አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.87K photos
25 videos
1.87K files
3.58K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
ግልጽነት የጎደለው የአሹራ ክፍያ ነገር•••
          ****
የአዲስ አበባ ግንባታና ቁጥጥር ባለስልጣን በመመሪያ ቁጥር ግፈቁባ/9561/3014፣ በ2014 ዓ.ም. ባወጣው የግንባታ ዋጋ ክለሳ መሰረት:-

ለሁሉም የህንጻ ዐይነቶች የግንባታ ተመን፣

1. G+0 ቤት ብር 10,000/ካሬ ሜትር፣
2. ከG+1 በላይ ለንግድ፣ ለመኖሪያ እንዲሁም ለቅይጥ ህንጻዎች ብር 12,200/ካሬ ሜትር፣
3. ለሆስፒታል አገልግሎት የሚሆን ህንጻ ብር 20,000/ካሬ ሜትር ፣

በሚል የዋጋ ትመና አውጥቶ ሰዎች የንብረት ስም ዝውውር በሚፈጽሙ ጊዜ ለመንግስት የሚከፈለው የ2% የቴምብርና የ4% የአሹራ ክፍያ በእዚህ ዋጋ ላይ ሲሰላ ቆይቷል።

ይሁንና ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ አዲስ የከለሰው መመሪያ ለህዝብ ግልጽ ባልተደረገበት ሁኔታ በቅርቡ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ ክፍለ ከተሞች ዜጎች የቤት ባለቤትነት ለማዘዋወር ጥያቄ ሲያቀርቡ  የቤቶች የግንባታ ዋጋ፣

1. G+0 ህንጻ ብር  20,000/ካሬ ሜትር፣
2. ከG+1 እስከ G+ 5 ህንጻ ብር 25,000/ካሬ ሜትር፣
3. ከG+6 እስከ G+ 10 ህንጻ ብር 30,000/ካሬ ሜትር፣
4. ከG+11 እስከ G+15 ህንጻ ብር 35,000/ካሬ ሜትር፣
5. ከG+15 ህንጻ በላይ ብር 40,000/ካሬ ሜትር፣

መሆኑን የሚገልጽ ነገር ተለጥፏል።

በየክፍለ ከተሞቹ ዜጎች ይሄንኑ አዲስ ወጣ የተባለ የዋጋ ትመና መሠረት ባደረገ መልኩ የአሹራ ክፍያ እየፈጸሙ ይገኛሉ።

መመሪያውን በተመለከተ...

1ኛ/የቤቱ ዓይነት ቅንጡ ህንጻም ይሁን እንደነገሩ የተገነባ ህንጻ ተመሳሳይ የግንባታ ዋጋ በካሬ ሜትር ማስቀመጡ፣

2ኛ/ኮንዶሚንየም የሚሸጡ ሰዎችን በተመለከተ መመሪያው ምንም ስለማይል ምድር ቤት ኮንዶሚንየም የሚሻሻጡ ሰዎች ዝቅተኛ አሹራ (20,000 በካሬ)፣ 6ኛ ፎቅ ላይ ያለ ቤት የሚሻሻጡ ሰዎች ከፍተኛ አሹራ (30,000 በካሬ) እንዲከፍሉ  ይገደዳሉ። ከእዚህ በተቃራኒ የቤት ሽያጭም ሆነ ኪራይ ዋጋ የሚወደደው ታች ባሉ ወለሎች ላይ መሆኑ እና መመርያው ይሄንን ከቁብ ያላስገባ መሆኑ፣

3ኛ/በቅርቡ ኢኮኖሚዬ hyperinflationary አይደለም (የሶስት አመት አጠቃላይ የግሽበት መጠኔ ከ100% አይበልጥም ) በማለት መግለጫ ያወጣ መንግስት፣ ዋነኛ የዋጋ ንረት መለኪያ የሆነው የግንባታ ወጪ በአመት ከ100% በላይ መናሩን ማመኑ፣ እንዲሁም

4ኛ/ መመሪያዎች ሲወጡ መመሪያው ለሚተገበርበት ህዝብ ግልጽ መሆን ሲኖርበት ያለመሆኑ እንዲሁም በመሬት ላይ ያሉ ነባራዊ ሁኔታዎችን ከግምት ውስጥ ያላስገባ መሆኑ

ግርምትን አጭሮብኛል።
------------------

Tilahun Girma Ango

#አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
#ሼር #Share
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
👍93
በህግ ስራ የታክስ አስተዳደር ስርዓት ላይ የተደረገው ጥናት አተገባበር ዙሪያ ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር ውይይት ተደረገ
********

የኢትዮጵያ የፌደራል ጠበ
ቆች ፣ የህግ አማካሪዎችና፣  የጥብቅና ድርጅቶችን የታክስ አስተዳደር ስርአት የህግ እና የአተገባበር ችግሮች ላይ ለበርካታ አመታት ሲቀርቡ የነበሩ ቅሬታዎችን ለመፍታት የሚያስችል ጥናት ለተከታታይ ወራት በኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ፣ በፍትህ ሚ/ር እና በገንዘብ ሚኒስቴር አማካኝነት ሲከናወን ቆይቶ መጠናቀቁ ይታወሳል::  ከጥናቱ መጠናቀቅ በኃላም በአዲስ አበባ ከተማ በጥናቱ ግኝቶችና መደምደሚያዎች ላይ ተከታታይ ውይይቶች ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር መከናወኑም የሚታወስ ነው::

የጠበቆች ማህበር ቀጣዩ የግብር ዘመን ላይ የባለፉት አመታት ችግሮችን ለመፍታት የአጭርና የረጅም ግዜ እቅዶችን በመንደፍ ያላሰለሰ ጥረቱን እንደሚቀጥልና ከፖሊሲ ውሳኔ ሰጪዎች እና ከቁልፍ ባለድርሻዎች ጋር ተከታታይ ውይይቶች እንደሚደረጉ ማሳወቁ ይታወሳል::

በዚህም በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ እና የሚመለከታቸው የስራ ሃላፊዎች ጋር በጥናቱ ግኝቶች እና ቀጣይ መወሰድ ስለሚገባቸው እርምጃዎች ዝርዝር ውይይቶች ተደርገዋል::

በመድረኩም  የኢትዮጵያ የፌደራል ጠበቆች ማህበር ተ/ፕሬዚዳንት አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው የጥናቱን ዳራ ፤ መነሻ ምክንያቶች ፤ አጠቃላይ ሂደቱንና ፤ የጥናቱን ቁልፍ መደምደሚያዎች እንዲሁም በቀጣይ በአጭርና በረጅም ግዜ መወሰድ ስለሚገባቸው እርምጃዎች ገለፃ ያደረጉ ሲሆን የጥናቱ ግብረሀይል አባላትም የጉዳዩን አንገብጋቢነት የሚገልፁ ሀሳቦችን አንፀባርቀዋል::
👍6
አለሕግAleHig ️
በህግ ስራ የታክስ አስተዳደር ስርዓት ላይ የተደረገው ጥናት አተገባበር ዙሪያ ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር ውይይት ተደረገ ******** የኢትዮጵያ የፌደራል ጠበቆች ፣ የህግ አማካሪዎችና፣  የጥብቅና ድርጅቶችን የታክስ አስተዳደር ስርአት የህግ እና የአተገባበር ችግሮች ላይ ለበርካታ አመታት ሲቀርቡ የነበሩ ቅሬታዎችን ለመፍታት የሚያስችል ጥናት ለተከታታይ ወራት በኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ፣ በፍትህ…
የገንዘብ ሚ/ር  ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ በመድረኩ እንደገለፁት ጉዳዩ በዚህ ደረጃ ተደራጅቶ መጠናቱ የተለየ እንደሚያደርገው ፤ የህግ ሙያ ለማደግ ፍትሃዊ ያልሆኑ አሰራሮች ሊታረሙ እንደሚገባ ገልፀው ፤ በቀረበው መሰረት የአጭርና የረጅም ግዜ መፍትሄዎቹ ላይ በተቻለ ፍጥነት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን እንዲሰራ ለሚመለከታቸው የስራ ክፍሎች የስራ መመሪያ ሰጥተዋል::

ማህበሩ ይህን ለበርካታ አመታት ሲንከባለል የቆየና ላለፉት 11 ወራት ብዙ የተደከመበትን ስራ ከዳር ለማድረስ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር  በመሆን ተገቢውን የመሪነት ሚናውን እየተወጣ የሚቀጥል ሲሆን ፤ የሚደርስባቸውን ውጤቶች በተለመዱት የማህበሩ የመገናኛ ዘዴዎች የሚያሳውቅ ይሆናል:: መላው የፌደራል ጠበቆችና የህግ አማካሪዎች እንደወትሮው ሁሉ የግብር ግዴታችሁን ለመወጣት ከግብር መክፈያ ወቅት ቀድሞ ተገቢውን ዝግጅት እያደረጋችሁእንድትቆዩ ማህበሩ ያሳስባል::

የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር
ሰኔ 07 ቀን 2015ዓ.ም
አዲስ አበባ ፣
#አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
#ሼር #Share
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
👍13👏1
👍1
Law of Traders & Business
👇👇👇👇👇👇👇👆👆👆
The Text book on Law of Traders & Business Organizations is out of print today. USAID Feteh sponsored the work. Participate colleagues Misganaw K, Gizachew S. & Dagnachew W.This is exemplary collaborative work representing four universities.

#አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
#ሼር #Share
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
👍20🔥3
የስብሰባ ጥሪ ፣
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ባዘጋጀዉ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የለዉጥ ፍኖተ-ካርታ ላይ ከጠበቆች ጋር ዉይይት ለማድረግ ማቀዱን ገልፆ 100 ጠበቆች በእለቱ እንዲገኙለት ጠይቆናል፡፡

በመሆኑም ዉይይቱ የሚካሄደዉ ቅዳሜ ሰኔ 17 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ጀምሮ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የስብሰባ አዳራሽ መሆኑን አውቃችሁ በዉይይት መድረኩ ላይ እንድትገኙ ጠበቆች የተጋበዛችሁ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር

ሰኔ 10 ቀን 2015ዓ.ም
አዲስ አበባ
4👍3👏1
ያለ ደረሰኝ (ቫት) ግብይት ማከናወን ወንጀል ሰ/መ/ቁ 211028
ያለ ደረሰኝ (ቫት) ግብይት ማከናወን ወንጀል ጋር በተያያዘ የድርጅት ሥራ አስኪያጅ የድርጅቱን አስተዳደር በሚመለከት በውክልና ለሌላ ሰው ያስተላለፈ መሆኑ እና ተወካዩም በተቀበለው ውክልና መሠረት ሥራውን የሚያከናውን መሆኑ በተረጋገጠ ጊዜ ተጠያቂ የሚሆነው ውክልናውን ተቀብሎ ስራውን በውክልና የሚያስተዳድረው ሰው እንጂ ስራ አስኪያጁ ወይም የድርጅቱ ባለቤት ሊሆን አይገባም።

አዋጅ ቁጥር 285/94 በአዋጅ ቁጥር 609/2001 እንደተሻሻለው በአንቀጽ 56/1/፤ አንቀጽ 22/1/ እና አንቀጽ 50/ለ/1 መሠረት የአንድ የንግድ ድርጅት ሥራ አስኪያጅ በወንጀል ተጠያቂ የሚሆነው እሱ የሚመራው ድርጅት የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ሆኖ ያለተጨማሪ እሴት ታክስ ደረሰኝ ግብይት ማከናወኑ ሲረጋገጥ እንደሆነ፤ የድርጅቱ ሃላፊነት ከተረጋገጠ የሥራ አስኪያጁ ሃላፊነት የሕግ ግምት የሚወሰድበት ስለመሆኑ እንገነዘባለን።
4 ለ 1 አብለጫ ድምጽ የተሰጠ
የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁ 983/08 አንቀጽ 131(1)(ለ)፤ 131(1)(ለ)፤ 128

#አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
#ሼር #Share
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
👍81🥰1
የፌድራል_ጠቅላይ_ፍርድ_ቤት_ሰበር_ሰሚ_ችሎት_በሰበር_መዝገብ_ቁጥር_219862_ግንቦት_26_ቀን_2014.pdf
828.9 KB
የፌድራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰበር መዝገብ ቁጥር 219862 ግንቦት 26 ቀን 2014 የተሰጠ ውሳኔ

ከባድ vs ቀላል የአካል ጉዳት የሰ/መ/ቁ. 219862/ያልታተመ/ 
አንድ ሰው በሌላ ሰው ላይ በፈፀመው የድብደባ ድርጊት የአጥንት ስብራት መድረሱ ቢረጋገጥና ቆይቶ ስብራቱ መዳኑ ቢረጋገጥ ጉዳት ያደረሰው ሰው ጥፋተኛ ሊባል የሚገባው በከባድ የአካል ጉዳት ማድረስ ወንጀል ሳይሆን በቀላል የአካል ጉዳት ማድረስ ወንጀል ነው። በከባድ የአካል ጉዳት ማድረስ ወንጀል ጥፋተኛ ለማለት ታሳቢ ሊደረግ የሚገባው ወንጀሉ ሲፈፀም የደረሰውን የጉዳት መጠን ሳይሆን በድብደባው ምክንያት የደረሰውን የመጨረሻ የጉዳት ውጤት ነው።
ሰ/መ/ቁ.156521፣ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 555፣ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 556
#አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
#ሼር #Share
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
👍141🥰1
219862 - Stamped.pdf
828.9 KB
አንድ ሰው በሌላ ሰው ላይ በፈፀመው የድብደባ ድርጊት የአጥንት ስብራት መድረሱ ቢረጋገጥና ቆይቶ ስብራቱ መዳኑ ቢረጋገጥ ጉዳት ያደረሰው ሰው ጥፋተኛ ሊባል የሚገባው በከባድ የአካል ጉዳት ማድረስ ወንጀል ሳይሆን በቀላል የአካል ጉዳት ማድረስ ወንጀል ነው። በከባድ የአካል ጉዳት ማድረስ ወንጀል ጥፋተኛ ለማለት ታሳቢ ሊደረግ የሚገባው ወንጀሉ ሲፈፀም የደረሰውን የጉዳት መጠን ሳይሆን በድብደባው ምክንያት የደረሰውን የመጨረሻ የጉዳት ውጤት ነው። ሰ/መ/ቁ.156521፣የወንጀል ሕግ አንቀጽ 555፣የወንጀል ሕግ አንቀጽ 556
#Click Ethiopian Laws
👆👆👆👆👆👆
👍11👏21
145_2015የአዲስ_አበባ_ከተማ_ነዋሪነት_ምዝገባ_መመሪያ.pdf
942.5 KB
# መመሪያ ቁጥር 144/2015 የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪነት ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ።
👍42
935_2015_የንግድ_ምዝገባ፣_ፈቃድ_እና_ድኅረ_ፈቃድ_ኢንስፔክሽን_መመሪያ_ቁጥር_935_2015.pdf
972.2 KB
935-2015 የንግድ ምዝገባ፣ ፈቃድ እና ድኅረ-ፈቃድ ኢንስፔክሽን መመሪያ ቁጥር- 935-2015
👍2
ቼክ ለማስከፈል የቀረበ ክስ.pdf
216.1 KB
ቼክ ለማስከፈል ስለሚቀርብ ክስ
አንድ ሰው በሂሳቡ ውስጥ በቂ ገንዘብ ሳይኖር ቼክ የጻፈ ከሆነ በወንጀል ሕግ ቁጥር 693 መሠረት በቼክ ማጭበርበር ወንጀል የሚቀጣ ሲሆን ድርጊቱ ሆን ተብሎ ወይም በሂሳቡ ውስጥ በቂ ገንዘብ እንደሌለው እያወቀ የተፈጸመ ከሆነ ቅጣቱ ከአስር አመት የማይበልጥ እስራት ሲሆን ድርጊቱ በቸልተኝነት ከተፈጸመ ደግሞ ከአንድ አመት የማይበልጥ ቀላል እስራት ነው፡፡
በመሆኑም ክፍያ ቼኩን የሰጠው ሰው በወንጀል የሚቀጣ ሲሆን ነገር ግን ቼክ የተሰጠው ሰው በቼኩ ላይ የተገለጸውን ገንዘብ እንዲከፈለው ለመጠየቅ ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት የፍትሐ ብሔር ክስ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
ቼክ ለማስከፈል የሚቀርብ ክስ እንደ ሌሌች መደበኛ ክሶች የመቀርብ ሳይሆን በፍትሐ ብሔር ሥነ-ሥርአት ሕጉ መሠረት በአጭር ሥነ-ሥርአት የሚታይ ነው፡፡
ስለዚህ ቼክ ይከፈለኝ በማለት በአጭር ሥነ-ሥርአት የሚቀርብ ሰው ተከሳሹ የተለየ መከራከሪያ እስካላቀረበ ድረስ ቼኩን ባለ ሂሳቡ መጻፉ ተረጋግጦ እንዲከፈለው የሚወሰን ሲሆን ክሱ ከዚህ በታች በተገለጸው ፎርም መሠረት ተዘጋጅቶ ጉዳዩን ለማየት ስልጣን ባለው በፍርሙ ውስጥ የተገለጹት እና ሌላ ከሳሹ አለኝ ከሚላቸው ማስረጃዎች ጋር ተያይዞ፤ ማስረጃዎች የቀረጥ ቴምብር ተመቶባቸው እና በበቂ ኮፒ ተዘጋጅቶ ይሆናል፡፡
#አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
#ሼር #Share
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
👍5
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Lawyer Mike 🔊የህግ ባለሙያ)
#ውክልና
ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች ጉዳዮቻቸውን ራሳቸው መፈፀም የማይችሉባቸው ሁኔታዎች ሊገጥሟቸው ይችላል፡፡ ለዚህ መፍትሄ ሆኖ በማገልገል ላይ ያለው ውክልና ነው፡፡ ሆኖም ውክልና በዘፈቀደ የሚደረግ ሳይሆን በህግ በተቀመጠው ሥርአት መሰረት የሚፈፀም ነው፡፡ በዚህ ፅሁፍ ስለ ውክልና ምንነት፣ ስለውክልና አይነቶች፣ ስለውክልና ጠቀሜታ እና ውክልና ቀሪ ስለሚሆንባቸው ሁኔታዎች በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡

የውክልና ምንነት

የፍትሐብሔር ህጉ አንቀጽ 2199 መሰረት ውክልና ማለት ተወካይ የተባለው ሰው ወካይ ለተባለው ሰው እንደርሱ በመሆን አንድ ወይም ብዙ ህጋዊ ስራዎችን በወካዩ ስም ለማከናወን ግዴታ ሚገባበት ውል ነው፡፡ በዚህም ተወካዩ ልክ እንደወካዩ በመሆን የወካዩን ሥራዎች በወካዩ ስም ለማከናወን የሚደረግ ውል ነው፡፡
ውክልና ከልዩ የውል ህጎች ውስጥ አንዱ እንደ መሆኑ መጠን አንድ ህጋዊ ውል ሊያሟላቸው ያሚገባውን በፍትሐብሔር ህጉ በአንቀፅ 1678 ስር የተቀመጡትን መስፈርቶች ሊያሟላ ይገባል፡፡ ይኸውም፡-

👉ውል ለመዋዋል ችሎታ ያለው ሰው መሆን
👉ጉድለት የሌለው ፈቃድ ወይም ስምምነት መኖር
👉በቂ የሆነ እርግጠኝነት ያለው የሚቻል እና ህጋዊ የሆነ ጉዳይ መሆን
👉የውል አፈፃፀም ፎርም በህግ የታዘዘ ሆኖ እንደ ትዛዙ ባይፈፀም ፈራሽነት የሚያስከትል ሲሆን ህግ በሚያዘው ልዩ ፎርም መሆን ናቸው፡፡

የፍትሐብሔር ህጉ አንቀጽ 2200 ወካይ ለተወካይ የውከልና ስልጣኑን በቃል ወይም በዝምታ ሊሰጥ የሚችል ሲሆን ህጉ የውከልና ስልጣኑ በተለያየ ፎርም መሰጠት አለበት በማለት የሚያዝ ከሆነ ግን ይህ መሟላት ይኖርበታል፡፡

የውክልና አይነቶች

በአጠቃላይ ሁለት አይነት የውክልና ስልጣን ሲኖር ይህም ጠቅላላ እና ልዩ ውክልና በመባል ይታወቃሉ::
👍91