#ተቋሙ_ሐሰተኛ_የትምህርት_ማስረጃን_ለማጥራት_ከባለድርሻ_አካላት_ጋር_በቅንጅት_እየሠራ_ነው
====== ====== ====
አዲስ አበባ፡- በፌዴራልና በክልል የመንግሥት ተቋማት በሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ተቀጥረው የሚሠሩ ግለሰቦችን ለማጥራት በትብብር እየተሠራ መሆኑን የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን ገለጸ።
የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ ወይዘሪት ማርታ አድማስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ተቋሙ ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃን ለማጥራት በሚሠራው መጠነ ሰፊ ሥራ የፌዴራልና የክልል ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሠሩ ነው።
የፌዴራልና የክልል ተቋማት አዲስ የሰው ኃይል ቅጥር ሲፈፅሙ እና የደረጃ ዕድገት ሲሠጡ የሠራተኞችን የትምህርት ማስረጃ ሐሰተኛ መሆንና አለመሆኑ እንዲጣራላቸው ወደ ተቋሙ መላካቸው አብረው የመሥራት ቁርጠኝነታቸውን ያሳያል ብለዋል።
እንደማሳያም የደበብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከክልል እስከ ወረዳ ያለው የመንግሥት መዋቅር ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃን በማጋለጥና በማጥራት ሂደት ቀዳሚ እንደሆነ ገልፀዋል። በተጨማሪም የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ህዝቦች ክልል፣ የጤና ሚኒስቴር፣ የጉምሩክ ኮሚሽን፣ ማዕከላዊ ስታስቲክስ እና ሌሎች የፌዴራልና የክልል ተቋማት ከትምህርት እና ሥልጠና ባለሥልጣን ጋር በቅርበት እየሠሩ መሆኑን ወይዘሪት ማርታ ተናግረዋል።
ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃን ለማጥራት ተማሪዎች አገር አቀፍ ፈተና ወስደው የፌዴራል ትምህርት ሚኒስቴር ያስቀመጠውን የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ነጥብ ማምጣታቸውንና መረጃ ተቀብሎ የማጥራት ሥራ እየሠራ መሆኑን አብራርተዋል።
====== ====== ====
አዲስ አበባ፡- በፌዴራልና በክልል የመንግሥት ተቋማት በሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ተቀጥረው የሚሠሩ ግለሰቦችን ለማጥራት በትብብር እየተሠራ መሆኑን የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን ገለጸ።
የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ ወይዘሪት ማርታ አድማስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ተቋሙ ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃን ለማጥራት በሚሠራው መጠነ ሰፊ ሥራ የፌዴራልና የክልል ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሠሩ ነው።
የፌዴራልና የክልል ተቋማት አዲስ የሰው ኃይል ቅጥር ሲፈፅሙ እና የደረጃ ዕድገት ሲሠጡ የሠራተኞችን የትምህርት ማስረጃ ሐሰተኛ መሆንና አለመሆኑ እንዲጣራላቸው ወደ ተቋሙ መላካቸው አብረው የመሥራት ቁርጠኝነታቸውን ያሳያል ብለዋል።
እንደማሳያም የደበብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከክልል እስከ ወረዳ ያለው የመንግሥት መዋቅር ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃን በማጋለጥና በማጥራት ሂደት ቀዳሚ እንደሆነ ገልፀዋል። በተጨማሪም የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ህዝቦች ክልል፣ የጤና ሚኒስቴር፣ የጉምሩክ ኮሚሽን፣ ማዕከላዊ ስታስቲክስ እና ሌሎች የፌዴራልና የክልል ተቋማት ከትምህርት እና ሥልጠና ባለሥልጣን ጋር በቅርበት እየሠሩ መሆኑን ወይዘሪት ማርታ ተናግረዋል።
ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃን ለማጥራት ተማሪዎች አገር አቀፍ ፈተና ወስደው የፌዴራል ትምህርት ሚኒስቴር ያስቀመጠውን የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ነጥብ ማምጣታቸውንና መረጃ ተቀብሎ የማጥራት ሥራ እየሠራ መሆኑን አብራርተዋል።