አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
Create your Twitter account! #Share us your twitter account.
we will follow you‼️
We will follow you!
#Twitter
@ALE_lawsocieties
በቤት ኪራ ጭማሪ ለተሰቃየ መልካም ዜና!
የቤት ኪራይ መጨመር በህግ ያስቀጣል ላልሰሙት አሰሙ!

የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪን ለመገደብ በወጣ ደንብ ላይ የተሰጠ መግለጫ!

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በከተማችን የኑሮ ውድነት እየተባባሰ እንደመጣ የሚታወቅ ነው፡፡ የኑሮ ውድነቱ በአብዛኛው አሳማኝ እና ምንም አይነት ኢኮኖሚያዊ ምክንያት የሌለው በሰውሰራሽ ምክንያቶች የተፈጠረ ነው፡፡ የኑሮ ውድነቱም የከተማችንን ነዋሪ ለከፍተኛ ችግር ዳርጓል፡፡
በሰሜን የሃገራችን ክፍል ሃገር በማፍረስ ተግባር ላይ የሚገኘውን የአሸባሪው ህወሃት እንቅስቃሴ ለማክሸፍ እየተደረገ ካለው ዘመቻ ጋር ተያይዞ የከተማችን ነዋሪ በገንዘብ መዋጮ፤ ለሠራዊት የሚሆን ስንቅ በማዘጋጀት፤ ደም ልገሳ እስከ ህይወት መስዋዕትነት እየከፈለ ባለበት በዚህ ወቅት ጥቂት ስግብግብ ግለሰቦች በተቃራኒው ቆመው ከኢትዮጵያዊነት ጨዋነት ፍፁም ባፈነገጠ መልኩ አሁን ካለው ችግር ላይ አላግባብ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ የተለያዩ ተግባራት ውስጥ ገብተው ይገኛሉ፡፡
መንግሥት እያጋጠመ ያለውን ችግር ለመቅረፍ ከውጭና ከውስጥ ያሉ ጫናዎችን ተቋቁሞ ሀገር የማፍረስ ተግባር እንዲከሽፍና የዜጎች የኑሮ ጫና እንዲቀንስ የተለያዩ እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ ይገኛል፡፡
በዚህም መሠረት እስከታችኛው የማኅበረሰብ ክፍልን የሚያሳትፍ የኢኮኖሚ አሻጥሩን ለመቀልበስ የተቋቋመው ግብረይል በርካታ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡
በአጭር ጊዜ ውስጥም ግብረሃይሉ ባካናወናቸው ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች በመታየት ላይ ይገኛል፡፡
ከመሠረታዊ የፍጆታ ዕቃዎች ባሻገር አለግባብና የወቅቱን ሁኔታ ያላገናዘበ የቤት ኪራይ ጭማሪ የነዋሪውን ሕይወት በእጅጉ እየፈተነው ይገኛል፡፡
ይህም ወቅታዊ ሁኔታን በመጠቀም አላግብ ለመክበር የሚደረግ ከኢትዮጵያዊ ጨዋነትና መተሳሰብ ጋር በፍፁም የሚቃረን ተግባር ነው፡፡
በ2012 ዓ.ም የኮቪድ 19 ወረርሽ በሀገራችን መገኘቱ ተከትሎ በርካቶች ችግር ውስጥ በገቡበት ወቅት የከተማችን ነዋሪዎች እርስ በእርስ ከመረዳዳትና ማዕድ ከመጋራት አልፎ በርካታ ቤት አከራዮች የወራት የቤት ኪራይ ዋጋ ለተከራይ በራሳቸው ተነሳሽነት ቀንሰው ችግሩን በጋራ ለመፍታት ኢትዮጵያው የመረዳዳት እሴታችን የታየበት እንደነበር ይታወሳል፡፡
ይህም በወቅቱ በሕግ ተቀምጦ የነበረውን የቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር የሚከለክለውን ድንጋጌ ሳይጨምር ነው፡፡
አሳማኝ ባልሆነ ምክንያት በቤት ክራይ ላይ ዋጋ ጭማሪ መታየቱን ነዋሪዎች ቅሬታቸውን እያሰሙ ነው፡፡
ስለሆነም አሁን እየታየ ያለውን አላግባብ የሆነ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ ለመገደብ የነዋሪውን ቅሬታ ምላሽ ለመስጠት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በቀን 18/12/13 ባደረገው መደበኛ ስብሰባው የቤት ኪራይ ጭማሪን ለ90 ቀናት ለማገድ በቀረበ ደንብ ላይ ተወያይቶ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል፡፡
በዚህም መሠረት ደንቡ ከፀደቀበት 18/12/13 ዓ.ም ጀምሮ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋ መጨመርም ሆነ ተከራይን ከቤት ማስወጣት ለ90 ቀናት የተከለከለ ሲሆን በቀጣይም ታይቶ ለተጨማሪ ቀናት ክልከላው ሊራዘም ይችላል፡፡
ደንቡን በመተላለፍ ጭማሪ የተደረገበት ተከራይ አቤቱታውን በፅሑፍ ለወረዳው ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት በማቅረብ መፍትሄ እንዲያገኝ የሚቻልበት ሥርዓት በደንቡ ተደንግጓል፡፡
በዚሀ መሰረት በሚቀርቡ አቤቱታዎች ላይ ማጣራት ተደርጎ ጭማሪ ባደረገ አካል ላይ በደንቡ ተዘርዝሮ በተቀመጠው መሰረት ተጠያቂ የሚደረግ ይሆናል፡፡
ምንም እንኳን ይህ ደንብ የወጣው ዜጎችን ካላስፈላጊ ጫና ለመከላከልና ጥፋተኞችን ተጠያቂ ለማድረግ ቢሆንም ህብረተሰባችን በኮቪድ ወረርሽኝ ወቅት ችግሮችን በመተሳሰብና በመደጋገፍ ለማለፍ ያሳየውን ኢትዮጵያዊ የጨዋነትና አብሮነት እሴቶቹን በማዳበር ይህን ወሳኝና አስቸጋሪ ጊዜ በጋራ ማለፍን ማዕከል በማድረግ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ የከተማ አስተዳደሩ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
ነሐሴ 22 ቀን 2013
አዲስ አበባ፤
አዲስ አበባ ፕሬስ ሴክሬታሪያት
የውጭ ሀገራት አንድ ሉአላዊት ሀገር እርዱኝ ሳትል ወይም ሌላ አካል ጣልቃ ገብቶብኛል እርዳታ እፈልጋለሁ ባላለችበት ሁኔታ ጣልቃ ሊገቡ የሚችሉበት international treaty አለ?save human right issue
selam ale tena yisetelegn ebakihin erdata felege nwu yekebel bet wust nwu yeminorewu keasadageye gar eso condomiya dersat ena ene bete endagegn yemiyadergegn hig ale malet memerya ebakine
ቢያውቋቸው ሊጠቀሙባቸው የሚችሉ ወሳኝ #ድረገፆች

ኢንተርኔት እንደዓለም ዳርቻ እጅግ ጥልቅ በሆነበት በአሁን ሰዓት ሁሉንም የድረገፅ አይነት
አውቆ መጠቀም ምናልባትም በዓለማችን በሚገኙ እያንዳንዱ ቦታዎች ተዘዋውሮ
እንደመጎብኘት እጅግ ሊከብድ ይችላል፡፡ ታዲያ እነዚህ ጥበብን፣ እውቀትን፣ ልምድን እና
በጠቅላላውም ህይወትን ለመቀየር የሚያስችሉትን፤ ወሳኝ ድረገፆች አውቆ ለመጠቀም
የሌሎች ጠቋሚነት እጅግ ወሳኝ ሆኖ ሊገኝ ይችላል፡፡ በመሆኑም ለዛሬ ከዚህ በፊት
የማያውቋቸው ነገር ግን ከዚህ በኋላ ቢያውቋቸው እጅግ ሊጠቀሙባቸው የሚችሉ ድረ
ገፆችን ከተለያዩ ምንጮች አሰባስበናል፡፡
ያወቁትን ሌሎች እንዲያውቁት ብታደርጉ የበለጠ ያተርፋሉ!!!
1. ከሌላው ዓለም ህዝብ ጋር ጥበብን፣ አውቀትን እና ልምድን ለማጋራትና ለማንሸራሸር
MentalFloss.com
Lifehacker.com
https://www.quora.com/
https://medium.com/
Lumosity.com
2. አዲስ ነገር መማር ሲፈልጉ
• Make code (Microsoft MakeCode) {Must visit!}
• Guitar ( https://www.justinguitar.com/ ) {you can thank}
• Duolingo (Learn a language for free)
• Tutorials Point (Tutorials)
• Experiments with Google
3. ለግራፊክስ ዲዛይነሮች ከphotoshop ውጭ ሌላ አማራጭ ሲፈልጉ
• Free Pik ( https://www.freepik.com/ )
• Flaticon ( https://www.flaticon.com/ )
• Adobe colour picker (Adobe Color CC)
• Pexels ( https://www.pexels.com/ )
• Video Pexels (Free stock videos - Pexels Videos)
• Canva (Amazingly Simple Graphic Design Software
4. ከEmail ውጭ ሌላ አማራጭ ይኖር ይሆን ካሉ
www.bluebottle.com
http://mail.yahoo.com
http://gmail.google.com
www.hotmail.com
www.walla.com
5. የጤናዬ ጉዳይ ያሳስበኛል ካሉ
www.nelh.nhs.uk
www.hpa.org.uk
www.food.gov.uk
www.bmj.com
www.avert.org
6. ሲደብሮትና እና ራሶን ለማንቃት ሲፈልጉ
• Ted ( https://www.ted.com/
www.7billionworld.com
www.beesbeesbees.com
www.sanger.dk
✳️ ጠቃሚ የመጽሐፍ ድረ ገጾችን እንጠቁማችሁ

◽️ http://gen.lib.rus.ec/
ይህ ድረ-ገጽ ማንኛው አይነት መፅሀፍ ማውረድ የሚያስችሎት
ሲሆን በሚሊዮን የሚቆጠር መፅሀፎች አሉት በዉስጡ
ከሚግኙ መፅሀፎች መካከል
🔺የትምህርት መፅሀፎች፤
🔺የሳይኮሎጂ መፅሀፎች፤
🔺ፍልስፍና መፅሀፎች ፤
🔺የታሪክ መፅሀፎች ይገኙበታል፡፡

◽️ http://sci-hub.org/
ይህ ድህረ-ገጽ ከ64 ሚሊዮን በላይ የጥናት ወረቀት የሚገኝ ሰለሆነ በቀላሉ ማዉረድ ይቻለሉ፡፡ በዚህ ድረ- ገጽ የተለያዩ መጻፎች በተለያ ምርጫ እና አይነት ያገኛሉ።

◽️ https://bookboon.com/
ይህ ድረገጽ ማንኛው አይነት የነጻ መጻፍ የሚያገኝበት
ሲሆን በየትኛዉም የክፍል ደረጃ ላሉ ተማሪዎች አንዲዉም በማንኛው የስራ ሁኔታ ላይ ላሉ ሰዎች ጠቃሚ ድርገጽ ነው፡፡

◽️ http://bookzz.org/ ቡክዚ አለማችን ለይ ትልቅ የመጻሀፍ ላይብረሪ ያለው ሲሆን በአማካኝ 2.6 ሚሊዮን መጻሀፍ በ ድረገጹ ይገኛል።

ይህ ድረገጽ ብዙ የቴክኖሎጂ መጽሀፍት ያሉት ሲሆን የፕሮግራሚንግ፤ ግራፊክስ፤ የኮምፒተር አጠቃቀም እና
የተለዩ የትምህርት መጻሃፎች ያገኛ
የተለያዩ ኮርሶችን መማር እና ማወቅ ለምትፈልጉ በሙሉ ማለትም ለምሳሌ #Programming , #Web_Development , #Networking እና ሌሎችም...(ከታች ያሉትን ሳይቶች ይጠቀሙ)

1. www.codecademy.com
2. www.lynda.com
3. www.udemy.com
4. www.udacity.com
5. www.coursera.org
6. www.w3schools.com
7. www.thenewboston.org
8. www.programmr.com
9. www.codeavengers.com
10. www.codeschool.com
11. www.learnstreet.com
12. www.teamtreehouse.com
13. www.sqlzoo.net
14. www.codehs.com
15. www.teamtreehouse.com
16. www.html5rocks.com
17. www.codepen.io
18. www.sitepoint.com
19. www.tutorialspoint.com
20. www.javatpoint.com
21. www.cplusplus.com
22. www.learncpp.com
23. www.tutorialspoint.com
24. www.cprogramming.com
25. www.stackoverflow.com
26. www.learncodethehardway.org
27. www.bloc.io
28. www.howtocode.io
29. www.edx.org
30. www.instructables.com
31. www.developer.apple.com
32. www.developer.android.com
33. www.developers.google.com
34. www.developer.mozilla.org
35. www.msdn.microsoft.com
36. www.decompera.com
37. www.www.developphp.com
38. www.quackit.com
39. www.htmlite.com
40. www.siteduzero.com
41. www.dreamincode.net
42. www.phpbuddy.com
43. www.php.net
44. www.microsoftvirtualacademy.com
45. www.professormesser.com

ያወቁትን ማሳወቅ ብልህነት ነውና ጓደኞቻችንን አባል በመሆን ይጠቀሙ ዘንድ ጋብዙ። finally #Share
via Mastewal click Ethiopian law
NYALA INSURANCE S.C.

JOB TYPE Employee

JOB STATUS Full Time

ANNOUNCED

30 August, 2021

JOB TITLE; Legal Secretary

JOB LOCATION

Addis Ababa, Ethiopia

JOB PRESENTATION

Nyala Insurance Share Company (NISCO) wants to hire a qualified, competent, and motivated candidate for the following position on a permanent basis: 

Qualification and Experience:

 Diploma in Office Management and Secretarial Science

Two (2) years in office administration or secretarial function preferably in courts and/or insurance companies.

Post available. One

Duty station: Addis Ababa

Remuneration: 

Nyala Insurance offers a competitive and attractive remuneration package.

Age: Not more than 35

 Soft qualities required:

integrity, quick to respond, cooperative, and stress tolerance. 

VALID TILL 4 Sep, 2021
NYALA INSURANCE S.C.

Position: LEGAL SECRETARY

Job Time: Full-Time

Job Type: Permanent

Place of Work: Addis Ababa, Ethiopia

Application Deadline: Oct, 4/2021 (4 days left)

Nyala Insurance Share Company (NISCO) wants to hire a qualified, competent, and motivated candidate for the following position on a permanent basis: 

Qualification and Experience:

 Diploma in Office Management and Secretarial Science

Two (2) years in office administration or secretarial function preferably in courts and/or insurance companies.

Post available. One

Duty station: Addis Ababa

Remuneration: 

Nyala Insurance offers a competitive and attractive remuneration package.

Age:Not more than 35

 Soft qualities required:

integrity, quick to respond, cooperative, and stress tolerance. 

How to apply

Interested applicants who fulfill the above requirements are invited to submit their application with a non-returnable copy of CV and credentials to the under-mentioned postal address or in person at our HO (Protection House) 3rd floor Room No. 307 located around 22 Mazoria Mickey Leland Road.

N.B. Only short-listed applicants will be contacted and invited for an interview.
NYALA INSURANCE S.C. (NISCO) PROTECTION HOUSE P. 0. Box 12753 Addis Ababa
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
🔴🔴🔴አዲስ ወደዚህ ግሩፕ የምትገቡ ውድ ቤተሰብ እዚህ ግሩፕ ላይ ምንም ነገር ከመፃፋችሁ በፊት 5 ሰው ወደ ግሩፑ መቀላቀል አለባችሁ።🔴🔴🔴
 ሰብአዊ መብትን የሚያከብር መሆኑ፡- አሳልፎ የመስጠት ጥያቄ የቀረበለት አገር የቀረበለትን ጥያቄ በመቀበል ወይም በመከልከል ለሚሰጠው ውሳኔ የሚያገናዝባቸው ልዩ ልዩ መነሻዎች እንደሚኖሩ የሚጠበቅ ሲሆን በተለይ ተላልፎ የሚሰጠው ሰው የሰብአዊ መብት ጥሰት በተለይም ተላልፎ ከተሰጠ በኋላ ለአካላዊ ድብደባና ወ.ዘ.ተ ቅጣቶች የማይጋለጥ መሆኑን፣ በፍርድ ሂደትም ቢሆን ሊጠበቁለት የሚገቡ መሰረታዊ የሂደት መብቶች የሚጠበቁለት መሆኑን ማረጋገጥ የሚጠበቅበት ይሆናል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ ተፈላጊው ሰው የተፈለገበት መነሻ ዘሩን፣ ሀይማኖቱን፣ ዜግነቱን፣ ብሔሩን፣ የፖለቲካ አስተያየቱን ወይም ማሕበረሰባዊ መደቡን መሰረት ያደረገ ከሆነ ጥያቄው ውድቅ እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡ ስለሆነም የትብብር ጥያቄ በእነዚህ ላይ ተመስርቶ ያልቀረበ መሆኑን ማረጋገጥ አስፈላጊ ነው፡፡
 የተጠያቂውን አገር ሕግ ያገናዘበ መሆን፡- አሳልፎ የመስጠት ጉዳይ በዋናነት የሚወሰነው ትብብር በተጠየቀው አገር ሕግ እና ለጉዳዩ ተፈጻሚነት ባላቸው ስምምነቶች መሰረት ነው፡፡ በተለይ ግን አንዳንዶቹ ጉዳዮች ብዙውን ጊዜ የሚወሰኑት ትብብር በተጠየቀው አገር ሕግ መሰረት በመሆኑ የተጠያቂው አገር ሕግ በእነዚህ ጉዳዮች ላይ የሚደነግገውን ማወቅ ለውጤታማ ተላልፎ የመሰጠት ሂደት በጣም አስፈላጊና መሰረታዊ ነው፡፡ ይልቁንም ትብብር ጠያቂው አገርና ትብብር በተጠየቀው አገር የሚከተሉት የሕግ ሥርዓት (Legal System) የተለያየ ከሆነ የሕግ አሰራራቸው ይበልጥ የመራራቅ ዝንባሌ የሚኖረው በመሆኑ ከዚህ አንጻር የአገሩን ሕግ መገንዘብ አስፈላጊነቱ ከፍተኛ ነው፡፡ በተጠያቂው አገር ሕግ ውስጥ መገናዘብ ከሚገባቸው ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል ከአሳልፎ መስጠት ጉዳይ አንጻር መገናዘባቸው ይበልጥ አስፈላጊ የሆነው የሚከተሉት ናቸው፡-
• አሳልፎ የመስጠት ጥያቄ ሊከለከል የሚችልባቸው መነሻዎችን ማወቅ፤
• ተፈላጊው ሰው ተላልፎ እስኪሰጥ ድረስ በእስር ሊቆይ ስለሚችልበት ሁኔታ ወይም እንዳይጠፋ ሆኖ ስለሚቆይበት ሁኔታ ማወቅ፤
• አሳልፎ የመስጠት ጥያቄው ከሚቀርብበት ጊዜ ጀምሮ ተላልፎ እንዲሰጥ በመፍቀድ ወይም በመከልከል ውሳኔ እስከሚሰጥበት ጊዜ ድረስ ያለው ቆይታ ወይም ጊዜ ምን ያህል እንደሆነ ማወቅ፤
ለውጤታማ የአሳልፎ መስጠት ጥያቄና ሂደት አስፈላጊና መሰረታዊ ጉዳዮች ናቸው፡፡

 የገደብ መርሕን (rule of specialty) ማክበር፡- የገደብ መርሕ የሚባለው የተፈለገው ሰው በተላልፎ ይሰጠኝ ጥያቄ በግልጽ ተጠቅሶ ከተመለከተው የወንጀል ጉዳይ ውጭ በሌላ ወንጀል በትብብር ጠያቂ አገር እንዳይጠየቅና እንዳይከሰሰ እንዲሁም ያለ አሳልፋ ሰጭዋ አገር ፍቃድ ለሌላ ሦሥተኛ አገር ተላልፎ እንዳይሰጥ የሚከለከል መርሕ ሲሆን ለዚህም ትብብር ጠያቂው አገር በምታቀርበው የአሳልፎ ይሰጠኝ ጥያቄ ውስጥ ይህን መርሕ እንደምታከብር ማረጋገጫ መስጠት ይኖርባታል፡፡ ከዚህ ባሻገር የአሳልፎ ይሰጠኝ ጥያቄው በውስጡ ከሚይዘው የተላልፎ ይሰጠኙን የተመለከተ ዝርዝር ባሻገር እንደአስፈላጊነቱ መሟላት ያለባቸውን የፍርድ ቤት የመያዣ ትዕዛዝ ወይም ፍርድ ወ.ዘ.ተ. ሰነዶች፣ ከጥያቄው ጋር አብሮ ማቅረብ ይገባል፡፡

አሳልፎ መስጠትን በተመለከተ ከላይ የተነሱት ጉዳዮች እንደተጠበቁ ሆነው በዚህ ሂደት ውስጥ በተለይ ከፍተኛ ሚና ያላቸው አካላት እንደአገሩ ሁኔታ ልዩነት ቢኖርም ማዕከላዊ ባለስልጣን ሆኖ የሚሰራ የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ወይም ፍትሕ ሚኒስቴር፣ የፍርድ ቤቶች፣ ፖሊስና ማረሚያ ቤቶች ሚና ተጠቃሽ ነው፡፡ አሳልፎ የመስጠት ጉዳይን በተመለከተ የመወሰን ስልጣን እንደአገሩ ሁኔታ በአስፈጻሚው አካል ወይም በፍርድ ቤት ሊወሰን የሚችል ሲሆን አገራችንን በተመለከተ የአሳልፎ መስጠት ጉዳዮችን ጨምሮ በወንጀል ጉዳዮች ዓለም ዓቀፍ ትብብርን የማድረግ ስልጣን በአዋጅ ቁጥር 943/2008 መሰረት ለጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተሰጠ ነው፡፡ ሆኖም ጉዳዮቹን ከመወሰን አንጻር ተፈጻሚነት ያለው ሕግ የተሟላና በበቂ ሁኔታ ግልጽ እንዲሆን ማድረግ አስፈላጊ ነው፤ ለዚህም ወደፊት እንደሚጸድቅ የሚጠበቀው የወንጀል ስነ ስርአትና የማስረጃ ሕግ በረቂቁ የያዘው ጉዳይ ወሳኝነት የሚኖረው ይሆናል፡፡

በአገራችን ሁኔታ የአሳልፎ መስጠት ጥያቄ ሊቀርብ የሚገባው በአዋጁ መሰረት ለጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ሲሆን አገራችን ለሌሎች አገራት የምታቀርበው የአሳልፎ መስጠት ጥያቄ የሚቀርበውም በዚሁ አካል አማካኝነት ነው፡፡ ይሁን እንጂ የአሳልፎ መስጠት ትብብር ስኬታማ እንዲሆን የሌሎች ባለድርሻ አካላት ማለትም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የኢሚግሬሽን፣ ፍርድ ቤቶች፣ የብሔራዊ ኢንተርፖል፣ የፖሊስና ማረሚያ ቤት ተቋማት ሚና እጅግ ከፍተኛ ነው፡፡
የኢፌዲሪ ጠቅላ አቃቤ ህግ
https://t.me/NegereFej
Negere Feg
#ነገረ #ፈጅ
የሀገራት አለምአቀፍ ግንኙነት መርሆች
---------------------

ሰላም ጤና ይስጥልን ውድ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የፌስቡክ ገጽ ተከታታዮቻችን እንዴት ናችሁ ለዛሬ የሀገራት አለማቀፍ ግንኙነት መርሆዎች ምንድን ናቸው በሚለው ላይ አንድ ጥንቅር ወደ እናንተ ልናደርስ ወደናል ከወዲሁ መልካም ንባብ ተመኝን፡፡

1. የሀገራት ግንኙነትና የሚመራበት ህግ ማዕቀፍ

የአለም ሀገራት በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ግንኙነት ይፈጥራሉ፡፡ በተለይ በአሁኑ ወቅት የአለም ሀገራት የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር በጋራ የሚሰሩበት ወቅት ላይ እንገኛለን፡፡ የሀገራት ግንኙነት በኢኮኖሚ፣ ንድግ፣ በፖለቲካ ወይም በፀጥታ ዘርፍ በትብብር መስራት ላይ የተመሰረተ ሊሆን ይችላል፡፡

በሀገራት መካከል የሚደረግ ማናቸውም ግንኙነት የሚገዛው በአለምአቀፍ ህግ መሰረት ነው፡፡አለምአቀፍ ህግ ደግሞ የራሱ የሆኑ መርሆዎች፣ መብቶችና የሀገራት ግዴታዎች ያሉት ሰፊ ማእቀፍ ነው፡፡ አለምአቀፍ ህግ በተለያዩ የአለምአቀፍ ግንኙነት ዘርፎች ገዢ የሆኑ ድንጋጌዎችና ደንቦች አሉት፡፡የአለም አቀፍ ህግ ምንጭ በዋናነት የሀገራት የፅሁፍ ስምምነት (ሁለትዮሽም ሆነ ባለብዙ)፣ የዳበረና የታወቀ ልማድ፣ ጠቅላላ መርሆች እና እነዚህን የሚያረጋግጡ አለምአቀፍ ፍርዶችና የታወቁ ምሁራን ፅሁፎች ናቸው፡፡

2. የሀገራት ግንኙነት መርሆች ምንድን ናቸው?

እንያንዳንዱ ሀገር ትልቅም ሆነ ትንሽ፣ ደሀም ሆነ ባለፀጋ እኩል መብትና ግዴታ አለው፡፡ በተጨማሪም የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤትና የሚያስተዳድረው ግዛት አንድነት የማይደፈር፣ በሀገሩ ያሉ ሰዎችና ንብረት ላይ ሙሉ ስልጣን ያለው ነው፡፡ ከዚህም አንፃር የሚከተሉት የታወቁና የተጠበቁ የአለምአቀፍ ህግ ግንኙነት መርሆች ናቸው፡- ሁሉም ሀገራት እኩል መሆናቸው፣ ሀገራት ሉዓላዊ ስልጣን ያላቸው መሆናቸው፣ አለምአቀፍ ግንኙነቶችን በቅን ልቦና ማድረግ፣ በአንድ ሀገር የውስጥ ጉዳይ ማንም ጣልቃ መግባት አለመቻሉ፣ በአለምአቀፍ ግንኙነት ራስን በመከላከል ካልሆነ በቀር ሀይልን አለመጠቀም፣ አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ መፍታት የሚሉት ይገኙበታል፡፡

ሀገራት ግንኙነታቸውን እና በተለያዩ ጉዳዮች ያሉ ትብብራቸውን ለማሳለጥ በሁለትዮሽ ግንኙነትም ይሁን በባለብዙ ዘርፍ ግንኙነት በጋራ እየሆኑ አለምአቀፍ እና አህጉራዊ ድርጅቶችን መስርተው በጋራ ለመስራት ጥረት ያደርጋሉ፡፡ የማናቸውም ሀገራት ግንኙነት ከላይ በተመለከቱት አጠቃላይ የአለምአቀፍ ህጎች እና መርሆች የሚገዙ ናቸው፡፡ ማናቸውም ሀገር የሌላው ሀገር ሉአላዊነት፣ የግዛት አንድነት፣ የፖለቲካ ነፃነት፣ እኩልነት ማክበርና እና በውስጥ ጉዳይ ከመግባት መቆጠብ አለባቸው፡፡ አንድ ሀገር ከሌላ ሀገር ጋር ግንኙነቱ የሻከረ እንደሆነ ወይም አለመግባባት የተፈጠረ እንደሆነ ይህን ለማስተካከል ሰላማዊ በሆነ መንገድ በቀጥታ ወይም ሶስተኛ ወገንን ጨምሮ መነጋገርና ችግሮችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታት ከመጣር በዘለለ በሌላ ሀገር ጉዳይ ጣልቃ መግባት አይችሉም፡፡

በሌላ አገላለፅ በአንድ ሀገር ውስጥ አንድን ወገን መደገፍ ሌላውን መቃወም ወይም አንድ መንግስት ይህን አድርግ ይህን አታድርግ በማለት ኢኮኖሚያዊ ወይም ፖለቲካዊ ጫና ወይም ማእቀብ በመንግስት ላይ ማድረግ በአንድ ሀገር የውስጥ ጉዳይ በቀጥታ ጣልቃ መግባት ማለት ነው፡፡ አንድ ሀገር በሌላ ሀገር ውስጥ ጉዳይ ላይ በራሱም ሆነ ሌሎች ሀገራት ጫና እንዲያደርጉበት፣ እንዲያገሉት ወይም ግንኙነት እንዳያደርጉ ማድረግ ግልፅ የሆነ በውስጥ ጉዳይ ጣልቃ የመግባት እርምጃ እና የአለም አቀፍ ህግ ጥሰት ነው፡፡ ነገር ግን ሀገራት ከእነዚህ መርሆች ውጭ የተለያዩ ምክንያቶችን መነሻ በማድረግ በሌላ ሀገር የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ሲገቡ እና የተለያዩ ጫናዎችን ሲፈጥሩ ይስተዋላል፡፡ በተለይም ግብዣ ሳይቀርብና ፈቃድ ሳይሰጥ በአንድ ሀገር የውስጥ አስተዳደር ጉዳይ በመግባት እንዲህ አድረጉ ወይም እንደዚህ አታድርጉ በማለት በውስጥ ጉዳይ ውሳኔ አሰጣጥ ላይ ጫና ለመፍጠር የሚደረግ ጥረት አለምአቀፍ ህግን የጣሰ ተግባር ነው፡፡

በሌላ በኩል ሀገራት በፈቃዳቸው ያቋቋሙት እና አባል የሆኑበት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋነኛ አላማዎች ወይም ተግባራት መካከል አለምአቀፍ ሰላምና ፀጥታ ማስጠበቅ፣ የሀገራትን ወዳጅነት በሉአላዊ እኩልነት ላይ ተመስርቶ ማራመድ፣ የኢኮኖሚ ማህበራዊና ባህላዊ ችግሮችን ለመፍታትና ሰብአዊ መብቶችን ለማስከበር በትብብር መስራት ይገኙበታል፡፡ ከዚህ አንፃር በአንድ ሀገር ያሉ ሁነቶች አለምአቀፍ ሰላምና ጸጥታን የሚመለከቱ ከሆኑ ወይም በሁለት ሀገራት መካከል ያለ ግንኙነት አለምአቀፍ ሰላምና ፀጥታን የሚያደፈርስ ከሆነ ጉዳዩን በመመልከት ህጋዊ የሆነ መፍትሄ የመስጠት ሀላፊነት ይኖረዋል፡፡ አባል ሀገራትም በዚህ ማእቀፍ ውስጥ ለመስራት ይችላሉ፡፡

የሀገራት ግንኙነት ሊመራ የሚገባው በዚህ ማዕቀፍ ቢሆንም በአንድ ሀገር ውስጥ ሊከሰት የሚችለው ችግር አለምአቀፍ ሰላምና ፀጥታን የሚመለከቱ ጉዳዮች ባልሆነ ጊዜ የሀገራትን ግንኙነት መርሆችን ተከትሎ መንቀሳቀስ ላይ የወጥነት ችግር እና መርህን መሰረት አለማድረግ እንደ ችግር ይታያል፡፡ አለምአቀፍ ሰላምና ፀጥታን የሚመለከት ችግር ባጋጠመ ጊዜ የግጭቶች አካሄድ አለምአቀፍ ህግን ያከበረ እንዲሆን እና ወደ ጎረቤት ሀገሮች ግጭቶች እና ችግሮች ተስፋፍተው አካባቢያዊ ሰላምና ፀጥታን የሚያደፈርስ እንዳይሆን የመከታተልና የመደገፍ ስራ እንደ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ያሉ ተቋማት ሊሰሩ ይችላሉ፡፡ ከዚህም አንፃር ቢሆን የተባበሩት መንግስታት በጉዳዩ የሚመለከተው በአንድ ሀገር የውስጥ ጉዳይ ሳይሆን ሀገራት የገቡትን አለምአቀፍ ግዴታ ከማክበራቸው አንፃር እና የሀገራት እርምጃ ከአለም አቀፍ ሰላምና ፀጥታ መጠበቅ ላይ ከሚኖረው ተፅእኖ አንፃር ብቻ ሊሆን ይገባል፡፡

በሌላ በኩል የሰብአዊ መብት ጥሰቶች የሚያጋጥሙ ቢሆን የአንድ ሀገር የውስጥ ጉዳይ እና አለምአቀፍ ግዴታን የመወጣት ጉዳይ ነው፡፡ የሰብአዊ መብት ጥሰት ከፍ ያለ እና ስርአታዊ (systemic) መልክ ያለው ሲሆን የተባበሩት መንግስታት ችግሩን ለመቅረፍ ድጋፍና ትብብር እንዲያደርግ የሚጋብዝ ከሚሆን ውጪ አለምአቀፍ ሰላምና ፀጥታን የሚያናጋ እስካልሆነ ድረስ በስልጣኑ ስር የሚወድቅ ጉዳይ አይሆንም፡፡ በተመሳሳይ የሰብአዊ እርዳታ በምግብም ሆነ መጠለያ በስፋት ማስፈለጉ የአንድ ሀገር የውስጥ ጉዳይ ቢሆንም አለምአቀፍ ህብረተሰቡ ድጋፍ የማድረግ ሰብአዊ ግዴታ አለበት፡፡ ከዚህ አንፃርም የተባበሩት መንግስታት ድጋፍ ከማድረግ ባለፈ አንድን ሀገር ይህን አድርግ ይህን አታድርግ ለማስባል የሚበቃ አይደለም፡፡ ወደእዚህ ደረጃ ከፍ ሊል የሚችለው ችግሩ አለምአቀፍ የሰላምና ፀጥታ ችግር ወደ መሆን ደርሷል ወይም ሊደርስ ይችላል የሚባል ሲሆን ብቻ ነው፡፡

በመሆኑም ሀገራት በአለምአቀፍ ግንኙነታቸው አንዱ የሌላውን እኩልነት እና ሉአላዊነት ማክበር፣ በቅን ልቦና ግንኙነቶችን ማድረግ፣ በሌሎች ሀገሮች የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ አለመግባትና ጫና አለማድረግ ያስፈልጋል፡፡ የተባበሩት መንግስታት በበኩሉ የስልጣንና ሀላፊነት ወሰኑን በሚገባ በመጠበቅ አለምአቀፍ ሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ ማተኮር እና የአባል ሀገራትን እኩልነት እና ሉአላዊነት ማክበርና ማስከበር ይጠበቅበታል፡፡ በተጨማሪም ሀገራት አለምአቀፍ ግዴታቸውን ለመወጣት የሚያደርጉትን ጥረት የመደገፍ እና ሰብአዊ ድጋፍ የማድረግ አለምአቀፍ ግዴታውን በተቻለ መጠን ለመወጣት ጥረት ማድረግ ይኖርበታል፡፡
ውድ አንባቢያን ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁን የጹሁፍ ጥንቅር በዚሁ አበቃን በቀጣይ በሌላ ፕሮግራም እስክንገናኝ ሰላም፡፡
ጠ.አቃቤ ህግ #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
Forwarded from Bayissa Lemessa
How are you my fellow friends and lawyers, I call you for your help. Do you have any knowledge that succession ( ውርስ) have period of limitation. I am confronting with some which say since the period of limitation for the succession is lapsed the claim for the succession should have be dismissed. I lack any legal provision either to support or opposite the argument provided to me
አሸብር_አውዴ_ከ_ደቡብ_ብሔሮች_ብሔረሰቦችና_ሕዝቦች_ብሔራዎ_ክልላዊ_መንግስት_የወላይጋ_ምድብ_ዓቃቤ_ሕግ.pdf
719.5 KB
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰበር ሰሚ ችሎት ሰኔ 30 ቀን 2013 ዓ.ም በዋለው ችሎት በመዝገብ ቁጥር 189472 “ክስ ወደ ሌላ ሥፍራ ይዛወርልኝ (Change of venue)” ላይ የቀረበን የሰበር አቤቱታ መርምሮ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ የውሳኔ ግልባጩን ለግንዛቤ እንዲሆናችሁ እንዲህ አካፈልናችሁ፡፡
ሰበር‼️ መልካም ዜና! ኑሮ ውድነት ላስጨነቀው!
ስንዴ፣ ዘይት፣ ስኳር እና ሩዝ ከቀረጥና ታክስ ነጻ እንዲሆኑ ተወሰነ!
የዋጋ ንረት በህብረተሰቡ ላይ የሚያሳድረውን ጫና ለመቀነስ ስንዴ፣ ዘይት፣ ስኳር እና ሩዝ ከቀረጥና ታክስ ነጻ እንዲሆኑ መወሰኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የገንዘብ ሚኒስትር ዲኤታ ዶክተር ኢዮብ ተካልኝ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፥ ወሳኝ በሆኑ ሸቀጦች ላይ ቀረጥና ታክስ ማሻሻያ መደረጉን ተናግረዋል።
በመግለጫቸውም ፖስታ እና ማካሮኒ የጉምሩክ ቀረጡ እንዳለ ሆኖ ተጨማሪ እሴት ታክስ እንደተነሳላቸውም ነው የተናገሩት።

ስንዴ፣ ዘይት፣ ስኳር እና የሩዝ ምርቶች ከውጭም ሆነ ከሃገር ውስጥ ግዥ ሲፈጸም ከማንኛውም ቀረጥ ነጻ እንዲሆኑ ተወስኗልም ብለዋል በመግለጫቸው።
ከዚህ ባለፈም በዶሮ እንቁላል ላይ የነበረው ተጨማሪ እሴት ታክስ ፍላጎት እና አቅርቦት እስከሚጣጣም ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ ሆኖ ለገበያ እንዲቀርብ ተወስኗልም ነው ያሉት።
ይህም ከዛሬ ጀምሮ ለሚመለከታቸው መስሪያ ቤቶች እና አስፈጻሚ አካላት መመሪያ መተላለፉን አንስተዋል።
ሚኒስትር ዲኤታው በመግለጫቸው የፍራንኮ ቫሉታ ፈቃድ በመራዘሙ ምርት ማስገባት የጀመሩ መቀጠል እንደሚችሉም ጠቁመዋል።
ፋና BC.
#Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
Junior Attorney
#nile_insurance_sc
#legal_services
#law
#attorney
Addis Ababa

LLB Degree in Law or related field of study

Minimum Years Of Experience: #0_years

Deadline: September 11, 2021

How To Apply:
In person at Nile Insurance SC Head Office, located at Gotera area, around Nation and Nationalities square, to Human Resource Management Division 3rd floor. For additional information contact Tel. 0114426000