ፍቅረኛሞች ከነበሩት ከዳኛ ትንሳዔና ከገቢዎች ሠራተኛዋ ዙፋን ህይወት ህልፈት ምን እንማራለን❓❓❓
~~~................❓
ይሄ እኮ ከዓለም ዋንጫ ጨዋታ በላይ ትንታኔ የሚሻና ለብዙዎች መማሪያና ማስተማሪያ ሊሆን የሚገባው ጉዳይ ነው።
ትንሳዔ ህግ የተማረ ዳኛ ነው። ፍሬሽ ተመራቂ አይደለም። የረጅም ጊዜ ልምድ ያለውና የተረጋጋም ነው ይባልለታል። ታድያ እንዴት እንዲህ ያለ አጥፍቶ የመጥፋት ውሳኔ ላይ ደረሰ?
ዙፋን በገቢዎች መሥሪያ ቤት የምትሠራ፣ የትንሳዔ የሀገሩ ልጅና ፍቅረኛው ናት። እሷስ ትንሳዔን እልህ ለማስያዝና "አሳብድሃለሁ" እያለች ለመቅበጥና ለመወስለትን ምን አደፋፈራት? "እልህ ምላጭ ያስውጣል" ተረትን ማሰብ እንዴት አቃታት?
የማወራው ከእዚህ መንደር በቃረምኩት መረጃ ነው።
ልጄ እንደ ዙፋን እንድትሆን አልፈልግም። ልጄ እንደ ትንሳዔ እንዲሆን አልፈልግም። ክስተቱ ለጥናትና መፍትሔ ፍለጋ መነሻ እንዲሆን ያስፈልጋል።
"የሰው ሆዱን የወፍ ወንዱን ማወቅ አይቻልም" ይሉት አባባል አለ። ሰው ተማርሮ ሲጨክን እንዲህ በራሱም በሚወደውም ሊጨክን እንደሚችል ገምቶ ፍቺንና መለያየትን በእርጋታና በመስማማት መፈጸም ተገቢ ነው።
ህግን ተማምኖ "ልክ አስገባዋለሁ" የሚለው ድፍረት ብዙ እንደማያዋጣ ከበቂ በላይ ክስተቶች አይተናል።
"ፍቅር እውር ነው" ይል ነበር;ቀዳሚው ትውልድ። ያ ትውልድ የሰው ባህሪይ ገብቶታል!
ያሁኑ ትውልድ ትምክህቱን በህግ ላይ ብቻ አድርጎ ብዙ ሰው ጠፋ። የሰው ልጅ ስነ-ልቦናን እስክንረዳ ስንት ሰው አሲድ ይደፋበት? ስንት ሰው ጥይት ይርከፍከፍበት? ስንት ሰው መርዝ ይጋት? ስንት ሰው ይሙት? ስንት ሰው ተያይዞ ይለቅ?
ወንዱ ገዳይ ባይሞት ኖሮ ይሄኔ ሰልፍ እንውጣ ባዮች ሺ ነበሩ። አሁን ግን ዝም ዝም ዝም ብቻ። ለምን? እነርሱ መፍትሔያቸው ከቅጣት ያለፈ አይደለማ! ተቀጪ ካጡ መፍትሔ የላቸውም።
መፍትሔው ሰልፍ አይደለም። መፍትሔው ፍርድ አይደለም። መፍትሔው ህግ አይደለም። መፍትሔው ቅጣት አይደለም።
መፍትሔው የወንድ ልጅ ሳይኮሎጂን መረዳት ነው። መፍትሔው የሴትን ልጅ ባህሪይ መረዳት ነው። መፍትሔው የማህበሩን ሳይኮሎጂ መረዳት ነው። መፍትሔው አሰቃቂ ርምጃዎች ለምን በዙ ብሎ ምክንያቱን መፈለግ ነው። መፍትሔው ህጉን ከሰው ባህሪ ጋር አጣጥሞ ማስተካከል ነው።
ትንሳዔ ህግ ያውቃል። የደረሰበትን የስነ-ልቦና ጉዳት ህግ እንደማይፈታለት ገብቶታል። እናም ህጉን ተሻግሮ ውሳኔውን በእጁ ወሰነ።
የሀገራችን ህግ የሰው ሳይኮሎጂን ሊያጤን ይገባል። ህግ የሰው ሳይኮሎጂን፣ ባህልን፣ ሃይማኖትን፣ የማህበረሰቡን የጋራ እሴት ከግምት ሊያስገባ ያስፈልጋል። ያለዚያ ብዙ ሰው ሊያልቅ ነው። ህግ ይቀጣል እንጂ ህግ ነፍስ አያድንም፣ ነፍስ አይመልስም።
ልጄ ሆይ! እህቴ ሆይ! "ሰው በህግ ብቻ አይኖርም" የሚለውን ቃል አስተውዪ።
ግዴለም ከመሞት መሰንበት ይሻላል። እልህን ወደጎን አድርጎ በጥበብና በፍቅር መኖር ይሻላል። አብሮ መሆን ካልተቻለም በጥበብና በመከባበርና በፍቅር መለያየት ይሻላል።
ከእንግዲህ የሞቱትን "ነፍስ ይማር" ማለት እንጂ ሌላ ምን ማለት ይቻላል?
መፍትሔው ልብ መግዛት ነው። ሁልሽም ከዚህ ትምህርት ውሰጂ! ያልተነገሩ ብዙ እንዲህ ያሉ ክስተቶች አሉ።
ወንዱ በፊት ለፊት በጉልበት የገደላት ሴት፣ ሴቷም በጓዳ እንደ አይጥ በመርዝ ጭጭ ያደረገችው ወንድ ቁጥራቸው ቀላል አይደለም። ምንሊክ ሆስፒታል ያላወቀው የሰፈር ሀሜታ የሆነ ሞት ብዙ ነው።
የዛሬው ህግ ከትናንት በምን ተሻለ? ምንስ አጎደለ? ወፍ እንዳገሯ ትጮሃለችና የተውሶ ህግን ትቶ የአገሩን ስነ-ልቦና የተከተለ ህግ ማውጣት ይበጃል።
ግዴለም መከባበር ይበጃል። ግዴለም ህጉን ማረቅ ይበጃል። ግዴለም ፍቅር ይበልጣል።
ቀጣዩ ትውልድ ይንቃ! ያሁኑ እንኳ ተወዛግቧል፤ ገና እስኪነቃ ብዙ ማገዶ ይፈጃል፣ ብዙ ነፍስ ያስጨርሳል፣ ብዙ ሰልፍ ያሳየናል።
የነገው ትውልድ ግን ንቃ!
@Get Toughe
Via voice of justice
https://t.me/lawsocieties
~~~................❓
ይሄ እኮ ከዓለም ዋንጫ ጨዋታ በላይ ትንታኔ የሚሻና ለብዙዎች መማሪያና ማስተማሪያ ሊሆን የሚገባው ጉዳይ ነው።
ትንሳዔ ህግ የተማረ ዳኛ ነው። ፍሬሽ ተመራቂ አይደለም። የረጅም ጊዜ ልምድ ያለውና የተረጋጋም ነው ይባልለታል። ታድያ እንዴት እንዲህ ያለ አጥፍቶ የመጥፋት ውሳኔ ላይ ደረሰ?
ዙፋን በገቢዎች መሥሪያ ቤት የምትሠራ፣ የትንሳዔ የሀገሩ ልጅና ፍቅረኛው ናት። እሷስ ትንሳዔን እልህ ለማስያዝና "አሳብድሃለሁ" እያለች ለመቅበጥና ለመወስለትን ምን አደፋፈራት? "እልህ ምላጭ ያስውጣል" ተረትን ማሰብ እንዴት አቃታት?
የማወራው ከእዚህ መንደር በቃረምኩት መረጃ ነው።
ልጄ እንደ ዙፋን እንድትሆን አልፈልግም። ልጄ እንደ ትንሳዔ እንዲሆን አልፈልግም። ክስተቱ ለጥናትና መፍትሔ ፍለጋ መነሻ እንዲሆን ያስፈልጋል።
"የሰው ሆዱን የወፍ ወንዱን ማወቅ አይቻልም" ይሉት አባባል አለ። ሰው ተማርሮ ሲጨክን እንዲህ በራሱም በሚወደውም ሊጨክን እንደሚችል ገምቶ ፍቺንና መለያየትን በእርጋታና በመስማማት መፈጸም ተገቢ ነው።
ህግን ተማምኖ "ልክ አስገባዋለሁ" የሚለው ድፍረት ብዙ እንደማያዋጣ ከበቂ በላይ ክስተቶች አይተናል።
"ፍቅር እውር ነው" ይል ነበር;ቀዳሚው ትውልድ። ያ ትውልድ የሰው ባህሪይ ገብቶታል!
ያሁኑ ትውልድ ትምክህቱን በህግ ላይ ብቻ አድርጎ ብዙ ሰው ጠፋ። የሰው ልጅ ስነ-ልቦናን እስክንረዳ ስንት ሰው አሲድ ይደፋበት? ስንት ሰው ጥይት ይርከፍከፍበት? ስንት ሰው መርዝ ይጋት? ስንት ሰው ይሙት? ስንት ሰው ተያይዞ ይለቅ?
ወንዱ ገዳይ ባይሞት ኖሮ ይሄኔ ሰልፍ እንውጣ ባዮች ሺ ነበሩ። አሁን ግን ዝም ዝም ዝም ብቻ። ለምን? እነርሱ መፍትሔያቸው ከቅጣት ያለፈ አይደለማ! ተቀጪ ካጡ መፍትሔ የላቸውም።
መፍትሔው ሰልፍ አይደለም። መፍትሔው ፍርድ አይደለም። መፍትሔው ህግ አይደለም። መፍትሔው ቅጣት አይደለም።
መፍትሔው የወንድ ልጅ ሳይኮሎጂን መረዳት ነው። መፍትሔው የሴትን ልጅ ባህሪይ መረዳት ነው። መፍትሔው የማህበሩን ሳይኮሎጂ መረዳት ነው። መፍትሔው አሰቃቂ ርምጃዎች ለምን በዙ ብሎ ምክንያቱን መፈለግ ነው። መፍትሔው ህጉን ከሰው ባህሪ ጋር አጣጥሞ ማስተካከል ነው።
ትንሳዔ ህግ ያውቃል። የደረሰበትን የስነ-ልቦና ጉዳት ህግ እንደማይፈታለት ገብቶታል። እናም ህጉን ተሻግሮ ውሳኔውን በእጁ ወሰነ።
የሀገራችን ህግ የሰው ሳይኮሎጂን ሊያጤን ይገባል። ህግ የሰው ሳይኮሎጂን፣ ባህልን፣ ሃይማኖትን፣ የማህበረሰቡን የጋራ እሴት ከግምት ሊያስገባ ያስፈልጋል። ያለዚያ ብዙ ሰው ሊያልቅ ነው። ህግ ይቀጣል እንጂ ህግ ነፍስ አያድንም፣ ነፍስ አይመልስም።
ልጄ ሆይ! እህቴ ሆይ! "ሰው በህግ ብቻ አይኖርም" የሚለውን ቃል አስተውዪ።
ግዴለም ከመሞት መሰንበት ይሻላል። እልህን ወደጎን አድርጎ በጥበብና በፍቅር መኖር ይሻላል። አብሮ መሆን ካልተቻለም በጥበብና በመከባበርና በፍቅር መለያየት ይሻላል።
ከእንግዲህ የሞቱትን "ነፍስ ይማር" ማለት እንጂ ሌላ ምን ማለት ይቻላል?
መፍትሔው ልብ መግዛት ነው። ሁልሽም ከዚህ ትምህርት ውሰጂ! ያልተነገሩ ብዙ እንዲህ ያሉ ክስተቶች አሉ።
ወንዱ በፊት ለፊት በጉልበት የገደላት ሴት፣ ሴቷም በጓዳ እንደ አይጥ በመርዝ ጭጭ ያደረገችው ወንድ ቁጥራቸው ቀላል አይደለም። ምንሊክ ሆስፒታል ያላወቀው የሰፈር ሀሜታ የሆነ ሞት ብዙ ነው።
የዛሬው ህግ ከትናንት በምን ተሻለ? ምንስ አጎደለ? ወፍ እንዳገሯ ትጮሃለችና የተውሶ ህግን ትቶ የአገሩን ስነ-ልቦና የተከተለ ህግ ማውጣት ይበጃል።
ግዴለም መከባበር ይበጃል። ግዴለም ህጉን ማረቅ ይበጃል። ግዴለም ፍቅር ይበልጣል።
ቀጣዩ ትውልድ ይንቃ! ያሁኑ እንኳ ተወዛግቧል፤ ገና እስኪነቃ ብዙ ማገዶ ይፈጃል፣ ብዙ ነፍስ ያስጨርሳል፣ ብዙ ሰልፍ ያሳየናል።
የነገው ትውልድ ግን ንቃ!
@Get Toughe
Via voice of justice
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
👍9
#ተቋሙ_ሐሰተኛ_የትምህርት_ማስረጃን_ለማጥራት_ከባለድርሻ_አካላት_ጋር_በቅንጅት_እየሠራ_ነው
====== ====== ====
አዲስ አበባ፡- በፌዴራልና በክልል የመንግሥት ተቋማት በሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ተቀጥረው የሚሠሩ ግለሰቦችን ለማጥራት በትብብር እየተሠራ መሆኑን የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን ገለጸ።
የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ ወይዘሪት ማርታ አድማስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ተቋሙ ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃን ለማጥራት በሚሠራው መጠነ ሰፊ ሥራ የፌዴራልና የክልል ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሠሩ ነው።
የፌዴራልና የክልል ተቋማት አዲስ የሰው ኃይል ቅጥር ሲፈፅሙ እና የደረጃ ዕድገት ሲሠጡ የሠራተኞችን የትምህርት ማስረጃ ሐሰተኛ መሆንና አለመሆኑ እንዲጣራላቸው ወደ ተቋሙ መላካቸው አብረው የመሥራት ቁርጠኝነታቸውን ያሳያል ብለዋል።
እንደማሳያም የደበብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከክልል እስከ ወረዳ ያለው የመንግሥት መዋቅር ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃን በማጋለጥና በማጥራት ሂደት ቀዳሚ እንደሆነ ገልፀዋል። በተጨማሪም የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ህዝቦች ክልል፣ የጤና ሚኒስቴር፣ የጉምሩክ ኮሚሽን፣ ማዕከላዊ ስታስቲክስ እና ሌሎች የፌዴራልና የክልል ተቋማት ከትምህርት እና ሥልጠና ባለሥልጣን ጋር በቅርበት እየሠሩ መሆኑን ወይዘሪት ማርታ ተናግረዋል።
ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃን ለማጥራት ተማሪዎች አገር አቀፍ ፈተና ወስደው የፌዴራል ትምህርት ሚኒስቴር ያስቀመጠውን የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ነጥብ ማምጣታቸውንና መረጃ ተቀብሎ የማጥራት ሥራ እየሠራ መሆኑን አብራርተዋል።
====== ====== ====
አዲስ አበባ፡- በፌዴራልና በክልል የመንግሥት ተቋማት በሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ተቀጥረው የሚሠሩ ግለሰቦችን ለማጥራት በትብብር እየተሠራ መሆኑን የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን ገለጸ።
የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ ወይዘሪት ማርታ አድማስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ተቋሙ ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃን ለማጥራት በሚሠራው መጠነ ሰፊ ሥራ የፌዴራልና የክልል ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሠሩ ነው።
የፌዴራልና የክልል ተቋማት አዲስ የሰው ኃይል ቅጥር ሲፈፅሙ እና የደረጃ ዕድገት ሲሠጡ የሠራተኞችን የትምህርት ማስረጃ ሐሰተኛ መሆንና አለመሆኑ እንዲጣራላቸው ወደ ተቋሙ መላካቸው አብረው የመሥራት ቁርጠኝነታቸውን ያሳያል ብለዋል።
እንደማሳያም የደበብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከክልል እስከ ወረዳ ያለው የመንግሥት መዋቅር ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃን በማጋለጥና በማጥራት ሂደት ቀዳሚ እንደሆነ ገልፀዋል። በተጨማሪም የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ህዝቦች ክልል፣ የጤና ሚኒስቴር፣ የጉምሩክ ኮሚሽን፣ ማዕከላዊ ስታስቲክስ እና ሌሎች የፌዴራልና የክልል ተቋማት ከትምህርት እና ሥልጠና ባለሥልጣን ጋር በቅርበት እየሠሩ መሆኑን ወይዘሪት ማርታ ተናግረዋል።
ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃን ለማጥራት ተማሪዎች አገር አቀፍ ፈተና ወስደው የፌዴራል ትምህርት ሚኒስቴር ያስቀመጠውን የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ነጥብ ማምጣታቸውንና መረጃ ተቀብሎ የማጥራት ሥራ እየሠራ መሆኑን አብራርተዋል።
👍3
ምክር ቤቱ ሁለት ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ አጸደቀ
የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የብሔራዊ ክፍያ ሥርዓትን እና የመንግስትና የግል አጋርነት ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ አጽድቋል፡፡
የአዋጆቹን አስፈላጊነት አስመልክቶ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ደሳለኝ ወዳጄ እንዳሉት፤ የብሔራዊ ክፍያ ሥርዓቱን ደህንነት ለማስጠበቅና በፋይናስ ዘርፉ አስተማማኝና ቀልጣፋ ሥርዓት በመዘርጋት፤ ለውጦችን እና እድገት ታሳቢ ባደረገ መልኩ የክፍያ ስርአቱን ለማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን አስረድተዋል፡፡
የተከበሩ አቶ ደሳለኝ አያይዘውም፤ የመንግስት እና የግል አጋርነት ረቂቅ አዋጅን በሚመለከት የሀገራችንን የኢኮኖሚ እድገት ለማገዝ አስተዋፅኦ እንዳለው ጠቁመው፤ በመንግስትና በግል ባለሀብቶች በጋራ በሚሰሩ ፕሮጀክቶች ምቹ ምህዳር በመፍጠር፤ ለግል ሴክተሩ የእውቀትና ክህሎት ሽግግር በመፍጠር የፋይናንስ ሴክተሩን ለማሳደግ ጠቃሚ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
የምክር ቤቱ አባላት በበኩላቸው፤ የብሔራዊ ክፍያ ሥርዓት የሀገራችንን የፋይናስ ዘርፍ በማገዝ እድገት እና ብልጽግና ለማምጣት እንዲሁም የግል ዘርፉን በማሳተፍ ለኢኮኖሚው እድገት መነቃቀትን የሚፈጥር መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በሌላ በኩል የተከበሩ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ለመግስት እንደ ሀገር ተግዳሮት የሆነውን ሙስና እና ብልሹ አሰራር ለመከላከል ትልልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን በጨረታና በድርድር የሚለው ለኪራይ ሰብሳቢነት በር ስለሚከፍት በረቂቅ አዋጁ ላይ በጨረታ ብቻ በሚል ቢቀመጥ የተሻለ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ የተከበሩ ይናገር ደሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የክፍያ ሥርዓት አዋጁ ሙሉ በሙሉ የባንክ ስራን ተክቶ የማይሰራ በመሆኑ ከባንክ በመለስ ያሉ የክፍያ ስርአቶችን የውጭ ባለሃብቶችና ዜጎች እንዲሳተፉ ለማድረግ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
የባንክ ገዥው የተከበሩ ይናገር ደሴ (ዶ/ር) አክለውም የብሔራዊ የክፍያ ሥርዓት አዋጁ ስያሜን በተመለከተ፤ በብዙ የአፍሪካ ሀገራትም ጭምር ልምድ በመውሰድ ተሞክሮዎቹ ብሔራዊ የሚለው ስያሜ የጋራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
የቋሚ ኮሚቴው አባላት በበኩላቸው፤ የመንግስት እና የግል አጋርነት ያደጉ ሀገራት የተጠቀሙበት ሀገራቸውን ለማሳደግ ውጤታማ ስራ የሰሩበት በመሆኑ መንግስትና የግል ሴተክተሩ ተቀራርበው በመስራት ለፕሮጀክቶች ተፈጻሚንት ጉልህ ድርሻ እንዳለው ገልጸዋል፡፡
የብሔራዊ ክፍያ ሥርዓትን ለማሻሻል የቀረበው ረቂቅ አዋጅ፤ አዋጅ ቁጥር 1282/2015 ሆኖ በሶስት ድምጸ ተአቅቦ፤ በአብላጫ ድምጽ ጸድቀዋል፡፡
በተመሳሳይ መልኩ ምክር ቤቱ በውሎው፤ የመንግስትና የግል አጋርነትን ለማሻሻል የቀረበው ረቂቅ አዋጅ፤ አዋጅ ቁጥር 1283/2015 ሆኖ በአንድ ተቃውሞ እና በአንድ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ ጸድቀዋል፡፡
በ መኩሪያ ፈንታ
(ዜና ፓርላማ)፣ ታህሳስ 13፣ 2015 ዓ.ም፤
ParlamaNews
www.hopr.gov.et
https://t.me/lawsocieties
የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የብሔራዊ ክፍያ ሥርዓትን እና የመንግስትና የግል አጋርነት ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ አጽድቋል፡፡
የአዋጆቹን አስፈላጊነት አስመልክቶ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ደሳለኝ ወዳጄ እንዳሉት፤ የብሔራዊ ክፍያ ሥርዓቱን ደህንነት ለማስጠበቅና በፋይናስ ዘርፉ አስተማማኝና ቀልጣፋ ሥርዓት በመዘርጋት፤ ለውጦችን እና እድገት ታሳቢ ባደረገ መልኩ የክፍያ ስርአቱን ለማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን አስረድተዋል፡፡
የተከበሩ አቶ ደሳለኝ አያይዘውም፤ የመንግስት እና የግል አጋርነት ረቂቅ አዋጅን በሚመለከት የሀገራችንን የኢኮኖሚ እድገት ለማገዝ አስተዋፅኦ እንዳለው ጠቁመው፤ በመንግስትና በግል ባለሀብቶች በጋራ በሚሰሩ ፕሮጀክቶች ምቹ ምህዳር በመፍጠር፤ ለግል ሴክተሩ የእውቀትና ክህሎት ሽግግር በመፍጠር የፋይናንስ ሴክተሩን ለማሳደግ ጠቃሚ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
የምክር ቤቱ አባላት በበኩላቸው፤ የብሔራዊ ክፍያ ሥርዓት የሀገራችንን የፋይናስ ዘርፍ በማገዝ እድገት እና ብልጽግና ለማምጣት እንዲሁም የግል ዘርፉን በማሳተፍ ለኢኮኖሚው እድገት መነቃቀትን የሚፈጥር መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በሌላ በኩል የተከበሩ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ለመግስት እንደ ሀገር ተግዳሮት የሆነውን ሙስና እና ብልሹ አሰራር ለመከላከል ትልልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን በጨረታና በድርድር የሚለው ለኪራይ ሰብሳቢነት በር ስለሚከፍት በረቂቅ አዋጁ ላይ በጨረታ ብቻ በሚል ቢቀመጥ የተሻለ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ የተከበሩ ይናገር ደሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የክፍያ ሥርዓት አዋጁ ሙሉ በሙሉ የባንክ ስራን ተክቶ የማይሰራ በመሆኑ ከባንክ በመለስ ያሉ የክፍያ ስርአቶችን የውጭ ባለሃብቶችና ዜጎች እንዲሳተፉ ለማድረግ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
የባንክ ገዥው የተከበሩ ይናገር ደሴ (ዶ/ር) አክለውም የብሔራዊ የክፍያ ሥርዓት አዋጁ ስያሜን በተመለከተ፤ በብዙ የአፍሪካ ሀገራትም ጭምር ልምድ በመውሰድ ተሞክሮዎቹ ብሔራዊ የሚለው ስያሜ የጋራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
የቋሚ ኮሚቴው አባላት በበኩላቸው፤ የመንግስት እና የግል አጋርነት ያደጉ ሀገራት የተጠቀሙበት ሀገራቸውን ለማሳደግ ውጤታማ ስራ የሰሩበት በመሆኑ መንግስትና የግል ሴተክተሩ ተቀራርበው በመስራት ለፕሮጀክቶች ተፈጻሚንት ጉልህ ድርሻ እንዳለው ገልጸዋል፡፡
የብሔራዊ ክፍያ ሥርዓትን ለማሻሻል የቀረበው ረቂቅ አዋጅ፤ አዋጅ ቁጥር 1282/2015 ሆኖ በሶስት ድምጸ ተአቅቦ፤ በአብላጫ ድምጽ ጸድቀዋል፡፡
በተመሳሳይ መልኩ ምክር ቤቱ በውሎው፤ የመንግስትና የግል አጋርነትን ለማሻሻል የቀረበው ረቂቅ አዋጅ፤ አዋጅ ቁጥር 1283/2015 ሆኖ በአንድ ተቃውሞ እና በአንድ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ ጸድቀዋል፡፡
በ መኩሪያ ፈንታ
(ዜና ፓርላማ)፣ ታህሳስ 13፣ 2015 ዓ.ም፤
ParlamaNews
www.hopr.gov.et
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
👍2
ከዛሬ ጀምሮ ሲሚንቶ በነጻ ገበያ እንዲሸጥ ተወሰነ።
የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተሻለ በልሁ ከዚህ በፊት የነበረው የሲሚንቶ ሽያጭ መመሪያ መቀየሩን ገልጸዋል።
መመሪያው የሲሚንቶ ዋጋ በመንግሥት ተወስኖ እንዲሸጥ መደረጉ በርካታ ቅሬታዎች ሲነሳበት እንደነበር የጠቀሱት አቶ ተሻለ በዚህም ክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች፥ ሲሚንቶን በቀላሉ እንዳያገኙ አድርጓቸው እንደነበር ተናግረዋል ።
በተሻሻለው መመሪያ መሰረትም አከፋፋዮችን እና ቸርቻሪዎችን መምረጥ የፋብሪካዎቹ እድል ነው ብለዋል።
የፋብሪካዎቹ የመሸጫ ዋጋ ለጊዜው ምርታማነት እስከሚጨምር ድረስ የፋብሪካ ዋጋ በስድስት ወር አንድ ጊዜ በሚኒስቴሩ እንደሚወሰን ነው የተናገሩት።
መንግስት ከግብይቱ የወጣ ሲሆን በተሻሻለው መመሪያ መሰረትም መንግስት ሽያጩ ያለ ደረሰኝ እንዳይካሄድ ቁጥጥር እንደሚያደርግ አስረድተዋል። በግብይቱ ውስጥም ህጋዊ ንግድ ፍቃድ እና ደረሰኝ ግዴታ መሆናቸውን ጠቁመዋል። እያንዳንዱ ፋብሪካ የተደራሽነት አድማሱን በማስፋትም አከፋፋዩን የመምረጥ ፍላጎት እንዳለው ተናግረዋል።
ከዛሬ ጀምሮም ሲሚንቶ በየትኛውም ቦታ ቁጥጥር እና ክትትል ሳይደረግበት በነጻ ገበያ ይካሄዳል ነው ያለው ሚኒስቴሩ። ከፋብሪካ ሲሚንቶ የሚወጣ ማንኛውም ተሽከርካሪ የመዳረሻ ሰነድ መያዝ እንደሚኖርበትም ነው የተናገሩት።(ሼር)
https://t.me/lawsocieties
የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተሻለ በልሁ ከዚህ በፊት የነበረው የሲሚንቶ ሽያጭ መመሪያ መቀየሩን ገልጸዋል።
መመሪያው የሲሚንቶ ዋጋ በመንግሥት ተወስኖ እንዲሸጥ መደረጉ በርካታ ቅሬታዎች ሲነሳበት እንደነበር የጠቀሱት አቶ ተሻለ በዚህም ክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች፥ ሲሚንቶን በቀላሉ እንዳያገኙ አድርጓቸው እንደነበር ተናግረዋል ።
በተሻሻለው መመሪያ መሰረትም አከፋፋዮችን እና ቸርቻሪዎችን መምረጥ የፋብሪካዎቹ እድል ነው ብለዋል።
የፋብሪካዎቹ የመሸጫ ዋጋ ለጊዜው ምርታማነት እስከሚጨምር ድረስ የፋብሪካ ዋጋ በስድስት ወር አንድ ጊዜ በሚኒስቴሩ እንደሚወሰን ነው የተናገሩት።
መንግስት ከግብይቱ የወጣ ሲሆን በተሻሻለው መመሪያ መሰረትም መንግስት ሽያጩ ያለ ደረሰኝ እንዳይካሄድ ቁጥጥር እንደሚያደርግ አስረድተዋል። በግብይቱ ውስጥም ህጋዊ ንግድ ፍቃድ እና ደረሰኝ ግዴታ መሆናቸውን ጠቁመዋል። እያንዳንዱ ፋብሪካ የተደራሽነት አድማሱን በማስፋትም አከፋፋዩን የመምረጥ ፍላጎት እንዳለው ተናግረዋል።
ከዛሬ ጀምሮም ሲሚንቶ በየትኛውም ቦታ ቁጥጥር እና ክትትል ሳይደረግበት በነጻ ገበያ ይካሄዳል ነው ያለው ሚኒስቴሩ። ከፋብሪካ ሲሚንቶ የሚወጣ ማንኛውም ተሽከርካሪ የመዳረሻ ሰነድ መያዝ እንደሚኖርበትም ነው የተናገሩት።(ሼር)
https://t.me/lawsocieties
👍3
220830.pdf
825.3 KB
ከባንክ ሂሳቤ ላይ ገንዘብ አላአግባብ ወጪ በመደረጉ ባንኩ ገንዘቡን እንዲመልስ የሚል ክስ ሲቀርብ የፎረንሲክ ምረመራውን ውጤት ብቻ መሠረት በማድረግ ባንኩን ለክሱ ኃላፊ ማድረግ መሰረታዊ ስህተት ነው።
ሰ/መ/ቁ. 220830 ጥቅምት 29 ቀን 2015 ዓ/ም
በወጪ ማዘዣው ላይ የተመለከተዉ ፊርማ በሲስተሙ ላይ ከተመለከተዉ የፊርማ ናሙና ጋር ተመሳሳይ መሆን አለመሆኑን ለማረጋገጥ የወጪ ማዘዣው ላይ የተመለከተዉ ፊርማ ከናሙና ፊርማ ጋር የሚመሳሰል መሆን አለመሆኑ ገለልተኛ በሆነ አካል ታይቶ መረጋገጥ ይኖርበታል።
በመሆኑም ክስ ከቀረበበት ባንክ ዉጪ በሌሎች ባንኮች ከወጪ ማዛዣ ክፍያ ጋር በተያያዘ ልምድ ባላቸዉ የባንክ ባለሙያዎች እንዲታይ በማድረግ ባንኩ ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ ግዴታዉን የተወጣ መሆን አለመሆኑ ማረጋገጥ ይገባል፡፡ የባለሂሳቡ ባንክ ደብተር ቀርቦ ሂሳቡ ተቀንሶ የተጻፈ መሆን አለመሆኑ ሆነ የባለሂሳቡ መታወቂያ በማየት ባንኩ ያረጋገጠ መሆን አለመሆኑ ደግሞ በሰው ማስረጃ ሆኖ የባንክ ሂሳብ ደብተሩ ካለ በማስቀረብ መረጋገጥ ይኖርበታል።
https://t.me/lawsocieties
ሰ/መ/ቁ. 220830 ጥቅምት 29 ቀን 2015 ዓ/ም
በወጪ ማዘዣው ላይ የተመለከተዉ ፊርማ በሲስተሙ ላይ ከተመለከተዉ የፊርማ ናሙና ጋር ተመሳሳይ መሆን አለመሆኑን ለማረጋገጥ የወጪ ማዘዣው ላይ የተመለከተዉ ፊርማ ከናሙና ፊርማ ጋር የሚመሳሰል መሆን አለመሆኑ ገለልተኛ በሆነ አካል ታይቶ መረጋገጥ ይኖርበታል።
በመሆኑም ክስ ከቀረበበት ባንክ ዉጪ በሌሎች ባንኮች ከወጪ ማዛዣ ክፍያ ጋር በተያያዘ ልምድ ባላቸዉ የባንክ ባለሙያዎች እንዲታይ በማድረግ ባንኩ ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ ግዴታዉን የተወጣ መሆን አለመሆኑ ማረጋገጥ ይገባል፡፡ የባለሂሳቡ ባንክ ደብተር ቀርቦ ሂሳቡ ተቀንሶ የተጻፈ መሆን አለመሆኑ ሆነ የባለሂሳቡ መታወቂያ በማየት ባንኩ ያረጋገጠ መሆን አለመሆኑ ደግሞ በሰው ማስረጃ ሆኖ የባንክ ሂሳብ ደብተሩ ካለ በማስቀረብ መረጋገጥ ይኖርበታል።
https://t.me/lawsocieties
👍1👏1
ታስረው እንዲቀርቡ ታዘዘ።
የፍርድ ቤት መጥሪያ ፈርመው ወስደው ሳይቀርቡ የቀሩት የአ/አ ቤቶች ኮርፖሬሽን ኃላፊ አቶ ሽመልስ ታምራት ታስረው እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ተሰጠ።
የኮንዶሚኒዬም ቤቶች ዕጣ ተጭበርብሯል ተብሎ የከባድ ሙስና ወንጀል በቀረበባቸው ተከሳሾች ላይ የዓቃቢህግ 2ኛ ምስክር ሆነው የተቆጠሩት የአ/አ ቤቶች ኮርፖሬሽን ኃላፊ አቶ ሽመልስ ታምራት መጥሪያ ፈርመው ተቀብለው ባለመቅረባቸው ምክንያት ነው ታስረው እንዲቀርቡ ዛሬ ትዕዛዝ የተሰጠው።
ትዕዛዙን የሰጠው በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።
በአ/አ ከተማ በሀምሌ 1ቀን 2014 ዓ/ም ከኮንዶሚኒዬም ቤቶች ዕጣ አወጣጥ ጋር ተያይዞ ዕጣው ተጭበርብሯል ተብሎ የአ/አ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሙሉቀን ሀብቱን እና ምክትል ቢሮ ሀላፊ የሆኑትን አቶ አብርሀም ሰርሞሌን ጨምሮ በአጠቃላይ በ 11 ተከሳሾች ላይ በየደረጃው የከባድ ሙስና ወንጀል ክስ መመስረቱ ይታወሳል።
ተከሳሾቹ ወንጀሉን አለመፈጸማቸውንና ጥፋተኛ አለመሆናቸውን ገልጸው የሰጡትን የዕምነት ክህደት ቃል ተከትሎ ዓቃቢህግ ምስክር እንዲሰሙለት ጠይቆ ነበር።
በዚህ መሰረት ዓቃቢህግ በሀምሌ 1 ቀን 2014 ዓ/ም በአ/አ ከተማ ወጥቶ ከነበረው የ14ኛ ዙር 20/80 እና የ3ኛ ዙር የ40/60 ከኮንዶሚኒዬም ቤቶች ዕጣ አወጣጥ ስርዓት ጋር ተያይዞ እንዲሁም ለምቷል የተባለው ሶፍትዌርን የሚመለከት እና የተደረገ የኦዲት ስርዓትን ላይ ያተኮረ ምስክርነት እንዲሰማለት የምስክር ጭብጥ ካስመዘገበ በኋላ በህዳር 22 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ ፍርድ ቤቱ የዓቃቢህግ ምስክር ቃል መሰማት ጀምሮ ነበር።
ፍርድ ቤቱ እስካሁን የ 8 የዓቃቢህግ ምስክሮችን ቃል ያዳመጠ ሲሆን በ2ኛ የዓቃቢህግ ምስክር ሆነው የተቆጠሩት የአ/አ ቤቶች ኮርፖሬሽን ኃላፊ አቶ ሽመልስ ታምራት ግን መጥሪያ ደርሷቸው ፈርመው የወሰዱ ቢሆንም በችሎት ሳይቀርቡ ቀርተዋል።ፍርድ ቤቱም ግለሰቡ በፖሊስ ታስረው በይደር እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
Via:- Tarik Adugna
https://t.me/lawsocieties
የፍርድ ቤት መጥሪያ ፈርመው ወስደው ሳይቀርቡ የቀሩት የአ/አ ቤቶች ኮርፖሬሽን ኃላፊ አቶ ሽመልስ ታምራት ታስረው እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ተሰጠ።
የኮንዶሚኒዬም ቤቶች ዕጣ ተጭበርብሯል ተብሎ የከባድ ሙስና ወንጀል በቀረበባቸው ተከሳሾች ላይ የዓቃቢህግ 2ኛ ምስክር ሆነው የተቆጠሩት የአ/አ ቤቶች ኮርፖሬሽን ኃላፊ አቶ ሽመልስ ታምራት መጥሪያ ፈርመው ተቀብለው ባለመቅረባቸው ምክንያት ነው ታስረው እንዲቀርቡ ዛሬ ትዕዛዝ የተሰጠው።
ትዕዛዙን የሰጠው በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።
በአ/አ ከተማ በሀምሌ 1ቀን 2014 ዓ/ም ከኮንዶሚኒዬም ቤቶች ዕጣ አወጣጥ ጋር ተያይዞ ዕጣው ተጭበርብሯል ተብሎ የአ/አ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሙሉቀን ሀብቱን እና ምክትል ቢሮ ሀላፊ የሆኑትን አቶ አብርሀም ሰርሞሌን ጨምሮ በአጠቃላይ በ 11 ተከሳሾች ላይ በየደረጃው የከባድ ሙስና ወንጀል ክስ መመስረቱ ይታወሳል።
ተከሳሾቹ ወንጀሉን አለመፈጸማቸውንና ጥፋተኛ አለመሆናቸውን ገልጸው የሰጡትን የዕምነት ክህደት ቃል ተከትሎ ዓቃቢህግ ምስክር እንዲሰሙለት ጠይቆ ነበር።
በዚህ መሰረት ዓቃቢህግ በሀምሌ 1 ቀን 2014 ዓ/ም በአ/አ ከተማ ወጥቶ ከነበረው የ14ኛ ዙር 20/80 እና የ3ኛ ዙር የ40/60 ከኮንዶሚኒዬም ቤቶች ዕጣ አወጣጥ ስርዓት ጋር ተያይዞ እንዲሁም ለምቷል የተባለው ሶፍትዌርን የሚመለከት እና የተደረገ የኦዲት ስርዓትን ላይ ያተኮረ ምስክርነት እንዲሰማለት የምስክር ጭብጥ ካስመዘገበ በኋላ በህዳር 22 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ ፍርድ ቤቱ የዓቃቢህግ ምስክር ቃል መሰማት ጀምሮ ነበር።
ፍርድ ቤቱ እስካሁን የ 8 የዓቃቢህግ ምስክሮችን ቃል ያዳመጠ ሲሆን በ2ኛ የዓቃቢህግ ምስክር ሆነው የተቆጠሩት የአ/አ ቤቶች ኮርፖሬሽን ኃላፊ አቶ ሽመልስ ታምራት ግን መጥሪያ ደርሷቸው ፈርመው የወሰዱ ቢሆንም በችሎት ሳይቀርቡ ቀርተዋል።ፍርድ ቤቱም ግለሰቡ በፖሊስ ታስረው በይደር እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
Via:- Tarik Adugna
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
👍3❤1
አከፋፋይ ምረጡ ማለት እና ዋጋ ተምኜላችሁ ሽጡ ማለት ነፃ ገበያ ማለት አይደለም😝‼️
የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ፦ ከዛሬ ጀምሮ ሲሚንቶ በየትኛውም ቦታ ቁጥጥር እና ክትትል ሳይደረግበት #በነጻ_ገበያ ይካሄዳል። ስለዚህ ሲሚንቶ ፋብሪካዎች አከፋፋዮችን እና ቸርቻሪዎችን መምረጥ የፋብሪካዎቹ እድል ነው! የፋብሪካዎቹ የመሸጫ ዋጋ ለጊዜው ምርታማነት እስከሚጨምር ድረስ የፋብሪካ ዋጋ በስድስት ወር አንድ ጊዜ #በሚኒስቴሩ እንደሚወሰን ገልጿል።
#አማካይ_የሲሚንቶ_ዋጋ
- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 590.3ብር
- አሁን ፋብሪካዎች ያስገቡት የመሸጫ ዋጋ ➤ 1014.6ብር
- እንዲሸጡ የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤ 758.1ብር
ታዲያ ይህ ማለት እኮ መባል ያለበት ሲሚንቶ አምራቾች አከፋፋይ መርጣችሁ በተተመነላችሁ ዋጋ ሽጡ እንጂ በትርጉም ደረጃ #ነፃ_ገበያ ማለት አይደለም!
በዋሲሁን በላይ
https://t.me/lawsocieties
የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ፦ ከዛሬ ጀምሮ ሲሚንቶ በየትኛውም ቦታ ቁጥጥር እና ክትትል ሳይደረግበት #በነጻ_ገበያ ይካሄዳል። ስለዚህ ሲሚንቶ ፋብሪካዎች አከፋፋዮችን እና ቸርቻሪዎችን መምረጥ የፋብሪካዎቹ እድል ነው! የፋብሪካዎቹ የመሸጫ ዋጋ ለጊዜው ምርታማነት እስከሚጨምር ድረስ የፋብሪካ ዋጋ በስድስት ወር አንድ ጊዜ #በሚኒስቴሩ እንደሚወሰን ገልጿል።
#አማካይ_የሲሚንቶ_ዋጋ
- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 590.3ብር
- አሁን ፋብሪካዎች ያስገቡት የመሸጫ ዋጋ ➤ 1014.6ብር
- እንዲሸጡ የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤ 758.1ብር
ታዲያ ይህ ማለት እኮ መባል ያለበት ሲሚንቶ አምራቾች አከፋፋይ መርጣችሁ በተተመነላችሁ ዋጋ ሽጡ እንጂ በትርጉም ደረጃ #ነፃ_ገበያ ማለት አይደለም!
በዋሲሁን በላይ
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
Forwarded from ነገረ ፈጅ Negere Fej 📕
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በፓስተር ዮናታን አክሊሉ፣ በነቢይ ኢዩ ጩፋ እና የሚያገለግሉበት ቤተ ክርስቲያን ላይ ክስ መሠረተች
=======#===
ረቡዕ ታሕሳስ 12 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በፓስተር ዮናታን አክሊሉ፣ በአዲስ ኪዳን ካህናት ቤተ ክርስቲያን፣ በክራይስት አርሚ ኢንተርናሽናል ቤተ ክርስቲያን እና በነቢይ ኢዩ ጩፋ ላይ ክስ መሠረተች።
በቤተክርስቲያንቷ ሕግ አገልግሎት መምሪያ በኩል ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ዳይሬክቶሬት የተላከው ክስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ ያነጣጠረ የጥላቻ ንግግርና አደገኛ የሆነ የሃይማኖትን ክብር የሚነካ የአምልኮ ሥርዓትና እምነትን የሚያንቋሽሽ የዘለፋ እና ሐሰተኛ ንግግር በመፍጠር ለሁከትና ብጥብጥ መነሻ የሚሆን ድርጊት በፈጸሙ ግለሰቦችና ተባባሪ ተቋማት ላይ የወንጀል ምርመራ እንዲጣራ የሚጠይቅ ነው።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የክስ ዝርዝር ከሥር ተያይዟል።
https://t.me/NegereFej
=======#===
ረቡዕ ታሕሳስ 12 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በፓስተር ዮናታን አክሊሉ፣ በአዲስ ኪዳን ካህናት ቤተ ክርስቲያን፣ በክራይስት አርሚ ኢንተርናሽናል ቤተ ክርስቲያን እና በነቢይ ኢዩ ጩፋ ላይ ክስ መሠረተች።
በቤተክርስቲያንቷ ሕግ አገልግሎት መምሪያ በኩል ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ዳይሬክቶሬት የተላከው ክስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ ያነጣጠረ የጥላቻ ንግግርና አደገኛ የሆነ የሃይማኖትን ክብር የሚነካ የአምልኮ ሥርዓትና እምነትን የሚያንቋሽሽ የዘለፋ እና ሐሰተኛ ንግግር በመፍጠር ለሁከትና ብጥብጥ መነሻ የሚሆን ድርጊት በፈጸሙ ግለሰቦችና ተባባሪ ተቋማት ላይ የወንጀል ምርመራ እንዲጣራ የሚጠይቅ ነው።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የክስ ዝርዝር ከሥር ተያይዟል።
https://t.me/NegereFej
👍12👎5🔥2
220830.pdf
825.3 KB
ከባንክ ሂሳቤ ላይ ገንዘብ አላአግባብ ወጪ በመደረጉ ባንኩ ገንዘቡን እንዲመልስ የሚል ክስ ሲቀርብ የፎረንሲክ ምረመራውን ውጤት ብቻ መሠረት በማድረግ ባንኩን ለክሱ ኃላፊ ማድረግ መሰረታዊ የሕግ ስህተት ነው።
በወጪ ማዘዣው ላይ የተመለከተዉ ፊርማ በሲስተሙ ላይ ከተመለከተዉ የፊርማ ናሙና ጋር ተመሳሳይ መሆን አለመሆኑን ለማረጋገጥ የወጪ ማዘዣው ላይ የተመለከተዉ ፊርማ ከናሙና ፊርማ ጋር የሚመሳሰል መሆን አለመሆኑ ገለልተኛ በሆነ አካል ታይቶ መረጋገጥ ይኖርበታል።
በመሆኑም ክስ ከቀረበበት ባንክ ዉጪ በሌሎች ባንኮች ከወጪ ማዛዣ ክፍያ ጋር በተያያዘ ልምድ ባላቸዉ የባንክ ባለሙያዎች እንዲታይ በማድረግ ባንኩ ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ ግዴታዉን የተወጣ መሆን አለመሆኑ ማረጋገጥ ይገባል፡፡ የባለሂሳቡ ባንክ ደብተር ቀርቦ ሂሳቡ ተቀንሶ የተጻፈ መሆን አለመሆኑ ሆነ የባለሂሳቡ መታወቂያ በማየት ባንኩ ያረጋገጠ መሆን አለመሆኑ ደግሞ በሰው ማስረጃ ሆኖ የባንክ ሂሳብ ደብተሩ ካለ በማስቀረብ መረጋገጥ ይኖርበታል።
ሰ/መ/ቁ. 220830 ጥቅምት 29 ቀን 2015 ዓ/ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
#Bank #law #lawyer
#SAMUELGIRMA
Join 👈
https://t.me/lawsocieties
በወጪ ማዘዣው ላይ የተመለከተዉ ፊርማ በሲስተሙ ላይ ከተመለከተዉ የፊርማ ናሙና ጋር ተመሳሳይ መሆን አለመሆኑን ለማረጋገጥ የወጪ ማዘዣው ላይ የተመለከተዉ ፊርማ ከናሙና ፊርማ ጋር የሚመሳሰል መሆን አለመሆኑ ገለልተኛ በሆነ አካል ታይቶ መረጋገጥ ይኖርበታል።
በመሆኑም ክስ ከቀረበበት ባንክ ዉጪ በሌሎች ባንኮች ከወጪ ማዛዣ ክፍያ ጋር በተያያዘ ልምድ ባላቸዉ የባንክ ባለሙያዎች እንዲታይ በማድረግ ባንኩ ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ ግዴታዉን የተወጣ መሆን አለመሆኑ ማረጋገጥ ይገባል፡፡ የባለሂሳቡ ባንክ ደብተር ቀርቦ ሂሳቡ ተቀንሶ የተጻፈ መሆን አለመሆኑ ሆነ የባለሂሳቡ መታወቂያ በማየት ባንኩ ያረጋገጠ መሆን አለመሆኑ ደግሞ በሰው ማስረጃ ሆኖ የባንክ ሂሳብ ደብተሩ ካለ በማስቀረብ መረጋገጥ ይኖርበታል።
ሰ/መ/ቁ. 220830 ጥቅምት 29 ቀን 2015 ዓ/ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
#Bank #law #lawyer
#SAMUELGIRMA
Join 👈
https://t.me/lawsocieties
👍1
One_person_private_limited_Company_vs_Limited_Liability_Partnership.pdf
174.7 KB
ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (One-person private limited Company) እና ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበር (Limited Liability Partnership)
Via በአበጀ ካሣሁን
Via በአበጀ ካሣሁን
👍2
አዲሱ የንግድ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1243/2013
1. ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር
(One person private limited Company)
2. የህብረት ሽርክና ማህበር
(General partnership)
3. ሁለት ዓይነት ኃላፊነት ያለበት የሽርክና ማኅበር
(Limited Partnership)
4. የአሽሙር ሽርክና ማህበር
(Joint venture)
5. የአክሲዮን ማህበር
(Share compary)
6. ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል
(Private limited company)
https://t.me/lawsocieties
1. ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር
(One person private limited Company)
2. የህብረት ሽርክና ማህበር
(General partnership)
3. ሁለት ዓይነት ኃላፊነት ያለበት የሽርክና ማኅበር
(Limited Partnership)
4. የአሽሙር ሽርክና ማህበር
(Joint venture)
5. የአክሲዮን ማህበር
(Share compary)
6. ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል
(Private limited company)
https://t.me/lawsocieties
👍15
🔷Vacancy for Law office🔷
1. Junior Accountant
2. Junior Cashier and secretary
3. Accountant 1-2 year experience
4. Guday Asfetsami (ጉዳይ አስፈፃሚ)
👉 How to Apply 👈
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
lawsocieties@gmail.com
Or
consultantentrust@gmail.com
Deadline
Jan 10, 2023
Share for your friends
👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
1. Junior Accountant
2. Junior Cashier and secretary
3. Accountant 1-2 year experience
4. Guday Asfetsami (ጉዳይ አስፈፃሚ)
👉 How to Apply 👈
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
lawsocieties@gmail.com
Or
consultantentrust@gmail.com
Deadline
Jan 10, 2023
Share for your friends
👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
👍7🥰5