የውስጥ ማስታወሻ Internal Memo
ለሁሉም ዳይክቶሬት/ የስራ ክፍል ምድብ ችሎት
ከ፡- ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
ጉዳዩ፦ ወጥ የሆነ የውስጥ መፃፃፊያ ሚሞን እንድትጠቀሙ ስለማሳወቅ
የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ከሚያከናውናቸው ተግባራት አንዱ መለያዎችን ማዘጋጀት ወይም ምክረ ሃሳብ ማቅረብ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ይህን በሚመለከት ዳይሬክቶሬታችን በተደጋጋሚ ወጥ የሆነ የውስጥ መፃፃፊያ ሚሞ እንዲኖር ሲሰራ ቆይቷል፡፡
ስለሆነም የውስጥ መፃፃፊያ ሚሞው በሁሉም የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ወጥ በሆነ መልኩ ስራ ላይ እንዲውል ተብሎ ከጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕራዘዳንት ጽ/ቤት አቅጣጫ የተሰጠ በመሆኑ ሁሉም ጽ/ቤቶች፣ ዳይሬክቶሬቶች፣ ስራ ክፍሎች እና ምድብ ችሎቶች ይህ ደብዳቤ ከደረሳችሁ ቀን ጀምሮ ይህን የመፃፃፊያ ሚሞ እንድትጠቀሙ እያሳሰብን ቅጹን ከዚህ ደብዳቤ ጋር አባሪ አድርገን ያያዝን ሲሆን በተጨማሪም በፍርድ ቤቱ ቴሌግራም እንዲሁም በእቅድ ዝግጅት፣ ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት የቴሌግራም ገፅ ላይ የምንለጥፍ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
#ሼር ይደረግ
https://t.me/lawsocieties
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
ለሁሉም ዳይክቶሬት/ የስራ ክፍል ምድብ ችሎት
ከ፡- ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
ጉዳዩ፦ ወጥ የሆነ የውስጥ መፃፃፊያ ሚሞን እንድትጠቀሙ ስለማሳወቅ
የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ከሚያከናውናቸው ተግባራት አንዱ መለያዎችን ማዘጋጀት ወይም ምክረ ሃሳብ ማቅረብ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ይህን በሚመለከት ዳይሬክቶሬታችን በተደጋጋሚ ወጥ የሆነ የውስጥ መፃፃፊያ ሚሞ እንዲኖር ሲሰራ ቆይቷል፡፡
ስለሆነም የውስጥ መፃፃፊያ ሚሞው በሁሉም የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ወጥ በሆነ መልኩ ስራ ላይ እንዲውል ተብሎ ከጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕራዘዳንት ጽ/ቤት አቅጣጫ የተሰጠ በመሆኑ ሁሉም ጽ/ቤቶች፣ ዳይሬክቶሬቶች፣ ስራ ክፍሎች እና ምድብ ችሎቶች ይህ ደብዳቤ ከደረሳችሁ ቀን ጀምሮ ይህን የመፃፃፊያ ሚሞ እንድትጠቀሙ እያሳሰብን ቅጹን ከዚህ ደብዳቤ ጋር አባሪ አድርገን ያያዝን ሲሆን በተጨማሪም በፍርድ ቤቱ ቴሌግራም እንዲሁም በእቅድ ዝግጅት፣ ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት የቴሌግራም ገፅ ላይ የምንለጥፍ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
#ሼር ይደረግ
https://t.me/lawsocieties
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
TOR_NORAD_MODER_SAVERY_AND_HUMAN_RIGHTS_TRAINING_AUGUST_2022_docx.pdf
182.1 KB
The Ethiopian Human Rights Council (EHRCO) is looking for a consultant(s) to facilitate a two-day capacity-building training for business leaders about modern slavery and business, as well as how businesses can develop self-assessment frameworks and codes of conduct to comply with laws, policies, and standards of conduct on good and malpractices in order to combat modern slavery.
To this end, EHRCO invites interested and qualified consultants to train different business leaders in three regions namely Bahirdar, Hawassa and Addis Ababa in a two-day capacity-building training.
Qualified consultant(s) can apply to facilitate the training and can find the full TOR attached above.
To this end, EHRCO invites interested and qualified consultants to train different business leaders in three regions namely Bahirdar, Hawassa and Addis Ababa in a two-day capacity-building training.
Qualified consultant(s) can apply to facilitate the training and can find the full TOR attached above.
የችሎት ውሎ !!
የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈጸመው ግለሰብ በእስር ተቀጣ ተከሳሽ ከድር መሃመድ በቤተሰቦቹ ቤት በቤት ሰራተኝነት ታገለግል የነበረችው ዙለይካ ጀማል ላይ በሃምሌ ወር 2ዐ13 ዓ.ም በፈጸመው የአስገድዶ መድፈር እና ከድርጊቱ በኋላ የተፈጸመውን ጽንስ ለማስወረድ ባደረገው ሙከራ በፈጸመው የጽንስ ማስወረድ ሙከራ ወንጀል በሁለተኛ ክስነት የምስራቅ ስልጢ ወረዳ ዐቃቤ ህግ ክስ አቅርቦበታል።
ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የወረዳው ፍርድ ቤት ተከሳሽን ነጻ ነው በማለት በሁለተኛው ክስ በ1ዓመት ከ3ወር ቀላል እስራት ወስኖበታል።
በውሳኔው ቅሬታ የተሰማው ዐ/ህግ ለስልጤ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት
ይግባኝ አቅርቧል።ከፍተኛ ፍርድ ቤቱም የስር ፍርድ ቤትን ውሳኔ
በማሻሻል በ1ዓመት ከ6ወር እስራት ወስኗል።
በዚህ ውሳኔ ቅር የተሰኘው የዞኑ ዐቃቤ ህግ ጉዳዩን በይግባኝ ለደቡብ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አቅርቦ ክርክር በማድረግ ከፍተኛ ፍርድ ቤቱ በቅጣት አጣጣል ላይ የፈጸመውን ስህተት በማረም ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ በቀን 19/12/2014 በዋለው ችሎት ተከሳስሽን በ 8ዓመት ከ5ወር ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።
መረጃው የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ – Siltie Zone Justice Department
https://t.me/lawsocieties
የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈጸመው ግለሰብ በእስር ተቀጣ ተከሳሽ ከድር መሃመድ በቤተሰቦቹ ቤት በቤት ሰራተኝነት ታገለግል የነበረችው ዙለይካ ጀማል ላይ በሃምሌ ወር 2ዐ13 ዓ.ም በፈጸመው የአስገድዶ መድፈር እና ከድርጊቱ በኋላ የተፈጸመውን ጽንስ ለማስወረድ ባደረገው ሙከራ በፈጸመው የጽንስ ማስወረድ ሙከራ ወንጀል በሁለተኛ ክስነት የምስራቅ ስልጢ ወረዳ ዐቃቤ ህግ ክስ አቅርቦበታል።
ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የወረዳው ፍርድ ቤት ተከሳሽን ነጻ ነው በማለት በሁለተኛው ክስ በ1ዓመት ከ3ወር ቀላል እስራት ወስኖበታል።
በውሳኔው ቅሬታ የተሰማው ዐ/ህግ ለስልጤ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት
ይግባኝ አቅርቧል።ከፍተኛ ፍርድ ቤቱም የስር ፍርድ ቤትን ውሳኔ
በማሻሻል በ1ዓመት ከ6ወር እስራት ወስኗል።
በዚህ ውሳኔ ቅር የተሰኘው የዞኑ ዐቃቤ ህግ ጉዳዩን በይግባኝ ለደቡብ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አቅርቦ ክርክር በማድረግ ከፍተኛ ፍርድ ቤቱ በቅጣት አጣጣል ላይ የፈጸመውን ስህተት በማረም ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ በቀን 19/12/2014 በዋለው ችሎት ተከሳስሽን በ 8ዓመት ከ5ወር ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።
መረጃው የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ – Siltie Zone Justice Department
https://t.me/lawsocieties
Vision Fund Micro Finance
በሚከተሉት የስራ መደቦች ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
Position:-
1: Attorney I
2: Deputy Branch Manager
📚የትምህርት ዓይነት እና ደረጃ
University degree/ diploma in economics/ accounting/ business administration/ banking/management/ marketing/ cooperative/ agricultural economics/ Rural development or related social sciences and business fields;
🇪🇹 የስራቦታ:-Gibe & Gibe, SNNPR.
🧭የምዝገባ ጊዜ ፡ እስከ መስከረም
1/2014 ዓ.ም
🔔ስለ ስራው ሙሉ መረጃ ለማየት እና ለማመልከት ቀጣዩን ሊንክ ይጠቀሙ
https://jobs.amazonethiopia.com/job/vision-fund-micro-finance/
በሚከተሉት የስራ መደቦች ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
Position:-
1: Attorney I
2: Deputy Branch Manager
📚የትምህርት ዓይነት እና ደረጃ
University degree/ diploma in economics/ accounting/ business administration/ banking/management/ marketing/ cooperative/ agricultural economics/ Rural development or related social sciences and business fields;
🇪🇹 የስራቦታ:-Gibe & Gibe, SNNPR.
🧭የምዝገባ ጊዜ ፡ እስከ መስከረም
1/2014 ዓ.ም
🔔ስለ ስራው ሙሉ መረጃ ለማየት እና ለማመልከት ቀጣዩን ሊንክ ይጠቀሙ
https://jobs.amazonethiopia.com/job/vision-fund-micro-finance/
#VisionFund MFI#
▪️1 - Intermediate Teler
▪️2 - Attorney I
▪️3 - Deputy Branch Manager
▪️Find More Details here
💧💧💧💧💧
https://bit.ly/3Q8xOIc
▪️Deadline - September 06/22
▪️1 - Intermediate Teler
▪️2 - Attorney I
▪️3 - Deputy Branch Manager
▪️Find More Details here
💧💧💧💧💧
https://bit.ly/3Q8xOIc
▪️Deadline - September 06/22
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
Notice for Graduating Class of 2014 E.C
Pleasantly, this is to bethink you that your graduation date is on Tuesday 01/13/2014 E.C.
We're so proud of you, and honored to celebrate graduation day with you!
MTU School of law
Pleasantly, this is to bethink you that your graduation date is on Tuesday 01/13/2014 E.C.
We're so proud of you, and honored to celebrate graduation day with you!
MTU School of law
Fisical policy
Fisicla refers to the use of government spending and tax policies to influence economic conditions Macroeconomic especially conditions. These include aggregate demand for goods and services, employment, inflation, and economic growth.
During a recession, the government may lower tax rates or increase spending to encourage demand and spur economic activity. Conversely, to combat inflation, it may raise rates or cut spending to cool down the economy.
Fiscal policy is often contrasted with monitory policy which is enacted by central bankers and not elected government officials.
Fisicla refers to the use of government spending and tax policies to influence economic conditions Macroeconomic especially conditions. These include aggregate demand for goods and services, employment, inflation, and economic growth.
During a recession, the government may lower tax rates or increase spending to encourage demand and spur economic activity. Conversely, to combat inflation, it may raise rates or cut spending to cool down the economy.
Fiscal policy is often contrasted with monitory policy which is enacted by central bankers and not elected government officials.
EII.
የውጭ አገር ሰዎች /ኩባንያ #የንግድ_ምልክት የተቃዉሞ አቤቱታ ሰ/መ/ቁ 193292
የሀገራችን የንግድ ምዝገባና ጥበቃ አዋጅ ሆነ ሌሎች የሀገሪቱ አዕምሯዊ ንብረት ህጎች ከአለማቀፍ ስምምነቶች ጋር የተጣጣሙ ሆነው የተቀረፁ በመሆኑ፤ ሀገሪቱ ለውጪ ሀገር ሰዎች ዜጎቿ ያላቸውን መብትና ግዴታ በተመሳሳይ በማወቅ የንግድ ምልክት ምዝገባና ተያያዥ ተግባራትን ከረዥም ጊዜ ጀምሮ ስታካሂድ የኖረች መሆኑም የተረጋገጠ በመሆኑ የውጭ አገር ሰው /ኩባንያ/ ኢትዮጵያ ውስጥ የንግድ ምልክት በተመለከተ መቃወሚያው ማቅረብ ይችል።
የእንካ ለእንካ መርህ (principle of reciprocity) በሀገራት መካከል ግልፅ የሆነ ስምምነት ባይኖርም እንኳ አንድ ሀገር ለሀገሩ ዜጎች የሚያከብረውን መብት እና የሚጥለውን ግዴታ ለሌሎች ሀገሮች ዜጎችም በተመሳሳይ እንደሚያደርግ የሚያስገነዝብ ነው። በንግድ ምልክት ምዝገባና ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 501/98 አንቀጽ 3 ሥር የተመለከተው የእንካ ለእንካ መርህ ሊተረጎም የሚገባውም ሌላው ሀገር ለዜጎቹ የሚያደርገውን የንግድ ምልክት ምዝገባና ጥበቃ ለኢትዮጵያዊያን የማያደርግ ከሆነ የዚያ ሀገር ዜጎችም ሆነ ድርጅቶች በኢትዮጵያ የንግድ ምልክታቸው እንዲመዘገብና ጥበቃ እንዲደረግላቸው ለመጠየቅ እንዲሁም የተያያዥ መብቶች ተጠቃሚ ሊሆኑ አይችሉም ተብሎ ነው።
https://chilot.me/2022/09/03/objection-to-trademark-registration-by-foreign-companies-c-f-n-193292/
የእንካ ለእንካ መርህ (principle of reciprocity) በሀገራት መካከል ግልፅ የሆነ ስምምነት ባይኖርም እንኳ የውጭ አገር ሰው /ኩባንያ/ ኢትዮጵያ ውስጥ የንግድ ምልክት በተመለከተ መቃወሚያው ማቅረብ ይችላል።
ከችሎቱ ሐተታ በከፊል
የእንካ ለእንካ መርህ (principle of reciprocity) በዘርፉ የሚታወቅ ሲሆን መርሁ የሚይዘው ትርጉም “አንተ ባደረክግልኝ መጠን እኔም አደርግልሃለሁ” እንዲሁም “እኔ ባደረኩልህ መጠን አንተም ታደርጋለህ” የሚል ይዘት ያለው ነው፡፡ ይህን መርህ ተጠቅመው ሃገራት ጥቅማቸውን ያስከብራሉ የሌሎችንም ጥቅም በዚያው መጠን ያከብራሉ፡፡ ይህ የእንካ ለእንካ መርህ የ”ናሽናል ትሪትመንት” (National Treatment) አካል ሲሆን የ”ናሽናል ትሪትመንት” መሰረተ ሃሳብ የአለማቀፍ ልማዳዊ ህግን መሰረት የሚያደርግ ሆኖ በሃገራቱ መካከል ግልፅ የሆነ ስምምነት ባይኖር እንኳ አንድ ሀገር ለሀገሩ ዜጎች የሚያከብረውን መብት እና የሚጥለውን ግዴታ ለሌሎች ሀገሮች ዜጎችም በተመሳሳይ እንደሚያደርግ የሚያስገነዝብ ነው።
ከአእምሯዊ ንብረት መብት እና በልዩ ሁኔታም ከንግድ ምልክት ጋር በተያያዘም የ WTO እና TRIPS ስምምነት፤ እንዲሁም የበርን ኮንቬንሽን (Berne Convention)፣ የፓሪስ ኮንቬንሽን (Paris Convention)፣ እና የማድሪድ ፕሮቶኮል (Madrid Protocol) የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ እነዚህና መሰል የአለም አቀፍ ስምምነቶች የሚመሩበት መሰረታዊ መርህ ብሄራዊ ስምምነት ሲሆን ለአንድ ሀገር ዜጎች የሚጠበቀው መብት ወይም የሚጣለው ግዴታ በሌሎች ሀገሮች ዜጎችም ያለ አድሎ በእኩልነት ተፈጻሚነት እንዲኖረው የሚገባውን ግዴታ የሚመለከት ነው፡፡ ይህም ለአብነት በ TRIPS አለምአቀፍ ስምምነት አንቀጽ 3 ስር ተመልክቶ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ሀገራት ለውጭ ሀገር ዜጎች ጨምሮ የአእምሯዊ ንብረት መብት ጥበቃ የሚያደርጉ ሲሆን የሚሰጠው ጥበቃ አይነትና ተፈጻሚነት ግን የአለም አቀፍ ስምምነቶች አባል በሆኑት እና የሁለትዬሽ እና አህጉራዊ ስምምነቶችን ባጸደቁ ሀገራት የተሻለ ሆኖ ይታያል፡፡ አንዳንድ ሀገራት ደግሞ አብዛኞችን አለም አቀፍ ስምምነቶች ሳያጸድቁ ነገር ግን የአእምሯዊ ንብረት መብቶችን የተመለከቱ አለማቀፋዊ መርሆችና አሰራሮችን በሀገራቸው ህጎች ደንግገው ይገኛሉ፡፡ በዚህ መልኩ ለመብቱ ጥበቃ ከሚያደርጉ ሀገራት መካከል ኢትዬጵያ አንዷ ስትሆን አዋጅ ቁጥር 501/98 እና ሌሎቹ የአእምሯዊ ንብረት አዋጅና ደንቦች ይህን የሚያሳዩ ናቸው፡፡
By #Abrham_Yohanes
የሀገራችን የንግድ ምዝገባና ጥበቃ አዋጅ ሆነ ሌሎች የሀገሪቱ አዕምሯዊ ንብረት ህጎች ከአለማቀፍ ስምምነቶች ጋር የተጣጣሙ ሆነው የተቀረፁ በመሆኑ፤ ሀገሪቱ ለውጪ ሀገር ሰዎች ዜጎቿ ያላቸውን መብትና ግዴታ በተመሳሳይ በማወቅ የንግድ ምልክት ምዝገባና ተያያዥ ተግባራትን ከረዥም ጊዜ ጀምሮ ስታካሂድ የኖረች መሆኑም የተረጋገጠ በመሆኑ የውጭ አገር ሰው /ኩባንያ/ ኢትዮጵያ ውስጥ የንግድ ምልክት በተመለከተ መቃወሚያው ማቅረብ ይችል።
የእንካ ለእንካ መርህ (principle of reciprocity) በሀገራት መካከል ግልፅ የሆነ ስምምነት ባይኖርም እንኳ አንድ ሀገር ለሀገሩ ዜጎች የሚያከብረውን መብት እና የሚጥለውን ግዴታ ለሌሎች ሀገሮች ዜጎችም በተመሳሳይ እንደሚያደርግ የሚያስገነዝብ ነው። በንግድ ምልክት ምዝገባና ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 501/98 አንቀጽ 3 ሥር የተመለከተው የእንካ ለእንካ መርህ ሊተረጎም የሚገባውም ሌላው ሀገር ለዜጎቹ የሚያደርገውን የንግድ ምልክት ምዝገባና ጥበቃ ለኢትዮጵያዊያን የማያደርግ ከሆነ የዚያ ሀገር ዜጎችም ሆነ ድርጅቶች በኢትዮጵያ የንግድ ምልክታቸው እንዲመዘገብና ጥበቃ እንዲደረግላቸው ለመጠየቅ እንዲሁም የተያያዥ መብቶች ተጠቃሚ ሊሆኑ አይችሉም ተብሎ ነው።
https://chilot.me/2022/09/03/objection-to-trademark-registration-by-foreign-companies-c-f-n-193292/
የእንካ ለእንካ መርህ (principle of reciprocity) በሀገራት መካከል ግልፅ የሆነ ስምምነት ባይኖርም እንኳ የውጭ አገር ሰው /ኩባንያ/ ኢትዮጵያ ውስጥ የንግድ ምልክት በተመለከተ መቃወሚያው ማቅረብ ይችላል።
ከችሎቱ ሐተታ በከፊል
የእንካ ለእንካ መርህ (principle of reciprocity) በዘርፉ የሚታወቅ ሲሆን መርሁ የሚይዘው ትርጉም “አንተ ባደረክግልኝ መጠን እኔም አደርግልሃለሁ” እንዲሁም “እኔ ባደረኩልህ መጠን አንተም ታደርጋለህ” የሚል ይዘት ያለው ነው፡፡ ይህን መርህ ተጠቅመው ሃገራት ጥቅማቸውን ያስከብራሉ የሌሎችንም ጥቅም በዚያው መጠን ያከብራሉ፡፡ ይህ የእንካ ለእንካ መርህ የ”ናሽናል ትሪትመንት” (National Treatment) አካል ሲሆን የ”ናሽናል ትሪትመንት” መሰረተ ሃሳብ የአለማቀፍ ልማዳዊ ህግን መሰረት የሚያደርግ ሆኖ በሃገራቱ መካከል ግልፅ የሆነ ስምምነት ባይኖር እንኳ አንድ ሀገር ለሀገሩ ዜጎች የሚያከብረውን መብት እና የሚጥለውን ግዴታ ለሌሎች ሀገሮች ዜጎችም በተመሳሳይ እንደሚያደርግ የሚያስገነዝብ ነው።
ከአእምሯዊ ንብረት መብት እና በልዩ ሁኔታም ከንግድ ምልክት ጋር በተያያዘም የ WTO እና TRIPS ስምምነት፤ እንዲሁም የበርን ኮንቬንሽን (Berne Convention)፣ የፓሪስ ኮንቬንሽን (Paris Convention)፣ እና የማድሪድ ፕሮቶኮል (Madrid Protocol) የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ እነዚህና መሰል የአለም አቀፍ ስምምነቶች የሚመሩበት መሰረታዊ መርህ ብሄራዊ ስምምነት ሲሆን ለአንድ ሀገር ዜጎች የሚጠበቀው መብት ወይም የሚጣለው ግዴታ በሌሎች ሀገሮች ዜጎችም ያለ አድሎ በእኩልነት ተፈጻሚነት እንዲኖረው የሚገባውን ግዴታ የሚመለከት ነው፡፡ ይህም ለአብነት በ TRIPS አለምአቀፍ ስምምነት አንቀጽ 3 ስር ተመልክቶ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ሀገራት ለውጭ ሀገር ዜጎች ጨምሮ የአእምሯዊ ንብረት መብት ጥበቃ የሚያደርጉ ሲሆን የሚሰጠው ጥበቃ አይነትና ተፈጻሚነት ግን የአለም አቀፍ ስምምነቶች አባል በሆኑት እና የሁለትዬሽ እና አህጉራዊ ስምምነቶችን ባጸደቁ ሀገራት የተሻለ ሆኖ ይታያል፡፡ አንዳንድ ሀገራት ደግሞ አብዛኞችን አለም አቀፍ ስምምነቶች ሳያጸድቁ ነገር ግን የአእምሯዊ ንብረት መብቶችን የተመለከቱ አለማቀፋዊ መርሆችና አሰራሮችን በሀገራቸው ህጎች ደንግገው ይገኛሉ፡፡ በዚህ መልኩ ለመብቱ ጥበቃ ከሚያደርጉ ሀገራት መካከል ኢትዬጵያ አንዷ ስትሆን አዋጅ ቁጥር 501/98 እና ሌሎቹ የአእምሯዊ ንብረት አዋጅና ደንቦች ይህን የሚያሳዩ ናቸው፡፡
By #Abrham_Yohanes
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
የሚተላለፉ #የገንዘብ #ሰነዶች በኢትዮጵያ #የንግድ #ህግ
መግቢያ
በሀገራችን የንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ ንግድን ከማፋጠን እና የፋይናንስ ግብይትን ከማሳለጥ አንጻር የገንዘብነት ዋጋ ያላቻው የሚተላለፉ ሰነዶች የሚጫወቱት ሚና እጅግ ከፍተኛ እንደሆነ ይታመናል፡፡ በዚህ አጭር ጽሁፍ እነዚህኑ የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች ምንነት እና የሀገራችን የሚተዳደሩበትን የህግ ማእቀፍ በአጭሩ እናያለን፡፡
የህግ ማእቀፍ
እስከቅርብ ጊዜ በስራ ላይ የነበረው የ1952ቱ የንግድ ህግ ስድስት መጽሐፍት የነበሩት ሲሆን የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶችና የባንክ ስራዎች በተመለከተ የደነገገው የህጉ ክፍል በመጽሀፍ አራት ስር የተደራጁ ናቸው፡፡ አዲሱ የንግድ ህግ አዋጅ ቁጥር 1243/2013 በይዘቱ በሶስት መጽሐፍት የተከፋፈለ ሲሆን የበፊቱ ንግድ ህግ መጽሐፍት 3 እና 4 የአዲሱ የንግድ ሕግ አካል ሳይሆኑ ራሳቸዉን ችለዉ የፋይናንስ አገልግሎት መድብል ወይም ኮድ ሆነው እንዲወጡ በመተው መጽሐፍ አንድ፣ሁለት እና አምስት የንግድ ሕግ ተብሎ እንዲሻሻል ተደርጎ በአዲሱ የንግድ ሕግ ተካተው ወጥተዋል፡፡ በዚህም አዲሱ የፋይናንስ አገልግሎት ህግ እስኪወጣ ድረስ የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች ወይም የንግድ ወረቀቶች በነባሩ የንግድ ህግ ምእራፍ አራት ድንጋጌዎች መሰረት የሚታዩ መሆናቸው ይቀጥላል፡፡
የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች ምንነት
በ1952ቱ የንግድ ህግ አንቀፅ 715 /1/ መሰረት የሚተላለፍ የገንዘብ ሰነድ ማለት መብቱ ከሰነዱ ተለይቶ ሊሰራበት ወይም ሊተላለፍ የማይችል የአገልግሎት መብት ያለበት ሰነድ ሁሉ ነው በማለት ይደነግጋል፡፡ ይህ ትርጉም የሚተላለፉ ሰነዶች የመብትና የግዴታ ማረጋገጫ ሰነዶች ናቸው ከማለት በተጨማሪ በሰነዶቹ ውስጥ የተመለከቱት መብቶች ከሰነዶች ተለይተው ሊተላለፉ /ሊሰራባቸው/ እንደማይችሉ የሚያመለክት ነው፡፡ ይህም አባባል ጠቅለል ባለ መልኩ ሲገለፅ የሚተላለፍ ሰነድ ማለት በሠነድ ላይ የተመለከተው መብት ከሰነድ ላይ ለይቶ ሊሰራበት እና ሊተላለፍ የማይችል የመብትና የዕዳ ማረጋገጫ ሰነድ መሆኑን የሚያስረዳ ነው፡፡
የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነድ አይነቶች
በ1952ቱ የንግድ ህግ አንቀፅ 732 መሰረት የንግድ ወረቀቶች ማለት በገንዘብ መክፈል የሚሆነውን ግዴታ የሚናገሩ የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች ናቸው፡፡
እነዚህ ሰነዶችም፡-
✅የሀዋላ ወረቀት /Bill of Exchange/
✅ለመክፈል ተስፋ ሰነድ /Promisory Note/፣
✅ቼክ /Cheques/፣
✅የመንገድ ቼክ/Travellers Cheques/፣
✅የእቃ መጋዘን ለተቀመጡ እቃዎች ምስክር ወረቀቶች/ደረሰኞች /warehouse goods deposit certificates/ ናቸው፡፡
የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች ሊያሟሏቸው ስለሚገቡ መስፈርቶች እና የሚያስከትሉት ህጋዊ ውጤት
የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች የሚወጡት በህግ ችሎታ ባላቸው ሰዎች ብቻ ነው፡፡ በ1952 የንግድ ህግ አንቀጽ 733 መሰረት ማናቸውም በውል ለመገደድ ችሎታ ያለው ሰው በንግድ ወረቀትም መገደድ እንደሚችል ደንግጓል፡፡ ማንኛውም ሰው በውል የሚገደደው በህግ ችሎታውን ያላጣ ከሆነ ብቻ ነው፡፡ ህጋዊ ችሎታ የሌላቸው ሰዎች ማለት በፍትሐብሔር ህጉ መሰረት የጸና ህጋዊ ውጤት የሚያስከትሉ ክንውኖችን ለማካሄድ አቅም የሌላቸው ሰዎች ሲሆኑ እነሱም ለአቅመ አዳም ያልደረሱ ህጻናት፣ በህግ ወይም በፍርድ ቤት ውሳኔ ከህጋዊ ውጤት ካላቸው ድርጊቶች ውስጥ ከመሳተፍ የተከለከሉ ሰዎች (ለምሳሌ የአእምሮ ህመምተኛ፣ በእርጅና ምክንያት የሚያደርጉትን ድርጊት ህጋዊ ውጤት የማያውቁ ሰዎች እና በወንጀል ቅጣት ከመብት በመሻር ውሳኔ በወንጀል ህጉ አንቀጽ 123 መሰረት የተወሰነባቸው ሰዎች) ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶችን ወይም የንግድ ወረቀቶች ማውጣት አይችሉም፡፡ ካወጡም አይገደዱባቸውም ማለት ነው፡፡
ሌላኛው መስፈርት ፊርማ ነው፡፡ የሚተላለፉ ሰነዶች ሲወጡ የግድ በአውጪው መፈረም አለባቸው፡፡ ይኸውም በሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች ባወጧቸው ሰዎች ወይም መግለጫውን በሰጡ ሰዎች የእጅ ፣ጽሁፍ ፊርማ ሊፈረሙ ይገባል፡፡ መፈረም ለማይችሉ ሰዎች በእጅ ምልክት ወይም ማህተም ማድረግ አለባቸው፡፡ በሁሉም ሁኔታ በንግድ ወረቀቶች ላይ መፈረም የማይሉ ሰዎች ሰነዱን ስለማውጣታቸው እና ይዘቱ በባለስልጣን ፊት ቀርቦ መረጋገጠ አለበት፡፡
በንግድ ህጉ አንቀጽ 719 መሰረት የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች በሁለት መደቦች ሊወጡ የሚችሉ ሲሆን እነሱም ለአምጪው ወይም ስሙ ለተጠቀሰው ወይም ለታዘዘለት ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ይህ ማለትም ላምጪው ተብለው የወጡ የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች ሰነዶቹን ለባለ ግዴታው ያቀረበ ማንም ሰው በሰነዶቹ የተገለጸው ገንዘብ ተከፋይ ባለመብት ይሆናል ማለት ነው፡፡ ባለእዳው የአምጪውን ማንነት ግምት ውስጥ ሳያስገባ ሰነዱን ያቀረበው ሰው በቀጥታ ባለመብት መሆኑን በመገንዘብ በሰነዱ ላይ የተጠቀሰውን ክፍያ መፈጸም ይኖርበታል ማለት ነው፡፡ እዚህ ላይ በህጉ አንቀጽ 721 እንደተገለጸው ሰነዱን ያቀረበው ሰው በሰነዱ የተገለጸው ግዴታ ባለመብት ለመሆኑ በቂ ማረጋገጫ ነው፡፡
ሁለተኛው የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች የሚወጣበት ፎርም ስሙ ለተጠቀሰው ወይም ለታዘዘለት ሰው ተብለው ሊወጣ ይችላሉ፡፡ ይህ ማለት የተከፋይነት ወይም የአገልግሎት ተጠቃሚነት ባለመብትን የመብቱን ተጠቀሚ ማንነት ቀድሞ በመለየት ይሄንኑም በተላላፊ የገንዘብ ሰነዶቹ ላይ በመግለጽ የወጡ ሰነዶች ናቸው፡፡ በሰነዱ የተገለጹ ገንዘብ ወይም ግደታዎች ባለ እዳ የሆነው ሰው ወይም ድርጅት አገልግሎቱን ወይም ክፍያውን ሰነዱን ላቀረበለት ሰው ሁሉ ቀጥታ የሚፈጽመው ሳይሆን በሰነዱ ስሙ ወይም ማንነቱ ለተገለጸው ሰው ብቻ መፈጸም አለባት፡፡ ስሙ የተገለጸው ሰው እና ሰነዱን ያቀረበው ሰው አንድ መሆናቸውን በመታወቂያና መሰል ሰነድ ማረጋገጫ መንገዶች አጣርቶ መክፈል አለበት፡፡
የአክስዮን ማህበር አክስዮንን በተመለከተ የቀድሞው የንግድ ህግ አክስዮኖች በሁለቱም መንገዶች ማለትም ለአምጪ ወይም ስሙ በአክስዮኑ ለተመዘገበው ሰው በማለት የሚወጡ እና የሚተላለፉ ሲሆን በአዲሱ የንግድ ህግ አዋጅ 1243/2013 አንቀጽ 267 መሰረት ግን አክስዮኖች በባለአክስዮኖች ስም በመመዝገብ መውጣት እንዳለባቸው ህጉ ደንግጓል፡፡ ቀደም ሲልም ለአምጪው ተብለው የወጡ አክስዮኖች በሶስት አመት ጊዜ ውስጥ ወደ ተመዝጋቢ ባለአክስዮንነት እንዲቀየሩ ተደንግጓል፡፡ ስለዚህ ለአምጪው ተብሎ የሚጠቀስ እና የሚወጣ አክስዮን በአዲሱ ንግድ ህግ መሰረት አዲሱ የንግድ ህግ ከወጣበት ቀን አንስቶ ከሶስት ዓመት በኋላ ህጋዊ ተቀባይነት የለውም ማለት ነው፡፡
በሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች ውስጥ የተገለጸ እዳ ባለእዳ የሆነ ሰው እዳውን መክፈል ያለበት ሰነዱን ከቀረበለት ብቻ ሲሆን ይህ ባለእዳ ክፍያውን ሲፈጽም ከባድ አታላይነት ወይም ቸልተኝነት ካልፈጸመ በስተቀር የገንዘብ ተከፋይ ትክክለኛው ሰው ባይሆን እንኳን ሰነዱ ባለገንዘብነት መብት ለሰጠው ሰው የክፍያ ጊዜው ሲደርስ ከከፈለ ከእዳው ነጻ መሆኑን ህጉ በአንቀጽ 716 ንኡስ አንቀጽ 3 ላይ ደንግጎ ይገኛል፡፡ ከዚህም የምንረዳው ይህ በሰነዶች የሚደረግ የገንዘብ ልውውጥ የፋየናንስ ግብይቱን እና አጠቃላይ የኢኮኖሚውን ፈጣን ግብይት ለማረጋገጥ ታስቦ የተቀረጸ ለግብይቱ የተደረገ የህግ ጥበቃ እና ዋስትና መሆኑን ነው፡፡
........ 👇ይቀጥላል👇👇👇👇
መግቢያ
በሀገራችን የንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ ንግድን ከማፋጠን እና የፋይናንስ ግብይትን ከማሳለጥ አንጻር የገንዘብነት ዋጋ ያላቻው የሚተላለፉ ሰነዶች የሚጫወቱት ሚና እጅግ ከፍተኛ እንደሆነ ይታመናል፡፡ በዚህ አጭር ጽሁፍ እነዚህኑ የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች ምንነት እና የሀገራችን የሚተዳደሩበትን የህግ ማእቀፍ በአጭሩ እናያለን፡፡
የህግ ማእቀፍ
እስከቅርብ ጊዜ በስራ ላይ የነበረው የ1952ቱ የንግድ ህግ ስድስት መጽሐፍት የነበሩት ሲሆን የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶችና የባንክ ስራዎች በተመለከተ የደነገገው የህጉ ክፍል በመጽሀፍ አራት ስር የተደራጁ ናቸው፡፡ አዲሱ የንግድ ህግ አዋጅ ቁጥር 1243/2013 በይዘቱ በሶስት መጽሐፍት የተከፋፈለ ሲሆን የበፊቱ ንግድ ህግ መጽሐፍት 3 እና 4 የአዲሱ የንግድ ሕግ አካል ሳይሆኑ ራሳቸዉን ችለዉ የፋይናንስ አገልግሎት መድብል ወይም ኮድ ሆነው እንዲወጡ በመተው መጽሐፍ አንድ፣ሁለት እና አምስት የንግድ ሕግ ተብሎ እንዲሻሻል ተደርጎ በአዲሱ የንግድ ሕግ ተካተው ወጥተዋል፡፡ በዚህም አዲሱ የፋይናንስ አገልግሎት ህግ እስኪወጣ ድረስ የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች ወይም የንግድ ወረቀቶች በነባሩ የንግድ ህግ ምእራፍ አራት ድንጋጌዎች መሰረት የሚታዩ መሆናቸው ይቀጥላል፡፡
የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች ምንነት
በ1952ቱ የንግድ ህግ አንቀፅ 715 /1/ መሰረት የሚተላለፍ የገንዘብ ሰነድ ማለት መብቱ ከሰነዱ ተለይቶ ሊሰራበት ወይም ሊተላለፍ የማይችል የአገልግሎት መብት ያለበት ሰነድ ሁሉ ነው በማለት ይደነግጋል፡፡ ይህ ትርጉም የሚተላለፉ ሰነዶች የመብትና የግዴታ ማረጋገጫ ሰነዶች ናቸው ከማለት በተጨማሪ በሰነዶቹ ውስጥ የተመለከቱት መብቶች ከሰነዶች ተለይተው ሊተላለፉ /ሊሰራባቸው/ እንደማይችሉ የሚያመለክት ነው፡፡ ይህም አባባል ጠቅለል ባለ መልኩ ሲገለፅ የሚተላለፍ ሰነድ ማለት በሠነድ ላይ የተመለከተው መብት ከሰነድ ላይ ለይቶ ሊሰራበት እና ሊተላለፍ የማይችል የመብትና የዕዳ ማረጋገጫ ሰነድ መሆኑን የሚያስረዳ ነው፡፡
የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነድ አይነቶች
በ1952ቱ የንግድ ህግ አንቀፅ 732 መሰረት የንግድ ወረቀቶች ማለት በገንዘብ መክፈል የሚሆነውን ግዴታ የሚናገሩ የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች ናቸው፡፡
እነዚህ ሰነዶችም፡-
✅የሀዋላ ወረቀት /Bill of Exchange/
✅ለመክፈል ተስፋ ሰነድ /Promisory Note/፣
✅ቼክ /Cheques/፣
✅የመንገድ ቼክ/Travellers Cheques/፣
✅የእቃ መጋዘን ለተቀመጡ እቃዎች ምስክር ወረቀቶች/ደረሰኞች /warehouse goods deposit certificates/ ናቸው፡፡
የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች ሊያሟሏቸው ስለሚገቡ መስፈርቶች እና የሚያስከትሉት ህጋዊ ውጤት
የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች የሚወጡት በህግ ችሎታ ባላቸው ሰዎች ብቻ ነው፡፡ በ1952 የንግድ ህግ አንቀጽ 733 መሰረት ማናቸውም በውል ለመገደድ ችሎታ ያለው ሰው በንግድ ወረቀትም መገደድ እንደሚችል ደንግጓል፡፡ ማንኛውም ሰው በውል የሚገደደው በህግ ችሎታውን ያላጣ ከሆነ ብቻ ነው፡፡ ህጋዊ ችሎታ የሌላቸው ሰዎች ማለት በፍትሐብሔር ህጉ መሰረት የጸና ህጋዊ ውጤት የሚያስከትሉ ክንውኖችን ለማካሄድ አቅም የሌላቸው ሰዎች ሲሆኑ እነሱም ለአቅመ አዳም ያልደረሱ ህጻናት፣ በህግ ወይም በፍርድ ቤት ውሳኔ ከህጋዊ ውጤት ካላቸው ድርጊቶች ውስጥ ከመሳተፍ የተከለከሉ ሰዎች (ለምሳሌ የአእምሮ ህመምተኛ፣ በእርጅና ምክንያት የሚያደርጉትን ድርጊት ህጋዊ ውጤት የማያውቁ ሰዎች እና በወንጀል ቅጣት ከመብት በመሻር ውሳኔ በወንጀል ህጉ አንቀጽ 123 መሰረት የተወሰነባቸው ሰዎች) ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶችን ወይም የንግድ ወረቀቶች ማውጣት አይችሉም፡፡ ካወጡም አይገደዱባቸውም ማለት ነው፡፡
ሌላኛው መስፈርት ፊርማ ነው፡፡ የሚተላለፉ ሰነዶች ሲወጡ የግድ በአውጪው መፈረም አለባቸው፡፡ ይኸውም በሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች ባወጧቸው ሰዎች ወይም መግለጫውን በሰጡ ሰዎች የእጅ ፣ጽሁፍ ፊርማ ሊፈረሙ ይገባል፡፡ መፈረም ለማይችሉ ሰዎች በእጅ ምልክት ወይም ማህተም ማድረግ አለባቸው፡፡ በሁሉም ሁኔታ በንግድ ወረቀቶች ላይ መፈረም የማይሉ ሰዎች ሰነዱን ስለማውጣታቸው እና ይዘቱ በባለስልጣን ፊት ቀርቦ መረጋገጠ አለበት፡፡
በንግድ ህጉ አንቀጽ 719 መሰረት የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች በሁለት መደቦች ሊወጡ የሚችሉ ሲሆን እነሱም ለአምጪው ወይም ስሙ ለተጠቀሰው ወይም ለታዘዘለት ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ይህ ማለትም ላምጪው ተብለው የወጡ የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች ሰነዶቹን ለባለ ግዴታው ያቀረበ ማንም ሰው በሰነዶቹ የተገለጸው ገንዘብ ተከፋይ ባለመብት ይሆናል ማለት ነው፡፡ ባለእዳው የአምጪውን ማንነት ግምት ውስጥ ሳያስገባ ሰነዱን ያቀረበው ሰው በቀጥታ ባለመብት መሆኑን በመገንዘብ በሰነዱ ላይ የተጠቀሰውን ክፍያ መፈጸም ይኖርበታል ማለት ነው፡፡ እዚህ ላይ በህጉ አንቀጽ 721 እንደተገለጸው ሰነዱን ያቀረበው ሰው በሰነዱ የተገለጸው ግዴታ ባለመብት ለመሆኑ በቂ ማረጋገጫ ነው፡፡
ሁለተኛው የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች የሚወጣበት ፎርም ስሙ ለተጠቀሰው ወይም ለታዘዘለት ሰው ተብለው ሊወጣ ይችላሉ፡፡ ይህ ማለት የተከፋይነት ወይም የአገልግሎት ተጠቃሚነት ባለመብትን የመብቱን ተጠቀሚ ማንነት ቀድሞ በመለየት ይሄንኑም በተላላፊ የገንዘብ ሰነዶቹ ላይ በመግለጽ የወጡ ሰነዶች ናቸው፡፡ በሰነዱ የተገለጹ ገንዘብ ወይም ግደታዎች ባለ እዳ የሆነው ሰው ወይም ድርጅት አገልግሎቱን ወይም ክፍያውን ሰነዱን ላቀረበለት ሰው ሁሉ ቀጥታ የሚፈጽመው ሳይሆን በሰነዱ ስሙ ወይም ማንነቱ ለተገለጸው ሰው ብቻ መፈጸም አለባት፡፡ ስሙ የተገለጸው ሰው እና ሰነዱን ያቀረበው ሰው አንድ መሆናቸውን በመታወቂያና መሰል ሰነድ ማረጋገጫ መንገዶች አጣርቶ መክፈል አለበት፡፡
የአክስዮን ማህበር አክስዮንን በተመለከተ የቀድሞው የንግድ ህግ አክስዮኖች በሁለቱም መንገዶች ማለትም ለአምጪ ወይም ስሙ በአክስዮኑ ለተመዘገበው ሰው በማለት የሚወጡ እና የሚተላለፉ ሲሆን በአዲሱ የንግድ ህግ አዋጅ 1243/2013 አንቀጽ 267 መሰረት ግን አክስዮኖች በባለአክስዮኖች ስም በመመዝገብ መውጣት እንዳለባቸው ህጉ ደንግጓል፡፡ ቀደም ሲልም ለአምጪው ተብለው የወጡ አክስዮኖች በሶስት አመት ጊዜ ውስጥ ወደ ተመዝጋቢ ባለአክስዮንነት እንዲቀየሩ ተደንግጓል፡፡ ስለዚህ ለአምጪው ተብሎ የሚጠቀስ እና የሚወጣ አክስዮን በአዲሱ ንግድ ህግ መሰረት አዲሱ የንግድ ህግ ከወጣበት ቀን አንስቶ ከሶስት ዓመት በኋላ ህጋዊ ተቀባይነት የለውም ማለት ነው፡፡
በሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች ውስጥ የተገለጸ እዳ ባለእዳ የሆነ ሰው እዳውን መክፈል ያለበት ሰነዱን ከቀረበለት ብቻ ሲሆን ይህ ባለእዳ ክፍያውን ሲፈጽም ከባድ አታላይነት ወይም ቸልተኝነት ካልፈጸመ በስተቀር የገንዘብ ተከፋይ ትክክለኛው ሰው ባይሆን እንኳን ሰነዱ ባለገንዘብነት መብት ለሰጠው ሰው የክፍያ ጊዜው ሲደርስ ከከፈለ ከእዳው ነጻ መሆኑን ህጉ በአንቀጽ 716 ንኡስ አንቀጽ 3 ላይ ደንግጎ ይገኛል፡፡ ከዚህም የምንረዳው ይህ በሰነዶች የሚደረግ የገንዘብ ልውውጥ የፋየናንስ ግብይቱን እና አጠቃላይ የኢኮኖሚውን ፈጣን ግብይት ለማረጋገጥ ታስቦ የተቀረጸ ለግብይቱ የተደረገ የህግ ጥበቃ እና ዋስትና መሆኑን ነው፡፡
........ 👇ይቀጥላል👇👇👇👇
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
..........👆👆የቀጠለ 👆👆👆
ነገር ግን እዳ ከፋዩ ሰነዱን ከያዘው ሰው ጋር ባሉ የግል ግንኙነቶች በመመስረት በሰነዱ አጻጻፍ፣ ፎርም፣ ቃላት፣ የማስመሰል ፊርማ፣ ሰነዱን የማውጣት ችሎታ ወይም የውክልና ስልጣን አለመኖር እና ሌሎች ክስ ለማቅረብ አስፈላጊ የሆኑ ቅድመ ሁኔታዎች አለመሟላታቸውን በማንሳት እዳ ከፋዩ ሰነዱን የያዘውን ሰው እዳውን ላለመክፈል ሊቃወም ይችላል፡፡ ሆኖም አንድ በቅን ልቦና የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶችን የያዘ ሰው መልስ ተብሎ ሊከሰስ አይችልም፡፡ በሌላ በኩል የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶችን የያዘ ሰው የሰነዶቹን ለአምጪው ከሚለው ወደ ስም የተጻፈበት ሰው እንዲቀይርለት ሰነዶቹን ላወጣው ሰው በራሱ ኪሳራ ሊጠይቅ እንደሚችል ህጉ ይፈቅዳል፡፡
ሌላው የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነድ በትእዛዝ በሚል የሚተላለፍ ሲሆን ይህም የሚፈጸመው በህጉ አንቀጽ 724 እና ቀጥሎ ባሉ ድንጋጌዎች መሰረት በሰነዱ ጀርባ በመፈረም እና ባለመብት ለሆነው ሰው በመስጠት ነው፡፡ በዚሁ ህግ መሰረት በሰነዱ ጀርባ ላይ በመፈረም በትእዛዝ በሚል የሚተላለፉ ሰነዶች በጀርባው መፈረሙ በሰነዱ ላይ መገለጽ ያለበት ሲሆን በጀርባውም በጻፈው ሰው በራሱ መፈረም አለበት፡፡ እዚህ ላይ በጀርባው የተፈረመ ሰነድ የተፈረመለት ሰው ስም ባይገለጽም ህጋዊ ዋጋ አለው፡፡ ለዚህ አላማ ሲባል ለአምጪው ተብሎ በጀርባ የተፈረመበት ገንዘብ አስተላላፊ ሰነድ ልክ ስም እንዳልተገለጸበት ይቆጠራል፡፡ በዚህም ሰነዱን ያቀረበው ሰው በሰነዱ የተገለጹ ግዴታዎች ባለመብት ይሆናል ማለት ነው፡፡ በተጨማሪም በሰነዱ ጀርባ ሀተታ ማስገባትን ህጉ አይፈቅድም መፈረሙ ብቻ በቂ ነው፡፡ የገቡ ሀተታዎች ካሉም እንዳልገቡ ይቆጠራሉ፡፡
ከህጋዊ ውጤት አኳያ በጀርባው የተፈረመ ገንዘብ ማስተላለፊያ ሰነድ በሰነዱ ውስጥ የተገለጹትን መብቶች ሁሉ ያስተላልፋል፡፡ በዚህ መልክ የሚወጣ የገንዘብ ማስተላለፊያ ሰነድ በጀርባው ጽሁፍ ወይም ስም ያልተሞላበት ከሆነ አምጪው ባዶውን ቦታ በራሱ ወይም በሌላ ሰው ስም መሙላት፣ ሰነዱን እንደገና ስም ሳይጽፍ ወይም የሌላ ሰው ስም በማስገባት ማስተላለፍ የችላል፡፡ በተጨማሪም ይህ ሰነዱን የያዘው ሰው የሰነዱን ባዶ ቦታ ሳይሞላ በጀርባውም ሳይፈርም ለሶስተኛ ወገን ሰነዱን ማስተላለፍ ይችላል፡፡ በዚህ ሁኔታ በሰነዱ ጀርባ የሚፈርም ሰው ሰነዱን ያወጣው ሰው ስላልፈጸመው ግዴታ ተጠያቂነት የለበትም፡፡ ይህ ማለት በሰነዱ ጀርባ የሚፈርም ሰው ሰነዱን ያወጣው ሰው በሰነዱ ይዘት ውስጥ የገባው ግዴታ ሀላፊነት አለበት ማለት ነው፡፡ በሰነዱ በተገለጸው ልክ ሰነዱ የሚያስከትለውን ግዴታ በሰነዱ ጀርባ የፈርመው ሰው ልክ እንደ ሰነዱ አውጪ በመሆን በተገለጸው ግዴታ ሀላፊነት አለበት ማለት ነው፡፡ ሰነድ የተላለፈለት ሰው ሰነዱን ሲቀበል እዳ ከፋዩን ለመጉዳት እያወቀ ካላደረገው በስተቀር ሰነድ አውጪ ከሰነድ ፈራሚው ጋር ባለው የግል ግንኘነት ላይ ከተመሰረቱት መከራከሪያዎች በቀር በዋስትና ስም ሰነዱ የተላለፈለትን ሰው ሊቃወምባቸው አይችልም፡፡
ማጠቃለያ
ገንዘብ ማስተላለፊያ ሰነዶች ወይም የንግድ ወረቀቶች አገራዊ ኢኮኖሚውን በተፋጠነ የግብይት ስርአት እንዲመራ ማድረግ ወስጥ ከፍተኛ ሚና ያላቸው ሲሆን የፋይናንስ ተቋማት የገንዘብ ፍሰት ፖሊሲንም ከማሳለጥ እና ለኢንቨስትመንት በብድር የሚሰጥ ወይም ለገንዘብ ጠያቂ ደንበኞቻቸው የሚከፈል የተከፋይ ገንዘብ እጥረት (liquidity problem) እንዳይገጠማቸው ያደርጋሉ፡፡ በዚህም አገራዊ እና ተቋማዊ እድገትን በከፍተኛ ሁኔታ ያግዛሉ፡፡ ከዚህ ባለፈ ያልተመዘገበ (የካሽ) የግብይት ስርአት እንደ አገር ከፋይናንስ ስርአቱ ውስጥ እንዲቀንስ ማድረግ ላይ ጉልህ ሚና አላቸው፡፡
https://t.me/lawsocieties
ነገር ግን እዳ ከፋዩ ሰነዱን ከያዘው ሰው ጋር ባሉ የግል ግንኙነቶች በመመስረት በሰነዱ አጻጻፍ፣ ፎርም፣ ቃላት፣ የማስመሰል ፊርማ፣ ሰነዱን የማውጣት ችሎታ ወይም የውክልና ስልጣን አለመኖር እና ሌሎች ክስ ለማቅረብ አስፈላጊ የሆኑ ቅድመ ሁኔታዎች አለመሟላታቸውን በማንሳት እዳ ከፋዩ ሰነዱን የያዘውን ሰው እዳውን ላለመክፈል ሊቃወም ይችላል፡፡ ሆኖም አንድ በቅን ልቦና የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶችን የያዘ ሰው መልስ ተብሎ ሊከሰስ አይችልም፡፡ በሌላ በኩል የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶችን የያዘ ሰው የሰነዶቹን ለአምጪው ከሚለው ወደ ስም የተጻፈበት ሰው እንዲቀይርለት ሰነዶቹን ላወጣው ሰው በራሱ ኪሳራ ሊጠይቅ እንደሚችል ህጉ ይፈቅዳል፡፡
ሌላው የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነድ በትእዛዝ በሚል የሚተላለፍ ሲሆን ይህም የሚፈጸመው በህጉ አንቀጽ 724 እና ቀጥሎ ባሉ ድንጋጌዎች መሰረት በሰነዱ ጀርባ በመፈረም እና ባለመብት ለሆነው ሰው በመስጠት ነው፡፡ በዚሁ ህግ መሰረት በሰነዱ ጀርባ ላይ በመፈረም በትእዛዝ በሚል የሚተላለፉ ሰነዶች በጀርባው መፈረሙ በሰነዱ ላይ መገለጽ ያለበት ሲሆን በጀርባውም በጻፈው ሰው በራሱ መፈረም አለበት፡፡ እዚህ ላይ በጀርባው የተፈረመ ሰነድ የተፈረመለት ሰው ስም ባይገለጽም ህጋዊ ዋጋ አለው፡፡ ለዚህ አላማ ሲባል ለአምጪው ተብሎ በጀርባ የተፈረመበት ገንዘብ አስተላላፊ ሰነድ ልክ ስም እንዳልተገለጸበት ይቆጠራል፡፡ በዚህም ሰነዱን ያቀረበው ሰው በሰነዱ የተገለጹ ግዴታዎች ባለመብት ይሆናል ማለት ነው፡፡ በተጨማሪም በሰነዱ ጀርባ ሀተታ ማስገባትን ህጉ አይፈቅድም መፈረሙ ብቻ በቂ ነው፡፡ የገቡ ሀተታዎች ካሉም እንዳልገቡ ይቆጠራሉ፡፡
ከህጋዊ ውጤት አኳያ በጀርባው የተፈረመ ገንዘብ ማስተላለፊያ ሰነድ በሰነዱ ውስጥ የተገለጹትን መብቶች ሁሉ ያስተላልፋል፡፡ በዚህ መልክ የሚወጣ የገንዘብ ማስተላለፊያ ሰነድ በጀርባው ጽሁፍ ወይም ስም ያልተሞላበት ከሆነ አምጪው ባዶውን ቦታ በራሱ ወይም በሌላ ሰው ስም መሙላት፣ ሰነዱን እንደገና ስም ሳይጽፍ ወይም የሌላ ሰው ስም በማስገባት ማስተላለፍ የችላል፡፡ በተጨማሪም ይህ ሰነዱን የያዘው ሰው የሰነዱን ባዶ ቦታ ሳይሞላ በጀርባውም ሳይፈርም ለሶስተኛ ወገን ሰነዱን ማስተላለፍ ይችላል፡፡ በዚህ ሁኔታ በሰነዱ ጀርባ የሚፈርም ሰው ሰነዱን ያወጣው ሰው ስላልፈጸመው ግዴታ ተጠያቂነት የለበትም፡፡ ይህ ማለት በሰነዱ ጀርባ የሚፈርም ሰው ሰነዱን ያወጣው ሰው በሰነዱ ይዘት ውስጥ የገባው ግዴታ ሀላፊነት አለበት ማለት ነው፡፡ በሰነዱ በተገለጸው ልክ ሰነዱ የሚያስከትለውን ግዴታ በሰነዱ ጀርባ የፈርመው ሰው ልክ እንደ ሰነዱ አውጪ በመሆን በተገለጸው ግዴታ ሀላፊነት አለበት ማለት ነው፡፡ ሰነድ የተላለፈለት ሰው ሰነዱን ሲቀበል እዳ ከፋዩን ለመጉዳት እያወቀ ካላደረገው በስተቀር ሰነድ አውጪ ከሰነድ ፈራሚው ጋር ባለው የግል ግንኘነት ላይ ከተመሰረቱት መከራከሪያዎች በቀር በዋስትና ስም ሰነዱ የተላለፈለትን ሰው ሊቃወምባቸው አይችልም፡፡
ማጠቃለያ
ገንዘብ ማስተላለፊያ ሰነዶች ወይም የንግድ ወረቀቶች አገራዊ ኢኮኖሚውን በተፋጠነ የግብይት ስርአት እንዲመራ ማድረግ ወስጥ ከፍተኛ ሚና ያላቸው ሲሆን የፋይናንስ ተቋማት የገንዘብ ፍሰት ፖሊሲንም ከማሳለጥ እና ለኢንቨስትመንት በብድር የሚሰጥ ወይም ለገንዘብ ጠያቂ ደንበኞቻቸው የሚከፈል የተከፋይ ገንዘብ እጥረት (liquidity problem) እንዳይገጠማቸው ያደርጋሉ፡፡ በዚህም አገራዊ እና ተቋማዊ እድገትን በከፍተኛ ሁኔታ ያግዛሉ፡፡ ከዚህ ባለፈ ያልተመዘገበ (የካሽ) የግብይት ስርአት እንደ አገር ከፋይናንስ ስርአቱ ውስጥ እንዲቀንስ ማድረግ ላይ ጉልህ ሚና አላቸው፡፡
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
የውጭ ባንኮች የኢትዮጵያን ገበያ መቀላቀላቸውን አስመልክቶ የተለያዩ የድጋፍም ሆነ የተቃውሞ ሐሳቦች እየተንጸባረቁ ነው።
በዝርዝር ለመተቸትም ሆነ ለመደገፍ ፖሊሲዎች የአፈጻጸም መመሪያዎች እስኪወጡ መጠበቅ ተገቢ ስለሆነ፣ ለዛሬው ጥቅል ሐሳቦችንና ትኩረት የሚሹ ነጥቦች ብቻ በጨረፍታ አቀርባለሁ።
የዓለም አቀፍ ገበያ ድርጅትን (WTO) ለመቀላቀል አንዱ መስፈርት የሆነው ባንክና ቴሌን የመሳሰሉ ተቋማትን ለውጭ ኢንቨስተሮች ክፍት ማድረግ ነው። በዚህ ምክንያትም የውጭ ሀገር ባንኮች የሀገራችንን የባንኪንግ ኢንደስትሪ የመቀላቀላቸው ጉዳይ የጊዜ ጉዳይ እንጂ አይቀሬ እንደነበር የሚታወቅ ነው።
አሁን ሊያወያየን የሚችለው ጉዳይ ባንኮቹ ገበያውን እንዲቀላቀሉ የተፈቀደበት ወቅት ተገቢ ነበር ወይ? የመንግስት፣ የብሔራዊ ባንክና ሀገር በቀል ባንኮች አቅምና ቅደም ዝግጅታቸውስ ምን ይመስላል? የገበያችንን ስርዓት ( Market Structure ) ምን ያህል ሕጋዊነትን የተከተለና ለወንጀልና ወንጀለኞች ያልተጋለጠ ነው። የግብር አከፋፈል፣ የመረጃ አሰባሰብና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂያችን ምን ያህል ጥብቅና ለውንብድናና ለጠለፋ ( Hacking ) ያልተጋለጡ ናቸው የሚሉትና መሰል ጉዳዮች ይሆናሉ
የውጭ ሀገር ባንኮች ወደ ሀገራችን የሚመጡት ገበያ፣ ነባርና አዲስ ደንበኛና ትርፍ ፍለጋ ስለሆነ ስለ ሀገር እድገት በተለይ የሚጨነቁና የማይጠበቡ ልማታዊ እሳቤም የሌላቸው እንደሆነ የሚታወቅ ነው። የሚቀላቀሉት ገበያ ያለበት ሀገርም ሀገራቸው ስላልሆነ ትርፍ እስካገኙ ድረስ በማንኛውም መንገድ ከማትረፍ ወደኃላ የማይሉና የሕግ አስገዳጅነት እንጂ የሞራል ጥያቄ እምብዛም የማይገዳቸው ሊሆኑ እንደሚችሉ ታሳቢ መሆን አለበት። በተቃራኒው ደግሞ ሀገር በቀል ባንኮች ከትርፍ ባሻገር የሀገራቸው፣ የመንግስትና የልማታቸው አጋር ስለሆኑ ከሕግ ባሻገር በርካታ የውዴታ ግዴታና የሞራል ፈተና ስላለባቸው ውድድሩ የተለየ ጫና ሊያሳድርባቸው ይችላል።
የውጭ ሀገር ባንኮች በርካታ የውጭ ምንዛሬ ያመጣሉ የሚለውም እሳቤ የተጋነና በአብዛኛው የተሳሳተ መረጃ ነው። የውጭ ባንኮች የውጭ ምንዛሪ በገፍ ይዘው መጥተው በብር የመለወጥ ፍላጎት አይኖራቸውም። በአብዛኛውም ያለችውን ገበያና የውጭ ምንዛሪ መቀራመት ላይ እንደሚያተኩሩ ከሌሎች ሀገራት ተሞክሮ ይታወቃል።
ትርፋቸውንም በውጭ ምንዛሪ ከሀገር የማውጣት እድላቸው ጠባብ ስለሆነና ዋና መስርያ ቤታቸውን እንዲገነቡ ለሚሰበስቡት ብር ተመጣጣኝና ኃላፊነትና ግዴታ (Risk) እንዲወስዱ ካልተገደዱ በስተቀር ዘርፉ ቅርንጫፍ ተከራይቶ ቁሳቁስ በማሟላትና ገንዘብ በመሰብሰብ በትንሽ ኢንቨስትመንት የሚሰራ ስለሆነ ኢንቨስትመንታቸውንም ውስን በማድረግ ያለ በቂ ኃላፊነት፣ ስጋትና መተማመኛ ሊነግዱ ይችላሉ።
ሌላው ሀገር በቀል ባንኮች ከተደራሽነትና ሕዝብን ከማገልገል አኳያ ትርፍ ኖረም አልኖረ እንደ አቅማቸው ሁሉም ቦታ ቅርንጫፍ ይከፍታሉ። የውጭ ባንኮች ግን ሀብትና ኢኮኖሚያዊ አቅም በስፋት የሚታይባቸው አካባቢዎች ላይ ብቻ አትኩረው ሊሰሩ ስለሚችሉ አቅም ባለበት ቦታ ላይ ብቻ የሚኖረው ውድድሩ በሚፈጥረው ሽሚያ በሚፈጠረው አቅም መዳከም ምክንያት ቀሪው አካባቢና ማህበረሰብ የባንክ አገልግሎት ላያገኝ ይችላል።
ሌላው ሀገራችን ውስጥ የሚገኙ ከፍተኛ አስቀማጭና ተበዳሪዎች በጥቂት መቶዎች የሚቆጠሩ ሰለሆኑ እነዚህን ደንበኞችና ገበያ (Niche Market) ላይ ብቻ በማተኮር ወይም ከፍተኛ እጥረት ያለበት የውጭ ምንዛሪ አቅርቦትን በማባበያነት በመጠቀም፣ የኢንዱስትሪውን አቅም ከ70 በመቶ በላይ በቀላሉ ለመቆጣጠር ይችላሉ። ይህ ደግሞ የተዛባና ወደ አንድ ጎን ያጋደለ (Economic imbalance) ፣ ኢ-ፍትሐዊ ወይም ሚዛናዊ ያልሆነ ውድድር (Unfair Competition) ሊፈጥሩ ይችላሉ።
በዚህ መንገድ ከሞላ ጎደል ገበያውን መሉ ለሙሉ ለመቆጣጠር ስለሚችሉም የፈለጉትን የአገልግሎት ዋጋ በመጣል፣ ወለድ በመተማንና ለፈቀዱለትና ለሚመስላቸው ዘርፍ ብቻ በማበደር ኢኮኖሚውን ወደ ፈለጉበት በመጠምዘዝ ልማታዊ እድሎችን እስከማደናቀፍ ሊደርሱ ይችላሉ። የውጭ ምንዛሪ ሲፈቅዱ የሀገራቸው ምርት ብቻ እንዲገባ በማድረግም ሀገሪቱን የሸቀጥ ማራገፊያ ( Damping ground) ሊያደርገት ይችላሉ። እንደዚህ ዓይነት አካሄዶች በማደግ ላይ ባሉ በርካታ ሀገራት ላይ ያጋጠመ ፈተናና ችግር ነው። በአንዳድ ሀገራትም አንዴ ባንኮቹ ጡንቻ ካፈረጠሙ በኃላ ለተለያዮ ኃይሎች የፖለቲካ መሳርያ በመሆን የመንግስትን እጅ እስከ መጠምዘዝ የደረሱበት ሁኔታም ታይቷል።
የውጭ ባንኮች ወድ ሀገር ውስጥ መግባታቸው በጠንካራ ጎንነት ሊወሳ የሚችለው የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ ዘመናዊ የባንክ ሙያና እውቀት ስርጸት፣ አዳዲስ የማኔጅመንትና የአመራር ጥበብ ሽግግር የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ። ከዚህም በላይ ለነባርና ብቃት ላላቸው የባንክ ሰራተኞችን ጨምሮ ለአዳዲስ ስራተኞችም የስራ እድል ይፈጥራል።
የውጭ ባንኮቹ ሀገር ውስጥ መኖራቸው በወጭና በገቢ ንግድ ላይ የነበረውን የተንዛዛ አሰራርና ተደራራቢ የክፍያ ስርዓት ሊቀንስ ይችላል። ኢንደስትሪው በስርዓትና በሕግ ከተመራም የዘመነና ጤናማ ውድድርን ሊያስከትል ይችላል። በአጠቃላይ ዘመናዊ አሰራር በማስተዋወቅ አዲስ ሃብት ከውጭ ወደ ሀገር ውስጥ በማሸጋገርና በማበልጸግ የተቀማጭም ሆነ የውጭ ምንዛሪ ይበልጥ እንዲሳለጥና Economics of Scale ከፍ እንዲል ሊያግዝ ይችላል።
Mushe Semu
https://t.me/lawsocieties
በዝርዝር ለመተቸትም ሆነ ለመደገፍ ፖሊሲዎች የአፈጻጸም መመሪያዎች እስኪወጡ መጠበቅ ተገቢ ስለሆነ፣ ለዛሬው ጥቅል ሐሳቦችንና ትኩረት የሚሹ ነጥቦች ብቻ በጨረፍታ አቀርባለሁ።
የዓለም አቀፍ ገበያ ድርጅትን (WTO) ለመቀላቀል አንዱ መስፈርት የሆነው ባንክና ቴሌን የመሳሰሉ ተቋማትን ለውጭ ኢንቨስተሮች ክፍት ማድረግ ነው። በዚህ ምክንያትም የውጭ ሀገር ባንኮች የሀገራችንን የባንኪንግ ኢንደስትሪ የመቀላቀላቸው ጉዳይ የጊዜ ጉዳይ እንጂ አይቀሬ እንደነበር የሚታወቅ ነው።
አሁን ሊያወያየን የሚችለው ጉዳይ ባንኮቹ ገበያውን እንዲቀላቀሉ የተፈቀደበት ወቅት ተገቢ ነበር ወይ? የመንግስት፣ የብሔራዊ ባንክና ሀገር በቀል ባንኮች አቅምና ቅደም ዝግጅታቸውስ ምን ይመስላል? የገበያችንን ስርዓት ( Market Structure ) ምን ያህል ሕጋዊነትን የተከተለና ለወንጀልና ወንጀለኞች ያልተጋለጠ ነው። የግብር አከፋፈል፣ የመረጃ አሰባሰብና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂያችን ምን ያህል ጥብቅና ለውንብድናና ለጠለፋ ( Hacking ) ያልተጋለጡ ናቸው የሚሉትና መሰል ጉዳዮች ይሆናሉ
የውጭ ሀገር ባንኮች ወደ ሀገራችን የሚመጡት ገበያ፣ ነባርና አዲስ ደንበኛና ትርፍ ፍለጋ ስለሆነ ስለ ሀገር እድገት በተለይ የሚጨነቁና የማይጠበቡ ልማታዊ እሳቤም የሌላቸው እንደሆነ የሚታወቅ ነው። የሚቀላቀሉት ገበያ ያለበት ሀገርም ሀገራቸው ስላልሆነ ትርፍ እስካገኙ ድረስ በማንኛውም መንገድ ከማትረፍ ወደኃላ የማይሉና የሕግ አስገዳጅነት እንጂ የሞራል ጥያቄ እምብዛም የማይገዳቸው ሊሆኑ እንደሚችሉ ታሳቢ መሆን አለበት። በተቃራኒው ደግሞ ሀገር በቀል ባንኮች ከትርፍ ባሻገር የሀገራቸው፣ የመንግስትና የልማታቸው አጋር ስለሆኑ ከሕግ ባሻገር በርካታ የውዴታ ግዴታና የሞራል ፈተና ስላለባቸው ውድድሩ የተለየ ጫና ሊያሳድርባቸው ይችላል።
የውጭ ሀገር ባንኮች በርካታ የውጭ ምንዛሬ ያመጣሉ የሚለውም እሳቤ የተጋነና በአብዛኛው የተሳሳተ መረጃ ነው። የውጭ ባንኮች የውጭ ምንዛሪ በገፍ ይዘው መጥተው በብር የመለወጥ ፍላጎት አይኖራቸውም። በአብዛኛውም ያለችውን ገበያና የውጭ ምንዛሪ መቀራመት ላይ እንደሚያተኩሩ ከሌሎች ሀገራት ተሞክሮ ይታወቃል።
ትርፋቸውንም በውጭ ምንዛሪ ከሀገር የማውጣት እድላቸው ጠባብ ስለሆነና ዋና መስርያ ቤታቸውን እንዲገነቡ ለሚሰበስቡት ብር ተመጣጣኝና ኃላፊነትና ግዴታ (Risk) እንዲወስዱ ካልተገደዱ በስተቀር ዘርፉ ቅርንጫፍ ተከራይቶ ቁሳቁስ በማሟላትና ገንዘብ በመሰብሰብ በትንሽ ኢንቨስትመንት የሚሰራ ስለሆነ ኢንቨስትመንታቸውንም ውስን በማድረግ ያለ በቂ ኃላፊነት፣ ስጋትና መተማመኛ ሊነግዱ ይችላሉ።
ሌላው ሀገር በቀል ባንኮች ከተደራሽነትና ሕዝብን ከማገልገል አኳያ ትርፍ ኖረም አልኖረ እንደ አቅማቸው ሁሉም ቦታ ቅርንጫፍ ይከፍታሉ። የውጭ ባንኮች ግን ሀብትና ኢኮኖሚያዊ አቅም በስፋት የሚታይባቸው አካባቢዎች ላይ ብቻ አትኩረው ሊሰሩ ስለሚችሉ አቅም ባለበት ቦታ ላይ ብቻ የሚኖረው ውድድሩ በሚፈጥረው ሽሚያ በሚፈጠረው አቅም መዳከም ምክንያት ቀሪው አካባቢና ማህበረሰብ የባንክ አገልግሎት ላያገኝ ይችላል።
ሌላው ሀገራችን ውስጥ የሚገኙ ከፍተኛ አስቀማጭና ተበዳሪዎች በጥቂት መቶዎች የሚቆጠሩ ሰለሆኑ እነዚህን ደንበኞችና ገበያ (Niche Market) ላይ ብቻ በማተኮር ወይም ከፍተኛ እጥረት ያለበት የውጭ ምንዛሪ አቅርቦትን በማባበያነት በመጠቀም፣ የኢንዱስትሪውን አቅም ከ70 በመቶ በላይ በቀላሉ ለመቆጣጠር ይችላሉ። ይህ ደግሞ የተዛባና ወደ አንድ ጎን ያጋደለ (Economic imbalance) ፣ ኢ-ፍትሐዊ ወይም ሚዛናዊ ያልሆነ ውድድር (Unfair Competition) ሊፈጥሩ ይችላሉ።
በዚህ መንገድ ከሞላ ጎደል ገበያውን መሉ ለሙሉ ለመቆጣጠር ስለሚችሉም የፈለጉትን የአገልግሎት ዋጋ በመጣል፣ ወለድ በመተማንና ለፈቀዱለትና ለሚመስላቸው ዘርፍ ብቻ በማበደር ኢኮኖሚውን ወደ ፈለጉበት በመጠምዘዝ ልማታዊ እድሎችን እስከማደናቀፍ ሊደርሱ ይችላሉ። የውጭ ምንዛሪ ሲፈቅዱ የሀገራቸው ምርት ብቻ እንዲገባ በማድረግም ሀገሪቱን የሸቀጥ ማራገፊያ ( Damping ground) ሊያደርገት ይችላሉ። እንደዚህ ዓይነት አካሄዶች በማደግ ላይ ባሉ በርካታ ሀገራት ላይ ያጋጠመ ፈተናና ችግር ነው። በአንዳድ ሀገራትም አንዴ ባንኮቹ ጡንቻ ካፈረጠሙ በኃላ ለተለያዮ ኃይሎች የፖለቲካ መሳርያ በመሆን የመንግስትን እጅ እስከ መጠምዘዝ የደረሱበት ሁኔታም ታይቷል።
የውጭ ባንኮች ወድ ሀገር ውስጥ መግባታቸው በጠንካራ ጎንነት ሊወሳ የሚችለው የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ ዘመናዊ የባንክ ሙያና እውቀት ስርጸት፣ አዳዲስ የማኔጅመንትና የአመራር ጥበብ ሽግግር የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ። ከዚህም በላይ ለነባርና ብቃት ላላቸው የባንክ ሰራተኞችን ጨምሮ ለአዳዲስ ስራተኞችም የስራ እድል ይፈጥራል።
የውጭ ባንኮቹ ሀገር ውስጥ መኖራቸው በወጭና በገቢ ንግድ ላይ የነበረውን የተንዛዛ አሰራርና ተደራራቢ የክፍያ ስርዓት ሊቀንስ ይችላል። ኢንደስትሪው በስርዓትና በሕግ ከተመራም የዘመነና ጤናማ ውድድርን ሊያስከትል ይችላል። በአጠቃላይ ዘመናዊ አሰራር በማስተዋወቅ አዲስ ሃብት ከውጭ ወደ ሀገር ውስጥ በማሸጋገርና በማበልጸግ የተቀማጭም ሆነ የውጭ ምንዛሪ ይበልጥ እንዲሳለጥና Economics of Scale ከፍ እንዲል ሊያግዝ ይችላል።
Mushe Semu
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
Tsehay Insurance S.C በሚከተሉት የስራ መደቦች በርካታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
Position:-
1: Underwriting Officer II
2: Auditor II
3: Claims Officer II
4: Legal Officer I
📚የትምህርት ዓይነት እና ደረጃ
BA/BSc Degree in Management, Accounting, Economics, Computer Science or Law,related fields.
🇪🇹 የስራቦታ:- Addis Ababa
🧭የምዝገባ ጊዜ ፡ እስከ መስከረም
4/2015 ዓ.ም
🔔ስለ ስራው ሙሉ መረጃ ለማየት እና ለማመልከት ቀጣዩን ሊንክ ይጠቀሙ
https://jobs.amazonethiopia.com/job/tsehay-insurance-s-c-5/
Position:-
1: Underwriting Officer II
2: Auditor II
3: Claims Officer II
4: Legal Officer I
📚የትምህርት ዓይነት እና ደረጃ
BA/BSc Degree in Management, Accounting, Economics, Computer Science or Law,related fields.
🇪🇹 የስራቦታ:- Addis Ababa
🧭የምዝገባ ጊዜ ፡ እስከ መስከረም
4/2015 ዓ.ም
🔔ስለ ስራው ሙሉ መረጃ ለማየት እና ለማመልከት ቀጣዩን ሊንክ ይጠቀሙ
https://jobs.amazonethiopia.com/job/tsehay-insurance-s-c-5/