አንደኛው ወገን ፈርሟል በሚልም የሚደረግ ማዋዋል አይኖርም፡፡ በዚህም የአረጋጋጩ ሁሉም ተግባራት ወይም አገልግሎት ሰነዶችን የሚፈርሙ ሁሉም ወገኖች በአካል በመቅረባቸው ላይ የተመሰረተ ነው፡፡

2. ማንነትን መለየት (identification) ፈራሚው በአረጋጋጩ ፊት በአካል ከቀረበ በኋላ አረጋጋጩ የፈራሚው ግለሰብን ማንነት በጥንቃቄ ያጣራል፡፡ የፈራሚው ማንነት ማረጋገጥ ፈራሚው አስመሳይ አለመሆኑንና ታማኝ ባልሆነ ሰነድ እንዳያጭበረብር ዋስትና ነው፡፡

3. መሰረታዊ ግንዛቤ መፍጠርና የኃይል አለመኖር ማረጋገጥ (basic awareness and absence of duress):: የፈራሚዎችን ማንነት በማረጋገጥ ሂደት አረጋጋጩ ፈራሚዎች ስለ ጉዳዩ ተጠንቅቀውና ዕውቅና ኖሯቸው ያለምንም ማስገደድ ወይም ፍርሃት እየፈረሙ ለመሆናቸው ይታዘባል፣ የረጋግጣል፣ ጥርጣሬ እያለውና ተዋዋዮች አውቀውና በነፃ ፍቃዳቸው የገቡበት ተግባር መሆኑን በጥንቃቄ ያረጋግጣሉ፡፡

4. ሰነዶችን መመዘገብ (paper trail) አረጋጋጮች በህግ ወስደው ከመልካም ልምድ (best practice) መሰረት እያንዳንዱ የሚያረጋግጡት ሰነድ መመዝገብ ወይም ሪከረድ ማድረግ ይጠበቀባቸዋል፡፡ ይህም ሰነድ የህግ መዝገብ ስለሚሆን የማጭበርበር ተግባር ወይም የማጭበርበር ወንጀል በሚኖር ጊዜ ለዓቃቢ ህግ አይነተኛ ማስረጃ ይሆናል፡፡

5. የተሟላ ሰነዶች መቅረብ (complete documents) አረጋጋጮች ሰነዶች የተሟሉ መሆናቸውና በባዶ ሰነዶች (blanck cheque) እንዳያረጋግጡ ሁሉንም ሰነዶችና ገጾችን መመርመር ማጣራት ይኖርባቸዋል፡፡

የንግድ እንቅስቃሴ ከተጀመረበት ዘመን ጀምሮ የማጭበርበር ወንጀልም አብሮ የነበረ ነውና ይህን ለመቀነስ ወይም ለመከላከል፡-
• የተፃፉ ውሎችን በመመስረት እንዲረጋገጡ ማድረግ፣
• ወሳኝ የሆኑ ውሎችና ተግባራት በተዋዋይ ወገኖች ወይም ፈራሚዎች በዕውቀትና በነፃ ፈቃድ እየተፈፀሙ መሆናቸውን ለማረጋገጥ የውሎች ምዝገባ ሥርዓት ጊዜ የፈቀደው ሂደት መሆኑን መገንዘብ፣
• ቋሚና የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን (Real-estate) መመዝገብ ግልጽ የሆነ ህዝብ ሪከርድ (መዝገብ) ስለሆነ መንግስትና ተዋዋይ ወገኖች የሚተማመኑበት ሰነድ ነው፡፡
ስለዚህ በተዋወይ ወገኖች የሚደረጉ ውሎች፣ ስምምነቶችና ማረጋገጫዎች ለአጭበርባሪዎች የተጋለጡና ተገልጋዩን ለከፍተኛ ችግር ሊዳርጉ የሚችሉ ስለሆነ ማንኛውም ግለሰብ የሚፈልገውን ሰነድ በህግ ሥልጣን በተሰጠው አካል የተረጋገጠና የተመዘገበ ሰነድ ከሆነ ዋስትና ያለው መሆኑን አረጋጋጩም የሚቀርቡለትን ሰነዶች አስፈላጊውን ማጣራት በማድረግ ትክክለኛነታቸውን ማመሳከሪያዎችን በመጠቀም፣ በማረጋገጥና በመመዝገብ እምነት የሚጣልበት ሰነድ እንዲሆንና አጭበርባሪዎችን መከላከል የስፈልጋል፡፡
በአጠቃላይ የውሎች ምዝገባ ስርዓት አስፈላጊነቱና ጠቀሜታው በአጭሩ የሚከተሉት ናቸው፡-
 መንግስትና ዜጎች/ግለሰቦች/የሚያደርጓቸው ግንኙነቶች ህጋዊ ጥበቃና ዋስትና ለመስጠት፣
 ለፍትህ ሥርዓቱ እገዛ ማድረግ፣
 በተከራካሪ ወገኖች በፍርድ ቤቶች ሊፈጠር የሚችል የሙግት መጨናነቅን መቀነስ፣
 ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ማቀላጠፍ፣
 የእያንዳንዱ ዜጋ የዕለት ተዕለት ኑሮ በሕግ እንዲመራ ማድረግ ናቸው።

መመዝገብ ስለሚገባቸው ሰነዶች

መመዝገብ የሚገባቸው ሰነዶች በዋናነት የሰነዶች ማረጋገጥና ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 922/2008 አንቀጽ 9 ላይ የተጠቀሱት ሲሆኑ በአስገዳጅ ሁኔታ መመዝገብ እንዳለበቸው በንዑስ ቁጥር (1) ላይ የተዘረዘሩት ሰነዶች እና በዚህ አዋጅ መሰረት ካልተረጋገጡና ካልተመዘገቡ በስተቀር ህጋዊ ውጤት አይኖራቸውም በማለት
የተደነገጉት፡-

ሀ. አግባብ ባለው ህግ መሰረት መረጋገጥና መመዝገብ ያለባቸው ሰነዶች፣
ለምሳሌ፡- የማይንቀሳቀሱ ንብረቶች የሚመለከቱ ውሎች በጽሁፍ በሚገባ አኳኋን ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው ፊት መሆን አለባቸው፣ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1723፡፡ ስለኑዛዜ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 891 እና ስለ ንግድ ቤት ኪራይ በንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ ቁጥር 980/2008 አንቀጽ 10(1) መሰረት የተመለከቱ ሰነዶችና ውሎች እና የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ፡፡
ለ. የውክልና ሥልጣን መስጫ ወይም መሻሪያ ሰነዶች፣
ሐ. የንግድና ሌሎች ማኅበራት መመስረቻ ጽሁፎች፣ መተዳደሪያ ደንቦች እና ማሻሻያዎቻቸው፣
መ. ባለጉዳዮች እንዲረጋገጡላቸውና እንዲመዘገቡላቸው የሚያቀርቧቸው ሌሎች ሰነዶች ናቸው፡፡

የሽያጭ ውል፣ የመያዣ ውል፣ የስጦታ ውል፣ የብድር ውል፣ የሥራ ቅጥር ውል፣ የእንደራሴነት ውል፣ የውርስ መብት ድርሻ መልቀቅ ውል፣ ከጋብቻ በፊት ንብረት የማስመዝገብ ውል፣ ቃለ መሀላና ማረጋገጫ (Declaration) የመሳሰሉት የተለያዩ የስምምነት ውሎች ሁሉ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ይመዘገባሉ፡፡

ውሎችን የመመዝገብ ሥልጣን የተሰጣቸው የመንግስት አካላት

ውል ለመመዝገብ ሥልጣን በኢትዮጵያ በአዋጅ ቁጥር 922/2008 መሰረት በሌላ ህግ ውሎችን የመመዝገብ ሥልጣን የተሰጣቸው ተቋማት እንደተጠበቀ ሆኖ ውሎችን የመመዝገብ ሥልጣን የተሰጣቸው አካላት የሚከተሉት ናቸው፡-
1. የፌደራሉ ሰነድ የማረጋገጥና የመመዝገብ ሥራ በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ (በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተሞች)፣
2. በክልል መስተዳድሮች ሰነድ የማረጋገጥና የመመዝገብ ሥልጣን የተሰጣቸው አካላት (የክልል ፍትህ ቢሮዎች) ፣
3. የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ በኢትዮጵያ ኢምባሲዎችና ቆንስላ ጽ/ቤቶች እንዲሁም በኢትዮጵያ በሚገኙ የውጭ ሀገር ኢምባሲዎችና ቆንስላ ጽ/ቤቶች የተረጋገጡ ሰነዶች፤ በተቀባዩ ሀገር ሕግ እንዲረጋገጡ የሚፈለጉና እና ወደ ውጭ የሚላኩ ሰነዶችን ያረጋግጣል፣
4. በውጭ ሀገር የኢትዮጵያ ኢምባሲዎችና ቆንስላ ጽ/ቤቶች ወደ ኢትዮጵያ የሚላኩ ሰነዶችን ያረጋግጣሉ፣
5. የመከላከያ ሰራዊት የክፍል ሹሞች በግዳጅ ላይ የሚገኙ የሰራዊቱ አባላት የሚያቀርቡላቸውን ሰነዶች ያረጋግጣሉ፣
6. የፌደራል ማረሚያ ቤት ኃላፊዎች ከታራሚዎች ወይም ከቀጠሮ እስረኞች የሚያቀርቡላቸውን ሰነዶች ያረጋግጣሉ፣
7. የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የክፍል ሹሞች በግዳጅ ላይ ከሚገኙ የፌደራል የፖሊስ አባላት የሚያቀርቡላቸውን ሰነዶች ያረጋግጣሉ፡፡

የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን የሚመለከቱ ውሎችን አረጋግጦ ስለ መመዝገብ ጠቅላላ ሁኔታ
ውል በሁለትና ከዚያ በላይ በሆኑ ተዋዋይ ወገኖች መካከል የሚደረግ በህግ ተቀባይነት ያለው ስምምነት ነው፡፡ ነገር ግን በአንዳንድ ሁኔታዎች ሕጉ ተዋዋይ ወገኖች የተለየ ሂደት እንዲከተሉ ያስገድዳል፡፡ ከእነዚህ ልዩ ሁኔታዎች ውስጥ የውሉ ፎርም በጽሁፍ እንዲሆንና ውሉ ሥልጣን በተሰጠው አካል ፊት ማስመዝገብን ያካትታል፡፡

በፍትሐብሔር ህግ ቁጥር 1725 በግልጽ እንደተደነገገው የተለየ ፎርም /በፅሁፍ መሆን ያባቸው/ ሲል የሚያስቀምጣቸው የውል ዓይነቶች አሉ እነዚህም፡-
1. የማይንቀሳቀስ ንብረት የሚመለከቱ ውሎች፣
2. ከአስተዳደር መስሪያ ቤት ጋር የሚደረጉ ውሎች፣
3. ለብዙ ዘመን የሚቆዩ ውሎች ማለትም የዋስትና፣ የኢንሹራንስ እና ሌሎች በህግ በፅሁፍ መሆን አለባቸው የተባሉ ሌሎች ውሎች ናቸው፡፡

እነዚህን በተመለከተ ለሚደረጉ ውሎች ህጋዊነት በህጉ የተቀመጠውን ቅድመ ሁኔታ ማሟላት ግድ ይላል፡፡ የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን አስመልክቶ የተቀመጠን ቅድመ ሁኔታ በተመለከተ በፍትሐብሔር ህግ ቁጥር 1723(1) ተደንግጎ ይገኛል፡፡ ተዋዋይ ወገኖች ይህን ሳይፈጽሙ ቢገኙ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2877 በተጠቀሰው መሰረት ውሉ ፈራሽ ይሆናል፡፡ ለውሉ ህጋዊነት ማግኘት የውሉ ማረጋገጥና መመዝገብ ሌላው አስገዳጅና አስፈላጊው መከናወን ያለበት ተግባር ነው፡፡

በአጠቃላይ የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን በማስመልከት የሚፈጸሙ ውሎች ከሌሎች ውሎች ለየት ባለ ሁኔታ ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት ቀርበው እንዲረጋገጡ ማድረግ በአብዛኞቹ የሕግ ሥርዓቶች የሚፈጸም አካሄድ ነው፡፡ በተጨማሪም ሌሎች ሕግ ሥልጣን ባለው አካል ፊት እንዲመዘገቡ ያላቸውና እንዲሁም ተዋዋይ ወገኖች በራሳቸው ፈቃድ እንዲመዘገቡላቸው የሚፈልጓቸውን ውሎች ከሌሎች አስረጅ ሰነዶች ጋር በማድረግ ውሎችን ለመመዝገብ ሥልጣን ወደ ተሰጠው አካል ቀርበው የሚያደርጉት ውል ህጋዊ ውጤት እንዲኖረው ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡

©~በንቃተ ህግ፣ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ

አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
#ሼር #Share

#Telegram #channel:

https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties

#Telegram #Group:
https://t.me/AleHig
https://t.me/AleHig
https://t.me/
ማስታወቂያ ከኢፌዲሪ ፍትሕ ሚኒስቴር
በእጩ ዐቃቤ ሕግ ደረጃ ሶስት መደብ ተመዝጋቢዎችን አወዳድሮ ለመቅጠር በአዲስ ዘመን ጋዜጣ መስከረም 18/2016 ማውጣቱ ይታወቃል።

መስፈርቱን የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች እስከ ጥቅምት 17/2016 ዓ.ም ድረስ ከዚህ በታች በተቀመጠው ማስታወቂያ ላይ ባለው ፎርም ወይም በተቋሙ ድህረ ገጽ www.eag.gov.et ገብታችሁ አገልግሎታችን በሚለው ሥር በተቀመጠው ለእጩ ዐቃቤ ሕግ ደረጃ ቅጥር ተወዳዳሪዎች መመዝገቢያ ውስጥ ባለው ዝርዝር ማስታወቂያ መሰረት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን በፎርሙ ላይ የምትጭኑትን ማስረጃዎች ለፈተና በምትጠሩበት ጊዜ አንድ ቀን ቀድማችሁ ዋናውንና የማይመለስ ኮፒውን ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን።
https://docs.google.com/forms/d/1zdPhTTswHTdW8jltJNlyxZUgki56HAe0Oz7llsyQtCk/edit?ts=6527f279

©የኢፌዲሪ ፍትሕ ሚኒስቴር

አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
#ሼር #Share

#Telegram #channel:

https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties

#Telegram #Group:
https://t.me/AleHig
https://t.me/AleHig
https://t.me/
ማስታወቂያ
።።።።።።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ በዕጩ ዓቃቤ ሕግነት አወዳድሮ ለመቅጠር በአዲስ ዘመን ጋዜጣ እሁድ ጥቅምት 4 ቀን 2016 ዓ.ም እትም  ማውጣት ይታወቃል።
በመሆኑም ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ከጥቅምት 5 ቀን ጀምሮ ባሉ 15 የስራ ቀናት ውስጥ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
#ሼር #Share

#Telegram #channel:

https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties

#Telegram #Group:
https://t.me/AleHig
https://t.me/AleHig
https://t.me/
በችሎት ላይ ፤ ዳኞች ፊት 7 ዓመት ሙሉ በትዳር አብራው የኖረችውን ሴት አሰቃቂ በሆነ ሁኔታ በጩቤ ወጋግቶ የገደለው ግለሰብ " እድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበታል " ይለናል ተከታዩ ከኢቢሲ የተገኘ መረጃ።

ወንጀሉ የተፈፀመው በቀን 21/11/2015 ዓ.ም ረፋድ 5 ሰዓት ላይ ነው።

የተፈፀመበት ቦታ ደግሞ የምስራቅ ሀረርጌ ዞን የበደኖ ወረዳ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ውስጥ ሲሆን በአቶ ደረጀ ሰይፉ እና በወ/ሮ ትዕግስት ልኬለው መካከል በፍትሐ ብሔር የተወሰነ #የፍቺ_ሂደት እና #የንብረት_ክፍፍል ውሳኔ አፈፃፀም ሂደትን ለመስማት በተጠራ ችሎት ላይ ነው።

በዕለቱ ተከሳሽ አቶ ደረጀ ሰይፉ ሆን ብሎ እና ተዘጋጅቶበት በብብቱ ስር ይዞ በገባው ጩቤ የቀድሞ ባለቤቱ የነበረችውን ትዕግስት ልኬለውን እዛው ፍርድ ቤት ደጋግሞ በመውጋት በአሰቃቂ ሁኔታ #ገድሏታል

አቃቤ ህግ ተከሳሽ ደረጀ በባለቤቱ ላይ ከፈፀመው የግድያ ወንጀል በተጨማሪ ፦
- በወቅቱ በቁጥጥር ስር ሊያውለው የነበረን የፖሊስ አባል ለመግደል ሙከራ አድርጓል፣
- ችሎትን ተዳፍሯል፣
- የመንግስት ስራን አስተጓጉሏል የሚሉ ክሶችን መስርቶበታል።

ተከሳሽ ደረጀ ከባለቤቱ ትዕግስት ጋር ለ7 ዓመታት በትዳር የቆዩ ቢሆንም በመካከላቸው በተፈጠረ አለመግባባት ፍቺ ለመፈፀም በመስማማት የንብረት ክፍፍል ውሳኔ አፈፃፀምን ለመከታተል በችሎቱ በተገኙበት ወቅት ወንጀሉ መፈፀሙን አቃቤ ህግ አስረድቷል።

ዛሬ በዋለው ችሎት ተከሳሽ የመከላከያ ምስክር እና የቅጣት ማቅለያ እንዲያቀርብ በታዘዘው መሰረት የመከላከያ ምስክር ማቅረብ አለመቻሉ ፤ ከ14 ዓመታ በታች የሆኑ የ4 ልጆች አባት እና አስተዳዳሪ መሆኑን በቅጣት ማቅለያነት አቅርቧል።

ፍርድ ቤቱም ግራ ቀኙን ከሰማ በኋላ ፦
- አንደኛ ባለቤቱ ላይ በፈፀመው የግድያ ወንጀል፣
- ሁለተኛ ተከሳሽ ከዚህ ቀደም የወንጀል ሪከርድ ያለበት በመሆኑ
- ሶስተኛ ወንጀሉን የፈፀመው በችሎት ፊት በመሆኑ አቃቤ ህግ ባቀረበው የእድሜ ልክ እስራት እንዲቀጣ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ አስተላልፏል።

ይህንን መረጃ ከተመለከቱ በኃላ የተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ጉዳይ አስደንጋጭ እንደሆነባቸውና ፍርዱ በቂ ነው ብለው እንደማያምኑ ሲገልጹ ተመልክተናል።

- ችሎት ውስጥ እሷ እስልትገደል (ያውም ተደጋግሞ ተወግታ እስክትገደል) ድረስ ፖሊስ ምን ይሰራ ነበር ?
- እሷን እና እሱን አንድ ላይ ካላስቀመጧቸው እንዴት ደርሶ ሊገድላት ይችላል ?
- እዛው ዳኞች ፊት የተፈፀመ ወንጀል ላይ ለመወሰን እስከዛሬ ለምን ቆየ ? የሚሉ ጥያቄዎችን በማንሳት ፍትህ ካለ በዚህ ወንጀል ገዳይ ብቻ ሳይሆን ይህን መከላከል ያልቻሉ ሁሉ ሊጠየቁ ይገባል ፤ ግለሰቡ የሞት ፍርድ እንጂ እስራት አገባውም ነበር የሚሉ አስተያየቶች ተሰጥተው ተመልክተናል። ቅጣቱ ያበሳጫቸውም ብዙ ናቸው።

@tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
በችሎት ላይ ፤ ዳኞች ፊት 7 ዓመት ሙሉ በትዳር አብራው የኖረችውን ሴት አሰቃቂ በሆነ ሁኔታ በጩቤ ወጋግቶ የገደለው ግለሰብ " እድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበታል " ይለናል ተከታዩ ከኢቢሲ የተገኘ መረጃ።

ወንጀሉ የተፈፀመው በቀን 21/11/2015 ዓ.ም ረፋድ 5 ሰዓት ላይ ነው።

የተፈፀመበት ቦታ ደግሞ የምስራቅ ሀረርጌ ዞን የበደኖ ወረዳ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ውስጥ ሲሆን በአቶ ደረጀ ሰይፉ እና በወ/ሮ ትዕግስት ልኬለው መካከል በፍትሐ ብሔር የተወሰነ #የፍቺ_ሂደት እና #የንብረት_ክፍፍል ውሳኔ አፈፃፀም ሂደትን ለመስማት በተጠራ ችሎት ላይ ነው።

በዕለቱ ተከሳሽ አቶ ደረጀ ሰይፉ ሆን ብሎ እና ተዘጋጅቶበት በብብቱ ስር ይዞ በገባው ጩቤ የቀድሞ ባለቤቱ የነበረችውን ትዕግስት ልኬለውን እዛው ፍርድ ቤት ደጋግሞ በመውጋት በአሰቃቂ ሁኔታ #ገድሏታል

አቃቤ ህግ ተከሳሽ ደረጀ በባለቤቱ ላይ ከፈፀመው የግድያ ወንጀል በተጨማሪ ፦
- በወቅቱ በቁጥጥር ስር ሊያውለው የነበረን የፖሊስ አባል ለመግደል ሙከራ አድርጓል፣
- ችሎትን ተዳፍሯል፣
- የመንግስት ስራን አስተጓጉሏል የሚሉ ክሶችን መስርቶበታል።

ተከሳሽ ደረጀ ከባለቤቱ ትዕግስት ጋር ለ7 ዓመታት በትዳር የቆዩ ቢሆንም በመካከላቸው በተፈጠረ አለመግባባት ፍቺ ለመፈፀም በመስማማት የንብረት ክፍፍል ውሳኔ አፈፃፀምን ለመከታተል በችሎቱ በተገኙበት ወቅት ወንጀሉ መፈፀሙን አቃቤ ህግ አስረድቷል።

ዛሬ በዋለው ችሎት ተከሳሽ የመከላከያ ምስክር እና የቅጣት ማቅለያ እንዲያቀርብ በታዘዘው መሰረት የመከላከያ ምስክር ማቅረብ አለመቻሉ ፤ ከ14 ዓመታ በታች የሆኑ የ4 ልጆች አባት እና አስተዳዳሪ መሆኑን በቅጣት ማቅለያነት አቅርቧል።

ፍርድ ቤቱም ግራ ቀኙን ከሰማ በኋላ ፦
- አንደኛ ባለቤቱ ላይ በፈፀመው የግድያ ወንጀል፣
- ሁለተኛ ተከሳሽ ከዚህ ቀደም የወንጀል ሪከርድ ያለበት በመሆኑ
- ሶስተኛ ወንጀሉን የፈፀመው በችሎት ፊት በመሆኑ አቃቤ ህግ ባቀረበው የእድሜ ልክ እስራት እንዲቀጣ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ አስተላልፏል።

ይህንን መረጃ ከተመለከቱ በኃላ የተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ጉዳይ አስደንጋጭ እንደሆነባቸውና ፍርዱ በቂ ነው ብለው እንደማያምኑ ሲገልጹ ተመልክተናል።

- ችሎት ውስጥ እሷ እስልትገደል (ያውም ተደጋግሞ ተወግታ እስክትገደል) ድረስ ፖሊስ ምን ይሰራ ነበር ?
- እሷን እና እሱን አንድ ላይ ካላስቀመጧቸው እንዴት ደርሶ ሊገድላት ይችላል ?
- እዛው ዳኞች ፊት የተፈፀመ ወንጀል ላይ ለመወሰን እስከዛሬ ለምን ቆየ ? የሚሉ ጥያቄዎችን በማንሳት ፍትህ ካለ በዚህ ወንጀል ገዳይ ብቻ ሳይሆን ይህን መከላከል ያልቻሉ ሁሉ ሊጠየቁ ይገባል ፤ ግለሰቡ የሞት ፍርድ እንጂ እስራት አገባውም ነበር የሚሉ አስተያየቶች ተሰጥተው ተመልክተናል። ቅጣቱ ያበሳጫቸውም ብዙ ናቸው።

@tikvahethiopia
#Update

በፎፌክስ ትሬዲንግ ስም የሚያታልሉ ግለሰቦችንና ቡድኖችን በህግ ተጠያቂ ማድረግ እንደሚቻል ተገለፀ።

በፎሬክስ ትሬዲንግ የኦንላይን ስራ ትርፋማ እናደርጋችኋለን" የሚል የፌስቡክና የቴሌግራም ማስታወቂያ በሚያስነግሩ የተደራጁ ቡድኖች የተጭበረበሩ ሰዎችን አስመልክቶ ቲክቫህ ተከታታይ ዘገባ መስራቱ ይታወሳል።

ጉዳዩን አስመልክቶ የሚመለከተውን አካል ያነጋገርን ሲሆን ፥ በዚህ ጉዳይ ወንጀል ተፈፅሞብኛል የሚሉ ግለሰቦች የሚያቀርቡትን ጥቆማና መረጃ ተከትሎ ከህግ አካላት እና ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በመተባበር ጉዳዩን እንደሚያጣሩ የኢትዮጵያ ፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት የህዝብ ግንኙነትና የኮሚኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አቶ እንዳለ አሰፋ ለቲክቫህ ገልፀዋል። 

አቶ እንዳለ በፎሬክስ ትሬዲንግ የማጭበርበር ድርጊት ጉዳይ እስካሁን ጥቆማ ለመስሪያ ቤቱ እንዳልደረሰ የገለፁ ሲሆን "ወንጀል ተፈፅሞብኛል" የሚሉ ሰዎች በአቅራቢያቸው ለሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ወንጀል ምርመራ ክፍል ሪፖርት ማድረግ እንዳለባቸው በማሳሰብ ፥ በፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት መስሪያ ቤት በኩል የሚፈለገው እገዛ ለፖሊስ እንደሚሰጥ አስረድተዋል።

ይህን መሰል የማታለል ድርጊት በህግ እንዴት ይታያል?

ይህን ጉዳይ አስመልክቶ ያናገርናቸው ጠበቃ እና የህግ አማካሪ እንዲሁም በደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ክፍል መምህር የሆኑት አቶ እሱባለው አማረ የወንጀል ድርጊቱ ፈርጀ ብዙ የህግ ተጠያቂነት እንደሚያስከትል ገልፀዋል።

ጠበቃ እና የህግ አማካሪው አቶ እሱባለው ድርጊቱ በንብረት መብት (property right) ላይ ከሚፈፀም ወንጀል ጋር እንደሚያዝ ያስረዱ ሲሆን በዋናነት በንብረት ላይ ሊፈፀም ከሚችሉ ወንጀሎች ተብለው በወንጀል ህጋችን  ከተጠቀሱት መሃከል በ"አታላይነት" ወንጀል እንደሚያስጠይቅ ለቲክቫህ ገልፀዋል።

"አታላይነት" በወንጀል ህጉ ከአንቀፅ 692 ጀምሮ ሽፋን እንደተሰጠው የገለፁት የህግ መምህሩ ፥ "ማታለልን ያካተቱ ወንጀሎች" በሚል ንዑስ ስር ያለ የዚህ ድንጋጌ ንዑስ አንቀፅ 1 "ማንም ሰው የማይገባ ብልፅግና ለራሱ ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ አሳሳች የሆኑ ነገሮችን በመናገር፣ የራሱን ማንነት ወይም ሁኔታ በመሰወር ወይም መግለጽ የሚገባውን ነገር በመደበቅ ወይም የሌላውን ሰው የተሳሳተ እምነት ወይም ግምት በመጠቀም፣ በማድረግም ሆነ ባለማድረግ ሌላውን ሰው አታልሎ የራሱን ወይም የሶስተኛ ወገንን የንብረት ጥቅም የሚጎዳ አድራጎት እንዲፈፀም ያደረገ እንደሆነ የአታላይነት ወንጀል እንደተፈፀመ ያስቀምጣል" ሲሉ አስረድተዋል።

ይህ የወንጀል ድርጊት በቀላል እስራት ወይም
እንደነገሩ ከባድነት ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እስራትና በገንዘብ መቀጮ እንደሚያስቀጣም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት የህዝብ ግንኙነት እና የኮሚኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አቶ እንዳለ አሰፋ በፎሬክስ ስም የማታለል ወንጀል ተፈፅሞብኛል የሚሉ ሰዎች ወይም በጉዳዩ ላይ አጠራጣሪ ነገሮችን የተመለከቱ ግለሰቦች ፖሊስ ጋር ከመሄድ ባሻገር ለተቋሙ በስልክ ቁጥር +251-11-812-8261 ጥቆማ መስጠት እንደሚችሉ በማስረዳት ፥ ከሚመለከተው አካል ጋር በመተባበር ክትትል እንደሚደረግ ገልፀዋል።

በኦላይን የሚፈጸሙ የማጭበርበር ድርጊቶችን ለመጠቆም @tikvahmagbot ይጠቀሙ።

በጉዳዩ ላይ ለመወያየት https://t.me/tikvahforum/22079 ላይ ሀሳቦትን ያካፍሉን።

👋  @TikvahethMagazine
እነዚህ አራት መሠረታዊ የቼክ መገለጫዋች በቼኩ ላይ ከሌሉ ቼኩ ሕጋዊ አይደለምና ጥንቃቄ አድርጉ
..............................................
1ኛ/ቼኩን ተቀብሎ ክፍያ እንዲፈፅም የታዘዘው የባንክ ቤት ስም በግልፅ በቼክ ላይ ሊኖር ይገባል።ይህም ባንክ በህግ የባንክ ቤትን ስራ ለማከናወን ስልጣን የተሰጠው ተቋም ብቻ መሆን ይኖርበታል።በኢትዮጽያ ከሚገኙ ባንኮች ተመሳስሎ የሚፃፋ የባንክ ቤት ስሞች ስለሚኖሩ ቼኩ ላይ የተፃፈው ባንክ በኢትዮጵያ እውቅና ያለውና  ሕጋዊ ፈቃድ አውጥቶ በስራ ላይ የሚገኝ  ባንክ መሆኑን ማረጋገጥ ያስፈልጋል።በህጋዊ መልኩ ታትመው ከወጡት ጋር ተመሳስለው የሚሰሩ ቼክ መሳይ ሃሰተኛ ሰነዶች እየበዙ በመምጣታቸው ይህን በጥንቃቄ መመልከት ያስፈልጋል።በንግድ ሕጉ በግልፅ እንደተደነገገው ሕጋዊ እውቅና ካለው ባንክ ቼኩ ወጪ እስካልተደረገ ለክፍያ ወደ ባንክ ቢቀርብም ገንዘብ ክፍያ ተፈፃሚ አይሆንም።

2ኛ.ለቼክ አውጪው ሊከፈለው የሚገባውን የገንዘብ መጠን በግልፅ ሊፃፍበት ይገባል።  ይህም ሲባል ገንዘቡን ወጪ ለማድረግ ሌሎች መሟላት የሚገባቸውን ቅድመሁኔታዋች ያላመላከተ መሆን ይጠበቅበታል።አንዳንዶች ቼኩን ሲሰጡ ቼኩ ላይ የሚገልፁት ሌሎች ፅሁፎች ቼኩ ተቀባይነት እንዳይኖረው ያደርጋሉ።ለአብነት ያህል ይህ እስኪደረግ ድረስ ክፍያ ተፈፃሚ እንዳይሆን የሚሉ ክልከላዋች እና ሌሎች መሠል ፅሁፎች የቼኩን ሕጋዊነት የሚያሳጡ ስለሚሆኑ በቼኩ ላይ ከባንክ ወጪ የሚደረገው የገንዘብ መጠን ብቻ የተጠቀሰበት ብቻ እንጂ ሊሆን የሚገባው ከዚህ በተጨማሪ እንደቅድመሁኔታ ገንዘቡን ወጪ ለማድረግ የሚቀመጡ መስፈርቶች ቼኩ ዋጋ እንዲያጣ የሚያደርጉ ስለሆኑ በቼኩ ላይ የሚገለፁ ፅሁፎችን በጥንቃቄ መመልከት ያስፈልጋል።

3=ቼኩ የወጣበት ቦታ እና ጊዜ በቼኩ ላይ የተፃፈበት መሆን አለበት ።ቼኩ የወጣበትን ቦታናጊዜ የማይገልፅ ከሆነ ህጋዊ ቼክ አይደለም።
4/ በቼኩ ላይ የተገለፀው ገንዘብ ከመቼ ጀምሮ ወጪ መደረግ እንደሚችል ቀኑን ወሩን እና አመተምህረቱን የተገለፀበት እንዲሁም ገንዘቡ የሚከፈልበትን  የባንክ ቤት ስም ወይም ቦታ የሚገልፅ መሆን አለበት።ይህን ያላሟላ ቼክ ህጋዊ ያልሆነ ሀሰተኛ ቼክ ሲሆን 
ሀሰተኛ ቼክ ማለት ቼክን ለማተም ስልጣን ባለዉ ባንክ ቤት ታትሞ ያልተሰጠ ወይም ታትሞ ከተሰጠዉ ጋር ተመሳስሎ የተሰራ ቼክ መሳይ ሰነድ ነው። 

የወንጀል ተጠያቂነት
----------------------------
ማንም ሰዉ ይህንን ሀሰተኛ ቼክ የሰራ ፣ የተገለገለ ወይም ህጋዊ አስመስሎ ለሶስተኛ ወገን ያስተላለፈ እንደሆነ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የወንጀል ህግ
አንቀፅ 375 ና በተከታዮቹ አንቀፃች እንዲሁም በተደራቢነት በወ.ህ.ቁ 692 መሰረት
በማታለል ወንጀል ተጠያቂ ይሆናል።
Via Lawyer Henok
አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
#ሼር #Share

#Telegram #channel:
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties

#Telegram #Group:
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/AleHig
https://t.me/AleHig
https://t.me/
በፍትሐብሄር ክርክር የሰነድ ማስረጃS ማቅረብ የሚቻለው መቼ ነው??
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆

በአብዛኛው ፍ/ቤቶች የጽሑፍ ማስረጃዎች ከክስ ጋር ወይንም ከመከላካያ መልስ ጋር አብሮ ካልቀረበ መቅረብ አይችልም በሚል ሲከለክሉ ይታያል፡፡ ነገር ግን በሥነ-ሥርዓት ህጋችን ግን ከክስ ማመልከቻ ወይም ከመከላካያ መልስ በኋለ ክስ ከመሰማቱ በፊት ከመዝገቡ ጋር ተያይዞ ያልቀረበ የጽሑፍ ማስጃዎች ካሉ መቅረብ እንደሚችሉ ይደነግጋል፡፡

# ሀ . የፅሑፍ ማስረጃዎች በሙሉ ክርክሩን መስማትና ምስክሮችን መመርመር ከመጀመሩ በፊት ተጠቃለው መግባት አለባቸው፡፡

# ለ . በመጀመሪያ ደረጃ ከሳሹ ከክስ ማመልከቻው ጋር ተከሳሹ ደግሞ ከመከላከያ መልሱ ጋር ይጠቅመናል የሚሉትንና በእጃቸው የሚገኙትን ወይም ሊያቀርቡ የሚችሉትን የጽሑፍ ማስረጃ በሙሉ አያይዘው ማቅረብ አለባቸው (ቁ.223(1)) (ለ) እና 234 (1)፡፡

# ሐ . በሁለተኛ ደረጃ ተከራካሪ ወገኖች ለማቅረብ የሚችሉትንና ይጠቅማናል የሚሉትን ወይም ፍርድ ቤቱ እንዲቀርብ የጠየቀውንና አስቀድመው ፍርድ ቤት ያላቀረቡትን የፅሑፍ ማስረጃ ሁሉ በመጀመሪያው ቀነ ቀጠሮ ማቅረብ አለባቸው
(ቁ. 137 (1))

# መ. ማንኛውም አቤት ባይ ሰነዶችን ከአቤቱታው ጋር በማያያዝ ወይም ከቀነ ቀጠሮው በፊት ወይም በመጀመሪያው ቀነ ቀጠሮ ካላቀረበ በቀር ማስረጃዬ ከፍርድ ቤቱ መዝገብ ጋር ይያያዝልኝ ወይም ለማቅረብ ይፈቀድልኝ በማለት ለማመልከት አይችልም (137(3)፡

# ሠ . መቅረብ የሚገባቸው ማስረጃዎች ከተከራካሪዎች ወገኖች ባንዳኛው
ጉድለት ወይም በቂ ባልሆነ ምክንያት ሳይቀርቡ የቀሩ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ወዲያው ፍርድ ይሰጣል (ቁ. 256(1))፡፡

# ረ . ከላይ በ “መ” እና “ሠ” ሥር የተጠቀሱት አጠቃላይ ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆኖ ከአቤቱታ ጋር ወይም በመጀመሪያ ቀነ ቀጠሮ ያልቀረበ የፅሁፍ
ማስረጃ በሌላ ጊዜ ሊቀርብ የሚችልበት ልዩ ሁኔታዎች (exceptions) አሉ፡፡

እነዚህም፡-
#1. ፍርድ ቤቱ በራሱ አስተያየት ወይም በተከራካሪዎች ወገኖች አመልካችነት
በሌላ ፍ/ቤት ዘንድ የሚገኝ መዝገብ ወይም የጽሑፍ ማስረጃ እንዲቀርብ ማዘዝ
ይችላል (ቁ.148 (11))፡፡

#2. ማስረጃዎቹ ሳይቀርቡ የቀሩት ከባድና በቂ በሆነ ምክንያት መሆኑን ፍርድ ቤቱ ከተረዳ ስለ ክርክሩ አወሳሰንና ማስረጃ ያለመቅረቡ ስላስከተለው ኪሳራ
ተገቢ መስሎ የታየውን ትፅዛዝ በመስጠት ነገሩ የሚሰማበትን ቀነ ቀጠሮ ይወስናል (ቁ. 256 (1)፡፡ (ማስረጃው እንዲቀርብ ማዘዝ ይችላል፡፡)

#3. አስፈላጊ መስሎ ከታየው ፍርድ ቤቱ የክርክሩን ጭብጥ ከመያዙ በፊት በተከራካሪዎች ያልቀረበን የፅሑፍ ማስረጃ በትዕዛዝ አስቀርቦ መመርመር
ይችላል (ቁ. 149 (1) )፡፡

#4. ክርክሩ በሚሰማበት በማናቸውም ግዜ ፍርድ ቤቱ በተከራካሪዎቹ ያልቀረበ
ነገር ግን ለክርክሩ ጠቃሚ የሆነ የፅሑፍ ማስረጃ እንዲቀርብ ለማዘዝ ይችላል
(ቁ.164)፡

#5. ምስክሮችን መስቀለኛ ጥያቄ ለመጠየቅ ወይም ምስክሩ ነገሩን ለማስታወስ እንዲችል የሚቀርብ የጽሑፍ ማስረጃ በመጀመሪያ በይቀርብም ክርክሩ በሚስማበት ጊዜ መቅረብ ይችላል (137 (4))፡፡

👉ኢትዮ ህግ ቻናል
አለ_ህግ #Ale_Hig
#Lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties አለ_ህግ
@Lawsocieties  @Alehig
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

Facebook Page
https://www.facebook.com/lawsocieties/


Telegram Channel
https://t.me/lawsocieties


👇👇👇👇👇👇👇
👉Facebook Page 👈
👆👆👆👆👆👆👆


👇👇👇👇👇👇👇👇
👉Telegram Channel 👈
👆👆👆👆👆👆👆👆