አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
መቀለ ከተማ የስልክ አገልግሎት አገኘች።

በመቀለ ከተማ ተቋርጦ የነበረው የቴሌኮም አገልግሎት መጀመሩን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ተናገሩ።

በጦርነቱ ምክንያት ተቋርጦ የቆየው የስልክ አገልግሎት በዛሬው ዕለት መቐለ ላይ የተሳካ ጥሪ ማድረግ መቻሉን ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።

ኢትዮ ቴሌኮም 981 ኪሎ ሜትር የፋይበር ጥገና ተከናውኖ በ27 ከተሞች የስልክና ሌሎች የቴሌኮም አገልግሎቶችን ማስጀመር ተችሏል ብለዋል።

የቴሌኮም አገልግሎቱ ዳግም መጀመር በመቻሉ 61 የባንክ ቅርንጫፎችም ወደ ስራ እንዲገቡ ማድረግ እንደተቻለ ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ተናግረዋል።

EBC
እንኳን ደስ አላችሁ.... 🙏🙏🙏
🔷Supreme Court Of Oromia For Fresh Graduates

Position - Zonal Court Attorney

Required No:76
Qualification: LLB /Degree in Law
Experience: Not Required
     Apply here
       👇👇👇
https://shegerjobs.com/job/supreme-court-of-oromia/
Deadline: January 12/2023

Share for your friends
     👇👇👇
ዐቃቤ ሕግ አነስተኛ የቴምብር ቀረጥ ለመክፈል በማሰብ ንብረት ከሸጠችበት ትክክለኛ ዋጋ አሳንሳ ገልጻለች ባላት ግለሰብ ላይ ክስ መስርቷል፡፡

ዐቃቤ ህግ ሲፈን አበራ ገመቹ የተባለችው የ27 ዓመት ወጣት የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 አንቀጽ 123(1) (ለ) ስር የተደነገገውን በመተላለፍ የቴምብር ቀረጥ ላለመክፈል ወይም አነስተኛ የቴምብር ቀረጥ ለመክፈል በማሰብ የመኖሪያ ቤት ሽያጭ ከፈጸመችበት ትክክለኛ ዋጋ አሳንሳ በመግለጽ በመንግስት ጥቅም ላይ ጉዳት አድርሳለች ባላት ግለሰብ ላይ ነው ክስ የመሰረተው፡፡

የዐቃቤ ሕግ ክስ እንደሚያስረዳው ከሆነ ተከሳሽ መኖሪያ ቤቷን በተጨባጭ የሸጠችው በብር 7‚700.000 (ሰባት ሚሊዮን ሰባት መቶ ሺ) ሆኖ እያለ በሰነዶች ማረጋገጫ ፊት ቀርባ ስትዋዋል ባቀረበችው ሰነድ ግን በብር 1‚000‚000.00 (አንድ ሚሊዮን ብር) እንደሸጠች የገለጸች በመሆኑ እንዲሁም በሌላ የመኖሪያ ቤት ሽያጭ ቤቱን በተጨባጭ የሸጠችው በብር 17‚000.000 (አስራ ሰባት ሚሊዮን) ሆኖ እያለ በሰነዶች ማረጋገጫ ፊት ቀርባ ስትዋዋል ባቀረበችው ሰነድ በብር 1‚000‚000.00 (አንድ ሚሊዮን ብር) እንደሸጠች በመግለጽ የሰነዶቹን ትከክለኛ ባህሪ የደበቀች በመሆኑ ክስ ቀርቦባታል፡፡

በቀረበው ክስ ላይ ክርክር በመደረግ ላይ የሚገኝ ሲሆን ይህን ወንጀል ጨምሮ ተከሳሿ ከሌሎች ተከሳሾች ጋር በጋራ በአንድ መዝገብ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ክርክሩ በግልጽ ችሎት እተከናወነ ይገኛል፡፡
https://t.me/lawsocieties
በሲቪል መማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን የተዘጋጁት አራት መመሪያዎች በፍትህ ሚኒስቴር እና በባለስል መስሪያ ቤቱ ድህረ ገጽ ከተለቀቁበት ጊዜ አንስቶ ተግባራዊ ይሆናሉ፡፡
በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ  ወጥተው በፍትህ ሚንስቴር ቁጥር የተሰጣቸው መመሪያዎች ፡-
1.  ስለ ድርጅቶች መዋሃድ፣ መከፋፈል፣ መለወጥና መፍረስ የወጣ መመሪያ ቁጥር 936/2015
2.  የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በገቢ ማስገኛ ስራዎች ላይ የሚሰማሩበትን ሁኔታ ለመወሰኝ የወጣ መመሪያ ቁጥር 937/2015
3.  የአገር በቀል ድርጅቶች ምዝገባና አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 938/2015 እንዲሁም
4.  የጥቅም ግጭትን ለማስቀረት የወጣ መመሪያ ቁጥር 939/2015 የሚሉት ናቸው፡፡
ሙሉ መመሪያዎቹን በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ዌብሳይት፡- www.acso.gov.et
ሕጎች - ACSO
ወይም በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፍትህ ሚንስቴር ድህረ ገጽ
ህጎች (eag.gov.et)
ማግኘት የምትችሉ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡

https://t.me/lawsocieties
የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ሠራተኞቹ ከቢሮ ሳይወጡ ከ2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ አላግባብ አበል በልተዋል።


የማዕከሉ ሠራተኞች ባልተሳተፉበት ስብሰባ አበል ያወራርዱ እንደነበር እና ከሕግ አግባብ ውጭ የሆኑ ግዥዎች ሲፈጸሙ ነበር ተብሏል፡፡

በዚህም ከ46 ሺሕ ብር በላይ ከመስሪያ ቤቱ ውጭ ላሉ ባለሙያዎች ክፍያ ተፈጽሟል የተባለ ሲሆን፣ ከ204 ሺሕ ብር በላይም ለጸረ ሙስና ኮሚሽን ባለሙያ በሕግ አግባብ ውጭ የተከፈለ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

አዲስ ማለዳ
via #housinginaddisababa
https://t.me/lawsocieties
በስልካችን ላይ ሊኖሩ የማይገቡ አደገኛ መተግበሪያዎቸ

በውስጣቸው አጥፊ ቫይረሶችን የያዙ ነገር ግን አገልግሎት የሚሰጡ በመመስል የተሰሩ መተግበሪያዎች አሉ። ቀጥለው የተዘረዘሩ መተግበሪያዎች በስልኮቻችን ላይ ካሉ ልናጠፋቸው ይገባል።
የመተግበሪዎቹን መጠሪያ በተከታዩ ሊንክ ያገኛሉ፤ https://am.al-ain.com/article/apps-you-have-delete-from-smartphones
የወንጀል ህግ ምንነት እና አላማው
 ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የሰው ልጅ ሠላማዊ ህይወትን ለመምራት ከወንጀል የፀዳ ህብረተሠብ መፍጠር አለበት፡፡ ለዚህ ደግሞ ያለው አማራጭ የወንጀል ፍትህ አስተዳደርን መዘርጋት ነው፡፡ ይህ የወንጀል ፍትህ አስተዳደር እንዲኖር ህግ አውጭ፣ ህግ ተርጓሚና አስፈፃሚ አካላት መኖር አለባቸው፡፡ በዚሁ መሠረት ህግ አውጪው እንደ ወንጀል አድርጐ የሚቆጥራቸው ድርጊቶች እና ተገቢ ብሎ ያመነባቸውን ቅጣቶች ዘርዝሮ በህግ ያወጣል፤ ህግ ተርጓሚው ወንጀል ፈፅመዋል ተብለው የተከሰሱ ሠዎችን ሲቀርቡለት ማስረጃውን አዳምጦ ተገቢውን ውሣኔ ይሰጣል፡፡ አስፈፃሚው አካል በፖሊስ አማካኝነት ወንጀል እንዳይፈፀም ይከላከላል ተፈፅሞም ከሆነ ተጠርጣሪዎች ይዞ ለፍርድ ያቀርባል፡፡ ዓቃቤ ህግ መንግስትን በመወከል ክስ ያቀርባል፡፡ ማረሚያ ቤቶች ቅጣት የተወሰነባቸውን ጥፋተኞች ተቀብለው ያሰራሉ ሌሎች ቅጣቶችም ተወስነው ከሆነ ያስፈፅማሉ፡፡
ስለሆነም የወንጀል ህግና የወንጀል የፍትህ አስተዳደር መሠረታዊ አላማዎች የወንጀል አይነቶችን አስቀድሞ በማሣወቅ የአንድ ህብረተሠብ አባላት ይህንን አውቀው ከጥፋት እንዲታቀቡ ማድረግና ይህን ማስጠንቀቂያ በማይከተሉ ላይ ቅጣት መፈፀም ናቸው፡፡ በዚህም መሠረት የወንጀል ህግ የተለያዩ የህብረተሠብ አባላት ማለትም ሰዎች ከሠዎች ወይም ከቡድኖች ወይም ከመንግስት ጋር ያላው ግንኙነት ይወስናል፡፡ በህግ እውቅና በተሠጠው ግንኙነት መሠረት ድርጊታቸውን ማስተካከል የሚችሉ ህጉ ተፈፃሚ የማይሆንባቸው ሲሆን ይህን ማድረግ የማይቻላቻው በህጉ መሠረት ይዳኛሉ፡፡
ኢትዮጵያ ከላይ የተጠቀሰውን አላማ ለማሣካት በተለያዩ ጊዜያት የወንጀል ህጐች ድንግጋ በተግባር ላይ አውላለች፡፡ በ1923 ዓ.ም የተደነገገው ለመጀመሪያ ጊዜ በስራ ላይ የዋለው የወንጀል ህግ ነው፡፡ 1949 ዓ.ም የወጣው ደግሞ ሁለተኛውና ከ40 ዓመት በላይ በስራ ላይ የነበረ የወንጀል ህግ ነው፡፡ በየመሃሉም ተጨማሪና ያለውን ከፍተት ሊሞሉ የሚችሉ ህጐች በስራ ላይ ነበሩ፡፡
ኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የወንጀል ህግ ከ1949 ዓ.ም ጀሞሮ በስራ ላይ የነበረውን የወንጀለኛ መቅጫ ህግ በመተካት ከግንቦት 1 ቀን 1997 ዓ. ም ጀምሮ በተግባር ላይ ውሏል፡፡ በኢፌድሪ ህገ መንግስት አንቀፅ 52(5) ላይ በተሰጠው ስልጣንና ሃላፊነት መሠረት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የወጣ ነው፡፡ ይህ የወንጀል ህግ ህብረተሠቡን በጉዳት ለመጠበቅ የወጣና እንደ ወንጀል የሚቆጠሩ ድርጊቶችና ለነዚህ የተከለከሉ ድርጊቶች ተገቢ ተብለው የተዘረዘሩ ቅጣቶችን የሚዘረዝር ህግ ነው፡፡ ስለሆነም ቅጣት እና ወንጀል ሁለቱ የወንጀል ህግ መሠረታዊ ጉዳዮች ናቸው፡፡
@2020, Abrham Yohanes
https://t.me/lawsocieties
ዜና ሹመት

አቶ ዳጋቶ ኩምቤ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሆነዉ ተሹመዋል።

እንኳን በደህና መጡ

መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንልዎ እንመኛለን።
ስለባልና ሚስት የጋራ እና የግል ንብረቶች በተመለከተ የፌዴራሉን የቤተሰብ ሕግና የተመረጡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎችን መሰረት በማድረግ የቀረበ

በ፡ ሙሉቀን ሰይድ ሐሰን

በዚህ ጽሑፍ ጋብቻ በተጋቢዎቹ የግልና የጋራ ንብረት ላይ ስለሚኖረው ውጤት እንዲሁም በጋብቻ ውስጥ የተፈራ ንብረት የግል ወይም የጋራ ሊባል ሲለሚችልበት የሕግ አግባብ፤ በተጋቢዎቹ መካከል የሚደረግ የስጦታ ውል ሕጋዊ ውጤቱና የአደራረግ ስነ ስርዓቱ፣ በትዳር ውስጥ የወጣ ወጪ ለትዳር ጥቅም ዋለ ሊባል ስለሚችልባቸውና የማይቻልባቸው ሁኔታዎች ከፌዴራሉ የቤተሰብ ሕግ እንዲሁም ከሰበር ሰሚ ችሎት አስገዳጅ ውሳኔዎች አንጻር በተመረጡ የንብረት አይነቶች በመከፋፈል ዳሰሳ ተደርጓል፡፡ በጽሑፉ፦

- የግል ወይም የጋራ ንብረት ለማለት መሰረቱ
- የግል ንብረት
- ቤትና ይዞታን በተመለከተ
- ይዞታው ከጋብቻ በፊት በምሪት የተገኘ ሆኖ ቤቱ ግን በጋብቻ ውስጥ በጋራ የተሰራ በሆነ ጊዜ
- የአንደኛው ተጋቢ የግል የሆነ ቤትን በጋብቻ ውስጥ ባልና ሚስቱ እድሳት ካከናወኑ
- ከጋብቻ በፊት አንደኛው ተጋቢ ተበድሮ ቤት ቢሰራ እና ብድሩ በጋብቻ ጊዜ ከጋራ ሀብት ( ደመወዝ) ቢከፈል ቤቱ የጋራ? ወይስ የግል ሊባል ይገባል?
- በውርስ በተገኘ ንብረት ምትክ በካሳ መልክ ከመንግስት በተሰጠ ገንዘብ የተሰራ ቤትን በተመለከተ
- የስጦታ ውል በባልና ሚስት መሀከል የሚደረግበት የሕግ አግባብ
- ለትዳር ጥቅም የዋለ ገንዘብ
- የኮንዶሚኒየም ቤት
- የንግድ ፈቃድ

የሚሉ ነጥቦችን ይዟል።

መልካም ንባብ!

https://www.abyssinialaw.com/blog/joint-and-personal-property-of-spouses-under-ethiopian-law
የመረጃ ነፃነት ህግ ተግባራዊነት - ለመልካም አስተዳደር መስፈን
\\\\\\\\\\\\\\\\\\\\\\\
የሀገራችን ህገ መንግስት አንቀጽ 29 ዜጎች ያለማንም ጣልቃ ገብነት የመሰላቸውን አመለካከት የመያዝና ሃሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት እንዳላቸው ያብራራል። ሃሳብን በነፃነት የመግለጽ መብቶች ከሚረጋገጥባቸው መንገዶች መካከል መገናኛ ብዙሃን ተጠቃሽ ናቸው።በመሆኑም መገናኛ ብዙሃን በህገ መንግስቱ የተረጋገጠውን ሃሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት ተግባራዊ ለማድረግ እንዲቻል ጥራቱ የተጠበቀ፤ ወቅታዊ፤ ትክክለኛ፤ ቀልጣፋና አስተማማኝ የሆነ ለፖለቲካዊ፤ ለማህበራዊና ለኢኮኖሚያዊ እድገት አስተዋጾ የሚያደርግ አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው ይታመናል።
አለሕግAleHig ️
የመረጃ ነፃነት ህግ ተግባራዊነት - ለመልካም አስተዳደር መስፈን \\\\\\\\\\\\\\\\\\\\\\\ የሀገራችን ህገ መንግስት አንቀጽ 29 ዜጎች ያለማንም ጣልቃ ገብነት የመሰላቸውን አመለካከት የመያዝና ሃሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት እንዳላቸው ያብራራል። ሃሳብን በነፃነት የመግለጽ መብቶች ከሚረጋገጥባቸው መንገዶች መካከል መገናኛ ብዙሃን ተጠቃሽ ናቸው።በመሆኑም መገናኛ ብዙሃን በህገ መንግስቱ የተረጋገጠውን…
የመረጃ ነፃነት ህግ ተግባራዊነት - ለመልካም አስተዳደር መስፈን
\\\\\\\\\\\\\\\\\\\\\\\

ይህንኑ ሀገራዊ ሃላፊነት ለማስፈፀም እንዲቻል በአገሪቱ በመካሄድ ላይ ከሚገኘው ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ጋር በሚጣጣም መልኩ የተቀረፀው የመገናኛ ብዙሃንና የመረጃ ነፃነት አዋጅ ቁጥር 590/2000 ወጥቶ ተግባራዊ መሆን መጀመሩ ይታወቃል።በተለይ የመረጃ ነፃነት ህጉ ከህዳር 25/2004 ጀምሮ ተግባራዊ መሆን መጀመሩ ይፋ ሆኗል።አዋጁ ህገ መንግስታዊ መሰረት ያለውን ሃሳብን በፃነት የመግለጽ መብት የበለጠ የሚያጠናክርና ተግባራዊ የሚያደርግ ሲሆን፤ በዜጎች መካከል የሚደረገውን የሃሳብና የመረጃ ልውውጥ እንዲሁም በመገናኛ ብዙሃን የአሰራር ነፃነት ላይ እንቅፋት የሚፈጥሩ ተቋማዊና መዋቅራዊ ችግሮችን ያስወግዳል።
ከዚህም በተጨማሪ በነፃና በህጉ መሰረት ሃሳብን የመግለጽና የመገናኛ ብዙሃን ነፃነትን አስመልክቶ ያዳበርናቸውን አዎንታዊና ገንቢ ልምዶች የመጠበቅና ይበልጥ የማጠናከርን አስፈላጊነት በመረዳት ተግባራዊ እንዲሆን ታስቦ የተዘጋጀ ነው።ሌላው አዋጁ በመንግስት እጅ ያሉ መረጃዎችን የማግኘት መብት ለዴሞክራሲያዊ ህብረተሰብ የሚኖረውን ፋይዳ በአግባቡ የሚፈፀምበት ሁኔታ እውን ለማድረግ ድርሻው የጎላ ነው።
በዚህም መሰረት በህገ መንግስቱ የተረጋገጠውን ግልጽ የመንግስት የተጠያቂነት እሴትን ለማዳበርና ለማጠናከር እንዲሁም የህዝብን ጠቅምን የሚመለከቱ ጉዳዮች ይፋ ወጥተው ህዝብ እንዲወያይባቸው ለማድረግ የመንግስት ተቋማት ለማንኛውም መረጃ ፈላጊ መረጃዎችን የማቅረብ ግዴታ አለባቸው።ይህንን ግዴታ በማስፈፀምና መረጃ የማግኘት መብትን በማስተግበር ረገድ አዋጁ ስልጣን ከሰጣቸው ተቋማት መካከል አንዱ የኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ነው።
መረጃ ጠይቆ የማግኘት መብትን ከማረጋገጥ ጋር የተቆራኘው ይህ ሃላፊነት ተነፃፃሪ የህዝብንና የግለሰብ ጥቅሞችን ለማስጠበቅ የወጡ ተገቢ ገደቦች እንደተጠበቁ ሆኖ ከማንኛውም መንግስታዊ አካላት ዜጎች መረጃ ለመጠየቅ፤ ለማግኘትና ለማስተላለፍ ያላቸውን መብት ተፈፃሚ የማድረግ ዓላማን ተግባራዊ ለማድረግ ያገለግላል። ይህ ደግሞ የስልጣን ባለቤት የሆነውን የህዝብ ነፃ ተሳትፎ የሚያረጋግጥና ከሁሉም በላይ የአሰራር ግልጽነት፤ ተጠያቂነትና ውጤታማት የሰፈነበት መንግስታዊ ሥርዓትንና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን መሳኝ ነው።
መረጃ ማግኘት ዜጎች ሊነፈጉት የማይገባ መብት ነው።ስለሆነም ተቋሙ በመንግስት መ/ቤቶች ውስጥ መረጃ ለመስጠትና ለማመቻቸት የተደራጁ የህዝብ ግንኙነት ክፍሎች ለሚቀርብላቸው የመረጃ ጥያቄ ተገቢውን ምላሽ መስጠት እንዲችሉ በሀገሪቱ ውስጥ ለሚገኙ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በመረጃ ነፃነት ህጉ በተሰጠው ሃላፊነት መሰረት የክትትልና ድጋፍ ስራዎችን እያደረገ ሲሆን መንግስታዊ ተቋማቱ ደግሞ ህጉን እንዴት ተግባራዊ እያደረጉ እንደሆነ የቁጥጥር ስራዎችን አከናውኗል።ከዚህ በተጨማሪም የመረጃ ጥያቄዎች የሚቀርቡበትንና የሚስተናገዱበትን ፎርማቶችን በማዘጋጀትና ቴክኒካዊ ድጋፍ በመስጠት እንዲሁም የማብራሪያ ሰነዶችን በማሰራጨት የህዝብ ግንኙነት አካላት የተሻለ አፈፃፀም እንዲኖራቸው ሚናውን እየተወጣ ይገኛል።
ተቋሙ በመረጃ ነጻነት ዳይሬክቶሬት ዘርፉ በሚያከናውናቸው ተግባራት ህጉን ለመተግበር የሚያግዙ የተለያዩ የህግ ማእቀፎች እንዲዘጋጁ ሃሳብ በማቅረብ ድጋፍ ያደርጋል።መረጃዎችን አትሞ በማዘጋጀት ረገድም ግልጽ የአሰራር መመሪያ አዘጋጅቶ በመንግስት ተቋማት እንዲተገበር ያመቻቻል፡፡
በዘርፉ ከሚከናወኑ አበይት ተግባራት መካከልም መረጃ ከማግኘት መብት ጋር ተያይዞ የሚቀርቡ ቅሬታዎችን የመፍታት መፍትሄ አንዱ ሆኖ ይጠቀሳል።በዘርፉ የስራ እንቅስቃሴም ቅሬታዎችን ለመፍታት የሚያስችል ሥርዓት እንዲዘረጋ የማድረግ ሃላፊነት ተጥሎበታል ፡፡
የመረጃ ነጻነት ዳይሬክቶሬት ዘርፍ ከተለያዩ የመንግስት አካላት ስለ ህጉ አፈጻጸም ዓመታዊ ሪፖርት በመሰብሰብ ፣የተጠቃለለ ሪፖርት ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ያቀርባል።አዋጁን በመተግበር ሂደት ከተገኙ በጎ ተሞክሮዎችና ካጋጠመ ችግሮች በመነሳትም ለተሻለ አፈጻጸም የሚያበቃ የውሳኔ ሃሳብ ያቀርባል።በስራ ላይም ያውላል።
ለህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎችና አግባብነት ላላቸው አካላት ስለ ህጉ ይዘት ስልጠና የመስጠት ድርሻውን የሚወጣው ይህ ዘርፍ ከዋና እንባ ጠባቂ የሚሰጡ ሌሎች ጨማሪ ተግባራትን የመከወን ሃላፊነት አለበት፡፡
ዘርፉ መረጃ ከማግኘት መብት ጋር ተያይዞ የሚቀርቡለትን አቤቱታዎች በአስተዳደራዊ የይግባኝ ሂደት ተመልክቶ ውሳኔ ይሰጣል።የሰነዶችን አጠባበቅ አስተዳደርና አወጋገድን አስመልክቶም የሚመለከታቸውን ወገኖች በማማከር የተግባር መመሪያን ያዘጋጃል፡፡
በአጠቃላይ ተቋሙ የህዝብ የመረጃ የማግኘት መብትን ለማረጋገጥና መልካም አስተዳደርን አውን ለማድረግ ከሚመለከታቸው መንግስታዊ ባለድርሻ አካላት እና የመንግስት የልማት ድርጅቶች ጋር በቅንጅት በማስራት በመረጃ ነፃነት ህጉ የተሰጠውን ሃላፊነት ለመወጣት ከማናቸውም ጊዜ በላይ ተጠናክሮ እየሰራ ይገኛል።የመረጃ ነፃነት ህግ ተግባራዊ መሆን የግልጽነትንና የተጠያቂነትን አሰራር በማስፈን ለመልካም አስተዳደር መስፈን የበኩሉን ድርሻ ያበረክታል።
አዲስ ዘመን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ጋር በመተባበር ቅዳሜ ነሐሴ 29 ቀን 2013 ዓ.ም
224876.pdf
1 MB
የውርስ ሀብት በእጁ አድርጎ ያልያዘ ወራሽ በፍ/ብ/ህ/ቁ 1000(1) መሰረት የይርጋ መቃወሚያ ማንሳት አይችልም።
የፍ/ብ/ህ/ቁ 1000(1) ከሳሹ መብቱንና የውርሱ ንብረቶች በተከሳሹ መያዛቸውን ካወቀ ሶስት አመት ካለፈ በኋላ ስለወራሽነት ጥያቄ የሚቀርበው ክስ ተቀባይነት ለማግኘት እንደማይችል ደንግጓል፡፡ ይህ ድንጋጌ በይዘቱ የይርጋ መቃወሚያ ማንሳት የሚችለው የውርስ ንብረቶቹን በእጁ የያዘው ሰው ብቻ ስለመሆኑ የሚያስገነዝብ ነው፡፡
ሰ-መ-ቁ 224876 ቀን ጥቅምት 2 2015 ዓ.ም
#Click Ethiopian Laws