አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.84K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
Forwarded from 💪 👊
ሰላም ሰላም አለዎች እንዴት ናቹ... ሰላማቹ ብዝት ይበልልኝ... እስኪ የአብክመ ህብረት ስራ ማህበራት አዋጅ ቁጥር 220/2007 ካላቹ እስኪ ተባበሩኝ
የሰ-መ-ቁ 196228 ውሳኔ ግልባጭ.pdf
4 MB
ከፍርድ ቤት ውጪ በአማራጭ የሙግት መፍቻ መንገዶች እልባት የተሰጠ አንድ የፍትሐብሔት ጉዳይ በፍርድ ቤት ቀርቦ በቀጥታ ለአፈጻጸም ሊቀርብ የሚችልበትን ሁኔታ በተመለከተ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁ. 196228 ግንቦት 25 ቀን 2013 ዓ.ም በዋለው ችሎት የሰጠው ውሳኔ
ለጊዜው ስለሚሰጡ ማገጃዎችና ሌሎች ትዕዛዞች
=================
1. ከፍርድ በፊት ስለሚሰጥ የእስራት ትዕዛዝ (ፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 147-150)
1.1. ከሳሹ ወይም ተከሳሹ የተከሳሽ ከሳሽ በሚሆንበት ጊዜ ሌላኛው ወገን ዋስትና እንዲሰጥ ለፍ/ቤቱ ማመልከት ይችላል፡፡
1.2. ማመልከቻው በመኃላ ቃል የተደገፈ መሆን አለበት፡፡
1.3. ማመልከቻው ተቀባይነት ሊያገኝ የሚችለው በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 147 (1) (ሀ) ና (ለ) ሥር የተዘረዘሩት ሁኔታዎች ሲረጋገጡ ነው፡፡ ሁኔታዎቹም ሀ/ ተከሳሹ በማንኛውም ሁኔታ የዳኝነት ሥርዓቱን የሚያስናክል ድርጊት ሲፈጽም ወይም ለ/ ተከሳሹ ከኢትዮጵያ ግዛት ለመውጣት ሲዘጋጅና መውጣቱም ፍርዱን እንዳይፈጽም የሚያደርገው ሲሆን ነው፡፡
1.4. ፍ/ቤቱ ጥያቄውን ከተቀበለ ተከሳሽ ታስሮ እንዲቀርብ ያዛል፡፡
1.5. ተከሳሹ የሚፈለግበትን ዕዳ በመያዣ ካስቀመጠ የእስር ትዕዛዙ ተፈፃሚ አይሆንም፡፡
1.6. ተከሳሹ መያዣውን ካላስቀመጠ ወይም ፍ/ቤት ቀርቦ በቂ ምክንያት ካልሰጠ በቂ መያዣ እንዲያስቀምጥ ወይም ዋስ እንዲጠራ ይታዘዛል፡፡
1.7. የዋስትናው ወይም የመያዣው ዓይነትና ልክ እንዲሁም ዋስትናው የሚቆይበት ጊዜ በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 148(1) መሠረት ይወሰናል፡፡
1.8. ተከሳሹን ለማቅረብ ዋስ የሆነ ሰው ሳያቀርብ የቀረ እነደሆነ ተከሳሹ ሊከፍል የሚገባውን ገንዘብ እንዲከፍል ይገደዳል (ፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 148(2))፡፡
1.9. በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 149 በተደነገገው መሠረት የዋስትና ግዴታ ሊወርድ ይችላል፡፡ ዋስትናው ሲወርድ ተከሳሹ ሌላ ዋስ ማቅረብ ወይም ተመጣጣኝ የሆነ መያዣ ማስቀመጥ አለበት፡፡
1.10. ተከሳሹ ይህን ግዴታ ለመፈፀም እምቢተኛ ከሆነ እንደሁኔታው እስከ ስድስት ወር በማረፍያ ቤት እንዲቆይ ለማዘዝ ይቻላል (ፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 150)፡፡ ተከሳሹ አዲስ ዋስ ለመጥራት ወይም መያዣ ለማስጠት ዓቅም የሌለው ከሆነ ግን ይህ ትዕዛዝ መሰጠት የለበትም፡፡ ተከሳሹ በማንኛውም ጊዜ ትዕዛዙን ከፈፀመ የማሰር ትዕዛዙ መነሳት አለበት፡፡
2. ከፍርድ በፊት ንብረትን ማስከበር (ፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 151-153)
2.1 በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 151(1) (ሀ) ና (ለ) ሥር የተዘረዘሩት ሁኔታዎች መኖራቸውን ከሳሹ ወይም የተከሳሽ ከሳሹ በመኃላ ቃል በተደገፈ አቤቱታ ወይም በሌላ ሁኔታ ማስረዳት ይችላል፡፡
2.2 ፍ/ቤቱ አቤቱታውን መርምሮ እውነት መሆኑን ካረጋገጠ ተከሳሹ ዋስትና እንዲሰጥ ወይም ለክርክሩ መነሻ የሆነው ንብረት ወይም ግምቱ እንዲቀርብ በወሰነው ጊዜ እንዲያመጣ ወይም ደግሞ ከሚያዘው ገንዘብ ወይም ንብረት ላይ ለሚሰጠው ፍርድ ተመዛዛኝ የሚሆን መጠን ያለው ገንዘብ ወይም ንብረት በፍ/ቤቱ እንዲቀመጥ ወይም ይህን መያዣ የማይሰጥበትን ምክንያት ቀርቦ እንዲያስረዳ ያዛል (ፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 151(1) (ለ)) ፡፡
2.3 የሚያዘው ንብረት የግድ ከሳሹ ያመለከተው ሁሉ ሳይሆን ከክሱ ገንዘብ ጋር ተመጣጣኝ መሆን አለበት (ፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 151(3) እና (1))፡፡ እንዲሁም በቁ. 404 እና በሌላ ሕግ እንዳይከበር የተወሰነ ንብረት መያዝ የለበትም፡፡
2.4 ተከሳሹ ዋስ ያልጠራበትን ምክንያት በሚገባ ካስረዳ ወይም የሚፈለግበትን መያዣ ከሰጠ ንብረቱ ይለቀቅለታል፡፡ (ፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 152 (2) እና 153(4))፡፡
2.5 ንብረቱ በሚከበርበት ጊዜ የሦስተኛ ወገኖች መብት መጠበቅ አለበት (ፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 153(2)(3)፣ 428-421 እና 443)፡፡
3. ለጊዜው የሚሰጥ የማገድ ትዕዛዝ (ፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 154-159)
1.1 በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 154 (ሀ) ና (ለ) ሥር የተመለከቱት ሁኔታዎች በመኃላ በተደገፈ ቃል ወይም በሌላ መንገድ ሲረጋገጡ ነገሩ በፍርድ እስኪወሰን ድረስ ወይም ሌላ ትዕዛዝ እስኪሰጥ ድረስ ክርክር የተነሳበት ንብረት እንዳለ እንዲቆይ፣ ከመጥፋት እንዲድን እንዳይበላሽ ለሌላ ሰው ተላልፎ እንዳይሰጥ ወይም ሌላ ስፍራ እንዳይዘዋወር ወይም እንዳይባክን ፍ/ቤቱ አስፈላጊውን ትዕዛዝ መስጠት አለበት፡፡
1.2 ውል ወይም ሌላ ግዴታ ተደጋግሞ እንዳይፈርስ ወይም ለማፍረስ የተወሰደው አርምጃ እንዳይቀጥል የሚሰጠው ያማገጃ ትዕዛዝ በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 155 መሠረት ይፈፀማል፡፡
1.3 የማገጃ ትዕዛዝ ያለማክበር የፍትሐብሔረና የወንጀል ኃላፊነትን ሊያስከትለ ይችላል (ፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 156)፡፡
1.4 የማገጃ ትዕዛዝ መሰጠት ያለበት ማመልከቻው ለሌላቸው ወገን ከደረሰው በኃላ ነው፡፡ ከዚህ ወጪ ትዕዛዙ ሊሰጥ የሚችለው መዘግየቱ ጉዳት ሊያደርስ የሚችል መስሎ ሲታይ ብቻ ነው (ለምሳሌ ንብረቱ የሚጠፋ ወይም የሚበላሽ ሲሆን )
1.5 የማገጃ ትዕዛዝ በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 158 በተደነገገው መሠረት ሊነሳ፣ ሊሠረዝ ወይም ሊሻሻል ይችላል፡፡
4. ከፍርድ በፊት ስለሚሰጥ ትዕዛዝ (ፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 160-165)
1.1 ለክርክሩ መነሻ የሆነው ወይም የተያዘው ንብረት ክርክሩ እስኪሰማ ቢቆይ የሚበላሽ መሆኑን ወይም መቆየቱ ሌላ ጉዳት ያለው መሆኑን ከተረዳው ፍርድ ቤቱ ንብረቱ እንዲሸጥ ማዘዝ ይችላል፡፡
1.2 ክርክር የተነሳበትን ሀብት በአንድ ስፍራ አኑሮ መጠበቅ፣ እንደይበላሽ የሚደረግ ጥንቃቄና የመቆጣጠር ምርምራ በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 161 በተደነገገው መሠረት ይፈፀማል፡፡
1.3 በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 160 እና 161 መሠረት በሚቀርበው አቤቱታ ለፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ከመሰጠቱ በፊት ለሌላኛው ወገን ማስታወቂያ መስጠት አለበት (ፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 162)፡፡
የውርስ ጉዳይን የተመለከቱ የይርጋ ገደቦች ከተመረጡ የሰበር ውሳኔዎች ጋር በማጠቃስ የቀረበ፤

ኑዛዜን ለመቃወም የተቀመጠ ጊዜ ገደብ
///////
ኑዛዜ ፈራሽ ነው የሚል ክስ የሚቀርብበትን የጊዜ ገደብ በተመለከተ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 እና 974 ላይ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ በቁጥር 973 ላይ የተመለከተው ተፈጻሚ ሚሆነው ኑዛዜ ፈራሽ ነው የሚለውን ክስ ኑዛዜው ሲነገር በነበሩ ሰዎች የቀረበ እንደሆነ ነው፡፡ ይህም ማለት በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973/1/ ላይ እንደተገለጸው “ኑዛዜ ሲነበብ የነበሩ ወይም የተወከሉ ሰዎች ኑዛዜው አይጸናም ወይም አንዱ በኑዛዜው የተነገረው ቃል አይጸናም በማለት ክስ ለማቅረብ ያላቸውን ሀሳብ መግለጫ ወይም ስለ ክፍያው በሂሳብ አጣሪው የቀረበውን የድልድል አመዳደብ ሀሳብ ለመቃወም ኑዛዜው ከተነበበት አንስቶ በሚቆጠር የአስራ አምስት ቀን ጊዜ አላቸው”፡፡
በሌላ መልኩ ደግሞ ኑዛዜው ሲነበብ ያልነበሩ ሰዎች መቃወሚያቸውን መቼ ሊቀርቡ ይችላሉ ለሚለው በፍ/ሕ/ቁ 974/1/ እና 2 ላይ የተገለጸ ሲሆን በዚህም መሰረት “ በኑዛዜ ንባብ ሥነ-ሥርዓት ላልነበሩ ወይም በኑዛዜው ንባብ ሥነ-ሥርዓት በወኪልነት ላልሰሙ ሰዎች እንዲሁም ኑዛዜው በሌሉበት የተነበበ እንደሆነ ከዚህ በላይ የተገለጸው የጊዜ ገደብ ለመቁጠር መነሻ የሚሆነው ሥለ ክፍያው ድልድልና አመዳደብ ሀሳቡን ከተነገራቸው ቀን አንስቶ ነው”፡፡
በፍ/በ/ህ/ቁ 973/2/ ላይ በተገለጸው መሰረት ኑዛዜ ከፈሰሰበት ጊዜ ከአምስት ዓመት በኋላ ወይም ኑዛዜ የሌለ እንደሆነ ሟች ከሞተ ከአምስት ዓመት በኋላ ስለ ኑዛዜው መጽናትና ስለክፍያው አመዳደብ አጣሪው ያቀረበውን የድልድል ሀሳብ በማናቸውም አስተያየት ቢሆን መቃወሚያ ሊቀርብበት አይችልም፡፡
ከዚህ በላይ ከተገለጹት የሕግ ድንጋጌዎች ጋር በተያያዘ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት በሰ/መ/ቁ 82585 በቅጽ 15 ላይ አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ የሰጠ ሲሆን በትርጓሜውም “በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 እና 974 ድንጋጌዎች አቤቱታ አቅርቢው ኑዛዜ ሲነበብ የነበረ ወይም የተወከለ የመሆን አለመሆን መስፈርት መሰረት በማድረግ ይርጋው መቁጠር የሚጀምርበትን ጊዜ እና ፍጹም የሆነ የይርጋ ጊዜ በቁጥር 974/2/ ከመደንገጋቸው በስተቀር ሁለቱም ድንጋጌዎች ኑዛዜው ፈራሽ ነው የሚል ክስ የሚቀርብበትን ስርዓት የሚደነግጉ በመሆቸው ተያያዥነት አላቸው በማለት ኑዛዜ መኖሩን ማወቅ እና የኑዛዜውን ሙሉ ይዘት ማወቅ የተለያዩ ጉዳዮች ናቸው ሲል በፍ/ብ/ህ/ቁ 973/1/ የተመለከተው የ15 ቀን ጊዜ ገደብ የክስ ማቅረቢያ ጊዜ ሳይሆን የመግለጫ ማቅረቢያ ጊዜ ነው፡፡ በመሆኑም ስለ ኑዛዜ መኖር እንጂ ስለድልድሉ የማያውቅ ወራሽ መግለጫ የማቅረብ ግዴታ ስለማይኖርበት ጊዜው መቁጠር የሚጀምረው በኑዛዜው የተደረገውን ድልድል ካወቁበት ቀን ጀምሮ ነው” በማለት ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
በሟች የተደረገ ኑዛዜ ከውርስ የነቀለኝ በመሆኑ ሊፍርስ ይገባል በማለት ኑዛዜው ሲነበብ በነበረ አመልካች የሚቀርብ የክስ አቤቱታ ሊቀርብ ሚገባው በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 መሰረት በተገለጠው የጊዜ ገደብ ነው ወይስ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1123 በተገለጸው ጊዜ ውስጥ ነው? የሚለው አከራካሪ ጉዳይ በመሆኑ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት በሰ/መ/ቁ 152134 በቅጽ 23 ላይ አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡ በውሳኔውም መሰረት በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 ስለ ኑዛዜ መነበብ እንዲሁም ኑዛዜ ሲነበብ የነበሩ ሰዎች ኑዛዜው እንዲፈርስ አቤቱታ የሚያቀርቡበትን ሥርዓትና ጊዜውን በሚመለከት የሚደነግግ ነው፡፡ ይህ ድንጋጌ ኑዛዜው ከውርስ ነቅሎኛል /ነቅሎናል/ በማለት ኑዛዜው እንዲፈርስ የሚቀርብን ወይም የቀረበ አቤቱታን የሚመለከት አይይለም፡፡ በመሆኑም ኑዛዜው ከውርስ የመንቀል ውጤት ያለው በመሆኑ እንዲፈርስ በሚል የሚቀርብ የዳኝነት ጥያቄ ሊታይ የሚገባው በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1123 መሰረት ነውእንጂ በአንቀጽ 973 መሰረት አይደለም በማለት አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡ ስለዚህ ከዚህ በላይ በተጠቀሰው የሕግ ትርጓሜ መሰረት ኑዛዜ ሲነበብ የነበረ አመልካች ኑዛዜው ከውርስ ነቅሎኛል በማለት የሚያቀርበው የክስ አቤቱታ ሊቀርብ ሚገባው በፍ/ህ/ቁ 973 መሰረት ሳይሆን በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1123 መሰረት በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ነው የሚል መደምደሚያ ላይ መድረስ ይቻላል፡፡
በአጠቃላይ አንድ ኑዛዜ ፈራሽ ነው በሚል ስለሚቀርብ መግለጫ እና እንዲሁም መግለጫው እና ክሱ ሊቀርብ ስለሚገባው የጊዜ ገደብ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 እና 974 ተደንግጎ ይገኛል፡፡ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 ተፈጻሚነት የሚኖረው ኑዛዜ ሲነበብ በነበሩ ወይም በተወከሉ ሰዎች ጉዳይ ሲሆን በአንቀጽ 974 ድንጋጌ ደግሞ ተፈጻሚነቱ በኑዛዜ ሥነ-ሥርዓት ባልነበሩ ወይም ባልተወከሉ ሰዎች ጉዳይ ነው፡፡ ኑዛዜ ሲነበብ የነበረ አመልካች ኑዛዜው ከውርስ ነቅሎኛል በማለት የሚያቀርበው የክስ አቤቱታ ሊቀርብ ሚገባው በፍ/ህ/ቁ 973 መሰረት ሳይሆን በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1123 መሰረት ነው፡፡
//////
የወራሽነት ጥያቄ ለማቅረብ የተቀመጠ ጊዜ ገደብ🇪🇹
///////
የወራሽነት ጥያቄን ለማቅረብ የተቀመጠ የጊዜ ገደብ የሚመለከቱ የሕግ ድንጋጌዎች በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1000 ላይ የተመለከተ ሲሆን ወደዚህ ነጥብ ከመግባቴ በፊት ወራሽነት ጥያቄ ማለት ምን ማለት ነው የሚለውን እደሚከተለው ለመዳሰስ እሞክራለሁ÷
በፍ/ብ/ሕ/ቁ 996(1) ላይ በተገለጸው መሰረት ወራሽ የሆነ ሰው የሟቹ ወራሽ መሆኑንና ከውርሱ ላይ የሚያገኘውን ድርሻ የሚያመለክት የወራሽነት የምስክር ወረቀት እንዲሰጠው ለፍርድ ቤት ጥያቄ ማቅረብ ይቻላል በማለት የተገለጸ ሲሆን ይህ ማለት ፍ/ቤቱ የወራሽነት ምስክር እንዲሰጠው ወራሹ ሲፈልግ የሚጠይቀው እንጂ ሟችን ለመውረስ የግድ ከፍ/ቤቱ የወራሽነት ማስረጃ ማምጣት እንዳለበት የሚያስገድድ አይደለም፡፡ ሆኖም ግን በተግባር እንደሚስተዋለው ስመ ንብረቱ ለማዛወር እና ከሌሎች የሟች መብቶች ለመጠቀምና ለመስራት በፍ/ቤቱ የተረጋገጠ የወራሽነት የምስክር ወረቀት መጠየቁ የተለመደ አሰራር ሆኗል፡፡
ከዚህ በላይ የተጠቀሰውን መሰረት በማድረግ አንድ ሰው ዋጋ ያለው የወራሽነት ማስረጃ ሳይኖረው ውርሱን ወይም ከውርሱ አንዱን ክፍል በእጁ ያደረገ እንደሆነ እውነተኛው ወራሽ ወራሽነቱን እንዲታወቅለትና የተወሰዱበት የውርስ ንብረቶች እንዲመለሱለት በዚህ ሰው ላይ የወራሽነት ጥያቄ ክስ ሊያቀብበት ይችላል በማለት በፍ/ብ/ሕ/ቁ 999 ላይ ተደንግጓል፡፡ ስለዚህ ይህን መሰል የክስ አቤቱታ አቤቱታ መቼ ሊቀርብ ይገናል ለሚለው የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1000/1/ ላይ የጊዜ ገደብ ተቀምጧል፡፡
በዚሁ መሰረት ከሳሽ መብቱንና የውርሱን ንብረት በተከሳሽ መያዛቸውን ካወቅ ሶስት ዓመት ካለፈ በኋላ ስለ ወራሽነት ጥያቄ የሚቀርበው ክስ ተቀባይነት ሊያገኝ አይችልም፡፡ በሌላ መልኩ በአንቀጽ 1000(2) ላይ እንደተገለጸው “ሟቹ ከሞተበት ወይም ከሳሹ በመብቱ ለመስራት ከቻለበት ቀን አንስቶ አስራ አምስት አመት ካለፈ በኋላ ከዘር የወረደ ርስት ካልሆነ በቀር የውርስ ጥያቄ ክስ በማናቸውም አስተያየት ቢሆን ተቀባይነት አያገኝም የሚለው ተደንግጎ ይገኛል፡፡
ከዚህ በላይ በአንቀጽ 1000(1) እና (2) ላይ የተመለከቱት የጊዜ ገደቦች ከሌሎች የውርስ ሕግ ድንጋጌዎች በተለይም 1ኛ) አንድ ወራሽ የሟች ኑዛዜ ተጠቃሚ መሆን የሚችለው ኑዛዜ በእጁ እንደሚገኝ ለውርስ አጣሪው አቅርቦ ውርስ አጣሪው ኑዛዜውን በሚነበብበት ሰዓት ራሱ ወይም ወኪሉ ካልነበረ ወራሹ ኑዛዜው ከፈሰሰበት ቀን አንስቶ በአስራ አምስት አመታት ውስጥ መቃወሚያ ካላቀረበ ከዚያ በኋላ ሊቀርብ እንደማይችል በፍ/ሕ/ቁ 974(2) የተመለከተው በፍ/ሕ/ቁ 1000(1) ካለው የጊዜ ገደብ ጋር እንዴት ተጣጥሞ ተግባራዊ ይሆናሉ ከሚለው ጋር ጥያቄ የሚያስነሳ ሲሆን በሌላ መልኩ በፍ/ሕ/ቁ 1000(1) እና (2) አተረጓጎምና አፈጻጸም እንዴት መሆን አለበት በሚል አልፎ አልፎ ጥያቄ ሲያስነሳ ይስተዋላል፡፡ ስለዚህ በእነዚህ የሕግ ማዕቀፎች ላይ የተጠቀሱት የጊዜ ገደቦች በተመለከተ መከተል የሚገባንን የሕግ ትርጓሜ እንደሚከተው ለማብራራት ተሞክሯል÷ የፍ/ብ/ሕ/ቁ 974/2/ ተፈጻሚ የሚሆነው የሟች ውርስ የሚያጣራ ፤በሕግ በኑዛዜ ወይም በፍርድ ቤት የተሾመ የውርስ አጣሪ ፤ሟች አድርጎታል የተባለው ኑዛዜ አግኝቶ የኑዛዜውን ፎርምን የኑዛዜውን ዋጋ መኖር ፤የሟች ያለኑዛዜ ወራሾች ወይም አራት አካለመጠን ያደረሱ ሰዎች ባሉበት በፍ/ብ/ሕ/ቁ 968 በተመረመረበት ሁኔታ ነው፡፡ ሆኖም ግን ኑዛዜ ያለ መሆኑን ለውርስ አጣሪው ሳያሳውቅ ቀጥታ የኑዛዜ ወራሽ መሆኑ እንዲታወቅለት ለፍ/ቤት አመልክቶ የወራሽነት የምስክር ወረቀት በመውሰድ የሟች ንብረት በእጁ ያደረገ ሰው ወይም በሀሰት የሟች ያለኑዛዜ ወራሽ ነኝ ብሎ የሟችን ንብረት ከወሰደው ሰው ለማስመለስ አግባብ የሆነው የይርጋ ገደብ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 968 የተጠቀሰው ሳይሆን በፍብ/ሕ/ቁ 1000/1/ የተመለከተው ተፈጻሚነት ሊኖረው ይገባል፡፡
በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1000/1/ እና 1000/2/ አስመልክቶ የተለያዩ አተረጓገሞች የሚስተዋሉ ሲሆን ለዚህ ጽሁፍ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት በሰ/መ/ቁ 30158 ፤26422 እና 34011 በቅጽ 7/6/6/ እንዲሁም በቅጽ 11 በሰ/መ/ቁ 52407 የሰጠውን አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ ለመዳሰስ ሞክሬያለው፡፡ በዚሁ አግባብ በፍ/ሕ/ቁ 1000/2/ ላይ ሟች ከሞተ አስራ አምስት አመት በላይ ወይም ተከሳሹ በመብቱ ሊሰራበት ከቻለበት ቀን አንስቶ አስራ አምስት ዓመት ውስጥ ክስ ካልቀረበ አስራ አምስት ዓመት ካለፈው በኋላ ክስ ሊያቀርብ የሚቻለው ከዘር የወረደ ርስት በሆነ ንብረት ላይ ነው፡፡
ርስት የሚለው ቃል በፍ/ሕ/ቁ 1130 እና ስለ ንብረቶች በሚናገረው የፍ/ብሔር የህጉ ክፍል መሬት የሚያመለክት መሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡ በኢትዮጲያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማዕከል የተዘጋጀው የአማርኛ መዝገበ ቃላት ርዕስት የሚለው መሬትን የሚመለከት መሆኑን ጠቅሶ ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡ በዚሁ አግባብ ከዘር የወረደ ርዕስት የሚለው ቤትን አያጠቃልልም የሚል መደምደሚያ ላይ መድረስ ይቻላል፡፡ በርዕስት የሚተላለፍ መሬት ብቻ ማለት ሰለሆነ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1000/2/ መሰረት ለተወላጆች የሚተላለፍ መሬት ብቻ ነው የሚል መደምደሚያ ላይ መድረስ ይቻላል፡፡
በኢፌድሪ ህገ መንግስት መሰረት መሬት የመንግስትና የህዝብ ሀብት በመሆኑ ከዘር የወረደ ርዕስት ካልሆነ በስተቀር በማለት በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1000/2/ ላይ የተገለጸው የተሻረ እና ተፈጻሚነት የሌለው ነው በማለት አስገዳጅ ውሳኔ ተሰጥቷል፡፡
የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1000/1/ አፈጻጸምን በተመለከተ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት በሰ/መ/ቁ 32407 በቅጽ 11 ላይ ትርጓሜ የሰጠ ሲሆን በዚህም መሰረት በወራሾች መካከል የሚነሳ የውርስ ንብረት ክርክር በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1000/1/ በተደነገገው አግባብ በሶስት አመት ጊዜ ውስጥ መቅረብ ያለበት ሲሆን ወራሽ በሆነ እና ወራሽ ባልሆነ ተከራካሪ ወገን መካከል የሚቀርበው የውርስ ንብረት ይገባኛል ጥያቄ በፍ/ብ/ህ/ቁ 1677 እና 1845 መሰረት በአስር አመት ጊዜ ውስጥ ካልቀረበ መብቱ በይርጋ የሚታገድ ይሆናል፡፡
//////
የክፍፍል ጥያቄ በይርጋ የማይታገድ ስለመሆኑ
/////🇪🇹
ወራሾች ተለይተው የውርስ ሀብቱ ድርሻ ታውቆ ግን ክፍፍል ሳይደረግ የቆየ የውርስ ሀብት ያለ እንደሆነ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1062 በተገለጸው መሰረት እያንዳንዱ የጋራ ወራሾች ውርሱን እንከፋፈል በማለት በማንኛውም ጊዜ ለመጠየቅ የሚችሉ በመሆኑ የክፍፍል ጥያቄ በይርጋ የማይታገድ ይሆናል፡፡
//////
መደምደሚያ
///////
በአጠቃላይ አንድ ሰው ከዚህ አለም በሞት የተለየ እንደሆነ የውርስ ጉዳዩን በተመለከተ ወራሽ የሆነ ወገን ኑዛዜን ሚቃወምበት፤የወራሽነት ጥያቄ ሚያቀርብበትና ክፍፍል የሚጠይቅባቸው የጊዜ ገደቦች ከዚህ በላይ በተገለጸው አግባብ ተፈጻሚ ሚሆኑ ሲሆን ባለመብት የሆነ ወገን ጥያቄውን በህጉ በተመለከተው የጊዜ ገደብ ውስጥ ያላቀረበ እንደሆነ ውጤቱ መብቱን እስከማጣት የሚደረስ ይሆናል፡፡
#like #shareshare ያድርጉ።

(By Muluken Seid Hassen)
source Abyssinialaw.com
የሰ-መ-ቁ 196228 ውሳኔ ግልባጭ.pdf
4 MB
ከፍርድ ቤት ውጪ በአማራጭ የሙግት መፍቻ መንገዶች እልባት የተሰጠ አንድ የፍትሐብሔት ጉዳይ በፍርድ ቤት ቀርቦ በቀጥታ ለአፈጻጸም ሊቀርብ የሚችልበትን ሁኔታ በተመለከተ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁ. 196228 ግንቦት 25 ቀን 2013 ዓ.ም በዋለው ችሎት የሰጠው ውሳኔ
አስቸኳይ ማስታወቂያ ‼️
ተመርቀው ስራ በማፈላለግ ላይ ያሉ
5 ስራ ፈላጊዎች በኢንተርን(intern) መቅጠር ይፈልጋል።

ነገ ሀሙስ መጀመር የሚችሉ መሆን አለባቸው።
ነገ ሀሙስ 24/10/2013 ዓ.ም
ሳር ቤት ADAMS Pavilion ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር S14
በአካል ተገኙ እንላለን።

ለበለጠ መረጃ፤

Tel: +251 11 834 2741
or
Tel: +251 11 827 9746

............‼️ urgent ‼️.................
for tomorrow ............

We want additional 5 (five) interns.....?

only Five (5)

the person that who can work full day two (2) days per a week.
#Transparency_International_Ethiopia
via @Transparency_Ethiopia_Bot


@Transparency_Ethiopia_Bot
https://t.me/TransparencyEthiopia
@TransparencyEthiopia
https://t.me/TransparencyEthiopia
የኢትዮጵያ_ብሔራዊ_ምርጫ_ቦርድ_የ6ተኛዉ_አጠቃላይ_ሀገራዊ_ምርጫ_ዉጤት_.pdf
2.7 MB
#ምርጫ2013

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት ይፋ ያደረጋቸው የተረጋገጡ የምርጫ ውጤቶች ከላይ በ PDF ፋይል (2.7 MB) ተያይዟል።
. https://et.linkedin.com/jobs/view/associate-legal-expert-at-african-union-2581241876?refId=PSpMO1gkNPOGY7zJvcAmLg%3D%3D&trackingId=T5GzvjAlsiphTvSuMACWDQ%3D%3D&position=3&pageNum=0&trk=public_jobs_jserp-result_search-card&utm_campaign=google_jobs_apply&utm_source=google_jobs_apply&utm_medium=organic

TENURE OF APPOINTMENT: The Appointment will be made on a fixed term contract for a period of one (1) year, of which the first three (3) months will be considered as a probationary period. Thereafter, the contract may be renewed for a similar period subject to funding availability, satisfactory performance and agreed deliverables.

GENDER MAINSTREAMING: The AU Commission is an equal opportunity employer and qualified women are strongly encouraged to apply. REMUNERATION: The salary attached to the position is an annual lump-sum of US$ 85,212.07 (P2 Step 5) inclusive of all allowances for internationally recruited staff, and US$ 66,751.81 inclusive of all allowances for locally recruited staff of the African Union Commission. Applications must be made not later than 9 July 2021. Requisition ID: 504
ነፃ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት እና የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደቱ
----------*****-----------

መግቢያ

ሰዎች በወንጀልም ይሁን በፍትሐብሔር ጉዳይ ክስ ቀርቦባቸዉ ወይም ክስ አቅረበዉ ወደ ፍትህ አካላት በተለይም ፖሊስ ጣቢያና ፍርድ ቤት ሊቀርቡ ይችላሉ፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ ሕግን እና የሕግ ሥርዓትን አካሄድ ማወቅ ጠቃሚ ነዉ፡፡ ሆኖም ግን ሁሉም ሰዉ ሕግ የተማረ፣ ስለሕግ በቂ ዕውቀት እና ግንዛቤ ያለዉ ሊሆን ስለማይችል በሕግ ባለሙያ መደገፍ አስፈላጊ ይሆናል፡፡ በዚህ መሰረት አብዛኛቹ ሀገራት ነፃ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት ለሚገባቸዉ ሰዎች የሕግ ማዕቀፍ በማዉጣት አገልግሎቱን እየሰጡ ይገኛሉ፡፡

ሀገራችን ኢትዮጵያም ነፃ የሕግ ድጋፍ አገልግሎትን ለኅብረተሰቡ ተደራሽ ለማደረግ በተለይም ለጥቃት ተጋላጭ ለሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎችና የወንጀል ሰለባ ለሆኑ ሰዎች፣ ለበጎአድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት የሕግ ማዕቀፎችን ለአብነት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግስት አንቀጽ 20 (5)፣ የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 943/2008 አንቀጽ 6(4) (8) (11)፣ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ጠበቆች ፈቃድ አሰጣጥ ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 199/1992 እና የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ጠበቆች የሥነ- ምግባር ደንብ ቁጥር 57/1992 እንዲሁም የክልሎች ተመሳሳይ ሕጎችን በማዉጣት እና በመመሪያና በአሰራር ማንዋል በመደገፍ አገልግሎቱን እየሰጠች ትገኛለች፡:

1. ነፃ የሕግ ድጋፍ ምንነት፣ አስፈላጊነትና ዓላማ

የነፃ የህግ ድጋፍ አገልግሎት ማለት የፍትህ ስርዓቱ ፍትሐዊና ተደራሽ እንዲሆን ለጠበቃ ገንዘብ ለመክፈል ለማይችሉ፣ በኢኮኖሚ አቅም በአነስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ የገንዘብ አቅም ለሌላቸዉ ለበጎ አድራጎት ደርጅቶች እና ማኅበራት አገልግሎቱን በነፃ እንዲያገኙ ዓላማ አድርጎ የሚሰጥ አገልግሎት ነው፡፡ በተጨማሪም የነፃ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት የፍትሕ ሥርዓቱን ፍትሐዊና ሚዛናዊ የማድረግ ዓላማን ይዞ ለፍትሕ አሰጣጥ አስፈላጊ መሆኑ በተደነገገ ጊዜ እንዲሁም በክፍያ የሕግ አገልግሎት ሊገኝ በማይችልባቸዉ አካባቢዎችም ነዋሪ ለሆኑ ዜጎች ይሰጣል፡፡ ይህ አገልግሎት መንግስታዊ እና መንግስታዊ ባልሆኑ አገር በቀል ተቋማት በኩል የሚሰጥ ነዉ፡፡ ነፃ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት በራሱ መብት ነዉ፡፡ የሕግ ግንዛቤ መኖር ሰዎች ሊደርሱባቸው ከሚችሉ ጥቃቶች የመጠበቅ መብቶች እንዳሉዋቸው እንዲረዱ ቢያደርጓቸውም የነዚህ መብቶች ጥሰት ከደረሰ በኋላ ግን የሕግ ባለሙያዎች መግባት አለባቸው። ይህ የሚሆነዉ በጠበቃ ታግዞ ለመከራከር የገንዘብ አቅም የሌላቸዉ ሰዎች የፍትህ እርዳታ ማግኘት አስፈላጊ በመሆኑ ነዉ፡፡ ምክንያቱም በገንዘብ ማጣት ምክንያት ዜጎች ፍትሕ የማግኘት መብታቸዉን እንዳያጡ ለማድረግ ነዉ።
የፍትሕ ተደራሽነት በዉስጡ ሶስት መሰረታዊ መብቶችን የያዘ ሲሆን እነሱም፡- የሕግ ተደራሽነት፣ በሕግ ባለሙያ የመታገዝ መብት እና የፍርድ ቤት ተደራሽነት መብት ናቸዉ፡፡በዚህ ጽሁፍ የምንመለከተዉ በሕግ ባለሙያ የመታገዝ መብትን ነዉ፡፡ በሕግ ባለሙያ የመታገዝ መብት ማለት አንድ የወንጀል ተጠርጣሪ ወይም የፍትሐብሔር ወይም የአስተዳደር ሙግት ተሳታፊ የሆነ ግለሰብ ለጉዳዩ የሚረዳዉና ብቃት ያለዉ የሕግ ምክርና በዉክልና በፍርድ ቤት በሚደረግ ክርክር በክፍያ ወይም ያለ ክፍያ ለማግኘት የሚቻልበት አግባብ ነዉ፡፡ በዚህ ላይ ለማየት የምንሞክረዉ ግን በነፃ የሚሰጠዉን የሕግ ድጋፍ አገልግሎት ነዉ፡፡

2. በነፃ የሕግ ድጋፍ የሚሸፈኑ ጉዳዮች

በሕግ ባለሙያ የመታገዝ መብት በአብዛኛዉ ከወንጀል ጉዳይ ጋር በተገኛኘ መታየቱ የተለመደ ቢሆንም ወንጀል ነክ ባልሆኑ (ፍትሐብሔራዊና አስተዳደራዊ) ጉዳዮችም መብቱ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡ የፍትሐብሔር ጉዳዮች ምንም እንኳ እንደወንጀል ጉዳይ ሕይወትና ነፃነትን የሚያሳጡ ባይሆኑም የሀብትና ንብረት መብትን እና ማህበራዊ ጥቅሞችን አዳጋ ዉስጥ የመክትት ዉጤት ስለሚኖራቸዉ በፍትሐብሔር ጉዳይም የሕግ ባለሙያ ድጋፍ የማግኘት ጉዳይ አስፈላጊነቱ ትኩረት እያገኘ መጥቷል፡፡ የፍትሐብሔር ሥነ-ሥርዓት ሕግ ያለዉ ዉስብስብነትና ጠበቃ መቅጠር ከሚችሉ ተሟጋቾች ጋር ያለዉን የክርክር ሚዛን ማጣትን መመልከት የመብቱን አስፈላጊነት የበለጠ ለመረዳት ያስችላል፡፡ በተጨማሪም በሕግ ፊት እኩል የመዳኘት መብት (አንቀጽ 25)፣ የሴች መብት (አንቀጽ 35)፣ የህፃናት መብት (አንቀጽ 36)፣ የተያዙ ሰዎች መብት (አንቀጽ19) እና የተከሰሱ ሰዎች መብት (አንቀጽ 20) በበለጠ በአገራችን እንዲከበሩ ለማድረግ ነፃ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡ በሀገራችን ኢትዮጵያ ዜጎች ነፃ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ሆኔታ በማመቻቸት እና ሥርዓት በመዘርጋት ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል፡፡

3. ነፃ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት ተጠቃሚዎች

ነፃ የሕግ ድጋፍ ባለመብት ለሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎች በሕግ መሰረት ከክፍያ ነፃ የሆነ የሕግ ምክር፣ የክስ አቤቱታ የማዘጋጀት እና የመከራከር አገልግሎት የሕግ ባለሙያዎች ይሰጣል፡፡ አብዛኛዉን ጊዜ ይህን ድጋፍ የሚጠይቁት በገንዘባቸዉ ጠበቃ ማቆም የማይችሉ ቢሆኑም አልፎ አልፎም ቢሆን ሌሎች የገንዘብ አቅም ያላቸዉ የኅብረተሰብ ክፍሎችም ይህን አገልግሎት ሲጠይቁ ይስተዋላል፡፡ በዚህ አግባብ ተጠቃሚነት ለመለየት የተለያዩ የመመዘኛ መስፈርቶችን በማዉጣት አገልግሎቱን ተደራሽ ማድረግ አስፈላጊ ነዉ፡፡ የመመዘኛ መስፈርቶችን በተመለከተ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግስት የተቀመጡ መሰረታዊ መብቶችን ባማከለ መልኩ እንዲሁም የሀገራችን ኢኮኖሚያዊ አቅም ባገናዘበ መንገድ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች የኢኮኖሚ አቅም፣ ፆታ፣ ለመብት ጥሰት እና ለማኅበረሰቡ የሚያስገኘዉ ጠቀሜታ እና የመሳሰሉትን ጉዳዮች እንደመመዘኛ ነጥቦች ተወስዶ ነዉ፡፡ ነፃ የሕግ ድጋፍ አገልግሎቱ የሚሰጠዉ ግለሰብ የኢኮኖሚ አቅም እንደሌለዉ ለማረጋገጥ ግለሰቡ ከተለያዩ ምንጮች የሚያገኛቸዉን ገቢዎች፣ ቋሚ እና ተንቀሳቀሽ ንብረት ታይቶ ይሆናል፡፡

ስለሆነም ነፃ የሕግ ድጋፍ የሚሰጠዉ ጠበቃ አቁሞ ለመከራከር የገንዘብ አቅም ለሌላቸዉ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ የራሳቸዉ የሕግ ባለሙያ ለሌላቸዉ የኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ወይም የኢትዮጵያ ማኅበራት እና ለትክክለኛ ፍትሕ አሰጣጥ ሲባል ፍርድ ቤቶች ወደ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ እና ጠበቆች የሚልኳቸዉ ሰዎችና ድርጅቶች ሲሆን በወንጀል ደግሞ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግስት አንቀጽ 20 ንዑስ አንቀጽ (5) መሰረት የተከሰሱ ሰዎች ጠበቃ ለማቆም አቅም በማጣቸዉ ፍትሕ ሊጓደል የሚችልበት ሁኔታ ሲያጋጥም ከመንግስት ጠበቃ የማግኘት መብት ያላቸዉ በመሆኑ ፍ/ቤት በነፃ በሚመድባቸዉ ተከላካይ ጠበቆች የሚወከሉ ይሆናል፡፡

4. በነፃ የሕግ ድጋፍ የሚሰጡ የአገልግሎት ዓይነቶች

ነፃ የህግ አገልግሎት ከሕግ ምክር አገልግሎት ጀምሮ ተከራክሮ ማስወሰንና ማስፈፀምን ጭምር የሚያጠቃልል ሲሆን በዋናነት፡
• የሕግ ምክር አገልግሎት መስጠት፣