በቀደምት ታሪክ የተጀመረው ከክርስቶስ ልደት በፊት በ18ኛው ክፍለ ዘመን ሲሆን እሱም በባቢሎን ንጉሥ ሃሙራቢ ኮድ (የሃሙራቢ ህግ/ኮድ)ውስጥ አይንን ላጠፋ አይኑ ይጥፋ፣እጅ ለቆረጠ እጁ እንዲቆረጥ የሚል ህግ ነው፡፡ አሁን ከወንጀል አድራጊ የወንጀል ማድረግ መነሻ ሀሳብ ተነስተን ከግዜ ወደግዜ የወንጀል ህግ አላማ እና ግብ እያደገ መጥቷል፡፡ በ1996 አ.ም በወጣው የወንጀል ህግ አላማው ለጠቅላላው ጥቅም ሲባል የሀገሪቱን መንግስት የነዋሪዎችን፣ የህዝቦችን፣ የህብረተሰቡን ሰላም፣ ደህንነት፣ መብት እና ጥቅም ማስጠበቅ እና ማረጋገጥ ነው፡፡ ከዛም ይህንን አላማ ለማሳካት ወንጀል እንዳይፈፀም መከላከልን ግብ በዋነኛነት የያዘ ነው፡፡ ስለወንጀል ግንዛቤ በመፍጠር እና ማስጠንቀቂያ በመስጠት ከመከላከል ባለፈ ወንጀል ተፈፅሞ ሲገኝ ደግሞ ወንጀል ፈፃሚውን በመቅጣት ወንጀለኛውን ከሌላ ወንጀል ድርጊት መፈፀም እንዲቆጠብ በማድረግ እና ህብረተሰቡን ከወንጀለኛው እንዲማር ሌላ ተጨማሪ ወንጀል እንዳይፈፀም የማድረግ አላማ ነው፡፡ ወንጀል አድራጊዎች ተቀጥተው ከጥፋታቸው ተምረው እና ታርመው ጥሩ ዜጋ እንዲሆኑ ማድረግ ነው፡፡
እድሜ አንፃር ስንመለከት፡- ሰዎች በእድሜያቸው መጠን ስለወንጀል ምንነት እና አፈፃፀም ያላቸው አረዳድ በእደሜያቸው ልክ የተለያየ እንደመሆኑ ቅጣትም ለመጣል እንዲሁ ይለያያል፡፡ የወንጀል ህጉ የወንጀል አድራጊን ከማስተማር እና የቅጣት አጣጣል ምጣኔን ለማምጣት ሲባል የወንጀል አድራጊዎችን በእድሜ ለይቶቷቸዋል፡፡ ይኸውም በሶስት የእድሜ ክልል የሚከፍለው ሲሆን፡- ከዘጠኝ (9) አመት በታች የሆኑትን ህፃናት በወንጀል ፍፁም ሊጠየቁ የማይችሉ፣ ከዘጠኝ(9) አመት እስከ አስራአምስት አመት(15) ዕድሜ ያሉት የጥንቃቄ እርምጃ (አንድ ቦታ ተወስነው እንዲቀመጡ፣የፀባይ ማረሚያ ቦታዎች እንዲሄዱ፣የተወሰኑ ቦታዎች ከመሄድ እንዲከለከሉ ማድረግ…) ሲሆን ይህ ቅጣት ውጤት ካላመጣ በስተቀር የገንዘብ ወይም የእስራት ቅጣት ሊቀጡ አይችሉም፣ ከአስራአምስት (15) አስከ አስራ ስምንት (18) አመት የሆኑት በመደበኛ ቅጣት የሚቀጡ ናቸው፡፡
እድሜ አንፃር ስንመለከት፡- ሰዎች በእድሜያቸው መጠን ስለወንጀል ምንነት እና አፈፃፀም ያላቸው አረዳድ በእደሜያቸው ልክ የተለያየ እንደመሆኑ ቅጣትም ለመጣል እንዲሁ ይለያያል፡፡ የወንጀል ህጉ የወንጀል አድራጊን ከማስተማር እና የቅጣት አጣጣል ምጣኔን ለማምጣት ሲባል የወንጀል አድራጊዎችን በእድሜ ለይቶቷቸዋል፡፡ ይኸውም በሶስት የእድሜ ክልል የሚከፍለው ሲሆን፡- ከዘጠኝ (9) አመት በታች የሆኑትን ህፃናት በወንጀል ፍፁም ሊጠየቁ የማይችሉ፣ ከዘጠኝ(9) አመት እስከ አስራአምስት አመት(15) ዕድሜ ያሉት የጥንቃቄ እርምጃ (አንድ ቦታ ተወስነው እንዲቀመጡ፣የፀባይ ማረሚያ ቦታዎች እንዲሄዱ፣የተወሰኑ ቦታዎች ከመሄድ እንዲከለከሉ ማድረግ…) ሲሆን ይህ ቅጣት ውጤት ካላመጣ በስተቀር የገንዘብ ወይም የእስራት ቅጣት ሊቀጡ አይችሉም፣ ከአስራአምስት (15) አስከ አስራ ስምንት (18) አመት የሆኑት በመደበኛ ቅጣት የሚቀጡ ናቸው፡፡
የሞት ቅጣት
የሞት ቅጣት ክቡር የሆነዉን የሰውን ህይወት የሚያሳጣ የቅጣት አይነት ከመሆኑ የተነሳ ሁለት ተቃራኒ አቋሞች ያሉትና በብዙ መንግስታት እና በአለም ዙሪያ ያሉ ሀገራት አከራካሪ ነው፡፡ ከሰብዓዊ መብቶች ተቆርቋሪዎች አንጻር የሚነሳ ሲሆን ሀሳባቸውን ሲገልፁ በህይወት የመኖር መብት በተፈጥሮ የተሰጠ የማይገረሰስ መብት እንደመሆኑ በፍርድ ሂደት ሊነፈግ አይችልም፡፡ የወንጀል ህጉ አላማ የወንጀል አድራጊን ማስተማር እና ማረም እንደመነሻ ያስቀመጠ በመሆኑ በሞት ቅጣት ወንጀል አድራጊን የሚያርም ሆነ የሚያስተምር አይደለም፣ በሞት ቅጣት ምክንያት ህብረተሰቡ ከወንጀለኛው ተምሮ ወንጀል ማስቀረት(መቀነስ) ይቻላል ቢባልም ተሟጋቾቹ እንደሚያነሱት የሞት ቅጣት በነበረበት ወቅት እና ባልነበረበት ወቅት ያለው የወንጀል መፈፀም መጠን ያልቀነሰ እና ልዩነት የሌለ በመሆኑ የሞት ቅጣት የሚያመጣው የተሻለ ለውጥ ባለመኖሩ ሊቀር ይገባል፣ ሌላው መከራከሪያ በሞት ቅጣት ከተቀጣ በኋላ ስህተት መሆኑ ቢታወቅ ወደኋላ የሚመለስ ባለመሆኑ የማይስተካከል ስህተት ይሆናል የሚሉ ሃሳቦች ያሉ ሲሆን በአንፃሩ ደግሞ የሞት ቅጣትን የሚደግፉት በሕይወት የመኖር መብት ተፈጥሮአዊ መብት ቢሆንም በከባድ ወንጀሎች አማካኝነት ግን የሞት ፍርድ ሊወሰድ ይችላል፡፡ ከተፈፀመው ወንጀል አንፃር ተመጣጣኝ ቅጣት እስከሆነ ድረስ የወንጀል ህጉም እንደቅጣት ስካስቀመጠው ድረስ እና ሌሎች ከወንጀል ድርጊት እንዲቆጠቡ እስካደረገ ድረስ ተፈፃሚነት ሊኖረው ይገባል የሚሉ ናቸው፡፡ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ በወንጀል ህግ የሞት ቅጣት የሚወሰነው ከባድ ለሆኑ ወንጀሎች እንደሆነ ከድንጋጌው ዝርዝር ሀሳብ ውስጥ አካቷል፡፡ የሞት ቅጣት ከተወሰነ በኋላ እንዲፈፀም በህገመንግስቱ መሰረት ፕሬዝዳነት መፈረም አለበት፡፡ የሞት ቅጣት በወንጀል ህጉ አንቀጽ 117 (1) መሰረት፡-
1. የወንጀል ድርጊቱ በሞት የሚያስቀጣ ስለመሆኑ ወንጀሉን በሚያቋቋመው የህጉ ልዩ ክፍል በግልጽ ተደንግጎ ሲገኝ፣
2. ወንጀሉ ፍፃሜ ያገኘ ማለትም በሙከራ ደረጃ ላይ ያልተገታ ሲሆን፣
3. ቅጣቱን የሚያቀልለት ምንም አይነት ማቅለያ ምክንያት የሌለ እንደሆነ፣
4. የተፈፀመው ወንጀል እጅግ በጣም ከባድና ወንጀለኛው በተለይ አደገኛ ሲሆን እና
5. አጥፊው የቅጣት ፍርድ በሚሰጥበት ጊዜ እድሜው 18 የሞላዉ ከሆነ ነዉ፡፡
=============
በኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ(2)
https://t.me/lawsocieties
የሞት ቅጣት ክቡር የሆነዉን የሰውን ህይወት የሚያሳጣ የቅጣት አይነት ከመሆኑ የተነሳ ሁለት ተቃራኒ አቋሞች ያሉትና በብዙ መንግስታት እና በአለም ዙሪያ ያሉ ሀገራት አከራካሪ ነው፡፡ ከሰብዓዊ መብቶች ተቆርቋሪዎች አንጻር የሚነሳ ሲሆን ሀሳባቸውን ሲገልፁ በህይወት የመኖር መብት በተፈጥሮ የተሰጠ የማይገረሰስ መብት እንደመሆኑ በፍርድ ሂደት ሊነፈግ አይችልም፡፡ የወንጀል ህጉ አላማ የወንጀል አድራጊን ማስተማር እና ማረም እንደመነሻ ያስቀመጠ በመሆኑ በሞት ቅጣት ወንጀል አድራጊን የሚያርም ሆነ የሚያስተምር አይደለም፣ በሞት ቅጣት ምክንያት ህብረተሰቡ ከወንጀለኛው ተምሮ ወንጀል ማስቀረት(መቀነስ) ይቻላል ቢባልም ተሟጋቾቹ እንደሚያነሱት የሞት ቅጣት በነበረበት ወቅት እና ባልነበረበት ወቅት ያለው የወንጀል መፈፀም መጠን ያልቀነሰ እና ልዩነት የሌለ በመሆኑ የሞት ቅጣት የሚያመጣው የተሻለ ለውጥ ባለመኖሩ ሊቀር ይገባል፣ ሌላው መከራከሪያ በሞት ቅጣት ከተቀጣ በኋላ ስህተት መሆኑ ቢታወቅ ወደኋላ የሚመለስ ባለመሆኑ የማይስተካከል ስህተት ይሆናል የሚሉ ሃሳቦች ያሉ ሲሆን በአንፃሩ ደግሞ የሞት ቅጣትን የሚደግፉት በሕይወት የመኖር መብት ተፈጥሮአዊ መብት ቢሆንም በከባድ ወንጀሎች አማካኝነት ግን የሞት ፍርድ ሊወሰድ ይችላል፡፡ ከተፈፀመው ወንጀል አንፃር ተመጣጣኝ ቅጣት እስከሆነ ድረስ የወንጀል ህጉም እንደቅጣት ስካስቀመጠው ድረስ እና ሌሎች ከወንጀል ድርጊት እንዲቆጠቡ እስካደረገ ድረስ ተፈፃሚነት ሊኖረው ይገባል የሚሉ ናቸው፡፡ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ በወንጀል ህግ የሞት ቅጣት የሚወሰነው ከባድ ለሆኑ ወንጀሎች እንደሆነ ከድንጋጌው ዝርዝር ሀሳብ ውስጥ አካቷል፡፡ የሞት ቅጣት ከተወሰነ በኋላ እንዲፈፀም በህገመንግስቱ መሰረት ፕሬዝዳነት መፈረም አለበት፡፡ የሞት ቅጣት በወንጀል ህጉ አንቀጽ 117 (1) መሰረት፡-
1. የወንጀል ድርጊቱ በሞት የሚያስቀጣ ስለመሆኑ ወንጀሉን በሚያቋቋመው የህጉ ልዩ ክፍል በግልጽ ተደንግጎ ሲገኝ፣
2. ወንጀሉ ፍፃሜ ያገኘ ማለትም በሙከራ ደረጃ ላይ ያልተገታ ሲሆን፣
3. ቅጣቱን የሚያቀልለት ምንም አይነት ማቅለያ ምክንያት የሌለ እንደሆነ፣
4. የተፈፀመው ወንጀል እጅግ በጣም ከባድና ወንጀለኛው በተለይ አደገኛ ሲሆን እና
5. አጥፊው የቅጣት ፍርድ በሚሰጥበት ጊዜ እድሜው 18 የሞላዉ ከሆነ ነዉ፡፡
=============
በኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ(2)
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
12ኛ-ክፍል ተማረወች በሙሉ Natural & Social-Science የተዘጋጀ Online Entrance Exam ከታች ባለዉ Website በመግባት መፈተን ይችላሉ።👇👇👇👇👇👇👇
🌐www.ethabstudent.com
🚐🙏ለጓደኞችዎ Share በማድረግ ይተባበሩ።
https://t.me/lawsocieties
🌐www.ethabstudent.com
🚐🙏ለጓደኞችዎ Share በማድረግ ይተባበሩ።
https://t.me/lawsocieties
Forwarded from 🇪🇹የሕግ ጉዳይ
Ethiopia Commodity Exchange (ECX) በዜሮ ዓመት ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
Postion:Junior Investigation and Enforcement Officer
📚የትምህርት ዓይነት እና ደረጃ:
LLB(Law) Degree from recognized University.
🇪🇹 የስራ ቦታ : Addis Ababa
🧭የምዝገባ ጊዜ ፡እስከ ጥቅምት
8/2015 ዓ.ም
🔔ስለ ስራው ሙሉ መረጃ ለማየት እና ለማመልከት ቀጣዩን ሊንክ ይጠቀሙ
https://jobs.amazonethiopia.com/job/junior-investigation-and-enforcement-officer/
Postion:Junior Investigation and Enforcement Officer
📚የትምህርት ዓይነት እና ደረጃ:
LLB(Law) Degree from recognized University.
🇪🇹 የስራ ቦታ : Addis Ababa
🧭የምዝገባ ጊዜ ፡እስከ ጥቅምት
8/2015 ዓ.ም
🔔ስለ ስራው ሙሉ መረጃ ለማየት እና ለማመልከት ቀጣዩን ሊንክ ይጠቀሙ
https://jobs.amazonethiopia.com/job/junior-investigation-and-enforcement-officer/
Legal Aid
Amhara Bank S.C
Addis Ababa
Full–time
Job Requirements Qualifications: - Diploma/Level IV in Law (COC is mandatory for Level graduates)Experience: - 3 years relevant experience in the banking industry or court.
How To Apply:
Only shortlisted candidates will be communicated
Hard copy or physical applications will not be accepted
The Bank has the right to cancel the post.
Interested applicants fulfilling the above requirements are invited to apply within five (5) consecutive days from October 7, 2022 to October 11, 2022 only via.
Application Form - Legal Aid
For any inquiry contact us on 690.
https://t.me/lawsocieties
Amhara Bank S.C
Addis Ababa
Full–time
Job Requirements Qualifications: - Diploma/Level IV in Law (COC is mandatory for Level graduates)Experience: - 3 years relevant experience in the banking industry or court.
How To Apply:
Only shortlisted candidates will be communicated
Hard copy or physical applications will not be accepted
The Bank has the right to cancel the post.
Interested applicants fulfilling the above requirements are invited to apply within five (5) consecutive days from October 7, 2022 to October 11, 2022 only via.
Application Form - Legal Aid
For any inquiry contact us on 690.
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
Company: Amhara Bank S.C
Job Type: Full Time
Work Place: Addis Ababa
Qualifications:
- LLB in Law. Experience:
- 1 year relevant experience in the banking industry or Court.
- Only shortlisted candidates will be communicated
- Hard copy or physical applications will not be accepted
- The Bank has the right to cancel the post. More Information
- Address Ethiopia
- Experience Level Junior
- Total Years Experience 0-5 Amhara Bank S.C
https://t.me/lawsocieties
Job Type: Full Time
Work Place: Addis Ababa
Qualifications:
- LLB in Law. Experience:
- 1 year relevant experience in the banking industry or Court.
- Only shortlisted candidates will be communicated
- Hard copy or physical applications will not be accepted
- The Bank has the right to cancel the post. More Information
- Address Ethiopia
- Experience Level Junior
- Total Years Experience 0-5 Amhara Bank S.C
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
Forwarded from ሕግ ቤት
Deutsche Gesellschaft für Internationale Zusammenarbeit (GIZ) GmbH ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
Position: - Adminstrative Specialist
📚ትምህርት ዓይነት እና ደረጃ:-
University degree in economics, law, or another related subject
🇪🇹 የስራ ቦታ ፡ አዲስ አበባ
🧭የምዝገባ ጊዜ ፡ እስከ ጥቅምት
08 /2015 ዓ.ም
🔔ስለ ስራው ሙሉ መረጃ ለማየት እና ለማመልከት ቀጣዩን ሊንክ ይጠቀሙ
https://tikusjobs.com/job/adminstrative-specialist/
Position: - Adminstrative Specialist
📚ትምህርት ዓይነት እና ደረጃ:-
University degree in economics, law, or another related subject
🇪🇹 የስራ ቦታ ፡ አዲስ አበባ
🧭የምዝገባ ጊዜ ፡ እስከ ጥቅምት
08 /2015 ዓ.ም
🔔ስለ ስራው ሙሉ መረጃ ለማየት እና ለማመልከት ቀጣዩን ሊንክ ይጠቀሙ
https://tikusjobs.com/job/adminstrative-specialist/
ያለመያዝ እና ያለመከሰስ መብት/Legal Immunity/
=============== ==========
ያለመያዝ እና ያለመከሰስ መብት ምንነት
ለህዝብ እና ሀገር ጥቅም ሲባል ለተወሰኑ ሰዎች የሚሰጥ በሁኔታ ላይ የተመረኮዘ የህግ ጥበቃ ሲሆን ይሄንን መብት የተጎናጸፉ ሰዎች በህግ የተደነገጉ ሁኔታዎችን እስካልተላለፉ ድረስ ወይም ከለላው እስካልተነሳ ድረስ ያለመያዝ እና ያለመከሰስ መብት አላቸው፡፡ ይህ ልዩ መብት ወይም (Privilege) ተደርጎ የሚወሰድ ሲሆን የሚሰጥበት አላማ ይህ መብት ወይም ጥበቃ የሚሰጣቸው ሰዎች ባላቸው ሀላፊነት እና ተግባር ምክንያት ስራቸውን በሚያደናቅፍ መልኩ በየምክንያቱ የማሰርና የመክሰስ ተግባር እንዳይኖር በማድረግ የሚያከናውኑትን ተግባር እና የሚወከሉትን ሀላፊነት መጠበቅ ነው፡፡ ይህ ልዩ መብት ጥፋት ወይም ወንጀል ለመፈፀም ፈቃድ ለመስጠት ወይም ተጠያቂነትን ለማስቆም (impunity) እንዲኖር አይደለም፡፡ ልዩ መብቱ የሚሰጣቸው ሰዎች ይታመናሉ ህግንም ያከብራሉ ከሚል እምነት ነው፡፡ ይህ ልዩ መብት የሚሰጠው በልዩ ሁኔታ እንደመሆኑ በጠባቡ የሚተረጎምና አስፈላጊ መሆኑ በታመነ ጊዜ ብቻ በአዋጅ የሚሰጥ መሆኑ ሌላው ባህሪው ነው፡፡ ከለላው የተሰጣቸው ሰዎች ጥፋት ወይም ከባድ ወንጀል ፈፅመው ሲገኙ ግን ይህን ሁኔታ በምርመራ ክፍሉ በቂ ጥርጣሬ ብቻ ሳይሆን ከለላውን በሚከታተለው አካል የጥርጣሬው ትክክለኛነት ተረጋግጦ በህግ እንዲጠየቁ ይደረጋል፡፡
ያለመያዝ እና ያለመከሰስ መብት ያላቸው አካላት
1. የምክር ቤት አባላት
ምክር ቤት ማለት የህግ አውጪው የመንግስት አካል ሲሆን የተወሰኑ ሀገራት ባለ አንድ ምክር ቤት (unicameral) ያላቸው ሲሆን ሌሎች ደግሞ ባለ ሁለት ምክር ቤት (bicameral) የሆኑ አሉ፡፡ ስያሜውን ስናይ በኮመን ሎው የህግ ስርዐት የሚከተሉ ሀገራት የላይኛው እና የታችኛው ምክር ቤት እያሉ የሚገልጹት ሲሆን በእንግሊዘኛ አጠራሩ house of lord and house of common ይባላል፡፡
ያለመከሰስ መብት በአብዛኛው ለነዚሁ ለህዝብ እንደራሴዎች የተሰጠ መብት ሲሆን አባላቱ የወከላቸውን ህዝብ ሃሳብ እና ፍላጎት በነጻነት እንዲገልጹ እና በውጤታማነት መወከል እንዲችሉ ለማስቻል ያለመ መብት ነው፡፡
በሀገራችን የስርዐተ-መንግስት አወቃቀር መሰረት በፌዴራል እና በክልል ደረጃ የህግ አውጪ አካላት ያሉ ሲሆን በፌደራል ደረጃ ሁለት ምክር ቤቶች አሉ፡፡ እነሱም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የፌደሬሽን ምክር ቤት ሲሆኑ ክልሎችም የየራሳቸው ምክር ቤቶች አሏቸው፡፡ እነዚህ የምክር ቤት አባላት በህገ-መንግስቱ አንቀጽ 54 ንኡስ አንቀጽ 4 እና በአንቀጽ 63 መሰረት የሁሉም ህዝብ ተወካይ ናቸው፡፡ በዚሁ መሰረት ማንኛውም የምክር ቤት አባል በምክር ቤቱ ውስጥ በሚሰጠው አስተያየት ምክንያት አይከሰስም፣ አስተዳደራዊ እርምጃም አይወሰድበትም፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ ማንኛውም የምክር ቤት አባል ከባድ ወንጀል ሲፈጽም በወ/መ/ስ/ስ/ህግ አንቀጽ 19 እና 20 መሰረት እጅ ከፈንጅ ካልተያዘ በስተቀር ያለ ምክር ቤቱ ፈቃድ አይያዝም በወንጀልም አይከሰስም፡፡ ሆኖም ይህ መብት ፍጹማዊ መብት አይደለም፡፡ ይልቁንም በሁኔታዎች ላይ የተመረኮዘ መብት ነው።
በመሆኑም የምክር ቤት አባላት አባል የሆኑበት ምክር ቤት ሲፈቅድ ወይም የምክር ቤቱ ፈቃድ ሳያስፈልግ ከባድ ወንጀል ሲፈጽሙ እጅ ከፈንጅ ከተያዙ የሚያዙበት እና የሚከሰሱበት የህግ አሰራር ያለ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡ በክልሎች ህገ-መንግስታት እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቻርተር አዋጅ ቁጥር 361/1995(እንደተሻሻለው) አንቀጽ 12 ንኡስ አንቀጽ 3 እና 4 እና ድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ቻርተር መሰረት የክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮቹ ምክር ቤት አባላት ከላይ በተገለጸው መልኩ ያለመያዝ እና ያለመከሰስ መብት ያላቸው ሲሆን ከባድ ወንጀል ሲፈጽሙ እጅ ከፈንጅ ከተያዙ ግን የሚያዙበት ሁኔታ በህግ ተደንግጓል፡፡ ለሌላ ወንጀል ጉዳይ ግን የምክር ቤቶቹ ፈቃድ ያስፈልጋል፡፡ እዚህ ላይ ከባድ ወንጀል ምንድን ነው ለሚለው የአገራችንን የወንጀል ህግ ማየት የሚስፈልግ ሲሆን ህጉ ግልጽ በሆነ ሁኔታ ያስቀመጠው ነገር የለም፡፡ ሆኖም የወንጀል ህጉ አንቀጽ 106 እና 108 ባስቀመጡት አግባብ ቀላል እስራት እና ጽኑ አስራት የሚያስቀጡ ወንጀሎችን እንደየሁኔታው ከባድ ወንጀልን ለመለየት በመስፈርትነት መጠቀም ይቻላል፡፡
2. የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ
በአለምአቀፍ ህግ መሰረት የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት የላካቸውን አገር እና አለምአቀፍ ድርጅት ወክለው ባሉበት አገር ፍርድ ቤት በወንጀልም ሆነ በፍትሐብሔር ያለመከሰስ መብት አላቸው፡፡ ይህ ያለመከሰስ መብት የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ በመኖሪያቸው እና በቢሮዎቻቸው ለሚያደርጓቸው እንቅስቃሴም የሚሰጥ መብት/የህግ ጥበቃ ነው፡፡ ይህ ጥበቃ ሀገራችንም ፈርማ ባፀደቀችው የ1961 የቬና ዲፕሎማሲ ግንኙነት ስምምነት መሰረት የሚሰጥ ሲሆን ለውጭ አገራት አምባሳደሮች፣ ቆንስላዎች እና የኢምባሲቸው ሰራተኞች የሚሰራ ነው፡፡ እንዲሁም ለአለምአቀፍ ድርጅት ዳይሬክተሮች እና ሰራተኞች ከስራቸው ጋር በተገናኘ ሀገራችን በፈረመችው የመቀመጫ ሀገር ስምምነት (host country agreement) የሚሰጥ የህግ ጥበቃ ሲሆን ሆኖም ይህ ያለመከሰስ መብት ፍጹም አይደለም፡፡ ወንጀል በሚፈጸምበት ጊዜ የላካቸውን አገር ወይም አለምአቀፍ ድርጅት የበላይ ሀላፊ ያለመከሰስ መብቱን እንዲያነሳ በመጠየቅ ሲነሳ መያዝ እና መጠየቅ የሚቻል ሲሆን ይሄንን ማድረግ ካልተቻለ ግን ተጠርጣሪውን ከአገር እንዲወጣ ማድረግ (persona non grata) የአንድ ሀገር ሉዓላዊ ስልጣን ነው፡፡
3. ዳኞች
በፌደራል የዳኝነት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1233/2013 አንቀጽ 34 ንኡስ አንቀጽ 2 መሰረት ማንኛውም ዳኛ ከባድ ወንጀል ሲፈጽም እጅ ከፈንጅ ካልተያዘ ወይም በዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ያለመከሰስ መብቱ ካልተነሳ በስተቀር ሊያዝ፣ ሊታሰር እና ክስ ሊቀርብበት አይችልም፡፡ ይህ ህግ ዳኞች በህገመንግስቱ አንቀጽ 79 ንኡስ አንቀጽ 2 እና 3 ላይ የተደነገገውን ዳኞች ከማንኛውም የመንግስት ባለስልጣን ወይም ሌላ አካል ነጻ ሆነው በህግ ብቻ እየተመሩ የዳኝነት አገልግሎትን ማከናወን እንዳለባቸው የተደነገገውን ለማስፈጸም የወጣ ህግ ነው፡፡ በዚህም ዳኞች በሚወስኑት ውሳኔ ፍትህን ለማስፈን ከየትኛውም አካል መያዝ፣ እስር እና ክስ ሳይደርስባቸው ነጻ ሆነው እንዲሰሩ ለማስቻል ሲሆን በዚህም ፍትህ ፈላጊው ማህበረሰብ ተጠቃሚ ይሆናል፡፡ ነገር ግን ይህ የህግ ጥበቃ ፍጹም እና ዳኞችም እንደፈለጉት እንዲሰሩ የሚፈቅድ አይደለም፡፡ ዳኞች ከላይ ባነሳነው የወንጀል ህግ እና የወንጀለኛ መቅጫ ስነስርአት ህግ መሰረት ከባድ ወንጀል ሲፈጽሙ እጅ ከፈንጅ ከተያዙ ቀጥታ የሚያዙበት፣ የሚታሰሩበት እና የሚከሰሱበት ሁኔታ ያለ ሲሆን ከባድ ወንጀል ባይሆንም ወንጀል ከፈጸሙ በዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ ተደርጎ ተይዘው ክስም የሚቀርብባቸው መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡
=============== ==========
ያለመያዝ እና ያለመከሰስ መብት ምንነት
ለህዝብ እና ሀገር ጥቅም ሲባል ለተወሰኑ ሰዎች የሚሰጥ በሁኔታ ላይ የተመረኮዘ የህግ ጥበቃ ሲሆን ይሄንን መብት የተጎናጸፉ ሰዎች በህግ የተደነገጉ ሁኔታዎችን እስካልተላለፉ ድረስ ወይም ከለላው እስካልተነሳ ድረስ ያለመያዝ እና ያለመከሰስ መብት አላቸው፡፡ ይህ ልዩ መብት ወይም (Privilege) ተደርጎ የሚወሰድ ሲሆን የሚሰጥበት አላማ ይህ መብት ወይም ጥበቃ የሚሰጣቸው ሰዎች ባላቸው ሀላፊነት እና ተግባር ምክንያት ስራቸውን በሚያደናቅፍ መልኩ በየምክንያቱ የማሰርና የመክሰስ ተግባር እንዳይኖር በማድረግ የሚያከናውኑትን ተግባር እና የሚወከሉትን ሀላፊነት መጠበቅ ነው፡፡ ይህ ልዩ መብት ጥፋት ወይም ወንጀል ለመፈፀም ፈቃድ ለመስጠት ወይም ተጠያቂነትን ለማስቆም (impunity) እንዲኖር አይደለም፡፡ ልዩ መብቱ የሚሰጣቸው ሰዎች ይታመናሉ ህግንም ያከብራሉ ከሚል እምነት ነው፡፡ ይህ ልዩ መብት የሚሰጠው በልዩ ሁኔታ እንደመሆኑ በጠባቡ የሚተረጎምና አስፈላጊ መሆኑ በታመነ ጊዜ ብቻ በአዋጅ የሚሰጥ መሆኑ ሌላው ባህሪው ነው፡፡ ከለላው የተሰጣቸው ሰዎች ጥፋት ወይም ከባድ ወንጀል ፈፅመው ሲገኙ ግን ይህን ሁኔታ በምርመራ ክፍሉ በቂ ጥርጣሬ ብቻ ሳይሆን ከለላውን በሚከታተለው አካል የጥርጣሬው ትክክለኛነት ተረጋግጦ በህግ እንዲጠየቁ ይደረጋል፡፡
ያለመያዝ እና ያለመከሰስ መብት ያላቸው አካላት
1. የምክር ቤት አባላት
ምክር ቤት ማለት የህግ አውጪው የመንግስት አካል ሲሆን የተወሰኑ ሀገራት ባለ አንድ ምክር ቤት (unicameral) ያላቸው ሲሆን ሌሎች ደግሞ ባለ ሁለት ምክር ቤት (bicameral) የሆኑ አሉ፡፡ ስያሜውን ስናይ በኮመን ሎው የህግ ስርዐት የሚከተሉ ሀገራት የላይኛው እና የታችኛው ምክር ቤት እያሉ የሚገልጹት ሲሆን በእንግሊዘኛ አጠራሩ house of lord and house of common ይባላል፡፡
ያለመከሰስ መብት በአብዛኛው ለነዚሁ ለህዝብ እንደራሴዎች የተሰጠ መብት ሲሆን አባላቱ የወከላቸውን ህዝብ ሃሳብ እና ፍላጎት በነጻነት እንዲገልጹ እና በውጤታማነት መወከል እንዲችሉ ለማስቻል ያለመ መብት ነው፡፡
በሀገራችን የስርዐተ-መንግስት አወቃቀር መሰረት በፌዴራል እና በክልል ደረጃ የህግ አውጪ አካላት ያሉ ሲሆን በፌደራል ደረጃ ሁለት ምክር ቤቶች አሉ፡፡ እነሱም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የፌደሬሽን ምክር ቤት ሲሆኑ ክልሎችም የየራሳቸው ምክር ቤቶች አሏቸው፡፡ እነዚህ የምክር ቤት አባላት በህገ-መንግስቱ አንቀጽ 54 ንኡስ አንቀጽ 4 እና በአንቀጽ 63 መሰረት የሁሉም ህዝብ ተወካይ ናቸው፡፡ በዚሁ መሰረት ማንኛውም የምክር ቤት አባል በምክር ቤቱ ውስጥ በሚሰጠው አስተያየት ምክንያት አይከሰስም፣ አስተዳደራዊ እርምጃም አይወሰድበትም፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ ማንኛውም የምክር ቤት አባል ከባድ ወንጀል ሲፈጽም በወ/መ/ስ/ስ/ህግ አንቀጽ 19 እና 20 መሰረት እጅ ከፈንጅ ካልተያዘ በስተቀር ያለ ምክር ቤቱ ፈቃድ አይያዝም በወንጀልም አይከሰስም፡፡ ሆኖም ይህ መብት ፍጹማዊ መብት አይደለም፡፡ ይልቁንም በሁኔታዎች ላይ የተመረኮዘ መብት ነው።
በመሆኑም የምክር ቤት አባላት አባል የሆኑበት ምክር ቤት ሲፈቅድ ወይም የምክር ቤቱ ፈቃድ ሳያስፈልግ ከባድ ወንጀል ሲፈጽሙ እጅ ከፈንጅ ከተያዙ የሚያዙበት እና የሚከሰሱበት የህግ አሰራር ያለ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡ በክልሎች ህገ-መንግስታት እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቻርተር አዋጅ ቁጥር 361/1995(እንደተሻሻለው) አንቀጽ 12 ንኡስ አንቀጽ 3 እና 4 እና ድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ቻርተር መሰረት የክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮቹ ምክር ቤት አባላት ከላይ በተገለጸው መልኩ ያለመያዝ እና ያለመከሰስ መብት ያላቸው ሲሆን ከባድ ወንጀል ሲፈጽሙ እጅ ከፈንጅ ከተያዙ ግን የሚያዙበት ሁኔታ በህግ ተደንግጓል፡፡ ለሌላ ወንጀል ጉዳይ ግን የምክር ቤቶቹ ፈቃድ ያስፈልጋል፡፡ እዚህ ላይ ከባድ ወንጀል ምንድን ነው ለሚለው የአገራችንን የወንጀል ህግ ማየት የሚስፈልግ ሲሆን ህጉ ግልጽ በሆነ ሁኔታ ያስቀመጠው ነገር የለም፡፡ ሆኖም የወንጀል ህጉ አንቀጽ 106 እና 108 ባስቀመጡት አግባብ ቀላል እስራት እና ጽኑ አስራት የሚያስቀጡ ወንጀሎችን እንደየሁኔታው ከባድ ወንጀልን ለመለየት በመስፈርትነት መጠቀም ይቻላል፡፡
2. የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ
በአለምአቀፍ ህግ መሰረት የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት የላካቸውን አገር እና አለምአቀፍ ድርጅት ወክለው ባሉበት አገር ፍርድ ቤት በወንጀልም ሆነ በፍትሐብሔር ያለመከሰስ መብት አላቸው፡፡ ይህ ያለመከሰስ መብት የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ በመኖሪያቸው እና በቢሮዎቻቸው ለሚያደርጓቸው እንቅስቃሴም የሚሰጥ መብት/የህግ ጥበቃ ነው፡፡ ይህ ጥበቃ ሀገራችንም ፈርማ ባፀደቀችው የ1961 የቬና ዲፕሎማሲ ግንኙነት ስምምነት መሰረት የሚሰጥ ሲሆን ለውጭ አገራት አምባሳደሮች፣ ቆንስላዎች እና የኢምባሲቸው ሰራተኞች የሚሰራ ነው፡፡ እንዲሁም ለአለምአቀፍ ድርጅት ዳይሬክተሮች እና ሰራተኞች ከስራቸው ጋር በተገናኘ ሀገራችን በፈረመችው የመቀመጫ ሀገር ስምምነት (host country agreement) የሚሰጥ የህግ ጥበቃ ሲሆን ሆኖም ይህ ያለመከሰስ መብት ፍጹም አይደለም፡፡ ወንጀል በሚፈጸምበት ጊዜ የላካቸውን አገር ወይም አለምአቀፍ ድርጅት የበላይ ሀላፊ ያለመከሰስ መብቱን እንዲያነሳ በመጠየቅ ሲነሳ መያዝ እና መጠየቅ የሚቻል ሲሆን ይሄንን ማድረግ ካልተቻለ ግን ተጠርጣሪውን ከአገር እንዲወጣ ማድረግ (persona non grata) የአንድ ሀገር ሉዓላዊ ስልጣን ነው፡፡
3. ዳኞች
በፌደራል የዳኝነት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1233/2013 አንቀጽ 34 ንኡስ አንቀጽ 2 መሰረት ማንኛውም ዳኛ ከባድ ወንጀል ሲፈጽም እጅ ከፈንጅ ካልተያዘ ወይም በዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ያለመከሰስ መብቱ ካልተነሳ በስተቀር ሊያዝ፣ ሊታሰር እና ክስ ሊቀርብበት አይችልም፡፡ ይህ ህግ ዳኞች በህገመንግስቱ አንቀጽ 79 ንኡስ አንቀጽ 2 እና 3 ላይ የተደነገገውን ዳኞች ከማንኛውም የመንግስት ባለስልጣን ወይም ሌላ አካል ነጻ ሆነው በህግ ብቻ እየተመሩ የዳኝነት አገልግሎትን ማከናወን እንዳለባቸው የተደነገገውን ለማስፈጸም የወጣ ህግ ነው፡፡ በዚህም ዳኞች በሚወስኑት ውሳኔ ፍትህን ለማስፈን ከየትኛውም አካል መያዝ፣ እስር እና ክስ ሳይደርስባቸው ነጻ ሆነው እንዲሰሩ ለማስቻል ሲሆን በዚህም ፍትህ ፈላጊው ማህበረሰብ ተጠቃሚ ይሆናል፡፡ ነገር ግን ይህ የህግ ጥበቃ ፍጹም እና ዳኞችም እንደፈለጉት እንዲሰሩ የሚፈቅድ አይደለም፡፡ ዳኞች ከላይ ባነሳነው የወንጀል ህግ እና የወንጀለኛ መቅጫ ስነስርአት ህግ መሰረት ከባድ ወንጀል ሲፈጽሙ እጅ ከፈንጅ ከተያዙ ቀጥታ የሚያዙበት፣ የሚታሰሩበት እና የሚከሰሱበት ሁኔታ ያለ ሲሆን ከባድ ወንጀል ባይሆንም ወንጀል ከፈጸሙ በዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ ተደርጎ ተይዘው ክስም የሚቀርብባቸው መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
4. የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮች
በኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1265/2014 መሰረት አገራዊ ምክክሩን እንዲያመቻች በኮሚሽን ደረጃ የተቋቋመ ህጋዊ ሰውነት ያለው አገራዊ ተቋም ሲሆን ይሄንኑ ኮሚሽን እንዲመሩ በኮሚሸነርነት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሰየሙ 11 ኮሚሽነሮች እንዳሉት ይታወቃል፡፡ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 15(1(ሀ) መሰረት እነዚህ ኮሚሽነሮች ያለመከሰስ መብት ያላቸው ሲሆን በዚሁ መሰረት ያለመከሰስ መብታቸው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ካልተነሳ ወይም ወንጀል ሲፈጽሙ እጅ ከፈንጅ ካልተያዙ በስተቀር በኮሚሽነርነት በሚያገለግሉበት ወቅት ያለመከሰስ መብት አላቸው፡፡ እነዚህ ኮሚሽነሮች ከባድ ሀላፊነት ያለባቸው ሲሆን ስራቸውም ከማንም አካል ተጽእኖ ነጻ ሆኖ መከናወን እንዲችል የዚህ አይነቱ ጥበቃ በህግ ተድርጎላቸው ይገኛል፡፡
5. የምርጫ ስራ አመራር ቦርድ አባላት
በምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1133/2011 አንቀጽ 4 ንኡስ አንቀጽ 1 መሰረት ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሙሉ ጊዜ የሚያገለግሉ 5 አባላት ያሉት ስራ አመራር ቦርድ ያለው ሲሆን በዚሁ አዋጅ አንቀጽ 15 ንኡስ አንቀጽ 6 መሰረት የስራ አመራር ቦርድ አባላት ሃላፊነት ላይ አስካሉ ድረስ ከባድ ወንጀል ሲፈጽሙ እጅ ከፈንጅ ካልተያዙ በስተቀር ያለ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይሁንታ ያለመያዝ እና በወንጀል ያለመከሰስ መብት አላቸው፡፡ ይህ መብት ስራ አመራሩ የተጣለበትን ከፍተኛ ሀላፊነት ያለ ተጽኖ በነጻነት አንዲወጣ ለማስቻል ታስቦ የተደነገገ ነው፡፡ ይሄም መብት ጊዜአዊ ሲሆን አባላቱ ሀላፊነታቸውን ሲለቁ ወይም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያለመከሰስ መብታቸውን ሲያነሳ የሚያበቃ ነው፡፡
6. ለምርጫ የተመዘገቡ እጩዎች
በአትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ስነምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 42 መሰረት የግልም ሆነ የፖለቲካ ፓርቲዎች እጩ ተወዳዳሪ /እጩ ተመራጭ/ የሆኑ ሰዎች ከተመዘገቡበት ቀን አንስቶ ምርጫው አልቆ ውጤቱ እስኪገለጽ ድረስ በወንጀል ተጠርጥረው ያለመያዝ መብት አላቸው፡፡ ነገር ግን ከባድ ወንጀል ፈጽመው እጅ ከፈንጅ ከተያዙ ተይዘው ሊከሰሱ ይችላሉ፡፡ የፈጸሙት ወንጀል እጅ ከፈንጅ ባይሆንም የህግ እርምጃ የሚወሰድባቸው ምርጫው አልቆ ውጤቱ ከተገለጸ በኋላ ነው፡፡ ተጠርጣሪው በምርጫው ያሸነፈ ከሆነ በዚሁ ህግ መሰረት ሊያዝ እና ሊታሰር የሚችለው ያለመከሰስ መብቱ በተወከለበት ምክር ቤት ከተነሳ በኋላ ነው፡፡ የዚህ ከለላ ዋነኛ አለማ የምርጫ ውድድሩን ፍትሀዊ ለማድረግ እና ተወዳዳሪዎች ያለምንም እስር እና ክስ እና ሌሎች እንቅፋቶች የሚወክሉትን መራጭ የህብረተሰብ ክፍል ሀሳብ እና ፍላጎት እንዲገልጹ ወይም እንዲያራምዱ ለማድረግ ነው፡፡ ነገር ግን ከለላውን ሽፋን በማድረግ ወንጀል ከፈጸሙ ከላይ በተገለጸው አግባብ ከተጠያቂነት አያመልጡም፡፡
7. የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነሮች
በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 210/2002 (በአዋጅ ቁጥር 1224/2012 እንደተሻሻለው) በአንቀጽ 35 መሰረት የኮሚሽኑ ከፍተኛ ሀላፊዎች እና መርማሪዎች ያለመከሰስ መብታቸው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ካልተነሳ ወይም ከባድ ወንጀል ሲፈጽሙ እጅ ከፈንጅ ካልተያዙ በስተቀር አይከሰሱም፡፡ እነዚህ የስራ ሃላፊዎችም በአዋጅ ቁጥር 1224/2012 አንቀጽ 2 ንኡስ አንቀጽ 1 መሰረት ዋና ኮሚሽነር፣ ምክትል ዋና ኮሚሽነሮች እና የልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ የተሾሙ ኮሚሽነሮችን ይጨምራል፡፡ በተጨማሪም በአዋጅ ቁጥር 210/2002 አንቀጽ 2 (10) እና አንቀጽ 35 መሰረት በዋና ኮሚሽነሩ የተሰየሙ የሰብአዊ መብት ጥሰት መርማሪዎችም የዚህ መብት ተጠቃሚ ናቸው፡፡
በአጠቃላይ የህግ ከለላ ያላቸው ሰዎች ከባድ ወንጀል ሲፈጽሙ እጅ ከፈንጅ ከተገኙ በቀጥታ በቁጥጥር ስር ሊውሉ የሚችሉ መሆኑን አይተናል፡፡ በሌላ በኩል የህግ ከለላ የወንጀል ተጠያቂነትን የሚያስቀር ሳይሆን ከለላው የተሰጣቸው ሰዎች ካለባቸው የስራ ሀላፊነት ልዩ ባህሪ አንጻር ተጽዕኖ እንዳይደርስባቸው ታስቦ የተደነገገ ሲሆን በወንጀል ከተጠረጠሩ ግን ይህ ከለላ በህጋዊ ሂደት ተነስቶ የሚጠየቁ ይሆናል፡፡
በዚህም መሰረት ከባድ ወንጀል ከእጅ ከፈንጅ ውጭ በሆነ ሁኔታ ወይም ቀላል ወንጀል ፈጽመዋል ተብሎ ከተጠረጠሩ በህግ የተሰጣቸው ያለመያዝ እና ያለመከሰስ ከለላቸው እንዲነሳ በሚመለከተው አስፈጻሚ የመንግስት አካል ጥያቄ ሲቀርብ ጉዳዩ የቀረበለት የሚመለከተው ምክር ቤት በምክር ቤቱ አሰራር እና የአባላት የስነ ምግባር ደምብ መሰረት ማመልከቻ የቀረበበትን የምክር ቤት አባል ወይም የስራ ሀላፊ ያለመከሰስ መብት መነሳት አሳማኝ ሆኖ ሲያገኘው ያነሳል፡፡
ተጠርጣሪው ዳኛ ከሆነ በተመሳሳይ ሁኔታ በፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ጉዳዩ ታይቶ ያለመያዝ እና ያለመከሰስ መብቱ የሚነሳ ይሆናል፡፡ ከለላው በዚህ መልኩ ከተነሳ በ|ላ የሚመለከተው ህግ አስከባሪ መርማሪ አካል ተጠረጣሪውን የሚይዝ ዓቃቤ ህግም ክስ የሚያቀርብበት ሲሆን ጥፋተኛ ሆኖ ከተገኘ የሚቀጣበት የህግ አሰራር መኖሩን ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ ከዚህም መረዳት እንደሚቻለው የህግ የበላይነት በማንኛውም ሰው ላይ በእኩልነት የሚረጋገጥ እና የሚፈጸም መሆኑን ነው፡፡
በዮሃንስ ግርማ
ከፍትህ ሚኒስቴር ንቃተ ሕግ፣ ትምህርት እና ስልጠና ዳይሬክቶሬት
በኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1265/2014 መሰረት አገራዊ ምክክሩን እንዲያመቻች በኮሚሽን ደረጃ የተቋቋመ ህጋዊ ሰውነት ያለው አገራዊ ተቋም ሲሆን ይሄንኑ ኮሚሽን እንዲመሩ በኮሚሸነርነት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሰየሙ 11 ኮሚሽነሮች እንዳሉት ይታወቃል፡፡ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 15(1(ሀ) መሰረት እነዚህ ኮሚሽነሮች ያለመከሰስ መብት ያላቸው ሲሆን በዚሁ መሰረት ያለመከሰስ መብታቸው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ካልተነሳ ወይም ወንጀል ሲፈጽሙ እጅ ከፈንጅ ካልተያዙ በስተቀር በኮሚሽነርነት በሚያገለግሉበት ወቅት ያለመከሰስ መብት አላቸው፡፡ እነዚህ ኮሚሽነሮች ከባድ ሀላፊነት ያለባቸው ሲሆን ስራቸውም ከማንም አካል ተጽእኖ ነጻ ሆኖ መከናወን እንዲችል የዚህ አይነቱ ጥበቃ በህግ ተድርጎላቸው ይገኛል፡፡
5. የምርጫ ስራ አመራር ቦርድ አባላት
በምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1133/2011 አንቀጽ 4 ንኡስ አንቀጽ 1 መሰረት ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሙሉ ጊዜ የሚያገለግሉ 5 አባላት ያሉት ስራ አመራር ቦርድ ያለው ሲሆን በዚሁ አዋጅ አንቀጽ 15 ንኡስ አንቀጽ 6 መሰረት የስራ አመራር ቦርድ አባላት ሃላፊነት ላይ አስካሉ ድረስ ከባድ ወንጀል ሲፈጽሙ እጅ ከፈንጅ ካልተያዙ በስተቀር ያለ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይሁንታ ያለመያዝ እና በወንጀል ያለመከሰስ መብት አላቸው፡፡ ይህ መብት ስራ አመራሩ የተጣለበትን ከፍተኛ ሀላፊነት ያለ ተጽኖ በነጻነት አንዲወጣ ለማስቻል ታስቦ የተደነገገ ነው፡፡ ይሄም መብት ጊዜአዊ ሲሆን አባላቱ ሀላፊነታቸውን ሲለቁ ወይም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያለመከሰስ መብታቸውን ሲያነሳ የሚያበቃ ነው፡፡
6. ለምርጫ የተመዘገቡ እጩዎች
በአትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ስነምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 42 መሰረት የግልም ሆነ የፖለቲካ ፓርቲዎች እጩ ተወዳዳሪ /እጩ ተመራጭ/ የሆኑ ሰዎች ከተመዘገቡበት ቀን አንስቶ ምርጫው አልቆ ውጤቱ እስኪገለጽ ድረስ በወንጀል ተጠርጥረው ያለመያዝ መብት አላቸው፡፡ ነገር ግን ከባድ ወንጀል ፈጽመው እጅ ከፈንጅ ከተያዙ ተይዘው ሊከሰሱ ይችላሉ፡፡ የፈጸሙት ወንጀል እጅ ከፈንጅ ባይሆንም የህግ እርምጃ የሚወሰድባቸው ምርጫው አልቆ ውጤቱ ከተገለጸ በኋላ ነው፡፡ ተጠርጣሪው በምርጫው ያሸነፈ ከሆነ በዚሁ ህግ መሰረት ሊያዝ እና ሊታሰር የሚችለው ያለመከሰስ መብቱ በተወከለበት ምክር ቤት ከተነሳ በኋላ ነው፡፡ የዚህ ከለላ ዋነኛ አለማ የምርጫ ውድድሩን ፍትሀዊ ለማድረግ እና ተወዳዳሪዎች ያለምንም እስር እና ክስ እና ሌሎች እንቅፋቶች የሚወክሉትን መራጭ የህብረተሰብ ክፍል ሀሳብ እና ፍላጎት እንዲገልጹ ወይም እንዲያራምዱ ለማድረግ ነው፡፡ ነገር ግን ከለላውን ሽፋን በማድረግ ወንጀል ከፈጸሙ ከላይ በተገለጸው አግባብ ከተጠያቂነት አያመልጡም፡፡
7. የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነሮች
በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 210/2002 (በአዋጅ ቁጥር 1224/2012 እንደተሻሻለው) በአንቀጽ 35 መሰረት የኮሚሽኑ ከፍተኛ ሀላፊዎች እና መርማሪዎች ያለመከሰስ መብታቸው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ካልተነሳ ወይም ከባድ ወንጀል ሲፈጽሙ እጅ ከፈንጅ ካልተያዙ በስተቀር አይከሰሱም፡፡ እነዚህ የስራ ሃላፊዎችም በአዋጅ ቁጥር 1224/2012 አንቀጽ 2 ንኡስ አንቀጽ 1 መሰረት ዋና ኮሚሽነር፣ ምክትል ዋና ኮሚሽነሮች እና የልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ የተሾሙ ኮሚሽነሮችን ይጨምራል፡፡ በተጨማሪም በአዋጅ ቁጥር 210/2002 አንቀጽ 2 (10) እና አንቀጽ 35 መሰረት በዋና ኮሚሽነሩ የተሰየሙ የሰብአዊ መብት ጥሰት መርማሪዎችም የዚህ መብት ተጠቃሚ ናቸው፡፡
በአጠቃላይ የህግ ከለላ ያላቸው ሰዎች ከባድ ወንጀል ሲፈጽሙ እጅ ከፈንጅ ከተገኙ በቀጥታ በቁጥጥር ስር ሊውሉ የሚችሉ መሆኑን አይተናል፡፡ በሌላ በኩል የህግ ከለላ የወንጀል ተጠያቂነትን የሚያስቀር ሳይሆን ከለላው የተሰጣቸው ሰዎች ካለባቸው የስራ ሀላፊነት ልዩ ባህሪ አንጻር ተጽዕኖ እንዳይደርስባቸው ታስቦ የተደነገገ ሲሆን በወንጀል ከተጠረጠሩ ግን ይህ ከለላ በህጋዊ ሂደት ተነስቶ የሚጠየቁ ይሆናል፡፡
በዚህም መሰረት ከባድ ወንጀል ከእጅ ከፈንጅ ውጭ በሆነ ሁኔታ ወይም ቀላል ወንጀል ፈጽመዋል ተብሎ ከተጠረጠሩ በህግ የተሰጣቸው ያለመያዝ እና ያለመከሰስ ከለላቸው እንዲነሳ በሚመለከተው አስፈጻሚ የመንግስት አካል ጥያቄ ሲቀርብ ጉዳዩ የቀረበለት የሚመለከተው ምክር ቤት በምክር ቤቱ አሰራር እና የአባላት የስነ ምግባር ደምብ መሰረት ማመልከቻ የቀረበበትን የምክር ቤት አባል ወይም የስራ ሀላፊ ያለመከሰስ መብት መነሳት አሳማኝ ሆኖ ሲያገኘው ያነሳል፡፡
ተጠርጣሪው ዳኛ ከሆነ በተመሳሳይ ሁኔታ በፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ጉዳዩ ታይቶ ያለመያዝ እና ያለመከሰስ መብቱ የሚነሳ ይሆናል፡፡ ከለላው በዚህ መልኩ ከተነሳ በ|ላ የሚመለከተው ህግ አስከባሪ መርማሪ አካል ተጠረጣሪውን የሚይዝ ዓቃቤ ህግም ክስ የሚያቀርብበት ሲሆን ጥፋተኛ ሆኖ ከተገኘ የሚቀጣበት የህግ አሰራር መኖሩን ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ ከዚህም መረዳት እንደሚቻለው የህግ የበላይነት በማንኛውም ሰው ላይ በእኩልነት የሚረጋገጥ እና የሚፈጸም መሆኑን ነው፡፡
በዮሃንስ ግርማ
ከፍትህ ሚኒስቴር ንቃተ ሕግ፣ ትምህርት እና ስልጠና ዳይሬክቶሬት
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
Ale Hig አለ ህግ Balageru TV live Now..... 👈👈
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
የስራ ቅጥር ማስታወቂያ
የኢፌዲሪ ፍትሕ ሚኒስቴር በአውሮፓ ህብረት የወንጀል ፍትህ ስርዓት ማሻሻያ በኢትዮጵያ ፕሮጀክት ስር ከዚህ በታች ተያይዞ በቀረበው የጋዜጣ እትም ላይ በተጠቀሱት የስራ መስኮች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም መስፈርቱን የምታሟሉ ሁሉ ማስታወቂያው ከወጣበት መስከረም 29 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
https://t.me/lawsocieties
Apply👆👆👆👆👆👆👆
የኢፌዲሪ ፍትሕ ሚኒስቴር በአውሮፓ ህብረት የወንጀል ፍትህ ስርዓት ማሻሻያ በኢትዮጵያ ፕሮጀክት ስር ከዚህ በታች ተያይዞ በቀረበው የጋዜጣ እትም ላይ በተጠቀሱት የስራ መስኮች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም መስፈርቱን የምታሟሉ ሁሉ ማስታወቂያው ከወጣበት መስከረም 29 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
https://t.me/lawsocieties
Apply👆👆👆👆👆👆👆
#የሙያ_ጥፋት_ምንድን_ነዉ?
(#Professional_Fault)
ሙያ የሚባለዉ ልዩ ስልጠና፣ልዩ ዕዉቀትና ችሎታ የሚጠይቅ የስራ መስክ ነዉ።ሙያ በከፍተኛ የትምህህርት ተቋማት ገብቶ በመማር የሚገኘዉን አንደሕክምናምህንድስና፣ሕግመምህርነት የመሳሰለዉን ሲሆን በስራ ላይ ባለሙያዎች የሚሰሩትን እያዩ ወይም አበሮ በመስራትም የሙያ ዕዉቀት በማግኘት ባሉያ መሆን ይቻላል።
አንድ ባለሙያ ሙያ ብቻ ሳይሆን የሙያዉን የስነ ምግባር ደንብ ጨምሮ ጠንቅቆ ማወቅና ኃላፊነቱን ከሙያዉ የስነ ምግባር ደንብ አንፃር በአግባቡ መወጣት ይጠበቅበታል።የሙያ ጥፋት ብዙን ጊዜ የሚከሰተዉ ባለሙያዉ የሙያ ተግባሩን በሚፈጽመበት ጊዜ የሙያ ደንቦች ባለማክበሩ የሚከሰተ ጥፋት ነዉ።
የሙያ ጥፋትን ፍትሐ ብሔር ሕጉ ምን ይላል?
በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2031 መሰረት በለዩ ሙያዉ አንድ ስራ የሚፈፅም ሰዉ የሙያ ስራዉ የሚመራበትን ደንብ መጠበቅ እንደሚገባዉ የሕግ ግዴታ ተጥሎበታል።ይህ ባለሙያ በተሰማራበት የሙያ ዘርፍ የተሰማሩ ሰዎች ሁሉ የሚያወቋቸዉን ደንቦች እና መመሪዎች ሳያከበር ቢቀር የሙያ ጥፋት ፈፀመ ይባላል። ለመሆኑ የሙያ ደንቦች
የሚባሉት የትኞቹናቸዉ?የሙያደንቦች በሕግ የተደነገጉወይም በሙያዉ የተሰማሩ ሰዎች አዉቀዉየሚገለገሉባቸዉ ከተለመዱ የመልካም አስራር መመሪያዎች የመነጩ ሊሆን ይችላል።
አንድ ባለሙያ የሙያ ደንቦችን ጣሰ የሚባለዉ መቼ ነዉ?ደንቦች በሕግ በግልፅ የታወጁ በሆነ ጊዜ የፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 2035 መሰረት ባለሞያዉ በግልጽ የተመለከተዉን ደንበና ስርዓት የጣሰ እንደሆን ጥፋተኛ ነዉ።
የሙያ ደንቦቹ በሕግ በግልፅ ያልተደነገጉ ሳይሆኑ ከተለመዱ የመልካም አሰራር መመሪያዎች የመነጨ በሆነ ግዜ የባለሙያዉ ተግባር ጥፋት የሚሆነዉ ሌላ ጥበብ ካለዉ አመዛዛኝ በሆነ ሰዉ አስራር የሚመራ ባለሙያ ጋር ሲነፃፀር ትክክል ሆኖ ያልተገኘ እነደሆነ ነዉ።
የሙያ ደንቦች ሁሌም ቋሚ ናቸዉን?አንዳንድ ሙያዎቸ የሚተዳደሩት አንዴ በተወሰኑና በልማድ ላይ በተመሰረቱ ደንቦች ብቻ ሳይሆን በየጊዜዉ እያደገ እየተቀያየረ በሚሄድ በስነ ጥበብ ደንቦች ጭምር ነዉ።በመሆኑም አንድ ባለሙያ በየጊዜዉ እነዚህን ደንቦች የመመለከትና በሙያዉም የሚደረገዉን ምርምርና ለዉጥ ሁሉ የማወቅ ግዴታዉን መዘንጋት የለበትም።
አንድ ባለሙያ በዉል የገባዉን ግዴታ እንዴት ይወጣዋል? በመርህ ደረጃ አንድ ሰዉ በዉለ የገባዉን ግዴታ ካለተወጣ ከአላፊነት አያመልጥም።ነገር ግን በፍትሐ ብሔረ ሕግ ቁጭር 1795 መሰረት በዉል ግንኙነት በአንድ ሙያ የሚችለዉን ያህል በቻ ለማድረግ ዉል የገባዉ በሙያዉ ደንቦች መሰረት የተቻለዉን ሁሉ በሙሉ ኃላፊነትና በጥንቃቄ ካከናወነ አላፊነት የለበትም።ይህም ብዙ ጊዜ የሚያጋጥመዉ የዕዉቀት ስራን በሚመለከቱ እንደ ሕክምና ባሉ ጉዳዮቸ ላይ ነዉ። ለምሳሌ አንድ ሐኪም በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 2647 ድንጋጌ መሰረት በኪነ ጥበብ ደንቦች ጥፋት ካላደረገ በቀር ለመታከም ለተዋዋለዉ ሰዉ አላፊነት የለበትም። ነገር ግን በሙያዉ ኪነ ጥበብ ደንቦች መሰረት መስራት የሚገባዉን ሳይሰራ በመቅረቱ ወይም መስራት የማይገባዉን በመስራቱ ምከንያት የሕክምና አገልገሎት በሰጠዉ ሰዉ ላይ ጉዳት የሚያመጣ ተግባር የፈፀመ እንደሆነ እንዲሁም ሕክምና ሊያደርግለት የተቀበለዉን ሰዉ በቂ ባልሆነ ምክንያት ሳይረዳዉ የቀረ እንደሆነ በሰራዉ ተጠያቂ ነዉ።
በሙያ ስራ ሰለሚደረግ ጥፋትና የፍትሐ ብሔር ኃላፊነት፡ በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 2030 መሰረት አንደ ሰዉ ሕሊናን ወይም መልካም ጠባይን ተቃዋሚ በሆነ ዓይነት የማየገባዉን ስራ የሰራ ወይም የሚገባዉን ሳይሰራ የቀረ እንደሆነ ጥፋት አንደፈፀመ ይቆጠራል።
በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 2031 መሰረት በልዩ ሙዉ አንድ ስራ የሚፈጽም ሰዉ በስነ ጥበብ ወይም ራሱ በሚሰራዉ ኪነ ጥበብ ደንቦች መሰረት ያሉበትን ግዴታዎች አለመከተሉ ሲገለጽ ባለመጠንቀቅ ወይም በቸልተኝነት ጥፋተኛ ሆኖ በተገኘ ጊዜ አላፊ/ተጠያቂ/ ይሆናል።
እንዲሁም ለመጉዳት በማሰብ እያወቀ በሌላ ሰዉ ላየ ከፍ ያለ ጉዳት ያደረሰ ሰዉ በሰራዉ ስራ የጠያቂ ነዉ።
በሙያ ስራ ስለሚደረግ ጥፋትና የወንጀል አላፊነት፡ የወንጀል አላፊነት የሚኖረዉ በወንጀል ሕጉ እንዳይደረግ የተከለከለዉን በማድረግ ወይመ እንዲደረግ የታዘዘዉን ባለማድረግ ነዉ።
በወንጀል ሕግ ቁጥር69 መሰረት የሞያ ገዴታን ለመወጣት የተፈጸሙ ደረጊቶች ከሙያዉ ደንብና አሰራር ልማድ ዉጭ ካልሆኑና በከባደ የሙያ ጥፋት ካልተፈጸሙ በቀር አያሰቀጡም ይላል።ከድንጋጌዉ መረዳት እንደሚቻለዉ በሙያ ስራ የሚፈጸም ድርጊት ጥፋት ወይም ቸልተኝነት ከሌለበት በቀር አያስቀጣም።
በወንጀል ሕግ ቁጥር 575 መሰረት ማንም ሰዉ የሞያ ግዴታን በመተላለፍ አስቦ በሰዉ አካል ወይም ጤና ላይ ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ በወንጀል ተጠያቂ ይሆናል። ማንም ሰዉ በሕይወቱ፤ በሰዉነቱ፤ወይም በጤንነቱ ላይ ሊደርስ በሚችል ከባድ አደጋ ላይ የሚገኘዉን ሌላ ሰዉ ለመታደግ ወይም ለመርዳት የሙያ ግዴታ እያለበት ሊረዳዉ ሲችል አሰቦ ሳይረዳዉ የቀረ እንደሆነ በወንጀል ተጠያቂ ይሆናል።
ማንም ሰዉ የሌላ ሰዉን አካል ወይም ጤንነት የመጠበቅ የሙያ ግዴታ እያለበት በቸልተኝነት በሌላ ሰዉ አካል ወይም ጤንነት ላይ ጉዳተ ያደረሰ እንደሆነ በወንጀል ሕግ ቁጥር 559 መሰረት ተጠያቂ ይሆናል።
እንዲሁም የሌላ ሰዉን ሕይወት፤ጤንነት ወይም ደህንነት የመጠበቅ የሙያ ግዴታ እያለበት በቸልተኝነት ሰዉን የገደለ ሰዉ ቅጣቱ እንደሚከብድበት የወንጀል ሕግ ቁጥር 543(2) ይደነግጋል።
በሙያ ጥፋት ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸዉ ሰዎች ምን መብት አላቸዉ? ጉዳት የደረሰበት ሰዉ የባለሙያዉን አድራጎት ጥፋት መሆኑንና በዚህም የተነሳ ጉዳት የደረሰበት መሆኑን በማስረዳተ በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 2028 መሰረት ለደረሰበት ጉዳት ካሳ እንዲከፈል ስልጣን ባለዉ ፍርድ ቤት ክስ ማቅረብ ይቻላል። ነገር ግን ጉዳያቸዉን በራሳቸዉ ለመከታተል በአቅም ምከንያት የማይችሉ ዜጎች የአቅም ችገ ያለባቸዉ መሆኑን የሚያሳይ ማስረጃ በመያዝ በጠቅላይ ዐቃቢ ሕግ በዋናዉ መ/ቤትና በልደታ ወንጀል ዘርፍ እንዲሁም በአዲስ አበባ አሰሩም የጠቅላይ ዐቃቢ ሕግ ምድን ጽ/ቤቶች በመቅረብ ጉዳያቸዉን ዐቃቢ ህጎች እንዲከታተሉላቸዉ ማመልከት ይችላሉ። እንዲሁም የአቅም ሳይሆን የሕግ ዕዉቀት ችግር ያለባቸዉ ዜጎችም እንዲሁ ወደ ጽ/ቤቶች በመምጣት የምክር አገልግሎት በነጻ ማግኘት ይቻላል።
ሙያን አክበሮ መስራት የዜግነት ግዴታ ነው! ሃላፊነታችንን በያለንበት የሙያ መስክ በብቃት እንወጣ!
Federal Justice and Law Institute
https://t.me/lawsocieties
(#Professional_Fault)
ሙያ የሚባለዉ ልዩ ስልጠና፣ልዩ ዕዉቀትና ችሎታ የሚጠይቅ የስራ መስክ ነዉ።ሙያ በከፍተኛ የትምህህርት ተቋማት ገብቶ በመማር የሚገኘዉን አንደሕክምናምህንድስና፣ሕግመምህርነት የመሳሰለዉን ሲሆን በስራ ላይ ባለሙያዎች የሚሰሩትን እያዩ ወይም አበሮ በመስራትም የሙያ ዕዉቀት በማግኘት ባሉያ መሆን ይቻላል።
አንድ ባለሙያ ሙያ ብቻ ሳይሆን የሙያዉን የስነ ምግባር ደንብ ጨምሮ ጠንቅቆ ማወቅና ኃላፊነቱን ከሙያዉ የስነ ምግባር ደንብ አንፃር በአግባቡ መወጣት ይጠበቅበታል።የሙያ ጥፋት ብዙን ጊዜ የሚከሰተዉ ባለሙያዉ የሙያ ተግባሩን በሚፈጽመበት ጊዜ የሙያ ደንቦች ባለማክበሩ የሚከሰተ ጥፋት ነዉ።
የሙያ ጥፋትን ፍትሐ ብሔር ሕጉ ምን ይላል?
በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2031 መሰረት በለዩ ሙያዉ አንድ ስራ የሚፈፅም ሰዉ የሙያ ስራዉ የሚመራበትን ደንብ መጠበቅ እንደሚገባዉ የሕግ ግዴታ ተጥሎበታል።ይህ ባለሙያ በተሰማራበት የሙያ ዘርፍ የተሰማሩ ሰዎች ሁሉ የሚያወቋቸዉን ደንቦች እና መመሪዎች ሳያከበር ቢቀር የሙያ ጥፋት ፈፀመ ይባላል። ለመሆኑ የሙያ ደንቦች
የሚባሉት የትኞቹናቸዉ?የሙያደንቦች በሕግ የተደነገጉወይም በሙያዉ የተሰማሩ ሰዎች አዉቀዉየሚገለገሉባቸዉ ከተለመዱ የመልካም አስራር መመሪያዎች የመነጩ ሊሆን ይችላል።
አንድ ባለሙያ የሙያ ደንቦችን ጣሰ የሚባለዉ መቼ ነዉ?ደንቦች በሕግ በግልፅ የታወጁ በሆነ ጊዜ የፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 2035 መሰረት ባለሞያዉ በግልጽ የተመለከተዉን ደንበና ስርዓት የጣሰ እንደሆን ጥፋተኛ ነዉ።
የሙያ ደንቦቹ በሕግ በግልፅ ያልተደነገጉ ሳይሆኑ ከተለመዱ የመልካም አሰራር መመሪያዎች የመነጨ በሆነ ግዜ የባለሙያዉ ተግባር ጥፋት የሚሆነዉ ሌላ ጥበብ ካለዉ አመዛዛኝ በሆነ ሰዉ አስራር የሚመራ ባለሙያ ጋር ሲነፃፀር ትክክል ሆኖ ያልተገኘ እነደሆነ ነዉ።
የሙያ ደንቦች ሁሌም ቋሚ ናቸዉን?አንዳንድ ሙያዎቸ የሚተዳደሩት አንዴ በተወሰኑና በልማድ ላይ በተመሰረቱ ደንቦች ብቻ ሳይሆን በየጊዜዉ እያደገ እየተቀያየረ በሚሄድ በስነ ጥበብ ደንቦች ጭምር ነዉ።በመሆኑም አንድ ባለሙያ በየጊዜዉ እነዚህን ደንቦች የመመለከትና በሙያዉም የሚደረገዉን ምርምርና ለዉጥ ሁሉ የማወቅ ግዴታዉን መዘንጋት የለበትም።
አንድ ባለሙያ በዉል የገባዉን ግዴታ እንዴት ይወጣዋል? በመርህ ደረጃ አንድ ሰዉ በዉለ የገባዉን ግዴታ ካለተወጣ ከአላፊነት አያመልጥም።ነገር ግን በፍትሐ ብሔረ ሕግ ቁጭር 1795 መሰረት በዉል ግንኙነት በአንድ ሙያ የሚችለዉን ያህል በቻ ለማድረግ ዉል የገባዉ በሙያዉ ደንቦች መሰረት የተቻለዉን ሁሉ በሙሉ ኃላፊነትና በጥንቃቄ ካከናወነ አላፊነት የለበትም።ይህም ብዙ ጊዜ የሚያጋጥመዉ የዕዉቀት ስራን በሚመለከቱ እንደ ሕክምና ባሉ ጉዳዮቸ ላይ ነዉ። ለምሳሌ አንድ ሐኪም በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 2647 ድንጋጌ መሰረት በኪነ ጥበብ ደንቦች ጥፋት ካላደረገ በቀር ለመታከም ለተዋዋለዉ ሰዉ አላፊነት የለበትም። ነገር ግን በሙያዉ ኪነ ጥበብ ደንቦች መሰረት መስራት የሚገባዉን ሳይሰራ በመቅረቱ ወይም መስራት የማይገባዉን በመስራቱ ምከንያት የሕክምና አገልገሎት በሰጠዉ ሰዉ ላይ ጉዳት የሚያመጣ ተግባር የፈፀመ እንደሆነ እንዲሁም ሕክምና ሊያደርግለት የተቀበለዉን ሰዉ በቂ ባልሆነ ምክንያት ሳይረዳዉ የቀረ እንደሆነ በሰራዉ ተጠያቂ ነዉ።
በሙያ ስራ ሰለሚደረግ ጥፋትና የፍትሐ ብሔር ኃላፊነት፡ በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 2030 መሰረት አንደ ሰዉ ሕሊናን ወይም መልካም ጠባይን ተቃዋሚ በሆነ ዓይነት የማየገባዉን ስራ የሰራ ወይም የሚገባዉን ሳይሰራ የቀረ እንደሆነ ጥፋት አንደፈፀመ ይቆጠራል።
በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 2031 መሰረት በልዩ ሙዉ አንድ ስራ የሚፈጽም ሰዉ በስነ ጥበብ ወይም ራሱ በሚሰራዉ ኪነ ጥበብ ደንቦች መሰረት ያሉበትን ግዴታዎች አለመከተሉ ሲገለጽ ባለመጠንቀቅ ወይም በቸልተኝነት ጥፋተኛ ሆኖ በተገኘ ጊዜ አላፊ/ተጠያቂ/ ይሆናል።
እንዲሁም ለመጉዳት በማሰብ እያወቀ በሌላ ሰዉ ላየ ከፍ ያለ ጉዳት ያደረሰ ሰዉ በሰራዉ ስራ የጠያቂ ነዉ።
በሙያ ስራ ስለሚደረግ ጥፋትና የወንጀል አላፊነት፡ የወንጀል አላፊነት የሚኖረዉ በወንጀል ሕጉ እንዳይደረግ የተከለከለዉን በማድረግ ወይመ እንዲደረግ የታዘዘዉን ባለማድረግ ነዉ።
በወንጀል ሕግ ቁጥር69 መሰረት የሞያ ገዴታን ለመወጣት የተፈጸሙ ደረጊቶች ከሙያዉ ደንብና አሰራር ልማድ ዉጭ ካልሆኑና በከባደ የሙያ ጥፋት ካልተፈጸሙ በቀር አያሰቀጡም ይላል።ከድንጋጌዉ መረዳት እንደሚቻለዉ በሙያ ስራ የሚፈጸም ድርጊት ጥፋት ወይም ቸልተኝነት ከሌለበት በቀር አያስቀጣም።
በወንጀል ሕግ ቁጥር 575 መሰረት ማንም ሰዉ የሞያ ግዴታን በመተላለፍ አስቦ በሰዉ አካል ወይም ጤና ላይ ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ በወንጀል ተጠያቂ ይሆናል። ማንም ሰዉ በሕይወቱ፤ በሰዉነቱ፤ወይም በጤንነቱ ላይ ሊደርስ በሚችል ከባድ አደጋ ላይ የሚገኘዉን ሌላ ሰዉ ለመታደግ ወይም ለመርዳት የሙያ ግዴታ እያለበት ሊረዳዉ ሲችል አሰቦ ሳይረዳዉ የቀረ እንደሆነ በወንጀል ተጠያቂ ይሆናል።
ማንም ሰዉ የሌላ ሰዉን አካል ወይም ጤንነት የመጠበቅ የሙያ ግዴታ እያለበት በቸልተኝነት በሌላ ሰዉ አካል ወይም ጤንነት ላይ ጉዳተ ያደረሰ እንደሆነ በወንጀል ሕግ ቁጥር 559 መሰረት ተጠያቂ ይሆናል።
እንዲሁም የሌላ ሰዉን ሕይወት፤ጤንነት ወይም ደህንነት የመጠበቅ የሙያ ግዴታ እያለበት በቸልተኝነት ሰዉን የገደለ ሰዉ ቅጣቱ እንደሚከብድበት የወንጀል ሕግ ቁጥር 543(2) ይደነግጋል።
በሙያ ጥፋት ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸዉ ሰዎች ምን መብት አላቸዉ? ጉዳት የደረሰበት ሰዉ የባለሙያዉን አድራጎት ጥፋት መሆኑንና በዚህም የተነሳ ጉዳት የደረሰበት መሆኑን በማስረዳተ በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 2028 መሰረት ለደረሰበት ጉዳት ካሳ እንዲከፈል ስልጣን ባለዉ ፍርድ ቤት ክስ ማቅረብ ይቻላል። ነገር ግን ጉዳያቸዉን በራሳቸዉ ለመከታተል በአቅም ምከንያት የማይችሉ ዜጎች የአቅም ችገ ያለባቸዉ መሆኑን የሚያሳይ ማስረጃ በመያዝ በጠቅላይ ዐቃቢ ሕግ በዋናዉ መ/ቤትና በልደታ ወንጀል ዘርፍ እንዲሁም በአዲስ አበባ አሰሩም የጠቅላይ ዐቃቢ ሕግ ምድን ጽ/ቤቶች በመቅረብ ጉዳያቸዉን ዐቃቢ ህጎች እንዲከታተሉላቸዉ ማመልከት ይችላሉ። እንዲሁም የአቅም ሳይሆን የሕግ ዕዉቀት ችግር ያለባቸዉ ዜጎችም እንዲሁ ወደ ጽ/ቤቶች በመምጣት የምክር አገልግሎት በነጻ ማግኘት ይቻላል።
ሙያን አክበሮ መስራት የዜግነት ግዴታ ነው! ሃላፊነታችንን በያለንበት የሙያ መስክ በብቃት እንወጣ!
Federal Justice and Law Institute
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
የይርጋ ጊዜና የዕዳ ጥያቄ ቅድሚያ የመብት ጥያቄ ስለሚቀርብበት የጊዜ ገደብ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011
አንቀጽ 163
የይርጋ ጊዜ
• በቅጥር ላይ ከተመሰረተ ግንኙነት የመነጨ ማንኛውም ክስ የጊዜ ገደቡ በዚህ አዋጅ ወይም አግባብ ባለው ሌላ ሕግ በሌላ አኳኋን ካልተወሰነ በስተቀር የመብቱን ጥያቄ ለማቅረብ ከሚቻልበት ቀን ጀምሮ እስከ 1 ዓመት ድረስ ካልቀረበ በይርጋ ይታገዳል፡፡
• ሠራተኛው የሥራ ውሉ ከሕግ ውጭ ተቋርጦብኛል በማለት ወደ ሥራው ለመመለስ የሚያቀርበው ክስ ውሉ
በተቋረጠ በ3 ወር ጊዜ ውስጥ ካልቀረበ በይርጋ ይታገዳል፡፡
• ሠራተኛው የሚያቀርበው የደመወዝ፣ የትርፍ ሰዓትና የሌሎች ክፍያዎች ጥያቄ መጠየቅ ከሚገባው ጊዜ ጀምሮ እስከ 6 ወር ባለው ጊዜ ውስጥ ካልቀረበ በይርጋ ይታገዳል፡፡
• የሥራ ውል በመቋረጡ ምክንያት በሠራተኛውም ሆነ በአሠሪው የሚቀርብ ማንኛውም የክፍያ ጥያቄ የሥራ ውሉ በተቋረጠ በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ካልቀረበ በይርጋ ይታገዳል፡፡
• በዚህ አዋጅ ድንጋጌዎች ባልተሸፈነ የይርጋ ጉዳይ ላይ አግባብ ያለው ሕግ ተፈፃሚነት ይኖረዋል፡፡
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011
አንቀጽ 163
የይርጋ ጊዜ
• በቅጥር ላይ ከተመሰረተ ግንኙነት የመነጨ ማንኛውም ክስ የጊዜ ገደቡ በዚህ አዋጅ ወይም አግባብ ባለው ሌላ ሕግ በሌላ አኳኋን ካልተወሰነ በስተቀር የመብቱን ጥያቄ ለማቅረብ ከሚቻልበት ቀን ጀምሮ እስከ 1 ዓመት ድረስ ካልቀረበ በይርጋ ይታገዳል፡፡
• ሠራተኛው የሥራ ውሉ ከሕግ ውጭ ተቋርጦብኛል በማለት ወደ ሥራው ለመመለስ የሚያቀርበው ክስ ውሉ
በተቋረጠ በ3 ወር ጊዜ ውስጥ ካልቀረበ በይርጋ ይታገዳል፡፡
• ሠራተኛው የሚያቀርበው የደመወዝ፣ የትርፍ ሰዓትና የሌሎች ክፍያዎች ጥያቄ መጠየቅ ከሚገባው ጊዜ ጀምሮ እስከ 6 ወር ባለው ጊዜ ውስጥ ካልቀረበ በይርጋ ይታገዳል፡፡
• የሥራ ውል በመቋረጡ ምክንያት በሠራተኛውም ሆነ በአሠሪው የሚቀርብ ማንኛውም የክፍያ ጥያቄ የሥራ ውሉ በተቋረጠ በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ካልቀረበ በይርጋ ይታገዳል፡፡
• በዚህ አዋጅ ድንጋጌዎች ባልተሸፈነ የይርጋ ጉዳይ ላይ አግባብ ያለው ሕግ ተፈፃሚነት ይኖረዋል፡፡
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
Company Name:
ENTRUST trading and Consultant PLC
Job Type: Full Time: Required number = 2
part time for 3 months: Required number =2
Salary= negotiable
Work Place: Addis Ababa
Qualifications:
- LLB in Law: including exit exam failed students.
Total Required number = 4
Position: In house legal officer
0_ year relevant experience
👇👇👇👇part two 👇👇👇👇
_Economy and marketing
Required number = 2
0_ year relevant experience
Additional required skills:
👉 computer knowledge
👉 writing skill (Amharic and English) afan Oromo language is an asset.
👉 word and excel Microsoft skills
👉 sociable and active learner
👉 willing to work outside office
👉 social media knowledge is plus
👉
- Only shortlisted candidates will be communicated
- Hard copy or physical applications will not be accepted
👉CV
👉Cover letter
👉Relevant supporting documents
apply now via the following email in 5 working dates.
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
gudayasfetsami@gmail.com
https://t.me/EntrustE
- The Entrust has the right to cancel the post.
More Information
0909039999
- Experience Level Junior
- Total Years Experience 0-2
👉 This vacancy has posted on today 13/10/2022.👈
https://t.me/EntrustE
ENTRUST trading and Consultant PLC
Job Type: Full Time: Required number = 2
part time for 3 months: Required number =2
Salary= negotiable
Work Place: Addis Ababa
Qualifications:
- LLB in Law: including exit exam failed students.
Total Required number = 4
Position: In house legal officer
0_ year relevant experience
👇👇👇👇part two 👇👇👇👇
_Economy and marketing
Required number = 2
0_ year relevant experience
Additional required skills:
👉 computer knowledge
👉 writing skill (Amharic and English) afan Oromo language is an asset.
👉 word and excel Microsoft skills
👉 sociable and active learner
👉 willing to work outside office
👉 social media knowledge is plus
👉
- Only shortlisted candidates will be communicated
- Hard copy or physical applications will not be accepted
👉CV
👉Cover letter
👉Relevant supporting documents
apply now via the following email in 5 working dates.
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
gudayasfetsami@gmail.com
https://t.me/EntrustE
- The Entrust has the right to cancel the post.
More Information
0909039999
- Experience Level Junior
- Total Years Experience 0-2
👉 This vacancy has posted on today 13/10/2022.👈
https://t.me/EntrustE
ትክክለኛ ፍርድ ለመስጠት ወይም ውሳኔ ለመወሰን የሚረዱ ቀዳሚ ነገሮች በሊቁ ወርቁ ተዘጋጀ፣
1. የሕግ ዕውቀት
ሥራንና ባለሙያን ማገናኘት (Specialization) እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ ለሕክምና ሐኪም፣ ለሕንጻና ግንባታ መሐንዲስ እንደሚያስፈልግ ለዳኝነትም የሕግ ባለሙያ ያስፈልጋል፡፡ የሚሰየመው ችሎት ከሚካሔደው ሙግት ወይም ክርክር ጋር የተገናኘ ሰፊ ዕውቀትና ልምድ ያለውና ስለጉዳዩ ማብራሪያ እና አስተያየት መስጠት የሚችል መሆን አለበት፡፡
2. የዳኝነት ነፃነት
የዳኝነት ነፃነት ለትክክለኛ ፍትሕ አሰጣጥ የማዕዘን ራስ መሆኑ በተግባር የተረጋገጠ ጉዳይ ነው፡፡ መሠረታዊ ተልዕኮውም በፍርድ ሥራ ወይም በውሳኔ አሰጣጥ ላይ ጥላቻና ፍራቻ፣ ስሜትና ግፊት ቦታ እንዳይኖራቸው ማድረግ ነው፡፡
ይህም ዳኛው ሕጉን ዐይቶ ክርክሩን ስምቶ በሕጉ መሠረት ውሳኔ እንዲሰጥ ለማስቻል ነው፡፡ ዳኛው በቁንጽል አመለካከት ወይም በዕውቀት እጥረት የሰጠው ፍርድ/ውሳኔ በይግባኝ ተመዝኖ የሚለወጥ ወይም የሚሻሻል ቢሆን የዳኝነት ሥርዐት የሚያጠናክር እንጂ የሚያስነቅፍ አይሆንም፡፡ በሌላ በኩል ፍርዱ በግፊት ወይም በስሜት፤ በጥላቻ ወይም በፍራቻ የተሰጠ ሆኖ በይግባኝ ሳይታረም የጸና ሆኖ ቢቀር በሁለት በኩል ለነቀፋ የተጋለጠ ይሆናል፡፡ ይኸውም በአንድ በኩል ተጽዕኖው ከውስጥም ይምጣ ከውጪ በራሱ ሕገ ወጥ መሆኑ ሲሆን፤ በሌላ በኩል ደግም ፍርዱ ወይም ውሳኔው በሕግ መሠረት ያልተሰጠ በመሆኑ ከራሱ አልፎ ሥርዓቱን ጭምር ለሥጋትና ሐሜት በመዳረግ አመኔታውን ስለሚያቃውስበት ነው፡፡ ይህም የዳኝነት ነፃነት የጥበቃ አድማስ ዳኚውንም ተዳኚውንም እንደሚያካትት ያመለክታል፡፡ ሁለቱም ካልተጠበቁ ለአደጋ የሚጋለጠው ዳኛው የሚተረጉመው፣ ተከራካሪው የሚማጸነው ሕግ ነው፡፡ ሕግ ሥርዓት ስለሆነ ለሥጋት ከተጋለጠ አመኔታ ስለሚያጣ ነፀብራቁ ከዚያ አልፎ ኅብረተሰቡን የሚያውክ ይሆናል፡፡
ስለዚህ የዳኝነት ነጻነት በቁንጽል ከተወሰነ ጉዳይ ጋር ተያይዞ የሚታይ ሳይሆን ሰፋ ብሎ ከኅብረተሰቡ የፍትሕ አስተዳደር ጋር የሚያያዝ ጉዳይ ነው፡፡
3. ነገርን በግልጽ ማየት
ክስን/ክርክርን ወይም ሙግትን በግልጽ መስማት ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው መብት ነው፡፡ ምስጢራዊነትን ስለሚያስወግድ በተከሳሹ ላይ የተነገረውን ክስ ከሳሹ እንዲያስረዳ ይገፋፋል፤ ተከሳሽም መከላከያውን ያለፍርሃትና ሥጋት ለማቅረብ ያስችለዋል፡፡ ዳኞችም በፍርሃት፣ በሥጋት ወይም በስሜት እንዳይፈርዱ የሕዝብ አስተያየት በታዛቢነት ይመለከታቸዋል፡፡ የግልጽ ችሎት ጽንሰ ሃሳብ እየዳበረና የሕግ ጥበቃ እያገኘም የመጣው በዚህ ምክንያት ነው፡፡
4. ሥርዓት
ክርክር/ሙግት የጨረባ ድግስ እንዳይሆን ሥርዓት እንዲከተል ማድረግ የተገባ ነገር ነው፡፡ ክስ እንዴት እንደሚቀርብ፣ መልስ እንዴት እንደሚሰጥ፣ ማስረጃ እንዴት እንደሚቀርብና እንዴትም እንደሚመዘን፣ ማን አስቀድሞ እንደሚናገር፣ ማን መልስ እንደሚሰጥ፣ ጥያቄ እንዴት እንደሚቀርብ፣ ወዘተ…ሥርዓት ካልተበጀ እውነትን የያዘው ተጎድቶ አፍ ያለው ረትቶ ሊሔድ ይችላል፡፡
5. ጭብጥ
ጭብጥ የሙግት ልብ ወይም እምብርት ነው፡፡ ጭብጥ ተለይቶ መውጣቱ ለግራ ቀኙና ለዳኛም እጅግ ጠቃሚና አስፈላጊ ነው፡፡ ሙግት ለማገዶ እንደሚሰበሰብ ፍልጥ ቢታሰብ ጭብጡ እንደማሠሪው ልጥ ሊመሰል ይችላል፡፡ ‹‹ለሺህ ፍልጥ ማሰሪው ልጥ›› ነውና ጭብጥ የሙግት መሰብሰቢያና ማሰሪያ ነው፡፡
ማሰሪያ የሌለው ፍልጥ እንደሚበታተንና ለአያያዝ እንደሚያስቸግር ሁሉ በጭብጥ ያልተያዘ ሙግትም ወደ ጭፍጫፊ ነጥቦች እየተሰነጣጠረና እየተሰበጣጠረ ስለሚሔድ መያዣ መጨበጫ የሌለው ይሆናል፡፡
በመሆኑም ጭብጥ የሙግት/ክርክር ዳር ድንበርና ይዘት ጭምር ወሳኝ ነው፡፡ ግራ ቀኙ የተለያዩበትን ሥረ ነገርና ሕጋዊ መሠረቱን አጥርቶ ያመለክታል፡፡ ተከራካሪዎቹ ጭብጣቸውን እንዲያስረዱ፣ በጭብጣቸው እንዲረጉ፣ ፈራጅም በጭብጡ ተወስኖ ማስረጃውን መዝኖ ክርክሩን አዳምጦ ሕጉን አገላብጦ ሙግትን እንዲቆርጥ ውሳኔውን እንዲሰጥ ያስችለዋል፡፡
6. ማስረጃ
ፍርድን በማስረጃ ማንተራስ እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ አስተያየት የሚቀረጸው በማስረጃ ላይ በመመሥረት ነው፡፡ ማስረጃ በሁለት ወገን የሚቀርብና አልፎ አልፎም ዕውቅ ነገር ሲያጋጥም ከፈራጅ ግንዛቤ (Judicial Notice) የሚፈልቅ ነው፡፡
#ሊቁ #ወርቁ
https://t.me/lawsocieties
1. የሕግ ዕውቀት
ሥራንና ባለሙያን ማገናኘት (Specialization) እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ ለሕክምና ሐኪም፣ ለሕንጻና ግንባታ መሐንዲስ እንደሚያስፈልግ ለዳኝነትም የሕግ ባለሙያ ያስፈልጋል፡፡ የሚሰየመው ችሎት ከሚካሔደው ሙግት ወይም ክርክር ጋር የተገናኘ ሰፊ ዕውቀትና ልምድ ያለውና ስለጉዳዩ ማብራሪያ እና አስተያየት መስጠት የሚችል መሆን አለበት፡፡
2. የዳኝነት ነፃነት
የዳኝነት ነፃነት ለትክክለኛ ፍትሕ አሰጣጥ የማዕዘን ራስ መሆኑ በተግባር የተረጋገጠ ጉዳይ ነው፡፡ መሠረታዊ ተልዕኮውም በፍርድ ሥራ ወይም በውሳኔ አሰጣጥ ላይ ጥላቻና ፍራቻ፣ ስሜትና ግፊት ቦታ እንዳይኖራቸው ማድረግ ነው፡፡
ይህም ዳኛው ሕጉን ዐይቶ ክርክሩን ስምቶ በሕጉ መሠረት ውሳኔ እንዲሰጥ ለማስቻል ነው፡፡ ዳኛው በቁንጽል አመለካከት ወይም በዕውቀት እጥረት የሰጠው ፍርድ/ውሳኔ በይግባኝ ተመዝኖ የሚለወጥ ወይም የሚሻሻል ቢሆን የዳኝነት ሥርዐት የሚያጠናክር እንጂ የሚያስነቅፍ አይሆንም፡፡ በሌላ በኩል ፍርዱ በግፊት ወይም በስሜት፤ በጥላቻ ወይም በፍራቻ የተሰጠ ሆኖ በይግባኝ ሳይታረም የጸና ሆኖ ቢቀር በሁለት በኩል ለነቀፋ የተጋለጠ ይሆናል፡፡ ይኸውም በአንድ በኩል ተጽዕኖው ከውስጥም ይምጣ ከውጪ በራሱ ሕገ ወጥ መሆኑ ሲሆን፤ በሌላ በኩል ደግም ፍርዱ ወይም ውሳኔው በሕግ መሠረት ያልተሰጠ በመሆኑ ከራሱ አልፎ ሥርዓቱን ጭምር ለሥጋትና ሐሜት በመዳረግ አመኔታውን ስለሚያቃውስበት ነው፡፡ ይህም የዳኝነት ነፃነት የጥበቃ አድማስ ዳኚውንም ተዳኚውንም እንደሚያካትት ያመለክታል፡፡ ሁለቱም ካልተጠበቁ ለአደጋ የሚጋለጠው ዳኛው የሚተረጉመው፣ ተከራካሪው የሚማጸነው ሕግ ነው፡፡ ሕግ ሥርዓት ስለሆነ ለሥጋት ከተጋለጠ አመኔታ ስለሚያጣ ነፀብራቁ ከዚያ አልፎ ኅብረተሰቡን የሚያውክ ይሆናል፡፡
ስለዚህ የዳኝነት ነጻነት በቁንጽል ከተወሰነ ጉዳይ ጋር ተያይዞ የሚታይ ሳይሆን ሰፋ ብሎ ከኅብረተሰቡ የፍትሕ አስተዳደር ጋር የሚያያዝ ጉዳይ ነው፡፡
3. ነገርን በግልጽ ማየት
ክስን/ክርክርን ወይም ሙግትን በግልጽ መስማት ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው መብት ነው፡፡ ምስጢራዊነትን ስለሚያስወግድ በተከሳሹ ላይ የተነገረውን ክስ ከሳሹ እንዲያስረዳ ይገፋፋል፤ ተከሳሽም መከላከያውን ያለፍርሃትና ሥጋት ለማቅረብ ያስችለዋል፡፡ ዳኞችም በፍርሃት፣ በሥጋት ወይም በስሜት እንዳይፈርዱ የሕዝብ አስተያየት በታዛቢነት ይመለከታቸዋል፡፡ የግልጽ ችሎት ጽንሰ ሃሳብ እየዳበረና የሕግ ጥበቃ እያገኘም የመጣው በዚህ ምክንያት ነው፡፡
4. ሥርዓት
ክርክር/ሙግት የጨረባ ድግስ እንዳይሆን ሥርዓት እንዲከተል ማድረግ የተገባ ነገር ነው፡፡ ክስ እንዴት እንደሚቀርብ፣ መልስ እንዴት እንደሚሰጥ፣ ማስረጃ እንዴት እንደሚቀርብና እንዴትም እንደሚመዘን፣ ማን አስቀድሞ እንደሚናገር፣ ማን መልስ እንደሚሰጥ፣ ጥያቄ እንዴት እንደሚቀርብ፣ ወዘተ…ሥርዓት ካልተበጀ እውነትን የያዘው ተጎድቶ አፍ ያለው ረትቶ ሊሔድ ይችላል፡፡
5. ጭብጥ
ጭብጥ የሙግት ልብ ወይም እምብርት ነው፡፡ ጭብጥ ተለይቶ መውጣቱ ለግራ ቀኙና ለዳኛም እጅግ ጠቃሚና አስፈላጊ ነው፡፡ ሙግት ለማገዶ እንደሚሰበሰብ ፍልጥ ቢታሰብ ጭብጡ እንደማሠሪው ልጥ ሊመሰል ይችላል፡፡ ‹‹ለሺህ ፍልጥ ማሰሪው ልጥ›› ነውና ጭብጥ የሙግት መሰብሰቢያና ማሰሪያ ነው፡፡
ማሰሪያ የሌለው ፍልጥ እንደሚበታተንና ለአያያዝ እንደሚያስቸግር ሁሉ በጭብጥ ያልተያዘ ሙግትም ወደ ጭፍጫፊ ነጥቦች እየተሰነጣጠረና እየተሰበጣጠረ ስለሚሔድ መያዣ መጨበጫ የሌለው ይሆናል፡፡
በመሆኑም ጭብጥ የሙግት/ክርክር ዳር ድንበርና ይዘት ጭምር ወሳኝ ነው፡፡ ግራ ቀኙ የተለያዩበትን ሥረ ነገርና ሕጋዊ መሠረቱን አጥርቶ ያመለክታል፡፡ ተከራካሪዎቹ ጭብጣቸውን እንዲያስረዱ፣ በጭብጣቸው እንዲረጉ፣ ፈራጅም በጭብጡ ተወስኖ ማስረጃውን መዝኖ ክርክሩን አዳምጦ ሕጉን አገላብጦ ሙግትን እንዲቆርጥ ውሳኔውን እንዲሰጥ ያስችለዋል፡፡
6. ማስረጃ
ፍርድን በማስረጃ ማንተራስ እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ አስተያየት የሚቀረጸው በማስረጃ ላይ በመመሥረት ነው፡፡ ማስረጃ በሁለት ወገን የሚቀርብና አልፎ አልፎም ዕውቅ ነገር ሲያጋጥም ከፈራጅ ግንዛቤ (Judicial Notice) የሚፈልቅ ነው፡፡
#ሊቁ #ወርቁ
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/