አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
በወንጀል ክርክር ወቅት የመስቀለኛ ጥያቄ መጠየቂያ መርሆችና ቴክኒኮች
===========https://t.me/lawsocieties
ዐቃቤህግ በመደበኛ የወንጀል ክስ ለመስቀለኛ ጥያቄ ሂደት ሲቀርብ ስለጉዳዩ በተለይም ስለምስክርነቱ አስቀድሞ ሳይዘጋጅ ማለትም ዕዉቀት ሳይኖረዉ ነዉ:: መስቀለኛ ጥያቄ ሂደት እንኳንስ ያለቅድመዝግጅት ዝግጅትም ተደርጎ አስቸጋሪ ሥራ ነዉ:: የመከላከያ ምስክሮች ከመዋሸት እስከ ሆን ብሎ አለማስታወስ ድረስ መሰናክል ሊፈጥሩ ይችላሉ:: በመስቀለኛ ጥያቄ ሂደቱ ለዐቃቤህግ ተባባሪ ላይሆኑ ይችላሉ:: ስለዚህ ዐቃቤህግ በዚህ ሂደት ለማግኘት የሚፈልገዉን ምናልባትም ሊያገኝ የሚገባዉን ያለማግኘት ችግር ሊያጋጥመዉ ይችላል:: እንዲያዉም የራሱን ክስ ሊጎዳ የሚችል አጋጣሚ ሊፈጠር ይችላል:: ስለዚህ መስቀለኛ ጥያቄን ለማካሄድ ወይም ላለማካሄድ በከፍተኛ ጥንቃቄ መምረጥ አና ማካሄድ የግድ ነዉ:: ለዚህ ደግሞ አንዳንድ መርሆችንና ቴክኒኮችን ማወቅ ተገቢ ነዉ:: እነዚህ መርሆችና ቴክኒኮች በአሰራር ልማድ የምንፈጥራቸዉን ችግሮች ለማረም እገዛ ሊያደርጉ የሚችሉ ናቸዉ:: እነዚህን ቆየት ብለን የምናያቸዉ ሆኖ ከዚያ በፊት ስለመስቀለኛ ጥያቄ ሂደት ወሰን እና መጠን አንዳንድ ነገሮች እንይ::
በቅድሚያ ከላይ እንደተገለጸዉ መስቀለኛ ጥያቄ አስቸጋሪ ሂደት ነዉ:: አደጋዎቸ አሉት:: ስለዚህ መስቀለኛ ጥያቄ ማከሄድ ተመራጭ ላይሆን ይችላል:: መስቀለኛ ጥያቄ አለማካሄድ ምን ዉጤት አለዉ? በወ/መ/ህ/ሥ/ሥ/ቁ. 140 እንደተመለከተዉ መስቀለኛ ጥያቄ አለመጠየቅ በሌላዉ ወገን የተነገረዉን እንደማመን አያስቆጥርም:: ስለዚህ መስቀለኛ ጥያቄ ብዙም ባይደፈር ይመረጣል:: በተለይም የመስቀለኛ ጥያቄ ግብ ከሆኑት (የተቃራኒን ምስክርነት የማይታመን መሆኑን ማሳየት በክሱ ላይ የደረሰዉን ጉዳት ማስተካከል ወዘተ) አንዱን ወይም ከዚያ በላይ ለማሳካት የምንችል ወይም ተገቢ ካልሆነ በቀር ወይም ምስክሩ ለጉዳያችን የምንፈልገዉ መረጃ ብቸኛ ምንጭ ካልሆነ በቀር መስቀለኛ ጥያቄ ማካሄድ የሚመከር አይደለም::
ሆኖም ዘወትር እንደሚስተዋለዉ አንዳንድ ምስክሮች ባህሪያቸዉ ምንም ሳይጠየቁ መሄድ የለባቸዉም የሚያስብል ይሆናል:: በዚህ ጊዜ መስቀለኛ ጥያቄ ማንሳት የግድ ከሆነ ከላይ ሲባል እንደነበረዉ አደጋዉ የበዛ በመሆኑ መጠኑን ማሳነስ ይመከራል::
በወ/መ/ህ/ሥ/ሥ/ቁ. 137(3) ስር መስቀለኛ ጥያቄ በዋና ጥያቄ ጊዜ በተመለሱ ነገሮች ዉስጥ ያለዉን ስህተት አጠራጣሪ ወይም የማይታመን ቃል ለፍርድ ቤቱ ለመግለጽ ወይም ለማስተባበል የሚደረግ መሆኑ ተደንግጓል:: ስለዚህ ከዚህ የወጣ ጥያቄ ሲነሳ ተቃዉሞ ሊገጥም ይችላል:: ሆኖም በዋና ጥያቄ ከተፈጠረዉ ድንበር ወጥቶ መጠየቅ የሚቻልባቸዉ የተለዩ አጋጣሚዎች ይኖራሉ:: ለምሳሌ የምስክሩን ተዓማኒነት የሚመለከቱ ጥያቄዎች በዋና ጥያቄ ጊዜ ባይነሱም በጠቅላላዉ ምስክሩ የተናገረዉን ነገር ተዓማኒነት የሚመለከት ስለሚሆን ተቀባይነት ያለዉ አካሄድ ነዉ:: ለምሳሌ የተለመደዉ የተከሳሽ መከላከያ ክርክር (በወንጀሉ ጊዜ በወንጀሉ ቦታ አልነበርኩም) ሲቀርብ የሚነገረዉ ታሪክ የተፈጸመበትን ጊዜ ከወንጀሉ ጊዜ ጋር እንዲገጥም የማድረግ ነገር ስለሚኖር ምስክሩ ጊዜን በመለየት ረገድ ስላለዉ ችሎታ ለማረጋገጥ በዚህ ዙሪያ ጥያቄ ቢነሳ ሊከለከል አይገባም:: ምስክሩ ተዓማኒነቱ ምን ያህል እንደሆነ ለማሳየት የሚረዳ በመሆኑ ተገቢ ነዉ::

ከተዓማኒነት ጋር በተያያዘ ምስክሩ በነገሩ ዉስጥ ያለዉ ጥቅም ወይም ፍላጎት ሊታለፍ የማይገባዉ ነጥብ ነዉ:: ምስክሩ የሚሰጠዉ ምስክርነት ከነገሩ ዉስጥ ካለዉ ጥቅም ወይም ፍላጎት የተነሳ ከዕዉነት የራቀ ሊሆን ይችላል:: ስለዚህ በነገሩ ዉስጥ ጥቅም እንዳለዉ ማሳየት በሰጠዉ ምስክርነት ላይ ዕምነት እንዲታጣ ሊያደርግ ስለሚችል በዋና ጥያቄ አልተነሳም ተብሎ ቀሪ ሊደረግ አይገባም::
አንዳንዴ ምስክሩ ራሱ ለመስቀለኛ ጥያቄ በሚመልስበት ጊዜ በዋና ጥያቄ ጊዜ ላልተነሱ ሀሳቦች መንገድ ሊከፍት ይችላል:: በዚህ ጊዜ ምስክሩ ራሱ ባነሳዉ ነገር ላይ ሌላ መስቀለኛ ጥያቄ የማይጠየቅበት ምክንያት አይኖርም:: ስለዚህ ዐቃቤህግ እነዚህን አጋጣሚዎች በንቃት መጠባበቅ ይገባዋል፣ ለዚህም ምስክርነቱን በሚገባ ማዳመጥ ይኖርበታል፡፡
ከጭብጥ ከመዉጣት ሌላ በመስቀለኛ ጥያቄ ሂደት የማይፈቀድ ነገር ምስክርን ማስፈራራት እና ማንጓጠጥ ነዉ:: ምስክሩ ዐቃቤህግ የሚፈልገዉን እንዲል መገደድ የለበትም:: ይህን ማድረግ የሚቻለዉ ክህሎት በተሞላዉ የአጠያየቅ ዘዴ መሆን አለበት:: አዘዉትሮ በፍርድቤቶች በሚደረግ ክርክር ጊዜ የሚስተዋል በህግ ባለሙያዎች (ዐቃብያነህግ ጠበቆች ዳኞች) የሚባል አንድ ነገር አለ:: ምስክሩ እነዚህ ባለሙያዎች እንደፈለጉት ወይም ዕዉነት ነዉ ብለዉ እንደሚያስቡት ሳይናገር በቀረ ጊዜ በሃሰት መመስከር በወንጀል እንደሚያስቀጣ ይነግሩታል:: ይህ ነገር ማስፈራራት ከመሆኑ በተረፈ ነገሩ ተሰምቶ ሳያልቅ እና ምስክሩ የተናገረዉ ሃሰት ይሁን ዕዉነት ሳይረጋገጥ በጉዳዩም ላይ በምስክሩም ላይ ፍርድ የመስጠት ያህል ይሆናል:: ከዐቃቤህግ የህግ ጠባቂነት ሚና አኳያም የሰዉን መብት የሚደነግጉ ህጎችን የመጣስ ዉጤት ይኖረዋል::

የመስቀለኛ ጥያቄዎች ባህሪያት (መሪ ጥያቄ)፡-- ይህ የጥያቄ አይነት በመስቀለኛ ጥያቄ ሂደት ዉስጥ በህግ የተፈቀደ ቢሆንም ዐቃቤህግ (ሌሎች ባለሙያዎችም) ሲጠቀሙበት አይስተዋልም:: በርግጥ ይህ የጥያቄ አይነት ስለሚያስከትለዉ መልስ ማወቅን ስለሚጠይቅና ዐቃቤህግ ደግሞ ከላይ እንደተገለጸዉ ያለቅድመዝግጅት ስለሚቀርብ ይህን የጥያቄ አይነት ለመጠቀም አይደፋፈርም:: ሆኖም ዋና ጥያቄ የሚመስል ሂደት በማካሄድ ነገሮችን እንዲደገሙ ከማድረግና በዚህም ችሎትን ከማሰላቸት ግፋ ሲልም የዐቃቤህግን ክስ የሚያፈርስ አጋጣሚ ከመፍጠር በዚያዉ በችሎት በተደረገች ዝግጅትም ቢሆን መሪ ጥያቄ በመጠየቅ ምስክሩን እንዳሻዉ እንዳይናገር መቆጣጠር ይመከራል:: በመስቀለኛ ጥያቄ ሂደት ዋናዉ ግብ ምስክሩን መቆጣጠር የሚመሰክረዉን ነገር መወሰን በዚህም ለመዋሸት ያለዉን ዝንባሌ ወዘተ ማስቀረት ነዉ:: በዋና ጥያቄ ጊዜ ሊነሱ የሚገባቸዉ ዝግ ያልሆኑ ጥያቄዎችን በማንሳት ምስክሩ የሚናገረዉን ነገር ልቅ ማድረግ ሂደቱን ዐቃቤህጉ ሳይሆን ምስክሩ እንዲቆጣጠረዉ ማድረግ ይሆናል::

አጭርና ነጠላ ጥያቄ፡- የተከሳሽን ምስክር በመስቀለኛ ጥያቄ መቆጣጠር የሚቻልበት መንገድ ጥያቄዉን መሪ ጥያቄ በማድረግ ብቻ አይደለም:: ጥያቄዉን አጭር ማድረግም እንዲሁ በምስክሩ ላይ የበላይነትን ያስገኛል:: ጥያቄዉ ከአንድ በላይ ሃሳብ ከሌለዉ እና ርዝመቱም አጭር ከሆነ ምስክሩ ለዚሁ ብቻ መልስ እንዲሰጥ ሰለሚገደድ ብዙም መፈናፈኛ አይኖረዉም:: በተለይ ከአንድ በላይ ሃሳብ አለመያዙ ምስክሩ መርጦ የመመለስ ስራ እንዳይሰራ ያደርገዋል የመልሱ ወሰን የታጠረ ይሆናል::
ከዚህ በተያያዘ ከአንድ በላይ የሆኑ ጥያቄዎችን አነባብሮ በአንድ ጊዜ መጠየቅ የሚገኘዉን መልስ ግልጽ እንዳይሆን ያደርገዋል:: አንድ መልስ ቢሰጥ ለየትኛዉ ጥያቄ እንደተመለሰ ማወቅ አይቻልም:: ስለዚህ እንደዋና ጥያቄ ጊዜ በአንድ ጊዜ አንድ ጥያቄ ብቻ ማንሳት ተገቢ ይሆናል::
መልሱ የሚታወቅ (የሚረጋገጥ) ጥያቄ፡- የመስቀለኛ ጥያቄ መልሱ የሚታወቅ ወይም ማስረጃ ሊቀርብበት የሚችል መሆን ይኖርበታል:: ግን ቀደም ሲል እንደተገለጸዉ ትልቁ ችግር ስለመከላከያ ምስክርነትም ሆነ ስለምስክሩ አስቀድሞ የሚሰበሰብ ማስረጃ የለም:: ስለዚህ የዐቃቤህግ መስቀለኛ ጥያቄዎች በዕድል ባወጣ ያዉጣዉ ወዘተ ላይ ተመስርተዉ የሚጠየቁ ናቸዉ:: ሆኖም ማስረጃ በተሰበሰበባቸዉ አጋጣሚዎች ለምስክሩ የሚቀርብ መስቀለኛ ጥያቄ ሊመለስ የሚገባዉን መልስ የሚጠቁም ሊሆን ይገባል:: ለዚህ ጥያቄ የሚሰጠዉ መልስ ምንም ይሁን ምን በቂ ስለሚሆን የሚገኘዉ መልስ ምንነት ስጋት አይፈጥርም:: የሚፈለገዉን መልስ ምስክሩ አመነም አላመነም ዉጤቱን አይቀይረዉም:: ምክንያቱም ቢያምን ዐቃቤህግ እንደሚፈልገዉ ሆነለት ማለት ሲሆን ከካደ ደግሞ ማስረጃ ስላለ ምስክርነቱን ማስተባበልና በዚህም ምስክሩ ተዓማኒነት የሌለዉ መሆኑን ማሳየት ይቻላል::

የመስቀለኛ ጥያቄዎች አደረጃጀት፡- ዉጤታማ መስቀለኛ ጥያቄ በጥያቄዎች አይነት ብቻ የሚወሰን አይደለም:: የጥያቄዎቹ ቅደም ተከተልም (ቅንብር) የራሱ አስተወጽዖ ይኖረዋል:: በተለይ በመስቀለኛ ጥያቄ ጊዜ ምስክሩን በሚገባ መቆጣጠር እጅግ አስፈላጊ ከመሆኑ አኳያ የጥያቄዎቻችን አወቃቀር ይህን የመቆጣጠር ችሎታ የሚያሳጣ መሆን የለበትም:: ስለዚህ የተቃራኒ ወገንን ምስክር የምንጠይቅ እንደመሆኑ በቀላሉ የምንፈልገዉን ነገር ለማግኘት አስቸጋሪ ስለሚሆን የጥያቄዎቻችን አወቃቀር የምስክሩን ወዳጅነት የሚያስገኝ እንዲሆን የግድ ነዉ::
ዐቃቤህግ መስቀለኛ ጥያቄ ሊጠይቅ ከወሰነ በዚህ ጥያቄ ሊያሳካ የፈለገዉን ነገር በሂደቱ መጀመሪያ ላይ መግለጽ የለበትም:: ይህ ግብ በምስክሩ ከታወቀ የተቃራኒ ወገን ምስክር እንደመሆኑ የመስቀለኛ ጥያቄዉ ሂደት ወደዚህ ግብ እንዲደርስ መፍቀዱ አጠራጣሪ ነዉ:: ስለዚህ ይህን ግብ የሚደብቅ የጥያቄዎች ቅደምተከተል መኖር አለበት::
ከዚህ የተነሳ በመነሻዉ ላይ የሚጠየቁ ጥያቄዎች ከምስክሩ ጋር ፍጥጫን የማያስነሱ ምስክሩ በቀላሉ ሊያምናቸዉ ወይም ሊስማማባቸዉ የሚችሉ ፍሬነገሮችን የሚመለከቱ መሆን ይገባቸዋል:: ይህን ማድረግ በዐቃቤህጉና በተከሳሽ ምስክር መካከል ሰላማዊ ሁኔታ ይፈጥራል:: ስለዚህ ከምስክሩ የሚፈለገዉን ለማግኘት ቀላል ይሆናል ቢያንስ ምስክሩ መሰናክሎችን ከመፍጠር ይታቀባል::
ይህ ማለት ደግሞ ዐቃቤህግ ለክሱ እጅግ አስፈላጊ የሚላቸዉን ነጥቦች መጀመሪያ ላይ ማንሳት የለበትም ማለት ነዉ:: እነዚህን ጉዳዮች ከመነሻዉ ከገለጸ ምስክሩ የመስቀለኛ ጥያቄዉን ዓላማ በቀላሉ ማወቅ ስለሚችል እና ይህም ምስክሩ በዋና ጥያቄ ጊዜ ከተናገረዉ ሊቃረን ስለሚችል ምስክሩ ይህን የተፈለገ ነገር ለመስጠት አይፈቅድም:: በሚችለዉ መንገድ ራሱን ከመቃረን ለማዳን የማስተካከያ መረጃዎችን ከመግለጽ ያለፈ ነገር ለመፈጸም ፈቃደኛ እንዳይሆን ያደርገዋል:: ስለዚህ ዐቃቤህግ መነሻዉ ላይ ከዋና ጥያቄ ሂደት በተቃራኒ ዋና ነጥቦችን ሳይሆን ዝርዝር ጉዳዮችን (በተቻለ መጠን ምስክሩ የማይክዳቸዉን) እንዲያነሳ ይመከራል::
ከዚህ ሌላ ዐቃቤህግ የመስቀለኛ ጥያቄ ዓላማዉን ለመደበቅ በጥያቄና መልሱ ሂደት ጊዜ ከአንድ የጥያቄ ሃሳብ ወደሌላዉ በመዝለል ምስክሩ የነገሩን አቅጣጫ እንዳይገነዘብ ማድረግ ይችላል:: ለዚህም ጥያቄዎቹ በተለያየ ርዕስ ስር እንዲደራጁ ሊያደርግ ይገባል:: ከዚህ ጋር በተያያዘ የአካባቢ ማስረጃን አስመልክቶ ከዋና ጥያቄ ጋር በማያያዝ ያነሳነዉ ሃሳብ ለመስቀለኛ ጥያቄም አግባብነት ይኖረዋል:: በመስቀለኛ ጥያቄ ጊዜ ዓላማዉ ምስክሩ የዐቃቤህግን የክርክር አቅጣጫ እንዳይገነዘብ ማደረግ በመሆኑ የአካባቢ ማስረጃን የሚመለከቱ ጥያቄዎች እነዚህን ማስረጃዎቸ በአንድ ላይ የማሰባሰብ ባህሪ እንዳይኖራቸዉ ማድረግ ያስፈልጋል:: ምክንያቱም ከተሰባሰቡ ትርጉማቸዉ ግልጽ ስለሚሆን ምስክሩ የክርክሩን አቅጣጫ በቀላሉ እንዲረዳዉ በማድረግ መሰናክል እንዲፈጥር ይገፋፋዋል:: ስለዚህ መስቀለኛ ጥያቄዎች የአካባቢ ማስረጃዎች እንዲበታተኑ የማድረግ ችሎታ ሊኖራቸዉ ይገባል:: ለዚህም ከላይ እንደተመከለተዉ የጥያቄዎችን ቅድም ተከተለ በማዘባረቅ ከርዕስ ወደርዕስ መዟዟር አስፈለጊ ነዉ::
ከጥያቄዎች ቅደም ተከተል ጋር በተያያዘ አዘዉትሮ የሚታይ ስህተት አለ:: በመስቀለኛ ጥያቄ ጊዜ ምስክሩ ሊክዳቸዉ የማይችሉ ፍሬነገሮችን መሰረት በማድረግ ዐቃቤህግ ለሚያቀርባቸዉ ጥያቄዎች በሚገኙ መልሶች የሚገነባ ታሪክ ሊኖር ይችላል:: ከዚህ በኋላ የዚህን ሁሉ ጥያቄና መልስ እንድምታ (ድምዳሜ) ምስክሩ እንዲናገር ከተጠየቀ መልሱ የተከሳሹን ክርክር የሚጎዳ ከመሰለዉ ወይም ከሆነ ምስክሩ የጥያቄዉ አቅጣጫ ሰለሚገባዉ ቀደም ሲል የሰጣቸዉን መልሶች የሚያስተካክል መልስ ሊሰጥ ስለዚህ ለክሱ የሚረዳዉን ነገር የመደበቅ ተግባር ሊፈጽም ይችላል:: ይህም እንኳ ባይሆን ተከሳሹ ወይም ጠበቃዉ በክርክሩ ላይ በመስቀለኛ ጥያቄ ጊዜ የደረሰዉን ጉዳት በድጋሚ ጥያቄ ጊዜ የማስተካከል ስራ እንዲሰራ የማባነን ዉጤት ይኖረዋል:: ይህም ካልሆነ ፍርድቤቱ ራሱ በማጣሪያ ጥያቄ ጊዜ ነገሩን እንዲያነሳ ምስክሩም በዚህ አጋጣሚ ነገሩን የሚያድበሰብስ ወይም የሚያርም ተግባር እንዲፈጽም የማስታወስ ዉጤት ይኖረዋል:: በተግባር ሲደረግ የሚስተዋለዉም እንዲህ ያለ ዉጤትን የሚያመጣ አጠያየቅ ነዉ::
ስለዚህ ይህን የነገሩን ማሰሪያ ጥያቄ ዐቃቤህግ መጠየቅ የለበትም:: ቀላልና ተራ በሚመስሉ ጥያቄዎች የተገነባዉ ታሪክ እንድምታ ለፍርድቤቱ የሚተዉ ነዉ:: ምናልባት ለፍርድቤቱ ግልጽ የማይሆን ቢሆን በመስቀለኛ ጥያቄ የተሰጡ መልሶች የሚጠቁሙት ድምዳሜ ምን እንደሆነ በክርክር ማቆሚያ ንግግር ጊዜ መግለጽ ይቻላል::
ነገር ግን አሁን ባለዉ አሰራር ይህ ከላይ የተመለከተዉ የአሰራር አቅጣጫ ምን ያህል ያስኬዳል? የሚል ጥያቄ ማንሳት ተገቢ ነዉ:: ምክንያቱም የክርክር መዝጊያ ንግግር ወይም በተለምዶ አጠራሩ የመፋረጃ ሃሳብ እንዲቀርብ የሚያደፋፍሩ ፍርድቤቶች ጥቂት ከመሆናቸዉም በላይ እንዲቀርብ የሚያደርጉትም ቢሆኑ በአብዛኛዉ በጽሁፍ እንዲቀርብ የሚያደርጉ ሰለሆነ እንዲሁም የቀረበዉን ሃሳብ የሚጠቀሙበት ማለትም በዉሳኔ ጊዜ ከግምት የሚያስገቡት ፍርድቤቶች በእጀጉ ጥቂት በመሆናቸዉ ዐቃቤህግ በመስቀለኛ ጥያቄ ጊዜ ያስመሰከራቸዉ ፍሬነገሮች ድምር ዉጤት ምን እንደሆነ በክርክሩ ጊዜ (በመስቀለኛ ጥያቄ ማጠናቀቂያ ጊዜ) ካልጠቆመ እንዲህ የሚያደርግበት መድረክ አያገኝም:: ከዚህ የተነሳ ዐቃቤህግ ከተከሳሽ ምስክር ጋር በመስቀለኛ ጥያቄ ሂደት ዉስጥ ወይም ማሳረጊያ ላይ የምስክርነቱን እንድምታ እመን አትመን እሰጥ አገባ ዉስጥ ሲገባ ይታያል:: ስለዚህ ፍርድቤቶች የክርክር ማቆሚያ ንግግርን አሰራር እንዲያከብሩ ዐቃቤህግ መወትወት ዳኞችም ይህን አሰራር ባህል እንዲያደርጉት የግድ ነዉ::
ከዚህ በላይ ያየናቸዉ የጥያቄ አደረጃጀት ስራዎች ብቸኛ አይደሉም:: በርከት ያሉ በተለያዩ በለሙያዎች የሚቀርቡ ዘዴዎች አሉ:: ሆኖም ከላይ ያነሳናቸዉ ዘዴዎች ከኛ የአሰራር ልምድ ጋር ቁርኝት ስላላቸዉ ሊጠቀሱ በቅተዋል::
ሌሎች ቴክኒኮች፡- በመስቀለኛ ጥያቄ ጊዜ ቅድመዝግጅት ካለ ጥያቄዎችን በጽሁፍ አዘጋጅቶ የመቅረብ ነገር ሊኖር ይችላል:: ነገር ግን እንዲህ አይነቱ አቀራረብ መልካም አይደለም:: ጥያቄዎቹ በጽሁፍ ከተዘጋጁ ወይ እያነበቡ ለመጠየቅ ነዉ አለያም ሸምድዶ ከሃሳብ እያስታወሱ ለመጠየቅ ነዉ:: ሁለቱም ተመሳሳይ ናቸዉ:: ወረቀት ላይ የምናተኩር ከሆነ ወይም በአዕምሯችን ስለምናስታዉሰዉ ነገር የምናስብ ከሆነ ምስክሩን ዓይንለዓይን አንገናኝም ማለት ነዉ:: በመስቀለኛ ጥያቄ ጊዜ ከምስክሩ ጋር የዓይንላይን ግንኙነት መኖር ምስክሩን ለመቆጣጠር ይረዳል:: ከዚህም ሌላ ያልተጠበቁ ለክሱ የሚጠቅሙ አጋጣሚዎችን ለመጠቀም በጥያቄና መልሱ ሂደት ላይ ትኩረት ማድረግ ያስፈልጋል:: ጥያቄን ከወረቀት ላይ ወይም ከአዕምሮ ዉስጥ ማንበብ ይህን አትኩሮት ስለሚነፍግ በዚህም ረገድ ዐቃቤህግ ብሎም ክሱ ተጎጂ ይሆናሉ:: በተለይ ጥያቄዉ በርከት ያለ ከሆነ አንዱ ጥያቄ ተመልሶ ሌላ ለመጠየቅ በዝርዝሩ ዉስጥ የሚቀጥለዉ ጥያቄ ቦታ እንዳይጠፋ በማሰብ አትኩሮትን ወደዚሁ ጽሁፍ ለማድረግ መገደድ ይኖራል::
ከዚህ የተሻለዉ አማራጭ ጥያቄዉን በዝርዝር አለመጻፍ ነዉ:: ዝግጅቱ የግድ በጽሁፍ መሆን ካለበት የጥያቄዎቹን ሃሳቦች የያዙ ርዕሶችን ዝርዝር (አዉትላይን) አዘጋጅቶ መቅረብ ይመረጣል:: ርዕሶቹን ብቻ ከወረቀቱ ላይ በመመልከት ጥያቄዎቹን ከራስ ማመንጨት ይገባል::

አትኩሮትን ወደጥያቄና መልሱ ሂደት ማድረግ ተገቢ ስለመሆኑ ከፍ ብሎ ተጠቅሷል:: ከዚህ በተያያዘ ለመሰቀለኛ ጥያቄ የሚሰጡ መልሶችን ዐቃቤህግ ማድመጥ ይኖርበታል:: ለክሱ ገንቢ የሆኑ አጋጣሚዎችን ለመጠቀም የሚረዳ ከመሆኑም በላይ ምስክሩ ጥያቄዉን እየሸሸ የሚመልስ ከሆነ ይህን አስተዉሎ ጥያቄዉ እንዲመለስ ለማስገደድ (ምስክሩን ለመቆጣጠር) የሚያስችል ነዉ:: ከዚህ ከማድመጥ የሚያሰናክለዉ አንዱ ከላይ እንደተመለከትነዉ ጥያቄን በዝርዝር ጽፎ ቀርቦ በንባብ መጠየቅ ሲሆን ሌላኛዉ ደግሞ ምስክርነቱን በዝርዝር መጻፍ ነዉ:: ሰለዚህ እነዚህን የአሰራር ዘዴዎች ወይም ባህሪዎች ዐቃቤህግ ሊያስወግድ ይገባል::
አንዳንድ ጊዜ የተቃራኒ ወገን ምስክር ሳያስበዉ ወይም ከዐቃቤህግ የአጠያየቅ ብቃት የተነሳ ለክሱ ጠቃሚ ምስክርነት ሊስጥ ይችላል:: በሌሎች አጋጣሚዎች ደግሞ ክሱን የሚጎዳ ነገር ሊመሰክር ይችላል:: በዚህ ጊዜ ዐቃቤህግ እንደተሰጠዉ ምስክርነት ጠቃሚነት ወይም ጎጂነት ስሜቱ የሚለዋወጥ ከሆነ ምስክሩ በሰጠዉ ምስክርነት እያደረሰ ያለዉን ዉጤት በሚገባ እንዲገነዘብ ስለሚያደርገዉ የተከሳሹን ክርክር የሚጎዳዉን ምስክርነት ያስተካክላል የዐቃቤህግን ክስ የጎዳበትን ምስክርነት በማጠናከር የበላይነቱን ይዞ የክርክሩን ሂደት የመቆጣጠሩን ሚና ከዐቃቤህግ ይነጥቃል::
የተከሳሽ ምስክር ለዐቃቤህግ ክስ ገንቢ የሆነ ምስክርነት ከሚሰጥባቸዉ አጋጣሚዎች አንዱ መዋሸት ነዉ:: መዋሸቱን የምናዉቅ ከሆነ ከምስክርነቱ በተቃራኒ የሆነዉን ዕዉነተኛዉን ታሪክ የሚያሳይ ማስረጃ አለን ማለት ነዉ:: ስለዚህ ምስክሩ ሲዋሽ ካገኘነዉ በዚሁ ዉሸቱ እንዲቀጥልበት የሚያደርጉ ጥያቄዎችን ማንሳት እንጂ መዋሸቱን ያወቅንበት መሆኑን የሚገልጽ ምንም ነገር ማድረግ የለብንም:: ምክንያቱም ይህን ከገለጽን የዋሸበትን ሁኔታ ያስተካክላል ስለዚህ ዐቃቤህግ ምስክሩ የማይታመን ወይም የሚዋሽ መሆኑን የሚያስረዳበትን አጋጣሚ ያጣል ማለት ነዉ::
በብዙ አጋጣሚዎች አላዋቂ መስሎ ላለመታየት በሚደረግ ጥረት ክርክርን መጉዳት ሊከተል ይችላል:: ስለዚህ በማያዉቁት ጉዳይ ጥያቄ ከመጠየቅ አለመቦዘን ተገቢ ነዉ:: ለምሳሌ በባለሙያ ምስክርነት ጊዜ ለባለሙያዉ ወይም ስለጉዳዩ ዕዉቀት ላላቸዉ ሰዎች ተራ የሆነ ነገር ሁሉ ለዐቃቤህግ ግልጽ ላይሆን ይችላል:: ስለዚህ አላዋቂ ላለመምሰል የባለሙያ ምስክርነት በሚነገርበት ጊዜ ነገሩ እንደገባዉ ሰዉ ዝም ብሎ ማዳመጥ ጉዳቱን ማወቅ የሚቻለዉ ነገሩ ካለቀ በኋላ ሰለሚሆን ጥንቃቄ ይፈልጋል:: በዚህ ረገድ ግልጽ ያልሆነን ነገር ማብራሪያ እንዲሰጥበት መጠየቅ ሊያሳፍር አይገባም ምንም ያህል ተራ ነገር ቢሆን ወይም ቢመስል::
ቀደም ሲል ለማየት እንደተሞከረዉ መስቀለኛ ጥያቄ አደጋ ያለዉ ሂደት ነዉ እንደተገኘ የሚገባበት አይደለም:: ጥንቃቄ ያሻዋል:: ተመራጭ ሆኖ ወይም አማራጭ የሌለዉ ሆኖ ጥያቄዉ መካሄድ ያለበት ከሆነ የተመጠነ ሊሆን ይገባዋል:: በዚህ ጊዜ ምስክሩን ለመቆጣጠር መቻል ያስፈልጋል:: ለዚህም የማያጨቃጭቁ ጥያቄዎችን ማንሳት አንዱ ከምስክሩ ጋር ያለመፋጠጥ ሁኔታ መፍጠሪያ መንገድ ሲሆን ሌላዉ የጥያቄዉን ሂደት ዓላማ መደበቅ መቻል ነዉ:: ይህ ማለት ግን ምስክሩን ማፋጠጥ ወይም ማስጨነቅ በማንኛዉም አጋጣሚ ተገቢ አይደለም ማለት አይደለም:: ተቃራኒ ምስክር እንደመሆኑ የምንፈልገዉን ነገር በቀላሉ ሊሰጠን አይችልም ወይም አይፈቅድም:: ስለዚህ አንዳንድ ጊዜ ፍጥጫ አስፈላጊ ሊሆን ይችላል:: ትልቁ ጥያቄ ግን መቼ የሚለዉ ነዉ:: ይህን ነገር መቼ ማድረግና አለማድረግ እንዳለብን የምናዉቅባቸዉን አንዳንድ ሁኔታዎች መለየት ያስፍልጋል::
ምስክርን ማስጨነቅ ወይም ማፋጠጥ ተገቢ የሚሆንበት ጊዜ ምልክቶች - የምስክሩ መረጋጋት አለመቻል ከጠበቃዉ ርዳታን መጠበቅ መናደድ ወይም ማድበስበስ መጀመር የጠበቃዉ ማደናገሪያ ወይም አቅጣጫ ማስቀየሪያ ተቃዉሞዎች መበራከት - እነዚህና መሰል ሁኔታዎች ምስክሩ ለማፋጠጥ የተጋለጠ መሆኑን ጠቋሚ ናቸዉ:: በዚህ ጊዜ ምስክሩ የደበቀዉን ለማዉጣት ወይም ነገሮችን ማሳሳት ወይም ማዘባረቅ ጀምሮ ከሆነ የበለጠ ነገር የሚያበላሽበት ሁኔታ ዉስጥ መሆኑን መረዳትና ማፋጠጡን ማጠንከር ያስፈልጋል::
በዚህ ሁኔታ የተጀመረ ማፋጠጥ ቢኖርም ምስክሩ እየጠነከረ ከመጣና በቀላሉ የሚፈታ ሰዉ ካልሆነ ማፈግፈግ - መተዉ ተመራጭ ነዉ::
ምስክሩን ማፋጠጥ ተገቢ የማይሆንባቸዉ አጋጣሚዎች ሲኖሩ በቀጥታ ማጥቃትን ማስቀረት ተገቢ ነዉ:: ይህ ተገቢ የሚሆንባቸዉ ሁኔታዎች ባብዛኛዉ ሃዘኔታን ወይም አክብሮትን የሚያገኙ ሰዎች ምስክር የሆኑባቸዉ አጋጣሚዎች ናቸዉ:: እነዚህም - ህጻናት አዛዉንት የሃይማኖት ሰዎች ወይም አባቶች ወዘተ ናቸዉ:: በነዚህ አጋጣሚዎች በቂና አስተማማኝ ማስረጃ ካልኖረ በቀር እንደዚህ አይነት ሰዎችን ማፋጠጥና ማስጨነቅ በዳኞችና ሂደቱን በሚከታለዉ ህኅብረተሰብ ፊት የሚያስጸይፍ ሊሆን ስለሚችል ዉጤቱ አፍራሽ ይሆናልና ይህ አይነቱን አቀራረብ መተዉ ተገቢ ነዉ::

ምስክርን ስለማስተባበል፡- ከመስቀለኛ ጥያቄ ሂደት ጋር የማይነጣጠለዉ ይህ ምስክርን የማስተባበል ነገር በወ/መ/ህ/ሥ/ሥ/ቁ. 145 የተፈቀደ ነዉ:: ይህ ህግ ተከሳሽ የዐቃቤህግን ምስክር የሚያስተባብልበትን ሥነሥርዓት ብቻ የሚደነግግ ይመስላል:: ሆኖም በፖሊስ ጣቢያ የተሰጠ ምስክርነት ጽሁፍ ለምስክርነት ማስተባበያ ይሆን ዘንድ ከመፈቀዱ በፊት ለፍርድቤት የሚቀርበዉ በተከሳሽ ጥያቄ ብቻ ሳይሆን በዐቃቤህግም ጭምር ነዉ:: ከዚህ በኋላ ፍርድቤት ጽሁፉን ለማስተባበያነት እንዲሰጠዉ የሚያደርገዉ ለተከሳሹ ነዉ::
ያም ሆነ ይህ በተለመደዉ አሰራር መሰረት ዐቃቤህግ የራሱን ምስክር በተመለከተ ቃሉን እየለወጠ መሆኑን ለማስረዳት በፖሊስ ጣቢያ የሰጠዉን ቃል ጽሁፍ ለምስክሩ አሳይቶ ፊርማዉን እንዲያረጋግጥ ካደረገ በኋላ ለፍርድቤት በማቅረብ ሲያስወስን ይታያል:: በተመሳሳይ ሁኔታ የተከሳሹ ምስክር በፖሊስ ምርመራ ጊዜ የሰጠዉን ቃል ጽሁፍ ለማስተባበያነት እንዲታይለት ቢጠይቅ ምን ስህተት አለዉ? የተከሳሽ ምስክር በፖሊስ ጣቢያ የምስክርነት ቃል ሊያስመዘግብ ይችላል? የተከሳሽ ምስክር በወንጀል ምርመራ ጊዜ በጉዳዩ ላይ ቃሉን በምስክርነት ከሰጠ በኋላ ዐቃቤህግ ማስረጃ አድርጎ ሳይቆጥረዉ ቢቀርና ተከሳሽ ምስክሩ ቢያደርገዉ ለፖሊስ ምስክርነቱን የሰጠ ምስክር ሊባል አይችልም?
በኢትዮጵያ ህግ መሰረት የሚደረገዉ ማስተባበል ቀድሞ በተሰጠ ቃል ላይ የተመረኮዘ ነዉ:: ሆኖም የማስትባበል ስራ ቀደም ሲል በምስክሩ በተደረገ ሌላ ተግባርም ሊከናወን ይችላል:: እንዲሁም የምስክሩን ባህሪ (ምናልባትም የመዋሸት) እና በጉዳዩ ዉጤት ምስክሩ የሚኖረዉን ጥቅም በማሳየት ምስክሩን ማስተባበል ይቻላል::

ከወ/መ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 145 ዉጪ ያሉ ምስክር ማስተባበያ ዘዴዎች፡- የቀድሞ የምስክር ቃልንም በተመለከተ ህጉ በፖሊስ ጣቢያ የተመዘገበን ቃል ብቻ ይገልጻል:: ቀደም ሲል በፍርድቤት በማንኛዉም ጉዳይ የተመዘገበ ቃልስ ምስክሩን ለማስተባበል አይዉልም? የቀዳሚ ምርመራ ፍርድቤት የመዘገበዉ ምስክርነት ለዚህ አገልግሎት ማዋል አይቻልም? በክስ መስማት ጊዜ በፍርድቤት ከሚደረግ የቃል ምዝገባ ሌላ ቃልን ለመመዝገብ ብቻ በሚሰራ ፍርድቤት ቃል ሊመዘገብ አይችልም (የወ/መ/ህ/ሥ/ሥ/ቁ. 35)? ምስክሩ ባለዉ የሥራ ኃላፊነት መሰረት የጻፋቸዉ ጽሁፎች ወይም ደብዳቤዎች ምስክሩን ለማስተባበል አያገለግሉም?
በነዚህ በሁሉም ሆነ በፖሊስ ጣቢያ ቃል ምስክርን ለማስተባበል አስቀድሞ ይህን ቃል ወይም መጻጻፍ እና ይዘቱን ማወቅ እንደሚያስፈልግ አያጠያይቅም:: ለዚህ ደግሞ ከዚህ በፊት እንደተገለጸዉ ዝግጅት ማድረግ የማይታለፍ ይሆናል:: ፀጋዬ ደመቀ ሎየር
https://t.me/lawsocieties
https://www.facebook.com/lawsocieties/
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
ክፍል ፫

ጋብቻ በንብረት በኩል ስለሚኖረው ውጤት

አንቀጽ ፶፯ የባልና ሚስት የግል ሀብት (፩) ያለግብይት የተገኙ ንብረቶች

ባልና ሚስት ጋብቻቸውን በሚፈጽሙበት ጊዜ በየግል የነበሯቸው ንብረቶች ወይም ከጋብቻ በኋላ በውርስ ወይም በስጦታ በየግላቸው ያገኙዋቸው ንብረቶች የግል ንብረቶቻቸው ሆነው ይቀራሉ፡፡

አንቀጽ ፶፰ (፪) በግብይት የተገኙ ንብረቶች

፩. ባልና ሚስት ከተጋቡ በኋላ አንዱ የግል ሀብቱ በሆነ ንብረት ለውጥ ያገኘው ወይም በግል ገንዘቡ የገዛቸው ወይም የግል ንብረቱን ሸጦ የሚያገኘው ገንዘብ የግል ሀብቱ ይሆናል፡፡

፪. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (፩) የተመለከተው ድንጋጌ ተፈፃሚ የሚሆነው በግብይት የተገኘው ንብረት የግል ይባልልኝ ብሎ አንደኛው ወገን ጥያቄ ሲያቀርብ እና ፍርድ ቤት ሲያፀድቀው ብቻ ነው፡፡

አንቀጽ ፶፱ የግል ሀብትን ስለማስተዳደር (፩) መሠረቱ

፩. እያንዳንዱ ተጋቢ የግል ሀብቱን ራሱ ለማስተዳደርና ገቢውንም ለመቀበል ይችላል፡፡

፪. እያንዳንዱ ተጋቢ የግል ሀብቱን ራሱ ሊያዝበት ነፃነት አለው፡፡

አንቀጽ ፷ (፪) የግል ሀብት አስተዳደርን በጋብቻ ውል ስለመወሰን

፩. ባልና ሚስት አንደኛው የሌላውን ተጋቢ የግል ሀብት በሙሉ ወይም በከፊል እንዲያስተዳድርለት እና እንደአስፈላጊነቱ እንዲያዝበት በጋብቻ ውላቸው ሊወስኑ ይችላሉ፡፡

፪. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (፩) በተመለከተው አኳኋን ንብረት የማስተዳደር ሥልጣን የተሰጠው ተጋቢ በሌላኛው ተጋቢ ሲጠየቅ ስለንብረቱ አስተዳደር ዓመታዊ የሂሳብ መግለጫ የመስጠት ግዴታ አለበት፡፡
አንቀጽ ፷፩ (፫) ስለውክልና ሥልጣን

ከተጋቢዎች አንዱ የግል ሀብቱን በሙሉ ወይም በከፊል እንዲያስተዳድርለት ለሌላኛው ተጋቢ ውክልና መስጠት ይችላል፡፡

አንቀጽ ፷፪ የባልና ሚስት የጋራ ሀብት

፩. ባልና ሚስት ከግል ጥረታቸውና ከግል ወይም ከጋራ ንብረታቸው የሚያገኟቸው ገቢዎች ሁሉ የጋራ ሀብቶቻቸው ይሆናሉ፡፡

፪. በዚህ ሕግ በአንቀጽ ፶፰ ንዑስ አንቀጽ (፪) መሠረት የአንደኛው ተጋቢ የግል ሀብት ነው ካልተባለ በስተቀር፣ ባልና ሚስት ከተጋቡ በኋላ በግብይት የሚያገኙት ንብረት ሁሉ የጋራ ሀብታቸው ይሆናል፡፡

፫. በስጦታው ውል ወይም በኑዛዜው ቃል በሌላ አኳኋን ካልተመለከተ በስተቀር፣ በስጦታ ወይም በኑዛዜ ለተጋቢዎቹ የተሰጧቸው ንብረቶች ሁሉ የጋራ ሀብቶቻቸው ይሆናሉ፡፡

አንቀጽ ፷፫ የሕግ ግምት

፩. አንደኛው ተጋቢ የግል ሀብቱ መሆኑን ካላስረዳ በስተቀር ማንኛውም ንብረት በአንደኛው ተጋቢ ስም ብቻ የተመዘገበ ቢሆንም እንኳን የጋራ ሀብት እንደሆነ ይቆጠራል፡፡

፪. የግል ንብረት መሆኑን ሦስተኛ ወገኖች የሚያውቁት ወይም ሊያውቁት የሚገባ ካልሆነ በስተቀር፣ ባልና ሚስቱ ወይም ከሁለቱ አንዱ ይኸው ንብረት የግል ነው በማለት በሦስተኛ ወገን ላይ መቃወሚያ አድርገው ሊያቀርቡት አይችሉም፡፡

አንቀጽ ፷፬ ስለባልና ሚስት ገቢ (፩) መደበኛ የገቢ አስተዳደር

፩. ባልና ሚስት እያንዳንዳቸው ገቢያቸውን በየራሳቸው ይቀበላሉ፡፡

፪. ባልና ሚስት በየግላቸው የሚያገኙትን ገቢ የግል ወይም የጋራ የባንክ ሂሳብ በመክፈት ማስቀመጥ ይችላሉ፡፡

፫. ከባልና ከሚስት አንደኛው ሲጠይቅ፣ ሌላኛው ተጋቢ ያገኘውን የገቢ መጠን የማስታወቅ ግዴታ አለበት፡፡
አንቀጽ ፷፭ (፪) ልዩ ሁኔታ

፩. ከባልና ከሚስት አንዱ፣ ገቢውን ሌላኛው ተጋቢ እንዲቀበልለት ሥልጣን ለመስጠት ሙሉ ነፃነት አለው፡፡

፪. ከባልና ከሚስት በአንደኛው ጠያቂነት የአንደኛውን ገቢ ሌላኛው ተጋቢ እንዲቀበልና ለመቀበሉም ደረሰኝ እንዲሰጥ ፍርድ ቤት ሊወስን ይችላል፡፡

፫. በሌላ ሕግ በተለየ ሁኔታ ካልተደነገገ በስተቀር፣ ከባልና ከሚስት የአንደኛው ገቢ በሙሉ ወይም በከፊል እንዲከበር በፍርድ ቤት ሊታዘዝ ይችላል፡፡

አንቀጽ ፷፮ የጋራ ሀብትን ስለማስተዳደር

፩. ከባልና ከሚስት አንዱ፣ የጋራ ሀብታቸውን በሙሉ ወይም በከፊል እንዲያስተዳድር ግልጽ ስምምነት ከሌለ በስተቀር ባልና ሚስቱ የጋራ ሀብታቸውን በጋራ ያስተዳድራሉ፡፡

፪. ከባልና ከሚስት አንዱ ችሎታ የለውም ተብሎ ሲወሰን ወይም ንብረት የማስተዳደር መብቱን ሲገፈፍ ወይም በሌላ ማናቸውም ምክንያት የጋራ ሀብታቸውን ለማስተዳደር የማይችል ሆኖ ሲገኝ ሌላኛው ተጋቢ የጋራ ሀብቱን የማስተዳደሩን ተግባር ያከናውናል፡፡

አንቀጽ ፷፯ የማስታወቅ ግዴታ
ከተጋቢዎች አንዱ ብቻ የጋራ ሀብታቸውን በሚያስተዳድርበት ጊዜ የሀብቱን አስተዳደር በተመለከተ ለሌላኛው ተጋቢ መረጃ የመስጠት ግዴታ አለበት፡፡
አንቀጽ ፷፰ (፩) የተጋቢዎች ስምምነት አስፈላጊ ስለመሆኑ
በሌላ ሕግ በተለየ ሁኔታ ካልተደነገገ በስተቀር፣ በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ የተጋቢዎቹ ስምምነት አስፈላጊ ነው፤
ሀ) የጋራ የሆነውን የማይንቀሳቀስ ንብረት ለመሸጥ፣ ለመለወጥ፣ ለማከራየት በመያዣ ወይም በዋስትና ለመስጠት ወይም በሌላ በማናቸውም ሁኔታ በዚሁ ንብረት ላይ ሌሎች ሰዎች መብት እንዲያገኙ ለማድረግ፤

ለ) ዋጋቸው ከብር ፭፻ (አምስት መቶ) በላይ የሆኑ የሚንቀሳቀሱ የጋራ ንብረቶችን ወይም የገንዘብ ሰነዶችን፣ ለመሸጥ፣ ለመለወጥ በመያዣ ወይም በዋስትና ለመስጠት ወይም በሌላ በማናቸውም ሁኔታ ለማስተላለፍ፤

ሐ) ከብር ፻ (አንድ መቶ) በላይ ዋጋ ያለውን የጋራ ንብረት ወይም ገንዘብ ለሌላ ሰው በስጦታ ለማስተላለፍ፤

መ) ከብር ፭፻ (አምስት መቶ) በላይ ለመበደር ወይም ለማበደር ወይም ለሌላ ሰው ዋስ ለመሆን፡፡

አንቀጽ ፷ (፪) የስምምነት አለመኖር ስለሚያስከትለው ውጤት

፩. አንደኛው ተጋቢ ከዚህ በላይ የተመለከተውን ድንጋጌ ባለማክበር የውል ግዴታ ገብቶ የተገኘ እንደሆነ፣ ሌላኛው ተጋቢ ለፍርድ ቤት በሚያቀርበው ጥያቄ ግዴታው ሊፈርስ ይችላል፡፡

፪. ግዴታው እንዲፈርስ የሚቀርበው ጥያቄ ጠያቂው ወገን ግዴታው መገባቱን ከአወቀበት ቀን ጀምሮ ከስድስት ወር በኋላ ወይም በሌላ በማናቸውም ሁኔታ ግዴታው ከተገባ ከሁለት ዓመት በኋላ ሊቀርብ አይችልም፡፡

አንቀጽ ፸ የባልና ሚስት ዕዳ

፩. ከባል ወይም ከሚስት በግል የሚጠየቅ ዕዳ፣ ከባለዕዳው ተጋቢ የግል ሀብት፣ የግል ሀብቱ ዕዳውን ለመሸፈን በቂ በማይሆንበት ጊዜ ከጋራ ሀብታቸው ይከፈላል፡፡

፪. ዕዳው የመጣው ለትዳራቸው ጥቅም ከሆነ ከጋራ ሀብታቸው የጋራ ሀብታቸው፣ ዕዳውን ለመሸፈን በቂ በማይሆንበት ጊዜ ከባል ወይም ከሚስት የግል ሀብት ይከፈላል፡፡

አንቀጽ ፸፩ ለትዳር ጥቅም እንደተደረገ የሚቆጠር ዕዳ
የሚከተሉት ዕዳዎች ለትዳር ጥቅም እንደተደረጉ የሚቆጠሩ ናቸው፡፡

ሀ) ለባልና ለሚስት እንዲሁም ለልጆቻቸው የዕለት ኑሮ አስፈላጊ የሆኑትን ነገሮች ለማሟላት የተገቡ ዕዳዎች፤

ለ) ባል ወይም ሚስት ቀለብ ለመስጠት ያለባቸውን ግዴታ ለመወጣት የተደረጉ ወጪዎች፤

ሐ) ከባልና ከሚስት በአንደኛው ወይም በዕዳ ጠያቂው አለመልካችነት ለትዳር ጥቅም ስለመሆኑ ፍርድ ቤት የተቀበለው ሌላ ዕዳ፡፡
አንቀጽ ፸፪ የትዳር ወጪዎችን ስለመሸፈን
ተጋቢዎች የትዳራቸውን ወጪ ለመሸፈን እያንዳንዳቸው እንደየአቅማቸውና ችሎታቸው አስተዋጽኦ ማድረግ አለባቸው፡፡
አንቀጽ ፸፫ በተጋቢዎች መካከል ስለሚደረጉ ውሎች
ባልና ሚስቱ ተጋብተው በሚኖሩበት ጊዜ በመካከላቸው የሚያደርጓቸው ውሎች፣ ፍርድ ቤት ካላፀደቃቸው በስተቀር ውጤት አይኖራቸውም፡፡
https://t.me/lawsocieties
https://www.facebook.com/lawsocieties/
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
የሰበር ችሎት 10 የህግ አተረጓጎም ደንቦች
=================
ህግ እንደማንኛውም የስነ ጽሑፍ ስራ ህግ ለማውጣት ስልጣን የተሰጠው አካል የሚጽፈው ድርሰት ነው፡፡ በመርህ ደረጃ ማንበብ የሚችል ዜጋ ሁሉ (በሙያው መመረቅና መሰልጠን ሳያስፈልገው) ይህን ህግ አንብቦ ይረዳዋል ተብሎ ይገመታል፡፡ ይሁን እንጂ የተጻፈ ህግ ከሌሎች ድርሰቶች በእጅጉ የሚለው የራሱ ባህርይ፣ ዘይቤና የአጻጻፍ ስርዓት አለው፡፡ ስለሆነም በሁሉም ዜጋ ይቅርና ህጉን በሚጽፈው፣ በሚያስፈጽመውና በሚተረጉመው አካል ወጥና ተመሳሳይ መረዳት አይኖርም፡፡ የህጉ ቋንቋ የሚፈጥረው የአረዳድ ልዩነት አንድ ቦታ ላይ ሊቋጭ ስለሚገባው አንደኛው የመንግስት አካል የሚሰጠው ትርጉም ባልተግባቡት ወገኖች መካከል አሳሪ ይሆን ዘንድ ፍርድ ቤት ህጋዊና ህገ-መንግስታዊ ዕውቅናና ብቃት ያለው ተቋም ሆኖ ተቋቁሟል፡፡

ፍርድ ቤትም ቢሆን ግን አንድ ምላስ እንጂ አንድ ራስ የለውም፡፡ አንዲት ድንጋጌ በፌደራልና በክልል፣ በበላይና በበታች ፍ/ቤቶች ብሎም በውስጣቸው በሚገኙት ችሎቶች የተለያየ አንዳንዴም የተራራቀ መልዕክት ታስተላልፋለች፡፡ ሁልጊዜ ይህን መሰሉ አለመናበብ ባይኖርም ክስተቱ አይቀሬ ነው፡፡ አይቀሬነቱ የሚመነጨው ከአንባቢው (ዳኛው) ስህተትና ግድፈት ብቻ አይደለም፤ ከተነባቢው (ከተጻፈው ህግ) ልዩና ውስብስብ ባህርያት ጭምር እንጂ፡፡

የአገራችን የመጨረሻ፤ የበላይ ህግ ተርጓሚ የሆነው የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ሚና በእያንዳንዱ በቀረበለት መዝገብ ላይ ህጉ ምን እንደሚል ትርጉም መስጠት ብቻ አይደለም። ከዚህ ባለፈ የስር ፍርድ ቤቶች ምን ዓይነት የህግ አተረጓጎም ስልት መከተል እንዳለባቸው ጭምር መመሪያ መስጠት ይጠበቅበታል። ይሄ ደግሞ ወጥነት ከማስፈኑ በላይ የችሎቱን ስራ በእጅጉ ያቀልለታል። ለምሳሌ በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ለእያንዳንዱ ድንጋጌ ትርጉም ከመስጠት ባለፈ የስር ፍር ቤቶች ህጉን በምን ዓይነት የአተረጓጎም ስልት መተርጎም እንዳለባቸው አቅጣጭ ቢያስቀምጥ መሰረታዊ የህግ ስህተቶች ቁጥራቸው ይቀንሳል። በተለይ የህግ አተረጓጎም ስልትን የሚገዛ ዝርዝር ህግ በሌለበት /ከተወሰኑት ድንጋጌዎች በቀር/ በአገራችን የስር ፍርድ ቤቶች መከተል ስላለባቸው የህግ አተረጓጎም ስልት ግልጽ አቅጣጫ ማስቀመጥ ችሎት ዋነኛ ሚናው አድርጎ መውሰድ ይኖርበታል።
እስካሁን በሰበር ችሎት በተሰጡ ውሳኔዎች የህግ አተረጓጎም ስልትን በተመለከተ ጎልቶ የሚታይ ባናገኝም በተወሰኑ ውሳኔዎች ችሎቱ የተጠቀማቸው ስልቶች ጠቅለል ባለ አነጋገርም ቢሆን ተገልጸዋል። ከእነዚህ ውስጥ የተወሰኑት ተጨማሪ ማብራሪያ ሳይታከልባቸው በውሳኔዎቹ ላይ እንደተጠቀሱ እንደሚከተለው ቀርበዋል።

1/ ማራባት

ሰ/መ/ቁ. 79476 ቅጽ 18
ከድንጋጌው ውስጥ “...የሌሎችም ክፍያዎች..” ወይም “.. 0thher payments ~ የሚለው ሐረግ ጠቅላላ ቃል መሆኑ ግልጽ ሲሆን እንዲህ በሆነ ጊዜ ቃሉን ሕግ አውጪው የተጠቀመው ምንን ለማመላከት ነው? የሚለውን ጥያቄ ማንሣቱ ተገቢ ሲሆን የሕግ አተረጓጎም መርሆዎችን መሠረት በማድረግም ምላሹን ማግኘት ይቻላል፡፡ በዚህም መሠረት ከጠቅላላው ቃል በፊት የተዘረዘሩት የቃላት ዝርያ የሚያሣዩትን ሁኔታ በመመልከት ጠቅላላ ቃል ሌሎች ያልተዘረዘሩትን ተመሣሣይ ዝርያ ያላቸውን ቃላት ለመጠቀም ታስቦ የተቀመጠ ነው በሚል እንደሚተረጎም ተቀባይነት ያላቸው የሕግ አተረጓጎም መርሆዎች ያስገነዝባሉ፡፡

2/ ጥብቅ የሕግ አተረጓጐም መርህ

ሰ/መ/ቁ. 98263 ቅጽ 17
በፍርድ ውሳኔ የተሰጠበት ጉዳይ አፈፃፀም ለማስቀረት የፍርድ ባለመብት እና የፍርድ ባለዕዳ የሚያደርጉት የዕርቅ ውል፣ በፍ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 276 እና በፍ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 277/1/ የተደነገገውን ጥብቅ መስፈርት የሚያሟላ ባልሆነበት ጊዜ፣ ህጋዊ ውጤትና ተፈፃሚነት እንደማይኖረው የሚያረጋግጥ፣ ጥብቅ የሆነ የሕግ አተረጓጐም መርህ መከተል የፍርድ አፈፃፀም ስርዓቱን ውጤታማና ቀልጣፋ በሆነ ሁኔታ እንዲከናወን ለማድረግ አስፈላጊ ነው፡፡

3/ የቃል በቃል ንባብ /የተናጠል ንባብ/

ሰ/መ/ቁ. 57632 ቅጽ 12
የ2 ዳኞች የልዩነት ሀሳብ
ከላይ ከደረስንበት መደምደሚያ ላይ ለመድረስ ከዚህ በፊት ከላይ ከገለፅናቸው ምክንያቶች በተጨማሪ የአዋጅ ቁጥር 25/1988 አንቀጽ 9 አቀራረፅ እና የቃል በቃል ንባብ መገናዘብ አለበት የሚል እምነት አለን፡፡

ሰ/መ/ቁ 101271 ቅጽ 16
የአዋጅ ቁጥር 650/2001 አንቀጽ 44 ንዑስ አንቀጽ 1 መሰረታዊ ባህሪና ዓላማ እንደዚሁም ድንጋጌው በአካዳሚክ ሰራተኞች የይግባኝ መብት ላይ የሚኖረውን ሕጋዊ ውጤት ለመረዳት የድንጋጌውን የተናጠል የቃል በቃል ንባብ ማየት ብቻዉን በቂ አይደለም፡፡

4/ ዓላማ

ሰ/መ/ቁ. 93137 ቅጽ 15
የፍ.ስ.ስ.ሕ.ቁ. 6 ዓይነተኛ ዓላማ ተገቢ ሁኔታዎችና ፍሬ ነገሮች ተሟልተው መገኘታቸው ሲረጋገጥ በሀሰተኛ ማስረጃ፣ በመደለያና በመሰል ወንጀል ጠቀስ ድርጊቶች ምክንያት የተዛነፈውን ፍትሕ ወደነበረበት መመለስ ነው፡፡

5/ ተቃራኒ ንባብ

የሰ/መ/ቁጥር 46386 ቅጽ 13
በወንጀል ጉዳይ የተሰጠ ውሣኔ በዚያው ጉዳይ በፍታብሔር በማስረጃነት አግባብነት እና ብቃት የሚኖረው ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሕ/ቁ. 2149 ተቃራኒው ንባብ ያስገነዝበናል።

6/ ግልባጭ ንባብ

ሰ/መ/ቁ. 49635 ቅጽ 12

በፍ/ብ/ሕ/ቁ 2278 እንደተመለከተው የተሸጠን ነገር የተረከበ ገዥ የሽያጩን ዋጋ ወዲያውኑ የመክፈል ግዳታ ያለበት በመሆኑና የሽያጩ ዋጋ ያልተከፈለውው ሻጭ የተሸጠውን ነገር ሳያስረክብ በእጁ የማቆየት መብት የሚሰጠው ለመሆኑ የዚሁ ድንጋጌ ግልባጭ ንባብ ስለሚያስረዳ…

7/የተቃርኖ ንባብ

ሰ/መ/ቁ. 54129 ቅጽ 11
የአስተዳደር መስሪያ ቤት መብቱን የሚጠይቀውም ሆነ ግዴታውን የሚወጣው ለሥራ ተቋራጩ ሲሆን የአስተዳደር መሥሪያ ቤት ግንኙነት ከሥራ ተቋራጩ ጋር ብቻ የሚወሰን መሆኑን ከፍታብሔር ህግ ቁጥር 3205 እና ከፍታብሔር ህግ ቁጥር 3206 የተቃርኖ ንባብና ትርጉም ‛Acontrario reading and Interpretation‛ ለመገንዘብ ይቻላል፡፡

8/ ጥምር /ጣምራ/ ንባብ

ሰ/መ/ቁ. 86398 ቅጽ 17

የመቃወም አቤቱታው እና የማስረጃው ቅጂ የመቃወም ተጠሪ ለሆነው ወገን እንዲደርስ መደረግ የሚገባው መሆኑን ከመግለጽ በስተቀር የመቃወም ተጠሪው የጽሁፍ መልስ እና የመከላከያ ማስረጃ ማቅረብ እንደሚገባው በእነዚህ ድንጋጌዎች ላይ በግልጽ የተጻፈ ባይሆንም የመቃወም ተጠሪ የሆነው ወገን በፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ሕግ ቁጥር 234 ድንጋጌ መሰረት ለቀረበበት የመቃወም አቤቱታ ያለውን የመከላከያ መልስ እና ማስረጃ ማቅረብ የሚገባው ስለመሆኑ ከቁጥር 360(1) እና (2) ድንጋጌዎች ጣምራ ንባብ መገንዘብ ይቻላል፡፡

9/ አውድ ንባብ

ሰ/መ/ቁ. 67280 ቅጽ 11
ሕግ አውጪው የትምህርት ዝግጅትንና የሥራ ልምድን ለያይቶ እኩል ዋጋ በአንድ አንቀፅ ከሰጠ በኋላ በተከታዩ ድንጋጌ ተመሣሣይ መንፈስ ያለው አንቀፅ ያስቀምጣል ማለት ትርጉም አልባ ከመሆኑም በላይ የሕጎችን አውድ ንባብ (contextual interpretation) ትርጓሜ ያልተከተለ፤ አዋጁ ውጤት እንዲኖረውና በአዎንታዊ መንገድ ታይቶ ሥራ ሊይ እንዲውል ለማድረግ የሚያስችል የአተረጓጎም መንገድ ሆኖ አይገኝም፡፡

10/ ጠቅላላ እና ልዩ ህግ
ሰ/መ/ቁ. 39803 ቅጽ 8
ይሁንና የማይንቀሳቀስ ንብረትን ስጦታ በተመለከተ በተለይ በሚገዛው ከፍ ብሎ በተጠቀሰው የፍ/ብ/ሕ/ቁ 2443 እና 881 ዴንጋጌ መሠረት ይህ ሥርዓት መከናወን እንዳለበት አልተመለከተም፡፡ በጠቅላላ ሕግና በልዩ ሕግ መካከል አለመጣጣም ወይንም ልዩነት በሚኖርበት ጊዜ ልዩ ሕግ የበላይ ሆኖ ተፈፃሚነት ሊኖረው እንደሚችል /The Special prevail over the general/ ከሕግ አተረጓጎም መርህ መገንዘብ ይቻላል፡፡

ሰ/መ/ቁ. 24703 ቅጽ 7
የግራ ቀኙን ግንኙነት በተለይ የሚገዛው ልዩ ሕግ የሆነው የንግድ ሕጉ ስለሆነና በጠቅላላ ሕግና በልዩ ሕግ መካከል አለመጣጣም በሚኖርበት ጊዜ ልዩ ሕግ የበላይነት እንደሚኖረው /The special prevails over the general/ ከሕግ አተረጓጐም መርህ መገንዘብ የሚቻል እንደመሆኑ......
By Abraham Yohannes
https://t.me/lawsocieties
https://www.facebook.com/lawsocieties/
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
DON'T ARGUE WITH A DONKEY
DON'T ARGUE WITH A DONKEY‼️

The donkey said to the tiger:
- "The grass is blue".

The tiger replied:
- "No, the grass is green."

The discussion heated up, and the two decided to submit him to arbitration, and for this they went before the lion, the King of the Jungle.

Already before reaching the forest clearing, where the lion was sitting on his throne, the donkey began to shout:
- "His Highness, is it true that the grass is blue?".

The lion replied:
- "True, the grass is blue."

The donkey hurried and continued:
- "The tiger disagrees with me and contradicts and annoys me, please punish him."

The king then declared:
- "The tiger will be punished with 5 years of silence."

The donkey jumped cheerfully and went on his way, content and repeating:
- "The Grass Is Blue"...

The tiger accepted his punishment, but before he asked the lion:
- "Your Majesty, why have you punished me?, after all, the grass is green."

The lion replied:
- "In fact, the grass is green."

The tiger asked:
- "So why are you punishing me?".

The lion replied:
- "That has nothing to do with the question of whether the grass is blue or green. The punishment is because it is not possible for a brave and intelligent creature like you to waste time arguing with a donkey, and on top of that come and bother me with that question."

The worst waste of time is arguing with the fool and fanatic who does not care about truth or reality, but only the victory of his beliefs and illusions. Never waste time on arguments that don't make sense... There are people who, no matter how much evidence and evidence we present to them, are not in the capacity to understand, and others are blinded by ego, hatred and resentment, and all they want is to be right even if they are not.

When ignorance screams, intelligence is silent. Your peace and quiet are worth more.
Uhuru Kenyatta Quotes
https://t.me/lawsocieties
https://www.facebook.com/lawsocieties/
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
ተገቢ ያልሆነ ዋጋ ማናርና ሸቀጦችን የመደበቅ ተግባር የሕግና የሞራል ተጠያቂነት
-------------------------------------------

ተገቢ ያልሆነ ዋጋ መጨመር

ለአንድ ሀገር የዋጋ ንረት መከሰት በዋነኝነት ሁለት ዓይነት ኢኮኖሚያዊ ገፊ ምክንያቶች ያሉ መሆናቸውን የስነ-ቁጠባ ባለሞያዎች ይገልፃሉ። እነዚህም ከፍላጎት መጨመር የመነጨ የዋጋ ንረት(demand push inflation) እና የማምረቻ ዋጋ መጨመር(cost push inflation) ናቸው። ከእነዚህ ምክንያቶች አንፃር ሲመዘን በሀገራችን የተከሰተው የዋጋ ንረት እዚህ ደረጃ ሊደርስ የሚያስችል ኢኮኖሚያዊ አመክንዮ የለውም ወደሚለው ድምዳሜም ይደርሳሉ ምሁራኑ።

ሀገራችን የምትከተለው የኢኮኖሚ ስርዓት የነፃ ገበያ ኢኮኖሚ ስርዓት ቢሆንም በየትኛውም ሀገር ቢሆን መንግስት ጣልቃ የማይገባበት የገበያ ኢኮኖሚ የለም። መጠኑ ይለያይ እንጂ ነፃ የገበያ ኢኮኖሚ የሚከተሉ የበለጸጉትም ሆኑ ታዳጊ ሀገራት የገበያ ጉድለት ሲያጋጥማቸው መንግስት ጣልቃ ገብቶ ጉድለቱን የሚሞላበት አሰራር አለ። ኢትዮጵያም ከዚህ ነባራዊ ሁኔታ ውጭ ልትሆን አትችልም።

በንግድ ውድድርና የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 813/06 በአንቀፅ 25 ሥር “አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ የንግና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የዋጋ ቁጥጥር ሊደረግባቸው የሚገቡ መሰረታዊ የንግድ ዕቃዎች እና አገልግሎቶች ጥናት አድርጎ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት አቅርቦ በማስፈቀድ ዝርዝራቸውንና ዋጋቸውን በሕዝብ ማስታወቅያ ሊያሳውቅ ይችላል፡፡” በማለት ተደንግጓል፡፡ በመሆኑም የንግዱ ማሕበረሰብ ይህ አሰራር ያለ መሆኑን ተገንዝቦ በተለይም በእንደዚህ ዓይነት አስቸጋሪ ወቅት ሊተገበር የሚችል በመሆኑ ነቅቶ መከታተልና መተግበር ይጠበቅበታል፡፡ የንግድ ሚኒሰቴርም ለሸማቹ ሕብረተሰብ የራስ ምታት የሆኑትን ምርቶች የዋጋ ቁጥጥር እንዲደረግባቸው እየለየ ሕጉ ባስቀመጠለት ሥልጣንና ኃላፊነት መሰረት እንዲሰራበት ለመጠቆም እንወዳለን፡፡

በአሁኑ ሰዓት በርካታ ወገኖች ካላቸው ጥቂት ነገር ለተቸገረው በማካፈል ለወገን አለኝታነታቸውን በማስመስከር ላይ ይገኛሉ፡፡ በአንፃሩ ደግሞ ወረርሽኙን እንደመልካም አጋጣሚ በመቁጠር በእጃቸው ላይ ያለን የግድ ዕቃ በሕገ-ወጥ መንገድ በመደበቅ ገበያው ላይ ሰው ሰራሽ ዕጥረት እንዲፈጠር በማድረግ ሸማቹ እንዳይረጋጋና አማራጭ እንዲያጣ ካደረጉ በኋላ ባሻቸው ዋጋ የሚሸጡ፤ በወቅቱ ወደገበያ ያቀረቡትን ዕቃም ቢሆን ተመሳጥረው ከፍተኛ የሆነ የዋጋ ተመን በመተመን ተገቢ ያልሆነ ትርፍ የሚያጋብሱ ግልሰቦች አሉ፡፡

ነገር ግን ይህ በሀገር እና በወገን ላይ ከፍተኛ ጫና በሚያሳድር መልኩ የሚደረግ የዋጋ ማናር ተግባር ከሐይማኖቶች አስተምህሮም ሆነ ከሞራል አንፃር ብናየው በየትኛውም መመዘኛ ተቀባይነት የሌለውና አስነዋሪ ድርጊት መሆኑ እርግጥ ነው፡፡ በመሆኑም ይህን ክፉ ጊዜ ተባብረንና ተደጋግፈን ማለፍ የሚገባን ሆኖ ሳለ በሀገርና በወገን ላይ ሌላ ተጨማሪ ችግር መፍጠር የአንድ መልካም ዜጋ መገለጫ አይደለምና በጥብቅ ልናስብበት ይገባል፡፡

የንግድ ዕቃን ስለማከማቸት/መደበቅ

ዕቃን ማከማቸት እና መደበቅ ሰው ሰራሽ እጥረት በመፍጠር የገቢያ አለመረጋጋት እና የዋጋ ንረትን ከሚያስከትሉ ተግባራት መካከል የአንበሳውን ድርሻ ይይዛል። በንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች የዕቃውን በገበያ ላይ ያለውን ተፈላጊነት ከግምት ውስጥ በማስገባት የአቅርቦት ችግር በሌለበት ሁኔታ የአቅርቦት ችግር ያለ በማስመሰል በግለሰብ ወይም በቡድን ደረጃ ሊያከማቹ እና ሰው ሰራሽ እጥረት ፈጥረው በከፍተኛ ዋጋ የመሸጥ ተግባር ሲፈፅሙ ይስተዋላሉ። ይህ የንግዱ ማህበረሰብም ሆነ ሸማቹ ያለአግባብ የንግድ ዕቃን የማከማቸት ተግባር በዜጎች ላይ ወይም እንደ አጠቃላይ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያደርሰው ተፅእኖ በጣም ከባድ ነው።

በበንግድ ውድድርና የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ አንቀፅ 24 ንዑስ አንቀፅ 1 መሰረት አንድ ነጋዴ ከመደበኛ የግብይት ስርዓት ውጭ ወይም ነጋዴ ያልሆነ ሰው ለግል ወይም ለቤተሰብ ፍጆታ ከሚውል መጠን በላይ በንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በገቢያ ላይ እጥረት ያለበት መሆኑ በወጣ የህዝብ ማስታወቂያ የተገለፀ የንግድ ዕቃን ማከማቸት ወይም መደበቅ ክልክል መሆኑ ተደንግጓል። ነገር ግን ከተገቢው የንግድ አሰራር ውጪ ማከማቸትም ሆነ መደበቅ የማይቻለው በገበያ ላይ ዕጥረት ያለበትን የንግድ ዕቃ ብቻ ሳይሆን ማንኛውንም የንግድ ዕቃ መሆኑን የአዋጁን አንቀፅ 23(3) እና 24ን በጣምራ በማንበብ መገንዘብ ይቻላል፡፡

ይኼውም በአንቀፅ 23(3) ላይ “ሚኒስቴሩና ቢሮዎች በነጋዴዎች የሚፈፀም የንግድ ዕቃዎች ክምችት ወይም የመደበቅ ተግባር ላይ ቁጥጥር ያደርጋሉ” ተብሎ መደንገጉ ሲታይ የተጠቀሱት ተቋማት በሕገወጥ ነጋዴዎች የሚደረግን የምርት ማከማቸትና መደበቅ እየተቆጣጠሩ የንግድ ሥርዓቱን ሚዛን የማስጠበቅ ኃላፊነት የተጣለባቸው መሆኑን ነው፡፡ በመሆኑም የንግዱ ማሕበረሰብ ማንኛውንም ዓይነት የንግድ ዕቃ መደበቅ ወይም ማከማቸት ክልክል መሆኑን ተገንዝቦ እራሱን ከእንደዚህ ዓይነት ተግባር መቆጠብ ይጠበቅበታል፡፡

የማከማቸት እንዲሁም የመደበቅ ተግባራት ላይ የሚሳተፉ ግለሰቦችን በተመለከተ የአዋጁ አንቀፅ 43 ንዑስ አንቀፅ 4 እና 5 ላይ የተቀመጡ ድንጋጋጌዎች የተከማቸውን እቃ እንዲሁም ማጓጓዣውን መውረስን ጨምሮ እስከ አምስት አመት የሚደርስ ፅኑ እስራት እና የገንዘብ ቅጣቶችን አስቀምጠዋል።
“ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ ይጠብቅ!”
ምንጭ የኢፌደሪ ጠቅላይ አቃቤ ህግ
https://t.me/lawsocieties
https://www.facebook.com/lawsocieties/
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
ኤጀንሲው አቋርጦት የነበረውን የዉክልና፣ የሽያጭና የስጦታ ማፍረሻ አግልግሎት መጀመሩን አስታወቀ

የፌደራል የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ በአዲስ ሲስተም ዝርጋታ ምክንያት ለሳምንታት አቋርጦት የነበረውን የዉክልና፣ የሽያጭና የስጦታ ማፍረሻ አግልግሎት ከነሀሴ 1 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አሰራር በሁሉም ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች መስጠት መጀመሩን አስታውቋል፡፡

በተመሳሳይ በበጀት አመቱ በሁሉም ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች በውልና ውክልና ዘርፍ 530,836 የሚሆኑ አገልግሎቶች በኦን-ላይን ሲስተም የአሰራር ሥርዓት ታግዘው መሰጠታቸውን ኤጀንሲው ይፋ ያደረገው መረጃ ያሳያል፡፡

ተቋሙ በተለያዩ አገልግሎት ዘርፎች 909,292 ጉዳዮችን ለማከናወን በእቅድ ይዞ 833,190 ጉዳዮችን በማከናወን የዕቅዱን 91.6 % ለማሳካት መቻሉንም ነው የገለፀው፡፡

ከተሰጠው አገልግሎት 649 ሚሊየን ብር መሰብሰቡን የገለፀው ኤጀንሲው ይህም የእቅዱን 108 በመቶ ያሳካ ሲሆን ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ127 ሚሊዮን ብር ወይም 24.33 በመቶ ያህል ብልጫ ማሳየቱን ጠቅሷል።

ሐሰተኛ ሰነድ ይዘው የተገኙ 261 ሐሰተኛ ማስረጃዎች ጥቅም ላይ እንዳይውሉ በማድረግ ሊደርስ የነበረዉን ጉዳት ለማስቀረት መቻሉም ታውቋል፡፡

በተመሳሳይ ኤጀንሲው ከሁሉም የመንግስትና የግል ባንኮች ውክልና እና ሽያጭን ማጣራት የሚያስችል ሲስተም ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ማድረጉንም ገልጿል፡፡

ሐምሌ 3፤ 2013 ዓ.ም.
አዲስ ዘይቤ
Join us via our telegram channel!
https://t.me/lawsocieties
https://www.facebook.com/lawsocieties/
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
Lawyer


Bole Medhanialem, Zewdu Bldg 5th Floor Next to Kebe Pastry, Addis Ababa

  0988747248



WORK AT

Defense Construction Enterprise

JOB TYPE

Employee

JOB STATUS

Full Time

ANNOUNCED

09 August, 2021

JOB TITLE

Lawyer

JOB LOCATION

Addis Ababa, Ethiopia

JOB PRESENTATION

Vac No.:  003/2013

Defense Construction Enterprise wants to hire qualified applicants for the following vacant post.

Job Title: Lawyer

Required Education & Experience

LLB in Law and 4 years work experience OR

LLM in Law and 2 years work experience 

Work experience in the construction sector will be advantageous

Required Number: 01 (One)

Level: XIII

Salary: 10,180.00

Employment Type: Permanent

Place Work: Head Office

N.B. Work Experience will be counted after graduation 

SALARY

10,180.00 (ETB)

VALID TILL

18 Aug, 2021 (7 days left)
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
የክስ ምክንያት ምንድነው?🇪🇹
#Like #Comment #Share ያድርጉ

ለጥያቄው ምላሽ የሰበር ችሎት በ 6 መዝገቦች ላይ እንደሚከተለው የህግ ትርጓሜ ሰጥቷል።

1/ አንድ ሰው አንድን ነገር ከአንድ ሰው ላይ ለማግኘት ፍ/ቤቱ እንዲወስንለት ክስ ለማቅረብና ዳኝነት ለማግኘት የሚያስችለው የፍሬ ነገር ሁኔታ

ማንም ሰው በህግ ችሎታ ኖሮት በሌላ ሰው ላይ ማናቸውንም ክስ ለማቅረብ እንዲችል አስቀድሞ ለክሱ መነሻ በሆነው ነገር ወይም ክሱ በተመሠረተበት ነገር ላይ ጥቅም ወይም መብት ያለው መሆኑ መረጋገጥ እንደሚገባው የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 33 ይደነግጋል፡፡ በዚህም ከሣሽ ከተከሣሽ ላይ ሊፈፀም የሚችል መብት አለኝ ብሎ ለማለት አስቀድሞ ለመብቱ መገኘት መነሻ የሆነውን ነገር በማረጋገጥ የተጠየቀውን ዳኝነት ለማግኘት ከሣሹ በሕግ መብት ያለው መሆን ይኖርበታል፡፡
የክስ ምክንያት አለ ብሎ ለመወሰን የሚቻለው በክሱ ላይ የቀረበው ነገር ቢረጋገጥ ከሣሹ የጠየቀውን ዳኝነት ለማግኘት ሕግ ይፈቅድለታል ወይ? ለሚለው ጥያቄ አዎንታዊ ምላሽ መስጠት ሲቻል ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 16273 ቅጽ 2፣ ስለ አሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ የወጣ አዋጅ ቁ. 42/85 አንቀጽ 9፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 29፣ 80/2/፣ 224/2/፣ 23/1/ ሀ ፣ 224/2/፣ 23/1//ሀ/፣ 33፣ ሮበርት አለን ሴድለር በችሎቱ እንደተጠቀሰ

2/ ሻጭ ከሽያጭ ውሉ በሚመነጭ ግዴታ የተሸጠውን ነገር ስመ ሀብትነት በሚመለከተው ክፍል ቀርቦ ለማዛወር እንደገባው ግዴታ ይፈጽምልኝ የሚል ክስ የክስ ምክንያት አለው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 82234 ቅጽ 15

3/ አንድ ክስ ሊቀርብ የሚገባው የክስ ምክንያት ሲኖረው ሲሆን የክስ ምክንያትም ተከሣሽ ለከሣሽ ሊፈጽመው የሚገባው ግዴታ መኖሩ ጋር ተያይዞ ሊነሣ የሚችለውን ጥያቄ አዎንታዊ ምላሽ መስጠት የሚቻልበት ሁኔታ ስለመኖሩ ሲረጋገጥ የሚታወቅ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 33945 ቅጽ 12፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 231(1) ሀ

4/ ክስ ለማቅረብ የሚያስችል መነሻ ምክንያት
በፍ/ብ/ሕ/ሥ/ሥ/ቁ. 231 ላይ እንደተመለከተው ማንኛውም ፍርድ ቤት የክስ አቤቱታ ሲቀርብለት ተከሣሽ የሆነው ወገን ክሱን እንዲከላከል ከመጥራቱ በፊት ከሳሽ ክሱን ለማቅረብ የሚያስችል መነሻ ምክንያት ያለው ስለመሆኑና ፍ/ቤቱም አቤቱታውን ተቀብሎ ለማየት ስልጣን ያለው ስለመሆኑ መመርመር ይኖርበታል፡፡
ሰ/መ/ቁ. 32147 ቅጽ 6፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 231

5/ አንድ ሰው በተለያዩ ምክንያቶች በአባቱ ብቻ ሳይሆን በአሳዳጊው ስም ጭምር ሊጠራ የሚችልባቸው አጋጣሚዎች መኖራቸው የሚታወቅ ሲሆን እንዲህ ዓይነቱ ሰው ተገቢ ሆኖ ባገኘው ጊዜ በአሳዳጊው ስም ጭምር መጠራቱ ቀሪ ሆኖ በፍትሐብሔር ሕጉ መሰረት በአባቱ ስም ብቻ እንዲጠራ የመወሰን መብት ያለው በመሆኑ ይህንኑ መብቱን በፍርድ ለማረጋገጥ የሚያቀርበው የዳኝነት ጥያቄ የክስ ምክንያት የለውም የሚባልበት ሕጋዊ ምክንያት አይኖርም፡፡
ሰ/መ/ቁ. 95995 ቅጽ 15

6/ ከባዶ ቦታ ሽያጭ የመነጨ ግዴታ ለማስፈጸም የሚቀርብ አቤቱታ የክስ ምክንያት የለውም፡፡
ሰ/መ/ቁ. 27739 ቅጽ 6
በአብርሐም ዮሐንስ
#LegalServices #lawsocieties #Ethipianlawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
ውድ የተከበራችሁ የዚህ ቻናል እና ግሩፕ ቤተሰቦች የትዊትተር አካውንት የሌላችሁ የትዊተር አካውንት እንድትከፍቱና እንድትዘጋጁ የትዊተር አካዉንት እንዲኖራችሁ ትጠየቃላችሁ።
ከከፈታችሁ በሗላ የትዊተር አካዉንታችሁ እዚሁ ላይ ሸር በማድረግ Follow, Like and Retweet እናደርግላችሗለን።
ምክንያቱም፤
እንደ አንድ ዜጋ እውነትን ይዘን ዝም በማለታችን ውሸት ሀገራችንን ሲያፈርስ እንዳናይ የሀገራችንን እውነት ለአለም የምናሰማበት የትዊተር ዘመቻ ያስፈልገናል።

በዚህ ዘመን በአለም መንግስታት ውሳኔ ላይ ተፅዕኖ ፈጣሪ ከሆነው ሶሻል ሚዲያ ዋናው እና አንዱ Tweeter ነው።🩸

ስለ አከፋፈቱ የምናግዛችሁ ይሆናል።

📌ትዊት በምናደርግበት ሰዓት የትዊተር አካውንቶቻችን እንዳይዘጋብን የሚረዱ ጥቆማዎች‼️‼️

1.የትዊተር አካውንት ስም(username )በተቻለ መጠን ትክክለኛ ስም ያድርጉ

2.የትዊተር አካውንት ስም(username ) ከአንድ በላይ ቁጥር አያስገቡ

3.የትዊተር አካውንቶ ላይ ስልክ ቁጥርዎን መጨመር አይዘንጉ

4.Follow የሚያደርጓቸውን አካውንቶች ቁጥር በአንድ ጊዜ አያብዙ

5.የትዊተር ፎሎወር እናበዛለን የሚሉ መተግበሪያዎችን (applications )ፈፅመው አይጠቀሙ

6.ትዊተር በሚጠቀሙበት በተለይም ዘመቻ በሚያደርጉበት ጊዜ Tweet /Quote Tweet ሲያደርጉ የተወሰነ ደቂቃ ልዮነት ይኑረው(time gap of at least 5-10 minutes)

7.ዘመቻ ሲያደርጉ የሚፈልጓቸውን መልዕክተኛ በመምረጥ Schedule Tweet(በመረጡት የጊዜና የጊዜ ገደብ ራሱ tweet የሚያደርግሎትን አማራጭ ይጠቀሙ

8.እንደ tweet ሁሉ retweet የሚያደርጉበትን ድግግምሽ ክፍተት ይስጡ

9.ከስልክ ቁጥርዎ በተጨማሪ የኢሜል አድራሻ Account ላይ ማከልን አይዘንጉ

10. ዘመቻ ከሚደረግባቸው ወቅቶች ውጪ የራስዎን መልዕክት Tweet ያድርጉ

11.ደህንነታቸው የተረጋገጠ (Secured )መተግበሪያዎች (Twitter for Android/IOS) እና ማሰሻዎች ብቻ(Firefox, Chrome,Opera,Safari ) ትዊተርን ይጠቀሙ

12.ማንነት & አድራሻ መሰወሪያ (VPN) መተግበሪያዎችን አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ከመጠቀም ይቆጠቡ

13.በአጭር ጊዜ ውስጥ ብዙ ትዊቶችን like,reply ,retweet & quote tweet ከማድረግ ይቆጠቡ

14. ብዛት ላላቸው ተጠቃሚዎች ቀጥተኛ መልዕክት ከመላክ(direct messaging ) ይቆጠቡ

15 .የትዊተር የይለፍ ቃልዎን (twitter password )በመደበኛነት ይቀያይሩ : ተመሳሳይ የይለፍ ቃል (password) ከመጠቀም ይቆጠቡ።
via #UnityForEthiopia
base.apk
18.6 MB
Twitter for Android/IOS)
App ትዊተርን ይጠቀሙ‼️
via #UnityForEthiopia
Senior Attorney, Litigation


Job Summery

The Senior Attorney, Litigation is responsible for representing the Bank before judicial & quasi- judicial tribunals, preparation and handling of cases (pleading, defenses and petition).


Job Requirements:

Job Requirements

Academic & Professional Qualification

Bachelor’s Degree in Law from a reputable university.
Additional certification in law, banking, finance or similar fields is an added advantage

Experience

At least one (5) years experience 

Required Technical Competency

*Good understanding of court practice, litigation/dispute resolution with good knowledge in commercial law.
* Legal writing skills including ability to develop proposals, concept papers, position papers, legal memos and briefs as well as write reports.
* Experience in the litigation process- from institution of proceedings to settlement.
* Case management- ability to create appropriate litigation strategies, prioritize actions, ensure proper use of time and resources etc.

How To Apply:

How to Apply

1. Interested and qualified applicants should apply through 

https://forms.office.com/Pages/DesignPage.aspx?fragment=FormId%3DbeiahVyoYU60Iqj2TsjDW4jw3ZKRnaxBtKmvyXD88cZUMzhFWVpYWThHNThINjBZOVFNMjA0UllHTi4u%26Token%3Df66d650707fd43d2adc5ed7e3508198b

2.   Applicants should fill all the details on the vacancy application form and make sure you submit after completing all the questions

3.   Finally, please scan and attach all relevant credentials i.e. Uploading relevant credentials that verifies educational qualification, work experience licenses, certifications …. etc which are stated on the application form /CV shall be attached in PDF format (*mandatory) via (http://ethiojobs.net).

·         Applicants who do not have ethiojobs account need to register using personal email account,

·         CV‘s shall not be more than 3 pages and saved in PDF format (mandatory).

Posted:08.11.2021


Deadline:08.21.2021

Job Category:

Banking and Insurance, Legal
 

Employment:Full time

Location:Addis Ababa
Dashen Bank S.C
https://www.dashenbanksc.com/