አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.83K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የጋብቻ መፈፀም የሚያስከትለው ውጤት
#ጋብቻ አስፈላጊውን ቅድመ ሁኔታዎችን በማሟላት በሁለት ሰዎች (ባልና ሚስት) መካከል የሚፈጠም ህብረት እንደሆነ ይጠቀሳል፡፡ የሀገራችን ቤተሰብ ህግ ለጋብቻ ትርጉም ያልሰጠ ሲሆን ጋብቻ ለማቋቋም ሊሟሉ የሚገባቸውን ቅድመ ሁኔታዎችን እና ጋብቻ የሚፈፀመው በአንድ ወንድና በአንዲት ሴት መካከል እንደሆነ ያስቀምጣል፡፡

በህግ ፊት የፀና ጋብቻ ለመፈጸም የተለያዩ ቅድመ ሁኔታዎች መሟላት አለባቸው፡፡ በዚህ መሰረት የሁለቱ ሰዎች ፈቃድ መኖር፣ በህጉ የተቀመጠው ዝቅተኛ እድሜ መሟላት፣ የዝድና አለመኖር፣ በጋብቻ ላይ ጋብቻ አለመኖር መሟላት ያለባቸው ቅድመ ሁኔታዎች ናቸው፡፡

ጋብቻ በተለያዩ ሶስት መንገዶች ሊፈጸም ይችላል፡፡
እነዚህም በክብር መዝገብ ሹም ፊት የሚፈፀም፣ የሀይማኖት ጋብቻ እና የባህል ጋብቻ ናቸው፡፡ በእነዚህ መንገዶች የተፈፀመ ጋብቻ ተመሳሳይ ውጤት ያለው ሲሆን በእነዚህ መንገዶች አስፈላጊውን ሁኔታ በማሟላት የተፈጸመ ጋብቻ የሚያስከትለው ውጤቶች እንደሚከተለው ተብራርተዋል፡፡

1. ጋብቻ በተጋቢዎች ግላዊ ግንኙነት ላይ የሚያስከትለው ውጤት

i. አብሮ መኖር
ባልና ሚስት ጋብቻ ከፈፀሙ በኋላ አብረው እንዲኖሩ በህግ ግዴታ ተጥሎባቸዋል፡፡ የመኖሪያ ቦታቸውንም አብረው የሚወስኑ ይሆናል፡፡ ሆኖም ባልና ሚስቱ ለተወሰነ ወይም ላልተወሰነ ጊዜ ተለያይተው ለመኖር መስማማት አይከለከሉም፡፡ ይህ ስምምነት መቀየሩ አግባብ ካልሆነ በስተቀርም ተጋቢዎች ወይም ከሁለት አንዳቸው አስበው ሊቀይሩትም ይችላሉ፡፡ ለምሳሌ የባልና ሚስቱ የሥራ ቦታ ሊለያይ የሚችልበት አጋጣሚ ሲፈጠር ሁለቱም በያሉበት ሆነው ሥራቸውን ለመሥራት ሊስማሙ የሚችሉ ሲሆን አመቺ ሆኖ ካላገኙትም ሀሳባቸውን መቀየር ይችላሉ፡፡

ይህ ብቻ ሳይሆን ተጋቢዎች ጋብቻ ተሳስረው ሲኖሩ ለጤናቸው አደገኛ ካልሆነ በስተቀር ከጋብቻ የሚጠበቀውን መደበኛ የሩካቤ ሥጋ መፈፀምም ይጠበቅባቸዋል፡፡ ይህን የሚቃረን ስምምነት ውጤት አይኖረውም፡፡ በተጨማሪም በማንኛውም ሁኔታ አንዳቸው ለሌላኛው ታማኝ የመሆን ግዴታ አለባቸው፡፡ ይህ ሳይሆን ቀርቶ አንዳቸው ሳይታመኑ የአመንዝራነት ድርጊት ቢፈፅሙ በተበደለው ተጋቢ አቤቱታ አቅራቢነት በእስራት ወይም በመቀጮ ሊያስቀጣ የሚችል የወንጀል ተጠያቂነት የሚያስከትል ነው፡፡

ii. መከባበር፣ መተጋገዝና መደጋገፍ

ባልና ሚስት በትዳር በሚኖሩበት ጊዜ አንዳቸው ሌላኛውን የማገዝና የመደገፍ እንዲሁም ተከባብሮ የመኖር ሀላፊነት ተጥሎባቸዋል፡፡ ይህንን ሀላፊነት በስምምነት ፈፅሞ ሊያስቀሩት እንደማይችሉ በህግ ተደንግጓል፡፡

iii. ቤተሰብን በጋራ መምራት

ጋብቻ በሁለቱ ተጋቢዎች ተወስኖ የማይቀርና ልጆችን የሚፈጥርና የቤተሰብ መሰረት የሚሆን ተቋም ነው፡፡ በዚህም የልጆች አስተዳደግ፣ ትምህርት፣ ጤና ወዘተ የመሳሰሉ ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች በተጋቢዎች እንዲሟሉ ይጠበቃል፡፡ ከዚህ አንፃር ባልና ሚስት እኩል መብት እንዳላቸው በቤተሰብ ህግ ደንግጓል፡፡ በዚህም በማናቸውም ረገድ የቤተሰቡን ደህንነትና ጥቅም ለማስጠበቅ፣ ልጆቻቸው በመልካም ሥነ ምግባር እንዲታነፁ፣ ተገቢ ትምህርት እንዲቀርሙና ሀላፊነት የሚሰማቸው ዜጎች ሆነው እንዲያድጉ ለማድረግ ባልና ሚስቱ መተባበር ይጠበቅባቸዋል፡፡

2. ጋብቻ በንብረት ረገድ የሚያስከትለው ውጤት

ጋብቻ በተጋቢዎች ግላዊ ግንኙነት ላይ ውጤት እንዳለው ሁሉ በንብረት ረገድም የራሱ የሆነ ውጤት የሚያስከትል ነው፡፡ ንብረትን በተመለከተ ጋብቻ የግል እና የጋራ ንብረት ውጤት የሚስከትል ነው፡፡

i. የግል ንብረት ምንነትና አስተዳደር

የግል ንብረት የምንለው ሁለቱ ተጋቢዎች ከጋብቻው በፊት በየግል የነበሯቸው ንብረቶች ወይም ከጋብቻው በኋላ በውርስ ወይም በየግላቸው በስጦታ ያገኟቸው ንብረቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ንብረቶች በጋብቻውም ዘመን የግላቸው ሆነው ይቀጥላሉ፡፡ እነዚህን ንብረቶች ሸጦ የሚገዛው ንብረት የራሱ የሚሆን ሲሆን ይህ የሚሆነው ግን በፍርድ ቤት የግሌ ይባልልኝ ብሎ ሲጠይቅና ሲፀድቅለት ነው፡፡

የግል ንብረት አስተዳደርን በተመለከተ የግል ንብረቱ ባለቤት የሆነው ተጋቢ ሊያዝበት የሚችል ሲሆን ሌላኛው ተጋቢ እንዲያስተዳድረው በጋብቻ ውል ሊስማሙ የሚችሉ ከመሆኑም በላይ ውክልና በመስጠት ሌላኛው ተጋቢ እንዲያስተዳደር ሊያደርግ ይችላል፡፡

ii. የጋራ ንብረት ምንነትና አስተዳደር

የጋራ ንብረትን በተመለከተ የጋራ ንብረት የሚባለው ባልና ሚስት ከተጋቡ በኋላ በግብይት የሚያገኟቸው ንብረቶች፣ ባልና ሚስት በግል ጥረታቸው የሚገኝ ገቢ፣ ከግል እና ከጋራ ንብረታቸው የሚገኟቸው ገቢዎች ሁሉ ናቸው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በስጦታ ወይም በኑዛዜ በጋራ የተሰጧቸው ንብረቶች የጋራ ንብረቶች ናቸው፡፡ እዚህ ላይ መታወቅ ያለበት አንደኛው ተጋቢ የግል ሀብቱ መሆኑን ካላስረዳ በስተቀር በአንደኛው ተጋቢ ስም የተመዘገበ ሀብትም ቢሆን እንኳን የተጋቢዎች የጋራ ሀብት እንደሆነ የህግ ግምት የሚወሰድበት መሆኑ ነው፡፡

በንብረት አስተዳደር ረገድ የጋራ ንብረታቸውን አንደኛው ተጋቢ እንዲያስተዳድረው ካልተስማሙ፣ ችሎታ የለውም በሚል ካልተወሰነ፣ ንብረት የማስተዳደር መብቱ ካልተገፈፈ፣ ወይም በማናቸውም ምክንያት ንብረታቸውን ማስተዳደር የማይችል ሆኖ ካልተገኘ በስተቀር የጋራ ንብረታቸውን በጋራ ያስተዳድራሉ፡፡ ሆኖም በተጠቀሱት ምክንያቶች አንደኛው ተጋቢ ብቻውን ንብረቱን የሚያስተዳድር ከሆነ ለሌላኛው ተጋቢ መረጃ የመስጠት ሃላፊነት አለበት፡፡

በገቢ ረገድ ሁለቱም ተጋቢዎች ገቢያቸውን በየራሳቸው መቀበል የሚችሉ እንዲሁም በግል ወይም በጋራ የባንክ ሂሰብ ከፍተው ማስቀመጥ ይችላሉ፡፡ ይህ ማለት ግን አንደኛው ተጋቢ ሌላኛው ተጋቢ እንዲቀበልለት ስልጣን ለመስጠት የሚከለክለው ነገር የለም፡፡ በየግል የሚያገኙትንም ገቢ ሌላኛው ተገቢ ሲጠይቅ ማሳወቅ ግዴታ አለበት፡፡

ከንብረት በተጨማሪ በጋብቻ ውስጥ እዳ ሊኖር እንደሚችል የሚጠበቅ ነው፡፡ ልክ እንደንብረት ሁሉ እዳም የግል ወይም የጋራ ተብሎ የሚከፈል ነው፡፡ እዳው ለባልና ሚስት እና ለልጆቻቸው የዕለት ኑሮ አስፈላጊ የሆኑ ነገሮችን ለማሟላት ወይም ባል ወይም ሚስት ቀለብ የመስጠት ግዴታቸውን ለመወጣት የተገቡ እዳዎች እንዲሁም ከባልና ሚስት በአንደኛው ወይም በዕዳ ጠያቂው አመልካችነት ለትዳር ጥቅም ስለመሆኑ ፍርድ ቤት የተቀበለው እዳ በጋራ የሚከፍሉት ነው፡፡ ከዚህ ውጪ የሚኖረው እዳ የግል ይሆናል ማለት ነው፡፡ አከፋፈሉ ሲታይ የጋራ እዳ ከባልና ሚስቱ የጋራ ሀብት የሚከፈል ሲሆን ዕዳውን ለመሸፈን በቂ በማይሆን ጊዜ ከባል ወይም ከሚስት የግል ሀብት የሚከፈል ይሆናል፡፡

በአንፃሩ የግል ዕዳ ከባለዕዳው ተጋቢ የግል ሀብት የሚከፈል ሲሆን ዕዳው ለመሸፈን በቂ በማይሆንበት ጊዜ ከጋራ ሀብት የሚከፈል ይሆናል፡፡ እዚህ ላይ ልብ ሊባል የሚገባው ጉዳይ ከጋራ ሀብት ሲባል በድርሻው ልክ እንጂ የሌላኛውን ተጋቢ ጥቅም በሚነካ መልኩ ሊሆን እንደማይችል ነው፡፡
የንቃተ ህግ፣ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት
#አለ_ህግ #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share #lawsocieties
..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Lawyer Mike 🔊የህግ ባለሙያ)
የጋብቻ መፈፀም የሚያስከትለው ውጤት
#ጋብቻ አስፈላጊውን ቅድመ ሁኔታዎችን በማሟላት በሁለት ሰዎች (ባልና ሚስት) መካከል የሚፈጠም ህብረት እንደሆነ ይጠቀሳል፡፡ የሀገራችን ቤተሰብ ህግ ለጋብቻ ትርጉም ያልሰጠ ሲሆን ጋብቻ ለማቋቋም ሊሟሉ የሚገባቸውን ቅድመ ሁኔታዎችን እና ጋብቻ የሚፈፀመው በአንድ ወንድና በአንዲት ሴት መካከል እንደሆነ ያስቀምጣል፡፡

በህግ ፊት የፀና ጋብቻ ለመፈጸም የተለያዩ ቅድመ ሁኔታዎች መሟላት አለባቸው፡፡ በዚህ መሰረት የሁለቱ ሰዎች ፈቃድ መኖር፣ በህጉ የተቀመጠው ዝቅተኛ እድሜ መሟላት፣ የዝድና አለመኖር፣ በጋብቻ ላይ ጋብቻ አለመኖር መሟላት ያለባቸው ቅድመ ሁኔታዎች ናቸው፡፡

ጋብቻ በተለያዩ ሶስት መንገዶች ሊፈጸም ይችላል፡፡
እነዚህም በክብር መዝገብ ሹም ፊት የሚፈፀም፣ የሀይማኖት ጋብቻ እና የባህል ጋብቻ ናቸው፡፡ በእነዚህ መንገዶች የተፈፀመ ጋብቻ ተመሳሳይ ውጤት ያለው ሲሆን በእነዚህ መንገዶች አስፈላጊውን ሁኔታ በማሟላት የተፈጸመ ጋብቻ የሚያስከትለው ውጤቶች እንደሚከተለው ተብራርተዋል፡፡

1. ጋብቻ በተጋቢዎች ግላዊ ግንኙነት ላይ የሚያስከትለው ውጤት

i. አብሮ መኖር
ባልና ሚስት ጋብቻ ከፈፀሙ በኋላ አብረው እንዲኖሩ በህግ ግዴታ ተጥሎባቸዋል፡፡ የመኖሪያ ቦታቸውንም አብረው የሚወስኑ ይሆናል፡፡ ሆኖም ባልና ሚስቱ ለተወሰነ ወይም ላልተወሰነ ጊዜ ተለያይተው ለመኖር መስማማት አይከለከሉም፡፡ ይህ ስምምነት መቀየሩ አግባብ ካልሆነ በስተቀርም ተጋቢዎች ወይም ከሁለት አንዳቸው አስበው ሊቀይሩትም ይችላሉ፡፡ ለምሳሌ የባልና ሚስቱ የሥራ ቦታ ሊለያይ የሚችልበት አጋጣሚ ሲፈጠር ሁለቱም በያሉበት ሆነው ሥራቸውን ለመሥራት ሊስማሙ የሚችሉ ሲሆን አመቺ ሆኖ ካላገኙትም ሀሳባቸውን መቀየር ይችላሉ፡፡

ይህ ብቻ ሳይሆን ተጋቢዎች ጋብቻ ተሳስረው ሲኖሩ ለጤናቸው አደገኛ ካልሆነ በስተቀር ከጋብቻ የሚጠበቀውን መደበኛ የሩካቤ ሥጋ መፈፀምም ይጠበቅባቸዋል፡፡ ይህን የሚቃረን ስምምነት ውጤት አይኖረውም፡፡ በተጨማሪም በማንኛውም ሁኔታ አንዳቸው ለሌላኛው ታማኝ የመሆን ግዴታ አለባቸው፡፡ ይህ ሳይሆን ቀርቶ አንዳቸው ሳይታመኑ የአመንዝራነት ድርጊት ቢፈፅሙ በተበደለው ተጋቢ አቤቱታ አቅራቢነት በእስራት ወይም በመቀጮ ሊያስቀጣ የሚችል የወንጀል ተጠያቂነት የሚያስከትል ነው፡፡

ii. መከባበር፣ መተጋገዝና መደጋገፍ

ባልና ሚስት በትዳር በሚኖሩበት ጊዜ አንዳቸው ሌላኛውን የማገዝና የመደገፍ እንዲሁም ተከባብሮ የመኖር ሀላፊነት ተጥሎባቸዋል፡፡ ይህንን ሀላፊነት በስምምነት ፈፅሞ ሊያስቀሩት እንደማይችሉ በህግ ተደንግጓል፡፡

iii. ቤተሰብን በጋራ መምራት

ጋብቻ በሁለቱ ተጋቢዎች ተወስኖ የማይቀርና ልጆችን የሚፈጥርና የቤተሰብ መሰረት የሚሆን ተቋም ነው፡፡ በዚህም የልጆች አስተዳደግ፣ ትምህርት፣ ጤና ወዘተ የመሳሰሉ ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች በተጋቢዎች እንዲሟሉ ይጠበቃል፡፡ ከዚህ አንፃር ባልና ሚስት እኩል መብት እንዳላቸው በቤተሰብ ህግ ደንግጓል፡፡ በዚህም በማናቸውም ረገድ የቤተሰቡን ደህንነትና ጥቅም ለማስጠበቅ፣ ልጆቻቸው በመልካም ሥነ ምግባር እንዲታነፁ፣ ተገቢ ትምህርት እንዲቀርሙና ሀላፊነት የሚሰማቸው ዜጎች ሆነው እንዲያድጉ ለማድረግ ባልና ሚስቱ መተባበር ይጠበቅባቸዋል፡፡

2. ጋብቻ በንብረት ረገድ የሚያስከትለው ውጤት

ጋብቻ በተጋቢዎች ግላዊ ግንኙነት ላይ ውጤት እንዳለው ሁሉ በንብረት ረገድም የራሱ የሆነ ውጤት የሚያስከትል ነው፡፡ ንብረትን በተመለከተ ጋብቻ የግል እና የጋራ ንብረት ውጤት የሚስከትል ነው፡፡

i. የግል ንብረት ምንነትና አስተዳደር

የግል ንብረት የምንለው ሁለቱ ተጋቢዎች ከጋብቻው በፊት በየግል የነበሯቸው ንብረቶች ወይም ከጋብቻው በኋላ በውርስ ወይም በየግላቸው በስጦታ ያገኟቸው ንብረቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ንብረቶች በጋብቻውም ዘመን የግላቸው ሆነው ይቀጥላሉ፡፡ እነዚህን ንብረቶች ሸጦ የሚገዛው ንብረት የራሱ የሚሆን ሲሆን ይህ የሚሆነው ግን በፍርድ ቤት የግሌ ይባልልኝ ብሎ ሲጠይቅና ሲፀድቅለት ነው፡፡

የግል ንብረት አስተዳደርን በተመለከተ የግል ንብረቱ ባለቤት የሆነው ተጋቢ ሊያዝበት የሚችል ሲሆን ሌላኛው ተጋቢ እንዲያስተዳድረው በጋብቻ ውል ሊስማሙ የሚችሉ ከመሆኑም በላይ ውክልና በመስጠት ሌላኛው ተጋቢ እንዲያስተዳደር ሊያደርግ ይችላል፡፡

ii. የጋራ ንብረት ምንነትና አስተዳደር

የጋራ ንብረትን በተመለከተ የጋራ ንብረት የሚባለው ባልና ሚስት ከተጋቡ በኋላ በግብይት የሚያገኟቸው ንብረቶች፣ ባልና ሚስት በግል ጥረታቸው የሚገኝ ገቢ፣ ከግል እና ከጋራ ንብረታቸው የሚገኟቸው ገቢዎች ሁሉ ናቸው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በስጦታ ወይም በኑዛዜ በጋራ የተሰጧቸው ንብረቶች የጋራ ንብረቶች ናቸው፡፡ እዚህ ላይ መታወቅ ያለበት አንደኛው ተጋቢ የግል ሀብቱ መሆኑን ካላስረዳ በስተቀር በአንደኛው ተጋቢ ስም የተመዘገበ ሀብትም ቢሆን እንኳን የተጋቢዎች የጋራ ሀብት እንደሆነ የህግ ግምት የሚወሰድበት መሆኑ ነው፡፡

በንብረት አስተዳደር ረገድ የጋራ ንብረታቸውን አንደኛው ተጋቢ እንዲያስተዳድረው ካልተስማሙ፣ ችሎታ የለውም በሚል ካልተወሰነ፣ ንብረት የማስተዳደር መብቱ ካልተገፈፈ፣ ወይም በማናቸውም ምክንያት ንብረታቸውን ማስተዳደር የማይችል ሆኖ ካልተገኘ በስተቀር የጋራ ንብረታቸውን በጋራ ያስተዳድራሉ፡፡ ሆኖም በተጠቀሱት ምክንያቶች አንደኛው ተጋቢ ብቻውን ንብረቱን የሚያስተዳድር ከሆነ ለሌላኛው ተጋቢ መረጃ የመስጠት ሃላፊነት አለበት፡፡

በገቢ ረገድ ሁለቱም ተጋቢዎች ገቢያቸውን በየራሳቸው መቀበል የሚችሉ እንዲሁም በግል ወይም በጋራ የባንክ ሂሰብ ከፍተው ማስቀመጥ ይችላሉ፡፡ ይህ ማለት ግን አንደኛው ተጋቢ ሌላኛው ተጋቢ እንዲቀበልለት ስልጣን ለመስጠት የሚከለክለው ነገር የለም፡፡ በየግል የሚያገኙትንም ገቢ ሌላኛው ተገቢ ሲጠይቅ ማሳወቅ ግዴታ አለበት፡፡

ከንብረት በተጨማሪ በጋብቻ ውስጥ እዳ ሊኖር እንደሚችል የሚጠበቅ ነው፡፡ ልክ እንደንብረት ሁሉ እዳም የግል ወይም የጋራ ተብሎ የሚከፈል ነው፡፡ እዳው ለባልና ሚስት እና ለልጆቻቸው የዕለት ኑሮ አስፈላጊ የሆኑ ነገሮችን ለማሟላት ወይም ባል ወይም ሚስት ቀለብ የመስጠት ግዴታቸውን ለመወጣት የተገቡ እዳዎች እንዲሁም ከባልና ሚስት በአንደኛው ወይም በዕዳ ጠያቂው አመልካችነት ለትዳር ጥቅም ስለመሆኑ ፍርድ ቤት የተቀበለው እዳ በጋራ የሚከፍሉት ነው፡፡ ከዚህ ውጪ የሚኖረው እዳ የግል ይሆናል ማለት ነው፡፡ አከፋፈሉ ሲታይ የጋራ እዳ ከባልና ሚስቱ የጋራ ሀብት የሚከፈል ሲሆን ዕዳውን ለመሸፈን በቂ በማይሆን ጊዜ ከባል ወይም ከሚስት የግል ሀብት የሚከፈል ይሆናል፡፡

በአንፃሩ የግል ዕዳ ከባለዕዳው ተጋቢ የግል ሀብት የሚከፈል ሲሆን ዕዳው ለመሸፈን በቂ በማይሆንበት ጊዜ ከጋራ ሀብት የሚከፈል ይሆናል፡፡ እዚህ ላይ ልብ ሊባል የሚገባው ጉዳይ ከጋራ ሀብት ሲባል በድርሻው ልክ እንጂ የሌላኛውን ተጋቢ ጥቅም በሚነካ መልኩ ሊሆን እንደማይችል ነው፡፡
የንቃተ ህግ፣ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት
#አለ_ህግ #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share #lawsocieties
..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties