224876.pdf
1 MB
የውርስ ሀብት በእጁ አድርጎ ያልያዘ ወራሽ በፍ/ብ/ህ/ቁ 1000(1) መሰረት የይርጋ መቃወሚያ ማንሳት አይችልም።
የፍ/ብ/ህ/ቁ 1000(1) ከሳሹ መብቱንና የውርሱ ንብረቶች በተከሳሹ መያዛቸውን ካወቀ ሶስት አመት ካለፈ በኋላ ስለወራሽነት ጥያቄ የሚቀርበው ክስ ተቀባይነት ለማግኘት እንደማይችል ደንግጓል፡፡ ይህ ድንጋጌ በይዘቱ የይርጋ መቃወሚያ ማንሳት የሚችለው የውርስ ንብረቶቹን በእጁ የያዘው ሰው ብቻ ስለመሆኑ የሚያስገነዝብ ነው፡፡
ሰ-መ-ቁ 224876 ቀን ጥቅምት 2 2015 ዓ.ም
https://t.me/lawsocieties
የፍ/ብ/ህ/ቁ 1000(1) ከሳሹ መብቱንና የውርሱ ንብረቶች በተከሳሹ መያዛቸውን ካወቀ ሶስት አመት ካለፈ በኋላ ስለወራሽነት ጥያቄ የሚቀርበው ክስ ተቀባይነት ለማግኘት እንደማይችል ደንግጓል፡፡ ይህ ድንጋጌ በይዘቱ የይርጋ መቃወሚያ ማንሳት የሚችለው የውርስ ንብረቶቹን በእጁ የያዘው ሰው ብቻ ስለመሆኑ የሚያስገነዝብ ነው፡፡
ሰ-መ-ቁ 224876 ቀን ጥቅምት 2 2015 ዓ.ም
https://t.me/lawsocieties
የኑዛዜ አይነቶችና የኑዛዜ ማረጋገጫ
በኢትዮጵያ የውርስ ህግ ሰው ህይወቱ ካለፈ በኋላ በህይወት ዘመኑ ያፈራቸው ንብረቶቹን ለወዳጅ ዘመዶቹ እንዲከፋፈል የሚያደርግበት ሁለት አይነት መንገዶች አሉ፡፡ እነሱም ያለኑዛዜ የሚደረግ ውርስ እና በኑዛዜ የሚደረግ ውርስ ናቸው፡፡ በሁለቱም ዘዴዎች የሚደረግ የንብረት ማስተላለፍ ሂደት በፍትሐ ብሔር ህግ የሚገዛ ሲሆን ለውርሱ ተፈፃሚነት ህጉ ያስቀመጣቸው መስፈርቶች መሟላት ይኖርባቸዋል፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ የኑዛዜ አይነቶች እና የኑዛዜ ማረጋገጫ በዝርዝር ይዳሰሳሉ፡፡
የኑዛዜ አይነቶች
በኢትዮጵያ ህግ 3 የኑዛዜ ዓይነቶች አሉ፡፡ ሁሉም የኑዛዜ አይነቶች መከትል ያለባቸው ፎርማሊቲዎች ወይም ቅድመ ሁኔታዎች በ1952 ዓ.ም በወጣው የፍትሐ ብሔር ህጋችን ውስጥ በዝርዝር የተቀመጡ ሲሆን መስፈርቶቹ ያልተሟሉ እንደሆነ ኑዛዜው በህግ ፊት ውድቅ (ፈራሽ) ይሆናል፡፡ ህጉ የመስፈርቶቹን መሟላት በተመለከተ ጥብቅ (strict) ነው፡፡ ይህም የሆነበት ዋና ምክንያት የኑዛዜ ቃል በሚፈፀምበት ወቅት ተናዛዡ በህይወት ስለማይኖር ትክክለኛ ሀሳቡን ማወቅ የሚቻለው ትቶት ከሄደው የኑዛዜ ሰነድ ብቻ ነው፡፡ ስለሆነም ይህ ሰነድ ደግሞ ለአፈፃፀም እንዲያመች መስፈርቶቹን በሙሉ ግልፅ በሆነ ሁኔታ መከተል አለበት፡፡ በፍ/ህ/አ 880 ስር እንደተደነገገው 3ቱ የኑዛዜ አይነቶች
1. በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ (public will)
2. በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜ (holographic will)
3. በቃል የሚደረግ ኑዛዜ (oral will) ናቸው
• በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ ( የፍ/ብ/ህገ/ቁጥር 881-883)
በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ ተናዛዡ እየተናገረ ሌላ ሰው የሚፅፈው ወይም ተናዛዡ ራሱ የሚፅፈው የኑዛዜ አይነት ነው፡፡ ይህ ኑዛዜ በተናዛዡ ወይም በሌላ ሰው ከተፃፈ በኃላ ተናዛዡ እና ምስክሮች ባሉበት መነበብ አለበት፡፡ በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ ተቀባይነት እንዲኖረው ተናዛዡና ምስክሮች ባሉበት መነበቡ ብቻ በቂ አይደለም፡፡ ይልቁንም ይህ መስፈርት (formality) መሟላቱ በኑዛዜው ላይ መስፈር አለበት፡፡ ይኸውም በኑዛዜው ላይ "ይህ ኑዛዜ ተናዛዡ እና ምስከሮች ባሉበት ተነቧል" ተብሎ መገለጽ አለበት፡፡ በግልፅ በሚደረግ ኑዛዜ ላይ የምስክሮች ብዛት 4(አራት) መሆን ሲኖርበት አራቱም ምስክሮች ኑዛዜው ተነቦላቸው በኑዛዜው ላይ ፊርማቸውን ወዲያውኑ ማስፈር አለባቸው፡፡ በተጨማሪም በኑዛዜው ላይ ኑዛዜው የተደረገበት ቀን ማለትም ቀን፣ ወር፣ ዓመተ ምህረት መፃፍ አለበት፡፡
የምስክሮችን ብዛት በተመለከተ በግልፅ ለሚደረግ ኑዛዜ ከምስክሮቹ መካከል አንዱ ዳኛ ወይም ውል ለማዋዋል ሥልጣን የተሰጠው ሰው ሆኖ ኑዛዜውም የተደረገው ይህ ዳኛ ወይም ለማዋዋል ሥልጣን የተሰጠው ሰው ሥራቸውን በሚያካሄዱበት ክፍል ውስጥ የሆነ እንደሆነ ለኑዛዜው ዋጋ ማግኘት ሁለት ምስክሮች ብቻ በቂ ናቸው፡፡
በአጠቃላይ በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ የሚከተሉትን ፎርማሊቲዎች መከተል አለበት፡፡
በተናዛዡ በራሱ ወይም እሱ እየተናገረ በሌላ ሰው ሊፃፍ ይችላል
ተናዘዡና አራት ምስክሮች ባሉበት መነበብ አለበት
በኑዛዜው ላይ ተናዛዡና ምስክሮቹ ባሉበት መነበቡ በግልፅ መፃፍ አለበት
ኑዛዜው የተደረገበት ቀን፣ ወር እና ዓ.ም መፃፍ አለበት
አራት ምስክሮች መኖር አለባቸው፣
ተናዛዡና ምስክሮች ኑዛዜው እንደ ተነበበላቸው ወዲያውኑ ፊርማቸውን ወይም የጣት አሻራቸውን ማሳረፍ አለባቸው
በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ ምስክሮች አካለመጠንን የደረሱ (18 ዓመት የሞላቸው) ወይም በህግ ያልተከለከሉ መሆን አለባቸው
ምስክሮች ኑዛዜው የተፃፈበትን ቋንቋ ለማወቅና የተፃፈውን ለመስማት ወይም ለማንበብ ራሳቸው ችሎታ ያላቸው መሆን አለባቸው፡፡
እነዚህ ከላይ የተመለከቱት መስፈርቶች ካልተሟሉ ኑዛዜው ፈራሽ ይሆናል፡፡ ፍርድ ቤቶችም የኑዛዜ ቃልን ለማስፈፀም መሟላት ያለባቸው መስፈርቶችን በጥብቅ የሚቆጣጠሩ ሲሆን መስፈርቶቹ ካልተሟሉ ኑዛዜውን ውድቅ ያደርጉታል፡፡
• በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜ (የፍ/ብ/ህገ/ቁጥር 883-891)
በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደርግ ኑዛዜ ሙሉ በሙሉ በተናዛዡ የሚፃፍ የኑዛዜ አይነት ነው፡፡ ይህን የኑዛዜ አይነት የሚያደርገው የተማረ ወይም ኑዛዜው የሚፃፍበትን ቋንቋ መፃፍና ማንበብ በሚችል ሰው ሲሆን የምስክሮችን መኖር የሚፈልግ አይደለም፡፡ በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜ በተናዛዡ የእጅ ፅሁፍ ወይም በማሽን (በኮምፒዩተር) ሊፃፍ ይችላል፡፡ ተናዛዡ ኑዛዜውን በኮምፒዩተር የሚፅፈው ከሆነ በእያንዳንዱ ገፅ ላይ እራሱ ስለመፃፉ በእጅ ፅሁፉ ማመልከት አለበት፡፡ ይህም ኑዛዜውን ያደረገው ተናዛዡ እንደሆነ ለማረጋገጥ ይረዳል፡፡ ኑዛዜው በማሽንም ሆነ በእጅ ቢፃፍ ተናዛዡ በእንዳንዱ ገፅ ላይ ቀን ፅፎ ፊርማውን ማስፈር ይኖርበታል፡፡ በተጨማሪም በኑዛዜ ሰነድ ላይ ተናዛዡ ይህ ሰነድ "ኑዛዜ" ነው በማለት በግልፅ መግለፅ አለበት፡፡ እነዚህ መስፈርቶች ካልተሟሉ ኑዛዜው ፈራሽ ነው፡፡ በተጨማሪ በተናዛዡ ፅህፈት የሚደረግ ኑዛዜ ኑዛዜው በተደረገ በሰባት(7) ዓመት ውስጥ ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው ሰው ወይም ፍርድ መዝገብ ቤት መቀመጥ አለበት፡፡
በአጠቃላይ በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜ በህግ ፊት ተቀባይነት እንዲያገኝ እና ተፈፃሚነት እንዲኖረው የሚከተሉት መስፈርቶች በሙሉ መሟላት አለባቸው፡፡
ሙሉ ለሙሉ በተናዛዡ መፃፍ አለበት
በኑዛዜው ላይ በግልፅ "ይህ ሰነድ የኑዛዜ ሰነድ ነው "ተብሎ መገለፅ አለበት
በተናዛዡ በአያንዳንዱ ገፅ ላይ ቀን እና ፊርማ መስፈር አለበት
ኑዛዜው በተደረገ በሰባት አመት ውስጥ ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ዘንድ መቀመጥ አለበት፣( የፍ/ብ/ህገ/ቁጥር 903)
ተናዛዡ ግልፅ በሆነ ፊርማው ካላፀደቃቸው በስተቀር የተናዛዡን ፈቃድ ለመለወጥ የሚችል ፍቀት፣ ስርዝ ወይም ድልዝ ያለባቸው ኑዛዜዎች ፈራሽ ናቸው፡፡
ከእነዚህ ከላይ ከተገለፁት መስፈርቶች ውስጥ አንዱ ወይም ከአንድ በላይ ካልተሟላ ኑዛዜው ፈራሽ ይሆናል ወይም ተፈፃሚነት አይኖረውም፡፡ ነገር ግን ኑዛዜ ፈራሽ ሆነ ማለት ወራሾች ንብረት አያገኙም ማለት አይደለም፡፡ ይልቁንም ውርሱ በቁጥር 842 እና ተከታዮቹ መሰረተ ሳይናዘዝ የሞተ ሰው ውርስ በሚተላለፍበት ሂደት የሚተላለፍ ይሆናል፡፡
የቃል ኑዛዜ (የፍ/ብ/ህገ/ቁጥር 892-894)
የቃል ኑዛዜ ማለት አንድ ሰው የሞቱ መቃረብ ተሰምቶት የመጨረሻ የፍቃድ ቃሎቹን ለሁለት ምስክሮች የሚሰጥበት የኑዛዜ አይነት ነው፡፡ ከፍ/ህ/ ቁጥር 892 እንደምንረዳው የቃል ኑዛዜ በመደበኛ ሁኔታ (under normal circumstances) የሚደረግ አይደለም፡፡ ተናዛዡ ይህን የኑዛዜ አይነት የሚያደርገው በቅርብ ጊዜ እሞታለው ብሎ ሲያስብ ለምሳሌ አደጋ ደርሶበት ፅኑ ህመም ውስጥ ሆኖ ሊሆን ይችላል፡፡ እንዲህ ባለጊዜ ሌሎቹን የኑዛዜ አይነቶች ማለትም በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜን ወይም በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜን ለማድረግ ሁኔታዎች አይፈቅዱለትም ማለት ነው፡፡ በመሆኑም በቃል የሚደረግ ኑዛዜ ላይ ተናዛዡ የሚናዘዘው በተገደበ ሁኔታ (restricted testamentary disposition) ይሆናል፡፡ በዚህ የኑዛዜ አይነት ተናዛዡ ሙሉ ፍላጎቱን ለማንፀባረቅ አይችልም፡፡ ምክንያቱም ህጉ ገደቦችን አስቀምጧል፡፡
በፍ/ሕ/ቁጥር 893 መሰረት አንድ ሰው የቃል ኑዛዜ ማድረግ የሚችለው በተለይ በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ ነው፡፡
በኢትዮጵያ የውርስ ህግ ሰው ህይወቱ ካለፈ በኋላ በህይወት ዘመኑ ያፈራቸው ንብረቶቹን ለወዳጅ ዘመዶቹ እንዲከፋፈል የሚያደርግበት ሁለት አይነት መንገዶች አሉ፡፡ እነሱም ያለኑዛዜ የሚደረግ ውርስ እና በኑዛዜ የሚደረግ ውርስ ናቸው፡፡ በሁለቱም ዘዴዎች የሚደረግ የንብረት ማስተላለፍ ሂደት በፍትሐ ብሔር ህግ የሚገዛ ሲሆን ለውርሱ ተፈፃሚነት ህጉ ያስቀመጣቸው መስፈርቶች መሟላት ይኖርባቸዋል፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ የኑዛዜ አይነቶች እና የኑዛዜ ማረጋገጫ በዝርዝር ይዳሰሳሉ፡፡
የኑዛዜ አይነቶች
በኢትዮጵያ ህግ 3 የኑዛዜ ዓይነቶች አሉ፡፡ ሁሉም የኑዛዜ አይነቶች መከትል ያለባቸው ፎርማሊቲዎች ወይም ቅድመ ሁኔታዎች በ1952 ዓ.ም በወጣው የፍትሐ ብሔር ህጋችን ውስጥ በዝርዝር የተቀመጡ ሲሆን መስፈርቶቹ ያልተሟሉ እንደሆነ ኑዛዜው በህግ ፊት ውድቅ (ፈራሽ) ይሆናል፡፡ ህጉ የመስፈርቶቹን መሟላት በተመለከተ ጥብቅ (strict) ነው፡፡ ይህም የሆነበት ዋና ምክንያት የኑዛዜ ቃል በሚፈፀምበት ወቅት ተናዛዡ በህይወት ስለማይኖር ትክክለኛ ሀሳቡን ማወቅ የሚቻለው ትቶት ከሄደው የኑዛዜ ሰነድ ብቻ ነው፡፡ ስለሆነም ይህ ሰነድ ደግሞ ለአፈፃፀም እንዲያመች መስፈርቶቹን በሙሉ ግልፅ በሆነ ሁኔታ መከተል አለበት፡፡ በፍ/ህ/አ 880 ስር እንደተደነገገው 3ቱ የኑዛዜ አይነቶች
1. በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ (public will)
2. በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜ (holographic will)
3. በቃል የሚደረግ ኑዛዜ (oral will) ናቸው
• በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ ( የፍ/ብ/ህገ/ቁጥር 881-883)
በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ ተናዛዡ እየተናገረ ሌላ ሰው የሚፅፈው ወይም ተናዛዡ ራሱ የሚፅፈው የኑዛዜ አይነት ነው፡፡ ይህ ኑዛዜ በተናዛዡ ወይም በሌላ ሰው ከተፃፈ በኃላ ተናዛዡ እና ምስክሮች ባሉበት መነበብ አለበት፡፡ በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ ተቀባይነት እንዲኖረው ተናዛዡና ምስክሮች ባሉበት መነበቡ ብቻ በቂ አይደለም፡፡ ይልቁንም ይህ መስፈርት (formality) መሟላቱ በኑዛዜው ላይ መስፈር አለበት፡፡ ይኸውም በኑዛዜው ላይ "ይህ ኑዛዜ ተናዛዡ እና ምስከሮች ባሉበት ተነቧል" ተብሎ መገለጽ አለበት፡፡ በግልፅ በሚደረግ ኑዛዜ ላይ የምስክሮች ብዛት 4(አራት) መሆን ሲኖርበት አራቱም ምስክሮች ኑዛዜው ተነቦላቸው በኑዛዜው ላይ ፊርማቸውን ወዲያውኑ ማስፈር አለባቸው፡፡ በተጨማሪም በኑዛዜው ላይ ኑዛዜው የተደረገበት ቀን ማለትም ቀን፣ ወር፣ ዓመተ ምህረት መፃፍ አለበት፡፡
የምስክሮችን ብዛት በተመለከተ በግልፅ ለሚደረግ ኑዛዜ ከምስክሮቹ መካከል አንዱ ዳኛ ወይም ውል ለማዋዋል ሥልጣን የተሰጠው ሰው ሆኖ ኑዛዜውም የተደረገው ይህ ዳኛ ወይም ለማዋዋል ሥልጣን የተሰጠው ሰው ሥራቸውን በሚያካሄዱበት ክፍል ውስጥ የሆነ እንደሆነ ለኑዛዜው ዋጋ ማግኘት ሁለት ምስክሮች ብቻ በቂ ናቸው፡፡
በአጠቃላይ በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ የሚከተሉትን ፎርማሊቲዎች መከተል አለበት፡፡
በተናዛዡ በራሱ ወይም እሱ እየተናገረ በሌላ ሰው ሊፃፍ ይችላል
ተናዘዡና አራት ምስክሮች ባሉበት መነበብ አለበት
በኑዛዜው ላይ ተናዛዡና ምስክሮቹ ባሉበት መነበቡ በግልፅ መፃፍ አለበት
ኑዛዜው የተደረገበት ቀን፣ ወር እና ዓ.ም መፃፍ አለበት
አራት ምስክሮች መኖር አለባቸው፣
ተናዛዡና ምስክሮች ኑዛዜው እንደ ተነበበላቸው ወዲያውኑ ፊርማቸውን ወይም የጣት አሻራቸውን ማሳረፍ አለባቸው
በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ ምስክሮች አካለመጠንን የደረሱ (18 ዓመት የሞላቸው) ወይም በህግ ያልተከለከሉ መሆን አለባቸው
ምስክሮች ኑዛዜው የተፃፈበትን ቋንቋ ለማወቅና የተፃፈውን ለመስማት ወይም ለማንበብ ራሳቸው ችሎታ ያላቸው መሆን አለባቸው፡፡
እነዚህ ከላይ የተመለከቱት መስፈርቶች ካልተሟሉ ኑዛዜው ፈራሽ ይሆናል፡፡ ፍርድ ቤቶችም የኑዛዜ ቃልን ለማስፈፀም መሟላት ያለባቸው መስፈርቶችን በጥብቅ የሚቆጣጠሩ ሲሆን መስፈርቶቹ ካልተሟሉ ኑዛዜውን ውድቅ ያደርጉታል፡፡
• በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜ (የፍ/ብ/ህገ/ቁጥር 883-891)
በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደርግ ኑዛዜ ሙሉ በሙሉ በተናዛዡ የሚፃፍ የኑዛዜ አይነት ነው፡፡ ይህን የኑዛዜ አይነት የሚያደርገው የተማረ ወይም ኑዛዜው የሚፃፍበትን ቋንቋ መፃፍና ማንበብ በሚችል ሰው ሲሆን የምስክሮችን መኖር የሚፈልግ አይደለም፡፡ በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜ በተናዛዡ የእጅ ፅሁፍ ወይም በማሽን (በኮምፒዩተር) ሊፃፍ ይችላል፡፡ ተናዛዡ ኑዛዜውን በኮምፒዩተር የሚፅፈው ከሆነ በእያንዳንዱ ገፅ ላይ እራሱ ስለመፃፉ በእጅ ፅሁፉ ማመልከት አለበት፡፡ ይህም ኑዛዜውን ያደረገው ተናዛዡ እንደሆነ ለማረጋገጥ ይረዳል፡፡ ኑዛዜው በማሽንም ሆነ በእጅ ቢፃፍ ተናዛዡ በእንዳንዱ ገፅ ላይ ቀን ፅፎ ፊርማውን ማስፈር ይኖርበታል፡፡ በተጨማሪም በኑዛዜ ሰነድ ላይ ተናዛዡ ይህ ሰነድ "ኑዛዜ" ነው በማለት በግልፅ መግለፅ አለበት፡፡ እነዚህ መስፈርቶች ካልተሟሉ ኑዛዜው ፈራሽ ነው፡፡ በተጨማሪ በተናዛዡ ፅህፈት የሚደረግ ኑዛዜ ኑዛዜው በተደረገ በሰባት(7) ዓመት ውስጥ ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው ሰው ወይም ፍርድ መዝገብ ቤት መቀመጥ አለበት፡፡
በአጠቃላይ በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜ በህግ ፊት ተቀባይነት እንዲያገኝ እና ተፈፃሚነት እንዲኖረው የሚከተሉት መስፈርቶች በሙሉ መሟላት አለባቸው፡፡
ሙሉ ለሙሉ በተናዛዡ መፃፍ አለበት
በኑዛዜው ላይ በግልፅ "ይህ ሰነድ የኑዛዜ ሰነድ ነው "ተብሎ መገለፅ አለበት
በተናዛዡ በአያንዳንዱ ገፅ ላይ ቀን እና ፊርማ መስፈር አለበት
ኑዛዜው በተደረገ በሰባት አመት ውስጥ ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ዘንድ መቀመጥ አለበት፣( የፍ/ብ/ህገ/ቁጥር 903)
ተናዛዡ ግልፅ በሆነ ፊርማው ካላፀደቃቸው በስተቀር የተናዛዡን ፈቃድ ለመለወጥ የሚችል ፍቀት፣ ስርዝ ወይም ድልዝ ያለባቸው ኑዛዜዎች ፈራሽ ናቸው፡፡
ከእነዚህ ከላይ ከተገለፁት መስፈርቶች ውስጥ አንዱ ወይም ከአንድ በላይ ካልተሟላ ኑዛዜው ፈራሽ ይሆናል ወይም ተፈፃሚነት አይኖረውም፡፡ ነገር ግን ኑዛዜ ፈራሽ ሆነ ማለት ወራሾች ንብረት አያገኙም ማለት አይደለም፡፡ ይልቁንም ውርሱ በቁጥር 842 እና ተከታዮቹ መሰረተ ሳይናዘዝ የሞተ ሰው ውርስ በሚተላለፍበት ሂደት የሚተላለፍ ይሆናል፡፡
የቃል ኑዛዜ (የፍ/ብ/ህገ/ቁጥር 892-894)
የቃል ኑዛዜ ማለት አንድ ሰው የሞቱ መቃረብ ተሰምቶት የመጨረሻ የፍቃድ ቃሎቹን ለሁለት ምስክሮች የሚሰጥበት የኑዛዜ አይነት ነው፡፡ ከፍ/ህ/ ቁጥር 892 እንደምንረዳው የቃል ኑዛዜ በመደበኛ ሁኔታ (under normal circumstances) የሚደረግ አይደለም፡፡ ተናዛዡ ይህን የኑዛዜ አይነት የሚያደርገው በቅርብ ጊዜ እሞታለው ብሎ ሲያስብ ለምሳሌ አደጋ ደርሶበት ፅኑ ህመም ውስጥ ሆኖ ሊሆን ይችላል፡፡ እንዲህ ባለጊዜ ሌሎቹን የኑዛዜ አይነቶች ማለትም በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜን ወይም በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜን ለማድረግ ሁኔታዎች አይፈቅዱለትም ማለት ነው፡፡ በመሆኑም በቃል የሚደረግ ኑዛዜ ላይ ተናዛዡ የሚናዘዘው በተገደበ ሁኔታ (restricted testamentary disposition) ይሆናል፡፡ በዚህ የኑዛዜ አይነት ተናዛዡ ሙሉ ፍላጎቱን ለማንፀባረቅ አይችልም፡፡ ምክንያቱም ህጉ ገደቦችን አስቀምጧል፡፡
በፍ/ሕ/ቁጥር 893 መሰረት አንድ ሰው የቃል ኑዛዜ ማድረግ የሚችለው በተለይ በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ ነው፡፡
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
የቀብሩን ሥነ-ሥርዓት የሚመለከቱትን ትዕዛዞች ለመስጠት
እያንዳንዱ ውርስ ከአምስት መቶ የኢትዮጵያ ብር የማይበልጥ የኑዛዜ ስጦታ ለማድረግ፣
አካለ መጠን ላላደረሱ ልጆቹ አስተዳዳሪን ወይም ሞግዚትን የሚመለከቱ ውሳኔዎችን ለመስጠት ነው፡፡
በቃል የሚደረግ ኑዛዜ ውስጥ ከብር አምስት መቶ በላይ ኑዛዜ ተደርጎ ከሆነ ከአምስት መቶ ብር በላይ ያለው ተቀናሽ ይሆናል፡፡ በቃል የተደረገ ኑዛዜ ከተደረገበት ከሶስት ወር በኋላ ተናዛዡ በህይወት የቆየ እንደሆነ ኑዛዜው ተፈፃሚ አይሆንም ወይም ፈራሽ ይሆናል፡፡ ምክንያቱም ተናዛዡ ያንያህል ጊዜ ሳይሞት ከቆየ በግልጽ የሚደረግ ኑዛዜን ወይም በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜን ለማድረግ እድል አለው ተብሎ ይገመታል፡፡
በሌላ በኩል ብዙ ኑዛዜዎች ካሉ አብሮ ተፈፃሚ ሊሆኑ በሚችሉበት መጠን ልዩ ልዩ ኑዛዜዎች አብረው ተፈጻሚ ይሆናሉ፡፡ ነገር ግን የሁለት ኑዛዜዎች ቃላት ሁለቱም ሊፈፀሙ ያልቻሉ ወይም የተቃረኑ እንደሆነ በኋላ የተደረገው ኑዛዜ ቅድሚያ ይሰጠዋል፡፡
በአጠቃላይ ንብረቱን በኑዛዜ ማስተላለፍ የሚፈልግ ሰው ሶስቱን የኑዛዜ አይነቶች ፎርማሊቲያቸውን በሟሟላት እንደየሁኔታው ሊጠቀምባቸው ይችላል፡፡ ኑዛዜ አድራጊው የኑዛዜ ቃላት ተፈፃሚነት እንዲያገኙ በህጉ የተቀመጡትን መስፈርቶች በጥንቃቄ መከተል አለበት፡፡ ይህ ካልሆነ ኑዛዜው ውድቅ ስለሚሆን የተናዛዡ ፍላጎት ተፈፃሚ አይሆንም ማለት ነው፡፡
የኑዛዜ ማስረጃ ወይም ማረጋገጫ
በኑዛዜው የሰፈረውን ቃልና ኑዛዜው መኖሩን ማስረዳት ያለበት በዚህ ኑዛዜ ተጠቃሚ ነኝ የሚለው ሰው ነው፡፡ በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ ወይም በተናዛዡ ፅሁፍ የተደረገ ኑዛዜ መኖር የሚረጋገጠው የኑዛዜውን ፅሁፍ ዋናውን በማቅረብ ወይም ለማዋውል ስልጣን በተሰጠው ሰው ዘንድ ወይም ፍርድ መዝገብ ቤት ሹም ተክክለኛ ሆኖ የተመሰከረ አንድ ግልባጭ በማቅረብ ነው፡፡ ኑዛዜዎቹን ለማስፈፀም በማናቸውም ሌላ መንገድ ለማስረዳት አይቻልም፡፡ ነገር ግን በጥፋት ወይም በቸልተኝነት ኑዛዜው እንዲጠፋ ካደረገ ሰው የጉዳት ኪሳራ ለማግኘት ከሆነ በማናቸውም አይነት መንገድ ኑዛዜዎችን ማስረዳት ይቻላል፡፡
በአጠቃላይ በአንድ ኑዛዜ ተጠቃሚ ነኝ የሚል ሰው ሁለት ነገሮችን በመሰረታዊነት ማስረዳት ያለበት ሲሆን እነሱም በተናዛዡ የተደረገውን ኑዛዜ በማቅረብ የኑዛዜን መኖር እና የኑዛዜውን ይዘት በማስረዳት ማለትም እሱ የኑዛዜው ተጠቃሚ (beneficiary) መሆኑን ማስረዳት ናቸው፡፡
በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልተጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
https://t.me/lawsocieties
እያንዳንዱ ውርስ ከአምስት መቶ የኢትዮጵያ ብር የማይበልጥ የኑዛዜ ስጦታ ለማድረግ፣
አካለ መጠን ላላደረሱ ልጆቹ አስተዳዳሪን ወይም ሞግዚትን የሚመለከቱ ውሳኔዎችን ለመስጠት ነው፡፡
በቃል የሚደረግ ኑዛዜ ውስጥ ከብር አምስት መቶ በላይ ኑዛዜ ተደርጎ ከሆነ ከአምስት መቶ ብር በላይ ያለው ተቀናሽ ይሆናል፡፡ በቃል የተደረገ ኑዛዜ ከተደረገበት ከሶስት ወር በኋላ ተናዛዡ በህይወት የቆየ እንደሆነ ኑዛዜው ተፈፃሚ አይሆንም ወይም ፈራሽ ይሆናል፡፡ ምክንያቱም ተናዛዡ ያንያህል ጊዜ ሳይሞት ከቆየ በግልጽ የሚደረግ ኑዛዜን ወይም በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜን ለማድረግ እድል አለው ተብሎ ይገመታል፡፡
በሌላ በኩል ብዙ ኑዛዜዎች ካሉ አብሮ ተፈፃሚ ሊሆኑ በሚችሉበት መጠን ልዩ ልዩ ኑዛዜዎች አብረው ተፈጻሚ ይሆናሉ፡፡ ነገር ግን የሁለት ኑዛዜዎች ቃላት ሁለቱም ሊፈፀሙ ያልቻሉ ወይም የተቃረኑ እንደሆነ በኋላ የተደረገው ኑዛዜ ቅድሚያ ይሰጠዋል፡፡
በአጠቃላይ ንብረቱን በኑዛዜ ማስተላለፍ የሚፈልግ ሰው ሶስቱን የኑዛዜ አይነቶች ፎርማሊቲያቸውን በሟሟላት እንደየሁኔታው ሊጠቀምባቸው ይችላል፡፡ ኑዛዜ አድራጊው የኑዛዜ ቃላት ተፈፃሚነት እንዲያገኙ በህጉ የተቀመጡትን መስፈርቶች በጥንቃቄ መከተል አለበት፡፡ ይህ ካልሆነ ኑዛዜው ውድቅ ስለሚሆን የተናዛዡ ፍላጎት ተፈፃሚ አይሆንም ማለት ነው፡፡
የኑዛዜ ማስረጃ ወይም ማረጋገጫ
በኑዛዜው የሰፈረውን ቃልና ኑዛዜው መኖሩን ማስረዳት ያለበት በዚህ ኑዛዜ ተጠቃሚ ነኝ የሚለው ሰው ነው፡፡ በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ ወይም በተናዛዡ ፅሁፍ የተደረገ ኑዛዜ መኖር የሚረጋገጠው የኑዛዜውን ፅሁፍ ዋናውን በማቅረብ ወይም ለማዋውል ስልጣን በተሰጠው ሰው ዘንድ ወይም ፍርድ መዝገብ ቤት ሹም ተክክለኛ ሆኖ የተመሰከረ አንድ ግልባጭ በማቅረብ ነው፡፡ ኑዛዜዎቹን ለማስፈፀም በማናቸውም ሌላ መንገድ ለማስረዳት አይቻልም፡፡ ነገር ግን በጥፋት ወይም በቸልተኝነት ኑዛዜው እንዲጠፋ ካደረገ ሰው የጉዳት ኪሳራ ለማግኘት ከሆነ በማናቸውም አይነት መንገድ ኑዛዜዎችን ማስረዳት ይቻላል፡፡
በአጠቃላይ በአንድ ኑዛዜ ተጠቃሚ ነኝ የሚል ሰው ሁለት ነገሮችን በመሰረታዊነት ማስረዳት ያለበት ሲሆን እነሱም በተናዛዡ የተደረገውን ኑዛዜ በማቅረብ የኑዛዜን መኖር እና የኑዛዜውን ይዘት በማስረዳት ማለትም እሱ የኑዛዜው ተጠቃሚ (beneficiary) መሆኑን ማስረዳት ናቸው፡፡
በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልተጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ጠበቃ ወንድሙ ኢብሳን በተመለከተ እስር ከተፈፀመባቸው ግዜ ጀምሮ ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለ ይገኛል::
-----------------------------------
ጠበቃ ወንድሙ ኢብሳ ጉዳዩ አሁንም በፍርድ (በይግባኝ ሂደት) ላይ ያለ እንደመሆኑ መጠን ማህበሩ በጉዳዩ ላይ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥቦ ቆይቷል::
በዚህም በታሰሩበት ኦሮሚያ ክልል ፍርድ ቤቶች ላይ ፍቃድ ያላቸውን ሁለት ጠበቆች ማህበሩ በመመደብ ተገቢው የህግ ሂደት እየተፈፀመ ይገኛል:: ከዚህ በተጨማሪ ማህበሩ የጉዳዩን ትክክለኛ ምክንያት ከተለያዩ አካላት ለማጥራትና ለማረጋገጥ ጥረቶችን ሲያደርግ ቆይቷል::
የይግባኝ ክርክሩም በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍ/ቤት በመጪው እሮብ ታህሳስ 26 ቀን 2015 ይሰማል::
የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር በአዋጅ ቁ. 1249/2013 ከተሰጡት ስልጣንና ተግባራት ዋነኛው የህግ የበላይነት መከበር ጋር የተያያዙ ተግባራት መሆናቸው እንዳሉ ሆኖ ጠበቆች በሀገራችን የህግ ስርአት ላይ የሚኖራቸውን የጎላ ሚና መወጣት እንዲችሉ እና ለደንበኞቻቸው ጥራት ያለው የህግ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስችሏቸው መብቶች መከበራቸውን የማረጋገጥ ሀላፊነት አለበት::
በጉዳዩ ላይ ማህበሩ ተገቢውን ክትትል እያደረገ የሚቀጥል ሲሆን በቀጣይ ተቋሙ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር በተገቢው የሚሄድበት መሆኑንና የሚደረስባቸው ሂደቶች በይፋ እንደሚገልፅ ያሳውቃል::
የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር
ታህሳስ 23 2015ዓ.ም
https://t.me/lawsocieties
-----------------------------------
ጠበቃ ወንድሙ ኢብሳ ጉዳዩ አሁንም በፍርድ (በይግባኝ ሂደት) ላይ ያለ እንደመሆኑ መጠን ማህበሩ በጉዳዩ ላይ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥቦ ቆይቷል::
በዚህም በታሰሩበት ኦሮሚያ ክልል ፍርድ ቤቶች ላይ ፍቃድ ያላቸውን ሁለት ጠበቆች ማህበሩ በመመደብ ተገቢው የህግ ሂደት እየተፈፀመ ይገኛል:: ከዚህ በተጨማሪ ማህበሩ የጉዳዩን ትክክለኛ ምክንያት ከተለያዩ አካላት ለማጥራትና ለማረጋገጥ ጥረቶችን ሲያደርግ ቆይቷል::
የይግባኝ ክርክሩም በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍ/ቤት በመጪው እሮብ ታህሳስ 26 ቀን 2015 ይሰማል::
የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር በአዋጅ ቁ. 1249/2013 ከተሰጡት ስልጣንና ተግባራት ዋነኛው የህግ የበላይነት መከበር ጋር የተያያዙ ተግባራት መሆናቸው እንዳሉ ሆኖ ጠበቆች በሀገራችን የህግ ስርአት ላይ የሚኖራቸውን የጎላ ሚና መወጣት እንዲችሉ እና ለደንበኞቻቸው ጥራት ያለው የህግ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስችሏቸው መብቶች መከበራቸውን የማረጋገጥ ሀላፊነት አለበት::
በጉዳዩ ላይ ማህበሩ ተገቢውን ክትትል እያደረገ የሚቀጥል ሲሆን በቀጣይ ተቋሙ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር በተገቢው የሚሄድበት መሆኑንና የሚደረስባቸው ሂደቶች በይፋ እንደሚገልፅ ያሳውቃል::
የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር
ታህሳስ 23 2015ዓ.ም
https://t.me/lawsocieties
ሰ-መ-ቁ 231739 ጥቅምት 04 ቀን 2015 ዓ.ም
በሰው የመነገድ እና ሰውን በሕገወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1178/2012 በመተላለፍ የሚቀርቡ የወንጀል ክሶች በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶች መታየት ያለባቸው በሶስት ዳኞች ነው።
ምንም እንኳን ይህ አዋጁ በሶስት ዳኞች የሚታዩ በማለት የለየው በአንቀጽ 4(2) እና አንቀጽ 8(3) የተመለከቱ ጉዳዮችን ቢሆንም በፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 መሠረት በማድረግ የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሶስት ዳኞች ስለሚታዩ ጉዳዮች ለመደንገግ የወጣው መመሪያ ቁጥር 009/2013 ዓ.ም የሕገወጥ ሰዎች ዝውውር እና ሰዎችን በሕገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ጉዳዮች በፌዴራሉ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በሶስት ዳኞች የሚታዩ መሆኑ በግልጽ የደነገገ በመሆኑ አዋጅ ቁጥር 1178/2012 በመተላለፍ የሚቀርቡ ሁሉም የወንጀል ክሶች መታየት ያለባቸው ያለ ልዩነት በሶስት ዳኞች ነው።
በሰው የመነገድ እና ሰውን በሕገወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1178/2012 በመተላለፍ የሚቀርቡ የወንጀል ክሶች በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶች መታየት ያለባቸው በሶስት ዳኞች ነው።
ምንም እንኳን ይህ አዋጁ በሶስት ዳኞች የሚታዩ በማለት የለየው በአንቀጽ 4(2) እና አንቀጽ 8(3) የተመለከቱ ጉዳዮችን ቢሆንም በፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 መሠረት በማድረግ የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሶስት ዳኞች ስለሚታዩ ጉዳዮች ለመደንገግ የወጣው መመሪያ ቁጥር 009/2013 ዓ.ም የሕገወጥ ሰዎች ዝውውር እና ሰዎችን በሕገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ጉዳዮች በፌዴራሉ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በሶስት ዳኞች የሚታዩ መሆኑ በግልጽ የደነገገ በመሆኑ አዋጅ ቁጥር 1178/2012 በመተላለፍ የሚቀርቡ ሁሉም የወንጀል ክሶች መታየት ያለባቸው ያለ ልዩነት በሶስት ዳኞች ነው።
በውልና ማስረጃ ምዝገባ ጽ/ቤት ፊት የቤት ሽያጭ ውል ተደርጎ እንደገና በዚያው ቤት ላይ በሌላ ቀን የመንደር ውል የሽያጭ ስምምነት ተደርጎ በፍርድ ቤት ክስ ሲቀርብ የመንደር የሽያጩ ውሉ በግልጽ ካልተካደ ህጋዊ ውጤት አለው።
በዚህ መዝገብ ተጠሪዎች (ሻጭ) እና አመልካች (ገዢ) በቀን 23/04/2010 ዓ/ም የመኖሪያ ቤት በብር 600,000 (ስድስት መቶ ሺ ብር) ለመሸጥ በውልና ማስረጃ ምዝገባ ጽ/ቤት ፊት የሽያጭ ውል አድርገዋል። እንደገና ይህንኑ ቤት በብር 1,300,000,00 (አንድ ሚሊየን ሶስት መቶ ሺህ ብር) ለመሸጥ በቀን 01/05/2010 ዓ/ም የመንደር ውል አድርገዋል።
ሻጭ ያልተከፈለ ቀሪ ብር 860,000.00(ስምንት መቶ ስልሳ ሺህ ብር) እንዲከፈላቸው ክስ ሲያቀርቡ ገዥ የሽያጭ ውል ስምምነት ሻጭ እንደሚሉት በቀን 01/05/2010 ዓ/ም የተደረገ ሳይሆን በቀን 23/04/2010 ዓ/ም ተደርጎ በውልና ሰነዶች ማረጋገጫ የፀደቀ ነው፡፡ በቀን 01/05/2010 ዓ/ም የተደረገ የቤት ሽያጭ ዉል ነዉ በማለት ተጠሪዎች ያቀረቡት ውል በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 1720 እና 1721 መሰረት ረቂቅ ሰነድ ነዉ፡፡ በመሆኑም ተጠሪዎች ብር 860,000.00 ይከፈለን በማለት ያቀረቡት ክስ ሙሉ በሙሉ ዉድቅ ሊሆን ይገባል በማለት ተከራክሯል፡፡
አቤቱታው የቀረበው ገዥ የመንደር ውሉን አልካዱም በሚል ቀሪ ገንዘቡን እንዲከፍሉ የሲዳማ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰጠው ውሳኔ ቅር በመሰኘት ሲሆን የፌዴራሉ የሰበር ችሎትም ገዥ ውሉን አልካዱም በሚል በክልሉ ሰበር ችሎት የተሰጠው ውሳኔ የህግ ስህተት የለበትም በማለት አጽንቶታል።
የሰ/መ/ቁጥር 216608 ጥቅምት 03 ቀን 2015 ዓ/ም
https://t.me/lawsocieties
በዚህ መዝገብ ተጠሪዎች (ሻጭ) እና አመልካች (ገዢ) በቀን 23/04/2010 ዓ/ም የመኖሪያ ቤት በብር 600,000 (ስድስት መቶ ሺ ብር) ለመሸጥ በውልና ማስረጃ ምዝገባ ጽ/ቤት ፊት የሽያጭ ውል አድርገዋል። እንደገና ይህንኑ ቤት በብር 1,300,000,00 (አንድ ሚሊየን ሶስት መቶ ሺህ ብር) ለመሸጥ በቀን 01/05/2010 ዓ/ም የመንደር ውል አድርገዋል።
ሻጭ ያልተከፈለ ቀሪ ብር 860,000.00(ስምንት መቶ ስልሳ ሺህ ብር) እንዲከፈላቸው ክስ ሲያቀርቡ ገዥ የሽያጭ ውል ስምምነት ሻጭ እንደሚሉት በቀን 01/05/2010 ዓ/ም የተደረገ ሳይሆን በቀን 23/04/2010 ዓ/ም ተደርጎ በውልና ሰነዶች ማረጋገጫ የፀደቀ ነው፡፡ በቀን 01/05/2010 ዓ/ም የተደረገ የቤት ሽያጭ ዉል ነዉ በማለት ተጠሪዎች ያቀረቡት ውል በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 1720 እና 1721 መሰረት ረቂቅ ሰነድ ነዉ፡፡ በመሆኑም ተጠሪዎች ብር 860,000.00 ይከፈለን በማለት ያቀረቡት ክስ ሙሉ በሙሉ ዉድቅ ሊሆን ይገባል በማለት ተከራክሯል፡፡
አቤቱታው የቀረበው ገዥ የመንደር ውሉን አልካዱም በሚል ቀሪ ገንዘቡን እንዲከፍሉ የሲዳማ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰጠው ውሳኔ ቅር በመሰኘት ሲሆን የፌዴራሉ የሰበር ችሎትም ገዥ ውሉን አልካዱም በሚል በክልሉ ሰበር ችሎት የተሰጠው ውሳኔ የህግ ስህተት የለበትም በማለት አጽንቶታል።
የሰ/መ/ቁጥር 216608 ጥቅምት 03 ቀን 2015 ዓ/ም
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
እንደ አማርኛ #ሀ እና እነደ እንግሊዝኛዋ #r አሽቃባጭ አላየሁም!
ተመልከቱልኝ ለሃብታሞች በየት ለድሃዎች በየት እንደሚገቡ
https://t.me/lawsocieties
ተመልከቱልኝ ለሃብታሞች በየት ለድሃዎች በየት እንደሚገቡ
https://t.me/lawsocieties
*1. ለወታደር:(ለሰላም(ለሉአላዊነት)
2. ለመምህር:(ለእውቀት)
3. ለዶክተር:(ለጤና)
4. ለዳኛ:(ለፍትህ ስርዓት ቤተሰብ) ለህግ
ዋጋ ያልሰጠች እና ክብር የሌላት አገር መጨረሻዋ ምንም ነው‼️
#አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties
2. ለመምህር:(ለእውቀት)
3. ለዶክተር:(ለጤና)
4. ለዳኛ:(ለፍትህ ስርዓት ቤተሰብ) ለህግ
ዋጋ ያልሰጠች እና ክብር የሌላት አገር መጨረሻዋ ምንም ነው‼️
#አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
#አለ_ህግ #Ale_Hig, ነፃ የህግ የማማከር አገልግሎት፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎች፣ ክሶች፣ የውል ፎርሞች፤ መፅሐፍቶች https://www.youtube.com/@Lawsocieties ሁሉንም ሕጎችና ባለሙያዎች እዚሁ ያገኛሉ🔴 All in one, for All. መሰረታዊ የህግ መረጃ እውቀት፤ ሀብት እና ሀይል ነው @LawsocietiesBot / lawsocieties@gmail.com
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
አንድ ሰው "መንግስት በጣም አዋጪ ለሆኑ ፕሮጀክቶቹ ገንዘብ በብዛት አትሞ በፍጥነት ቢሰራበት ችግሩ ምንድን ነው?"
ለጠየቀው ጥያቄ፣ ከኢኮኖሚ #ህግ አንፃር የተሰጠ ማብራሪያ፡፡
ገንዘብ #እንደፈለጉ በማተም የሚያስፈልጉ ወጪዎችን መሸፈን ይቻላል!
ነገር ግን አዲስ የሚታተመው ገንዘብ ኢኮኖሚው ከሚሸከመው የገንዘብ መጠን በላይ ከሆነ (መታተም ካለበት ዝቅተኛ መጠን ከበለጠ) እና ገንዘቡ ታትሞ የሚያርፍበት ሴክተር እና የአዲሱ ገንዘብ የስርጭት ሂደት ያልተጠና ሲሆን ነው አዲስ የሚታተመው ገንዘብ ችግር መሆን የሚጀምረው፡፡
.........................
በኢኮኖሚክስ አስተምሮት ገንዘብ በዘፈቀደ ሊታተም እና ሊሰራጭ አይችልም (በኢኮኖሚ እና በፖለቲካ አስተዳደር ደካማነት ብዙ ገንዘብ ማተም የፈለገ ሀገር መብቱ ነው! ነገር ግን በዋጋ ንረት ዋጋ የሚከፍለው ኢኮኖሚው ነው)፡፡ ገንዘብ ለአንድ ኢኮኖሚ አስፈላጊም አደጋም ነው! ለዚህም ሲባል የገንዘብ ፖሊሲ (Monetary policy) በጠንካራ ተቋማት (በዋናነት በብሄራዊ ባንክ) በከፍተኛ ክትትል እንቅስቃሴው እንዲመራ ይደረጋል፡፡
በኢኮኖሚክስ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት የተቀበለው ድንቁ ኢኮኖሚስት Milton Friedman በአንድ ሀገር የኢኮኖሚ ስርዓት ውስጥ የገንዘብ አቅርቦት ማደግ ያለበት በየዓመቱ ከጠቅላላው ምርት GDP ጋር ተመጣጣኝ በሆነ መጠን ወይም ፐርሰንት ነው (ስርዓቱ K-Percent Rule ይባላል) ስለዚህ የገንዘብ ኖት መጠን የሚወሰነው ጠቅላላ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ከሚኖረው እድገት እና እንቅስቃሴ አንጻር ከ3 ከመቶ ያልበለጠ ህትመት እንዲሆን ይመክራል፡፡
ጥያቄውን ያነሳልኝ ልጅ ኢኮኖሚክስን የተማረ ስላልነበር ለጠየቀው ጥያቄ መልስ መስጠት አለብኝ (እንዲሁም ኢኮኖሚክስን ላልተማራችሁ ሰዎች የሚረዳ ከሆነ) ጥያቄውን ለመመለስ ያህል…….....
የኢትዮጲያ ኢኮኖሚ በገበያው ያለው የቁሳቁስ እና የአገልግሎት አቅርቦት ከሰዎች የመግዛት ፍላጎት እና አቅም ጋር እየመዘነ ኢኮኖሚው በፈጠረው ሃብት አንጻር ተጨማሪ ገንዘብ ወደ ገበያው በተለያየ መንገድ መልቀቅ አለበት፡፡
ነገር ግን በተለይ የዋጋ ንረት ላለበት ኢኮኖሚ (ነባሩ የዋጋ ንረት ከገንዘብ ፈሰስ አንጻር የተባባሰ ከሆነ) ተጨማሪ ገንዘብ ተጨማሪ የሸማች አቅም በመጨመር ምርት በሚፈለገው ፍጥነት ወደ ገበያ ሳይመጣ ፉክክር እና ፍላጎትን በመፍጠር ያለው ምርት ላይ ዋጋ እንዲጨመር ሊያደርግ ይችላል (የዚህ አይነቱ አጋጣሚ በአንደኛው እና በሁለተኛው ጦርነት ወቅት በተወሰኑ የአውሮፓ ሀገራት፤ አፍሪካ ውስጥም በዝምባብዌ፤ በላይቤሪያ፤ ወዘተ ሆኖ ያውቃል)፡፡
#ለምሳሌ፡- መንግስት ግዙፍ የመስኖ ግድብን በመስራት 200ሺ ሄክታር የስንዴ ማሳን እስከማልማት የሚደርስን የፕሮጀክቱን ወጪ 20ቢሊየን ብር አትሞ ቢያዘጋጅ ብለን እናስብ፡፡ ቀጥታ ለመስኖ ግንባታ (ሲሚንቶ (የተወሰነ ግብዓት)፤ ብረት (የተወሰነ ግብዓት)፤ የግንባታ ማሽነሪ፤ ወዘተ) እና ለሰብል ዝግጅት (ምርጥ ዘር፤ የአፈር ማዳበሪያ፤ ለማጓጓዣ ነዳጅ፤ ጸረ-ሰብል መድሃኒት፤ ወዘተ) ኢኮኖሚው በብር ገዝቶ ማቅረብ ይችላል?
ስለዚህ ብር የሚያገለግለው ለሀገር ውስጥ ግብዓት (የውጪ ምንዛሬ ለማይጠይቁ ግብዓት ፍጆታ ካላቸው) እና የባለሙያ ክፍያ/የአገልግሎት ክፍያ ለመፈጸም ነው፡፡ ምክንያቱም የውጪ ምንዛሬ ለሚጠይቁ የፕሮጀክት ወጪዎች ብርን በቀጥታ መጠቀም ስለማይቻል ማለት ነው፡፡ ይህ ማለት በቂ የውጪ ምንዛሬ በሌለበት ብርን በማተም ብቻ ፕሮጀክቶችን ፋይናንስ በማድረግ ለማጠናቀቅ ከባድ ነው፡፡
ፕሮጀክቶች ለመጠናቀቅ ረጅም ጊዜ የመውሰድ ልምድ ስላላቸው እና አሁን በሀገራችን የሰዎች ቀጥተኛ ተሳትፎ በማሽኖች ስላልተተካ በየፕሮጀክቶቹ እና ለፕሮጀክቱ ግብዓት የሚያቀርቡ ተቋማት ከፍተኛ የሰው ሃይል ስለሆነ የሚጠቀሙት ከፍተኛ ክፍያ (በደሞዝ እና በስራ ማስኬጃ) በጠቅላላ ሂደቱ በሙሉ ይወጣል፡፡
ስለዚህ ለረጅም ጊዜ ለስራ ማስኬጃ የሚወጣው ወጪ ገበያ ውስጥ ለሸመታ በሚል ስለሚወጣ አቅርቦት እስካልተሻሻለ ያለው አነስተኛ አቅርቦት ላይ ገንዘብ ያላቸው ሸማቾች ሲጨመሩ ፉክክሩ እቃዎችን ከእጥረት የተነሳ ውድ እንዲሆኑ ያደርጋል፡፡
#ለምሳሌ፡- ይህ ፕሮጀክት እስኪጠናቀቅ ድረስ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ 10ሺ በቤታቸው/በቤተሰቦቻቸው ድጋፍ በቤት ያለስራ ተቀምጠው የነበሩ ወጣቶችን በወር የ5ሺ ብር ደሞዝተኛ ቢያድርግ፡ እነዚህ ሰዎች በየወሩ የ5ሺ ብር የአገልግሎትም ሆነ የቁሳቁስ ሸመታ ላይ ሊሳተፉ ይችላሉ! ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ምርት ወደ ገበያ ከማምጣቱ በፊት ወጣቶቹ ወደ ሸመታ በመግባታቸው ፉክክሩን በመጨመር ዋጋዎችን ከፍላጎት በተነሳ ምክንያት (Demand Pull Inflation) ውድ ሊያደርጉት ይችላሉ፡፡
በሌላ ጎን እነዚህ የ5ሺ ብር አዳዲስ ደሞዝተኞች የባንክ ደብተር አውጥተው በወር አንድ አንድ ሺ ብር ማስቀመጥ ቢጀምሩ ባንኮች የተቀበሉትን ቁጠባ በኢንቨስትመንት መልኩ ቢያበድሩት ድጋሚ ገንዘብ ወደ ገበያው ፈሰስ ሆኖ ተመሳሳይ ችግር ሊፈጥር ይችላል፡፡ በተለይ ገንዘብን በጥሬ ገንዘብነት መያዝ ለለመደ ማህበረሰብ ከባንኩ ቁጥጥር ውጪ የሚውለውን ገንዘብ መጠን ስለሚጨምረው የማክሮ ኢኮኖሚ ሚዛን መዛባቱ ሲባባስ በተለያዩ የMonetary ዘዴዎች ገንዘቡን ወደ ማዕከላዊ ባንኩ ለመሰብሰብ አስቸጋሪ ነው፡፡
አስተውሉ የታተመው ገንዘቡ ወደ ገበያ ሳይሰራጭ ለፕሮጀክት ብቻ ማዋል የሚባል አመክንዬ ሊኖር አይችልም! እንዲሁም የማክሮ ኢኮኖሚ ጉዳይ ሲወራ ስለጥቂት ሰዎች ሳይሆን ስለድምር ተጽዕኖው ነው የሚወራው፡፡ ምን ማለቴ ነው ? በቀላሉ ከላይኛው ምሳሌ በመነሳት ፕሮጀክቱ ሊኖር የሚችለው አንድ ቦታ ላይ ነው፡ ሰዎቹም 10ሺ ናቸው የሚል ክርክር ቢነሳ ጠንካራ አይደለም! ምክንያቱም የማክሮ ኢኮኖሚውም ሆነ የዋጋ ንረት የሚሰላው የየአካባቢዎቹን አማካይ ጥቅል ውጤት ተወስዶ ነው፡፡
#WaseAlpha
by Wase Belay
https://t.me/lawsocieties
ለጠየቀው ጥያቄ፣ ከኢኮኖሚ #ህግ አንፃር የተሰጠ ማብራሪያ፡፡
ገንዘብ #እንደፈለጉ በማተም የሚያስፈልጉ ወጪዎችን መሸፈን ይቻላል!
ነገር ግን አዲስ የሚታተመው ገንዘብ ኢኮኖሚው ከሚሸከመው የገንዘብ መጠን በላይ ከሆነ (መታተም ካለበት ዝቅተኛ መጠን ከበለጠ) እና ገንዘቡ ታትሞ የሚያርፍበት ሴክተር እና የአዲሱ ገንዘብ የስርጭት ሂደት ያልተጠና ሲሆን ነው አዲስ የሚታተመው ገንዘብ ችግር መሆን የሚጀምረው፡፡
.........................
በኢኮኖሚክስ አስተምሮት ገንዘብ በዘፈቀደ ሊታተም እና ሊሰራጭ አይችልም (በኢኮኖሚ እና በፖለቲካ አስተዳደር ደካማነት ብዙ ገንዘብ ማተም የፈለገ ሀገር መብቱ ነው! ነገር ግን በዋጋ ንረት ዋጋ የሚከፍለው ኢኮኖሚው ነው)፡፡ ገንዘብ ለአንድ ኢኮኖሚ አስፈላጊም አደጋም ነው! ለዚህም ሲባል የገንዘብ ፖሊሲ (Monetary policy) በጠንካራ ተቋማት (በዋናነት በብሄራዊ ባንክ) በከፍተኛ ክትትል እንቅስቃሴው እንዲመራ ይደረጋል፡፡
በኢኮኖሚክስ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት የተቀበለው ድንቁ ኢኮኖሚስት Milton Friedman በአንድ ሀገር የኢኮኖሚ ስርዓት ውስጥ የገንዘብ አቅርቦት ማደግ ያለበት በየዓመቱ ከጠቅላላው ምርት GDP ጋር ተመጣጣኝ በሆነ መጠን ወይም ፐርሰንት ነው (ስርዓቱ K-Percent Rule ይባላል) ስለዚህ የገንዘብ ኖት መጠን የሚወሰነው ጠቅላላ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ከሚኖረው እድገት እና እንቅስቃሴ አንጻር ከ3 ከመቶ ያልበለጠ ህትመት እንዲሆን ይመክራል፡፡
ጥያቄውን ያነሳልኝ ልጅ ኢኮኖሚክስን የተማረ ስላልነበር ለጠየቀው ጥያቄ መልስ መስጠት አለብኝ (እንዲሁም ኢኮኖሚክስን ላልተማራችሁ ሰዎች የሚረዳ ከሆነ) ጥያቄውን ለመመለስ ያህል…….....
የኢትዮጲያ ኢኮኖሚ በገበያው ያለው የቁሳቁስ እና የአገልግሎት አቅርቦት ከሰዎች የመግዛት ፍላጎት እና አቅም ጋር እየመዘነ ኢኮኖሚው በፈጠረው ሃብት አንጻር ተጨማሪ ገንዘብ ወደ ገበያው በተለያየ መንገድ መልቀቅ አለበት፡፡
ነገር ግን በተለይ የዋጋ ንረት ላለበት ኢኮኖሚ (ነባሩ የዋጋ ንረት ከገንዘብ ፈሰስ አንጻር የተባባሰ ከሆነ) ተጨማሪ ገንዘብ ተጨማሪ የሸማች አቅም በመጨመር ምርት በሚፈለገው ፍጥነት ወደ ገበያ ሳይመጣ ፉክክር እና ፍላጎትን በመፍጠር ያለው ምርት ላይ ዋጋ እንዲጨመር ሊያደርግ ይችላል (የዚህ አይነቱ አጋጣሚ በአንደኛው እና በሁለተኛው ጦርነት ወቅት በተወሰኑ የአውሮፓ ሀገራት፤ አፍሪካ ውስጥም በዝምባብዌ፤ በላይቤሪያ፤ ወዘተ ሆኖ ያውቃል)፡፡
#ለምሳሌ፡- መንግስት ግዙፍ የመስኖ ግድብን በመስራት 200ሺ ሄክታር የስንዴ ማሳን እስከማልማት የሚደርስን የፕሮጀክቱን ወጪ 20ቢሊየን ብር አትሞ ቢያዘጋጅ ብለን እናስብ፡፡ ቀጥታ ለመስኖ ግንባታ (ሲሚንቶ (የተወሰነ ግብዓት)፤ ብረት (የተወሰነ ግብዓት)፤ የግንባታ ማሽነሪ፤ ወዘተ) እና ለሰብል ዝግጅት (ምርጥ ዘር፤ የአፈር ማዳበሪያ፤ ለማጓጓዣ ነዳጅ፤ ጸረ-ሰብል መድሃኒት፤ ወዘተ) ኢኮኖሚው በብር ገዝቶ ማቅረብ ይችላል?
ስለዚህ ብር የሚያገለግለው ለሀገር ውስጥ ግብዓት (የውጪ ምንዛሬ ለማይጠይቁ ግብዓት ፍጆታ ካላቸው) እና የባለሙያ ክፍያ/የአገልግሎት ክፍያ ለመፈጸም ነው፡፡ ምክንያቱም የውጪ ምንዛሬ ለሚጠይቁ የፕሮጀክት ወጪዎች ብርን በቀጥታ መጠቀም ስለማይቻል ማለት ነው፡፡ ይህ ማለት በቂ የውጪ ምንዛሬ በሌለበት ብርን በማተም ብቻ ፕሮጀክቶችን ፋይናንስ በማድረግ ለማጠናቀቅ ከባድ ነው፡፡
ፕሮጀክቶች ለመጠናቀቅ ረጅም ጊዜ የመውሰድ ልምድ ስላላቸው እና አሁን በሀገራችን የሰዎች ቀጥተኛ ተሳትፎ በማሽኖች ስላልተተካ በየፕሮጀክቶቹ እና ለፕሮጀክቱ ግብዓት የሚያቀርቡ ተቋማት ከፍተኛ የሰው ሃይል ስለሆነ የሚጠቀሙት ከፍተኛ ክፍያ (በደሞዝ እና በስራ ማስኬጃ) በጠቅላላ ሂደቱ በሙሉ ይወጣል፡፡
ስለዚህ ለረጅም ጊዜ ለስራ ማስኬጃ የሚወጣው ወጪ ገበያ ውስጥ ለሸመታ በሚል ስለሚወጣ አቅርቦት እስካልተሻሻለ ያለው አነስተኛ አቅርቦት ላይ ገንዘብ ያላቸው ሸማቾች ሲጨመሩ ፉክክሩ እቃዎችን ከእጥረት የተነሳ ውድ እንዲሆኑ ያደርጋል፡፡
#ለምሳሌ፡- ይህ ፕሮጀክት እስኪጠናቀቅ ድረስ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ 10ሺ በቤታቸው/በቤተሰቦቻቸው ድጋፍ በቤት ያለስራ ተቀምጠው የነበሩ ወጣቶችን በወር የ5ሺ ብር ደሞዝተኛ ቢያድርግ፡ እነዚህ ሰዎች በየወሩ የ5ሺ ብር የአገልግሎትም ሆነ የቁሳቁስ ሸመታ ላይ ሊሳተፉ ይችላሉ! ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ምርት ወደ ገበያ ከማምጣቱ በፊት ወጣቶቹ ወደ ሸመታ በመግባታቸው ፉክክሩን በመጨመር ዋጋዎችን ከፍላጎት በተነሳ ምክንያት (Demand Pull Inflation) ውድ ሊያደርጉት ይችላሉ፡፡
በሌላ ጎን እነዚህ የ5ሺ ብር አዳዲስ ደሞዝተኞች የባንክ ደብተር አውጥተው በወር አንድ አንድ ሺ ብር ማስቀመጥ ቢጀምሩ ባንኮች የተቀበሉትን ቁጠባ በኢንቨስትመንት መልኩ ቢያበድሩት ድጋሚ ገንዘብ ወደ ገበያው ፈሰስ ሆኖ ተመሳሳይ ችግር ሊፈጥር ይችላል፡፡ በተለይ ገንዘብን በጥሬ ገንዘብነት መያዝ ለለመደ ማህበረሰብ ከባንኩ ቁጥጥር ውጪ የሚውለውን ገንዘብ መጠን ስለሚጨምረው የማክሮ ኢኮኖሚ ሚዛን መዛባቱ ሲባባስ በተለያዩ የMonetary ዘዴዎች ገንዘቡን ወደ ማዕከላዊ ባንኩ ለመሰብሰብ አስቸጋሪ ነው፡፡
አስተውሉ የታተመው ገንዘቡ ወደ ገበያ ሳይሰራጭ ለፕሮጀክት ብቻ ማዋል የሚባል አመክንዬ ሊኖር አይችልም! እንዲሁም የማክሮ ኢኮኖሚ ጉዳይ ሲወራ ስለጥቂት ሰዎች ሳይሆን ስለድምር ተጽዕኖው ነው የሚወራው፡፡ ምን ማለቴ ነው ? በቀላሉ ከላይኛው ምሳሌ በመነሳት ፕሮጀክቱ ሊኖር የሚችለው አንድ ቦታ ላይ ነው፡ ሰዎቹም 10ሺ ናቸው የሚል ክርክር ቢነሳ ጠንካራ አይደለም! ምክንያቱም የማክሮ ኢኮኖሚውም ሆነ የዋጋ ንረት የሚሰላው የየአካባቢዎቹን አማካይ ጥቅል ውጤት ተወስዶ ነው፡፡
#WaseAlpha
by Wase Belay
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/