list of laws 1934-2011.pdf
1.1 MB
LIST OF ALL PROCLAMATIONS
የአዋጆች ዝርዝር ከ1934 ዓ.ም. እስከ 2011 ዓ.ም. ድረስ
ከአዋጅ ቁ. 1-1934 እስከ 1100-2011 ዓ.ም ድረስ
በጠቅላይ ዓቃቤ ህግ የተዘጋጀ
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
የአዋጆች ዝርዝር ከ1934 ዓ.ም. እስከ 2011 ዓ.ም. ድረስ
ከአዋጅ ቁ. 1-1934 እስከ 1100-2011 ዓ.ም ድረስ
በጠቅላይ ዓቃቤ ህግ የተዘጋጀ
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
Exit Exam ውጤት #በትንሽ ነጥብ ልዩነት ያልመጣላችሁ ውድ የህግ ቤተሰቦች ውጤት በወጣ በ15 ቀን ውስጥ remark (እንደገና ይታረምልኝ) ጥያቄ በህግ ት/ቤታችሁ በኩል በፅሁፍ በማመልከት መጠየቅ ትችላላችሁ። ለበለጠ መረጃ የህግ ት/ቤታችሁን ሄድ ፤ ዲን ወይም ሀላፊ በመጠየቅ እንደገና ለማሳረም መስፈርቱን የምታሟሉ ከሆነ ብቻ ሂደቱን ጠብቃችሁ እንድታመለክቱ እናበረታታችኋለን።
የመረጃው ምንጭ @lawsocieties #አለ #ALE
We go together‼️
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
የመረጃው ምንጭ @lawsocieties #አለ #ALE
We go together‼️
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
Forwarded from Deleted Account
ALE families
Please share me if you have the english version of the new proclamation for amnesty 1096/2018.
Thankyou in advance.
Please share me if you have the english version of the new proclamation for amnesty 1096/2018.
Thankyou in advance.
መመሪያ ቁጥር 45-2007.pdf
34.7 MB
የከተማ የመሬት ይዞታ ማረጋገጥ እና ምዝገባ መመሪያ ቁጥር 45-2007
ታህሳስ 2007 ዓ.ም.
አውጭው ባለስልጣን፡ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
#DIRECTIVES
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
ታህሳስ 2007 ዓ.ም.
አውጭው ባለስልጣን፡ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
#DIRECTIVES
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
📌 #የከተማ መሬትና ቤት ይዞታ ስመ-ንብረት ዝውውር እንዴት ይፈፀማል ❓
በስመ ንብረት ዝውውር ወቅት መሟላት ያለባቸው መረጃዎች የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በወጣው አዋጅ ቁጥር 721/2004 አንቀፅ 33 ንዑስ አንቀፅ 2 አንፃር ሲታይ
🛑 1.1. የከተማ ቤትና ይዞታ ስመ-ንብረት ዝውውር ስለመፈጸም የሚከተሉት ማስረጃዎች/ሰነዶች ሲሟሉ የስመ ንብረት ዝውውር የሚፈጸም ይሆናል፤ 👇
1) ህጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት/ካርታ፣
2) ጸድቆ የተሰጠ የግንባታ ፕላን፣ የስራ ዝርዝር ግምት ወይም የጸደቀ የነባር ግንባታ ፕላን፣
3) ጸድቆ በተሰጠው የግንባታ ፕላን መሰረት ስለመገንባቱ እና ግንባታው ያለበት ደረጃ የተረጋገጠበት ማስረጃ/50% እና በላይ/፤
4) ውዝፍ የሊዝ/ኪራይ ዕዳ የሌለበት ስለመሆኑ የተሰጠ የማረጋገጫ ደብዳቤ ወይም ቀሪ የሊዝ ክፍያ ዕዳውን ገዥው ለመክፈል በፊርማ ያረጋገጠበት የስምምነት ደብዳቤ ፣
5) በንብረቱ ላይ የባንክ እዳ/የፍ/ቤት ዕግድ የሌለበት ስለመሆኑ ማረጋገጫ ሲቀርብ፣
6) የቤትና ይዞታ ስም ዝውውር ጥያቄው የቀረበው በህግ ባለመብት/በውርስ/በፍርድ አፈጻጸም ወይም በውክልና ከሆነ ይህንኑ የሚገልጽ ማስረጃ፤
7) በግለሰቦች ግዥና ሽያጭ ወይም ስጦታ ስምምነት ከሆነ በዉልና ማስረጃ በአካል ቀርቦ በእማኞች የተፈረመ የስምምነት የውል ማስረጃ ሲቀርብ፣
🛑 1.2. በሽያጭ/በስጦታ የሚተላለፍ ቤትና ይዞታ ስም-ዝውውር መሟላት ያለባቸው መስፈርቶች፣ 👇
1) ግንባታው በዋስትና ያልተያዘ እንዲሁም እዳ የሌለበት መሆኑ ሲረጋገጥ ወይም እዳው በሚመለከተው አካል በደብዳቤ መነሳቱ ሲረጋገጥ፣
2) የቤትና ይዞታ ሽያጭ ወይም የስጦታ ውሉ በምስክሮች ሲረጋገጥና በፍትህ ወይም በመሪ ማዘጋጃ ቤት ፊት ቀርቦ ሲጸድቅ፣
3) ግንባታው ጸድቆ በተሰጠው ዲዛይን መሰረት 50 በመቶና በላይ የተሰራ መሆኑ በባለሙያ ተረጋግጦ ሲቀርብ፣
4) በይዞታው ላይ ውዝፍ የቦታ ኪራይ የሌለበት ስለመሆኑ ወይም ውዝፍ የቦታ ኪራይ ክፍያ አጠናቆ የከፈለ ስለመሆኑ የቀረበ ክፍያ ደረሰኝ ማረጃ ሲቀርብ፣
5) የአገልግሎትና የገቢዎች ክፍያ በቤቱ ግምት መሰረት ስለመከፈሉ ሲረጋገጥ፣
🛑 #ዝውውሩ የሚፈፀመው #በሊዝ በተገኘ ይዞታና ግንባታ ላይ ከሆነ
1) የሊዝ ይዞታ ባለቤትነት ኦሪጅናል ካርታና ውል ሲቀርብ፣
2) በሊዝ ውል መሰረት ክፍያው የተጠናቀቀና ሌሎች ግዴታዎቹን የተወጣ መሆኑ ሲረጋገጥ ወይም የሊዝ እዳው ያልተጠናቀቀ ከሆነ ስም የሚዞርለት ወገን እዳውን ለመክፈል እና ነባሩን የሊዝ ውል ግዴታዎች የተቀበለ ስለመሆኑ ከከተማው በጽሁፍና በፊርማ አረጋግጦ ሲያቀርብ፣
3) በሊዝ የተገዛን የመሬት ይዞታ ለሌላ ሰው ለማስተላለፍ በቅድሚያ በገባው የሊዝ ውል መሰረት በተቀመጠው የጊዜ ገደብ የሚፈለገውን የግንባታ ደረጃ ያሟላ መሆኑ ወይም የግንባታ ፈቃድ የጊዜ ገደብ ያላለፈ ወይም የግንባታ ማራዘሚያ የተፈቀደለት መሆኑ ሲረጋጥ፣
4) የከተማ ቤትና ይዞታ ሽያጭ ወይም የስጦታ ውሉ በምስክሮች ሲረጋጥና በዉልና ማስረጃ ቀርቦ ሲጸድቅ ይሆናል፡፡
🛑 1.3. በውርስ የተገኘ ይዞታና ቤት የባለቤትነት ስመ-ንብረት ዝውውር አፈፃፀም፣
(ሀ) በውርስ የተላለፈ #ነባር_ይዞታ ዝውውር ለመፈፀም መሟላት ያለባቸው፡-
1) የሚዛወረው የመሬት ይዞታ ወይም ቤት ህጋ የባለቤትነት ማስረጃ/ካርታ ሲኖረው፣
2) ወራሾች የውርስ ባለመብትነትን የሚያረጋግጥ የፍርድ ቤት ውሳኔ ማስረጃ ሲያቀርቡ፣
3) ወራሾች በውርስ ያገኙትን ይዞታ ወይም ቤት በየግላቸው የባለቤትነት ማስረጃ ለመያዝ ሲፈልጉ ለእያንዳንዳቸው ድርሻ መጠን በፍ/ቤት የፀደቀ ማስረጃ ሲያቀርቡ ወይም የሁሉም ወራሾች የጋራ ስምምነት በውል አፅዳቂ አካል ጸድቆ ሲቀርብ፣
4) የእያንዳንዱ ወራሽ የድርሻ መጠን በፍርድ ቤት ያልተረጋገጠ ከሆነ የስም ዝውውሩ በሁሉም ወራሾች ስም በጋራ የሚፈፀም ይሆናል፡፡
የፍርድ ቤቱ የውርሱ ውሳኔ የይዞታ ክፍፍልን የሚያስከትል ሆኖ ሲገኝ የሚፈፀመው የወቅቱን አነስተኛ የይዞታ መጠን መስፈርት የሚያሟላ ከሆነ ብቻ ነው፡፡ ይህ ካልሆነም በተነፃፃሪ የመሬት ይዞታ ድርሻ ህግ ወይም በጋራ ሰነድ/ካርታ መሰረት ይስተናገዳል፡፡
ይዞታው በውሉ መሰረት ግንባታ ለመጀመር የተሰጠውን የጊዜ ገደብ ያለፈበት እና ግንባታው ያልተጀመረ ከሆነ በውርስ ሊተላለፍ አይችልም፡፡
(ለ) #በሊዝ የተያዘ ይዞታ ለህጋዊ ወራሽ የሚተላለፈውና ዝውውር የሚፈፀመው፡-
1) አውራሹ በገባው የሊዝ ውል ግዴታ መሰረት አመታዊውን የሊዝ ክፍያ የፈፀመና ሌሎች የሊዝ ግዴታችን በተገቢው መንገድ የተወጣ ሲሆን፣
2) ወራሽ አውራሽ የገባቸውን የውል ስምምነቶች(የሊዝ መብት፣ክልከላና ኃላፊነት) ሙሉ በሙሉ የተቀበለ መሆኑን በፊርማው ሲያረጋግጥና ውዝፍ ክፍያ ካለ ከፍሎ ደረሰኝ ሲያቀርብ ይሆናል፡፡
3) በሊዝ ውሉ መሰረት አውራሹ በህይወት እያለ ለግንበታ መጀመሪያ የተሰጠው የጊዜ ገደብ ካለፈና ግንባታ ካልጀመረ ውሉ ተቋርጦ ቦታው ለከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት ተመላሽ ይሆናል፡፡
አውራሽ በይዞታው ላይ ግንባታ ያልጀመረው ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት መሆኑ ከተረጋጠ አውራሽ በህይወት ቢኖር ኖሮ በመመሪያው መሰረት ሊፈቀድለት የሚችለው የግንባታ መጀመሪያ የማራዘሚያ ጊዜ ለወራሽ ሊፈቀድለት ይችላል፡፡
🛑 1.4. በባንክ ሃራጅ የሚሸጥ እና የሚወረስ ቤት የባለቤትነት ስም ዝውውር
1) በባንክ የተሸጠ ቤት የባለቤትነት ስም ዝውውር ለመፈፀም በሐራጅ ጨረታው አሸናፊ የሆነው ሰው ያሸነፈበትን ዋጋና ለዝውውሩ በውል የገባቸው ግዴታዎች ተገልፀው ከባንኩ የተፃፈ ህጋዊ ደብዳቤና ውል ሲቀርብ፣
2) በባንክ ዋስትና ተይዞ የነበረው ይዞታ የባለቤትነት ማረጃ/ካርታ በማህደሩ ውስጥ ካለው ሰነድ ጋር ተገናዝቦ ትክክለኛነቱ ሲረጋገጥ፣
3) ይዞታው በሌላ ባንክ ብድርና ዋስትና ያልተያዘ ወይም እገዳ የሌለበት መሆኑ ሲረጋገጥ፣
4) በሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃ ዋስትና የተመዘገበ ዋስትና ያለው ባንክ መኖሩ ከተረጋገጠ ባንኩ ስለ ይዞታው መሸጥ ሲፈቅድ፣
5) በባንክ ሃራጅ ሽያጭ እንዲዞር የተጠየቀው ቤትና ይዞታ የተሟላ ሰነድ የሌለው/ሰነድ አልባ ከሆነ በቅድሚያ በሥራ ላይ ባለው የሰነድ አልባ መመሪያ መሰረት ሰነድ ተሰጥቶት ሲቀርብ፣
6) ባንኩ ንብረቱን ባለበት ሁኔታ የሚረከብ ከሆነ የቤቱና ይዞታው ግምት እንደማንኛውም ቋሚ ንብረት ግምት ተሰልቶ ተገቢውን የአገልግሎትና የገቢ ክፍያ ሲፈጸም፣
7) ቤቱና ይዞታው ባንኩ በሚያወጣው ጨረታ የሚሸጥ ከሆነ ባንኩ ያቀረበው የጨረታ መነሻ ዋጋ በከተማው በኩል ተገቢ መሆኑ ተረጋግጦ በጨረታ ሲሸጥ እና የስም ማዛወሪያ ክፍያዎችን ስለመፈጸሙ የክፍያ ደረሰኝ ማስረጃ ሲያቀርብ የሥመ-ንብረት ዝውውሩ የሚፈጸም ይሆናል፣
በሳሙኤል ግርማ
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
በስመ ንብረት ዝውውር ወቅት መሟላት ያለባቸው መረጃዎች የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በወጣው አዋጅ ቁጥር 721/2004 አንቀፅ 33 ንዑስ አንቀፅ 2 አንፃር ሲታይ
🛑 1.1. የከተማ ቤትና ይዞታ ስመ-ንብረት ዝውውር ስለመፈጸም የሚከተሉት ማስረጃዎች/ሰነዶች ሲሟሉ የስመ ንብረት ዝውውር የሚፈጸም ይሆናል፤ 👇
1) ህጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት/ካርታ፣
2) ጸድቆ የተሰጠ የግንባታ ፕላን፣ የስራ ዝርዝር ግምት ወይም የጸደቀ የነባር ግንባታ ፕላን፣
3) ጸድቆ በተሰጠው የግንባታ ፕላን መሰረት ስለመገንባቱ እና ግንባታው ያለበት ደረጃ የተረጋገጠበት ማስረጃ/50% እና በላይ/፤
4) ውዝፍ የሊዝ/ኪራይ ዕዳ የሌለበት ስለመሆኑ የተሰጠ የማረጋገጫ ደብዳቤ ወይም ቀሪ የሊዝ ክፍያ ዕዳውን ገዥው ለመክፈል በፊርማ ያረጋገጠበት የስምምነት ደብዳቤ ፣
5) በንብረቱ ላይ የባንክ እዳ/የፍ/ቤት ዕግድ የሌለበት ስለመሆኑ ማረጋገጫ ሲቀርብ፣
6) የቤትና ይዞታ ስም ዝውውር ጥያቄው የቀረበው በህግ ባለመብት/በውርስ/በፍርድ አፈጻጸም ወይም በውክልና ከሆነ ይህንኑ የሚገልጽ ማስረጃ፤
7) በግለሰቦች ግዥና ሽያጭ ወይም ስጦታ ስምምነት ከሆነ በዉልና ማስረጃ በአካል ቀርቦ በእማኞች የተፈረመ የስምምነት የውል ማስረጃ ሲቀርብ፣
🛑 1.2. በሽያጭ/በስጦታ የሚተላለፍ ቤትና ይዞታ ስም-ዝውውር መሟላት ያለባቸው መስፈርቶች፣ 👇
1) ግንባታው በዋስትና ያልተያዘ እንዲሁም እዳ የሌለበት መሆኑ ሲረጋገጥ ወይም እዳው በሚመለከተው አካል በደብዳቤ መነሳቱ ሲረጋገጥ፣
2) የቤትና ይዞታ ሽያጭ ወይም የስጦታ ውሉ በምስክሮች ሲረጋገጥና በፍትህ ወይም በመሪ ማዘጋጃ ቤት ፊት ቀርቦ ሲጸድቅ፣
3) ግንባታው ጸድቆ በተሰጠው ዲዛይን መሰረት 50 በመቶና በላይ የተሰራ መሆኑ በባለሙያ ተረጋግጦ ሲቀርብ፣
4) በይዞታው ላይ ውዝፍ የቦታ ኪራይ የሌለበት ስለመሆኑ ወይም ውዝፍ የቦታ ኪራይ ክፍያ አጠናቆ የከፈለ ስለመሆኑ የቀረበ ክፍያ ደረሰኝ ማረጃ ሲቀርብ፣
5) የአገልግሎትና የገቢዎች ክፍያ በቤቱ ግምት መሰረት ስለመከፈሉ ሲረጋገጥ፣
🛑 #ዝውውሩ የሚፈፀመው #በሊዝ በተገኘ ይዞታና ግንባታ ላይ ከሆነ
1) የሊዝ ይዞታ ባለቤትነት ኦሪጅናል ካርታና ውል ሲቀርብ፣
2) በሊዝ ውል መሰረት ክፍያው የተጠናቀቀና ሌሎች ግዴታዎቹን የተወጣ መሆኑ ሲረጋገጥ ወይም የሊዝ እዳው ያልተጠናቀቀ ከሆነ ስም የሚዞርለት ወገን እዳውን ለመክፈል እና ነባሩን የሊዝ ውል ግዴታዎች የተቀበለ ስለመሆኑ ከከተማው በጽሁፍና በፊርማ አረጋግጦ ሲያቀርብ፣
3) በሊዝ የተገዛን የመሬት ይዞታ ለሌላ ሰው ለማስተላለፍ በቅድሚያ በገባው የሊዝ ውል መሰረት በተቀመጠው የጊዜ ገደብ የሚፈለገውን የግንባታ ደረጃ ያሟላ መሆኑ ወይም የግንባታ ፈቃድ የጊዜ ገደብ ያላለፈ ወይም የግንባታ ማራዘሚያ የተፈቀደለት መሆኑ ሲረጋጥ፣
4) የከተማ ቤትና ይዞታ ሽያጭ ወይም የስጦታ ውሉ በምስክሮች ሲረጋጥና በዉልና ማስረጃ ቀርቦ ሲጸድቅ ይሆናል፡፡
🛑 1.3. በውርስ የተገኘ ይዞታና ቤት የባለቤትነት ስመ-ንብረት ዝውውር አፈፃፀም፣
(ሀ) በውርስ የተላለፈ #ነባር_ይዞታ ዝውውር ለመፈፀም መሟላት ያለባቸው፡-
1) የሚዛወረው የመሬት ይዞታ ወይም ቤት ህጋ የባለቤትነት ማስረጃ/ካርታ ሲኖረው፣
2) ወራሾች የውርስ ባለመብትነትን የሚያረጋግጥ የፍርድ ቤት ውሳኔ ማስረጃ ሲያቀርቡ፣
3) ወራሾች በውርስ ያገኙትን ይዞታ ወይም ቤት በየግላቸው የባለቤትነት ማስረጃ ለመያዝ ሲፈልጉ ለእያንዳንዳቸው ድርሻ መጠን በፍ/ቤት የፀደቀ ማስረጃ ሲያቀርቡ ወይም የሁሉም ወራሾች የጋራ ስምምነት በውል አፅዳቂ አካል ጸድቆ ሲቀርብ፣
4) የእያንዳንዱ ወራሽ የድርሻ መጠን በፍርድ ቤት ያልተረጋገጠ ከሆነ የስም ዝውውሩ በሁሉም ወራሾች ስም በጋራ የሚፈፀም ይሆናል፡፡
የፍርድ ቤቱ የውርሱ ውሳኔ የይዞታ ክፍፍልን የሚያስከትል ሆኖ ሲገኝ የሚፈፀመው የወቅቱን አነስተኛ የይዞታ መጠን መስፈርት የሚያሟላ ከሆነ ብቻ ነው፡፡ ይህ ካልሆነም በተነፃፃሪ የመሬት ይዞታ ድርሻ ህግ ወይም በጋራ ሰነድ/ካርታ መሰረት ይስተናገዳል፡፡
ይዞታው በውሉ መሰረት ግንባታ ለመጀመር የተሰጠውን የጊዜ ገደብ ያለፈበት እና ግንባታው ያልተጀመረ ከሆነ በውርስ ሊተላለፍ አይችልም፡፡
(ለ) #በሊዝ የተያዘ ይዞታ ለህጋዊ ወራሽ የሚተላለፈውና ዝውውር የሚፈፀመው፡-
1) አውራሹ በገባው የሊዝ ውል ግዴታ መሰረት አመታዊውን የሊዝ ክፍያ የፈፀመና ሌሎች የሊዝ ግዴታችን በተገቢው መንገድ የተወጣ ሲሆን፣
2) ወራሽ አውራሽ የገባቸውን የውል ስምምነቶች(የሊዝ መብት፣ክልከላና ኃላፊነት) ሙሉ በሙሉ የተቀበለ መሆኑን በፊርማው ሲያረጋግጥና ውዝፍ ክፍያ ካለ ከፍሎ ደረሰኝ ሲያቀርብ ይሆናል፡፡
3) በሊዝ ውሉ መሰረት አውራሹ በህይወት እያለ ለግንበታ መጀመሪያ የተሰጠው የጊዜ ገደብ ካለፈና ግንባታ ካልጀመረ ውሉ ተቋርጦ ቦታው ለከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት ተመላሽ ይሆናል፡፡
አውራሽ በይዞታው ላይ ግንባታ ያልጀመረው ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት መሆኑ ከተረጋጠ አውራሽ በህይወት ቢኖር ኖሮ በመመሪያው መሰረት ሊፈቀድለት የሚችለው የግንባታ መጀመሪያ የማራዘሚያ ጊዜ ለወራሽ ሊፈቀድለት ይችላል፡፡
🛑 1.4. በባንክ ሃራጅ የሚሸጥ እና የሚወረስ ቤት የባለቤትነት ስም ዝውውር
1) በባንክ የተሸጠ ቤት የባለቤትነት ስም ዝውውር ለመፈፀም በሐራጅ ጨረታው አሸናፊ የሆነው ሰው ያሸነፈበትን ዋጋና ለዝውውሩ በውል የገባቸው ግዴታዎች ተገልፀው ከባንኩ የተፃፈ ህጋዊ ደብዳቤና ውል ሲቀርብ፣
2) በባንክ ዋስትና ተይዞ የነበረው ይዞታ የባለቤትነት ማረጃ/ካርታ በማህደሩ ውስጥ ካለው ሰነድ ጋር ተገናዝቦ ትክክለኛነቱ ሲረጋገጥ፣
3) ይዞታው በሌላ ባንክ ብድርና ዋስትና ያልተያዘ ወይም እገዳ የሌለበት መሆኑ ሲረጋገጥ፣
4) በሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃ ዋስትና የተመዘገበ ዋስትና ያለው ባንክ መኖሩ ከተረጋገጠ ባንኩ ስለ ይዞታው መሸጥ ሲፈቅድ፣
5) በባንክ ሃራጅ ሽያጭ እንዲዞር የተጠየቀው ቤትና ይዞታ የተሟላ ሰነድ የሌለው/ሰነድ አልባ ከሆነ በቅድሚያ በሥራ ላይ ባለው የሰነድ አልባ መመሪያ መሰረት ሰነድ ተሰጥቶት ሲቀርብ፣
6) ባንኩ ንብረቱን ባለበት ሁኔታ የሚረከብ ከሆነ የቤቱና ይዞታው ግምት እንደማንኛውም ቋሚ ንብረት ግምት ተሰልቶ ተገቢውን የአገልግሎትና የገቢ ክፍያ ሲፈጸም፣
7) ቤቱና ይዞታው ባንኩ በሚያወጣው ጨረታ የሚሸጥ ከሆነ ባንኩ ያቀረበው የጨረታ መነሻ ዋጋ በከተማው በኩል ተገቢ መሆኑ ተረጋግጦ በጨረታ ሲሸጥ እና የስም ማዛወሪያ ክፍያዎችን ስለመፈጸሙ የክፍያ ደረሰኝ ማስረጃ ሲያቀርብ የሥመ-ንብረት ዝውውሩ የሚፈጸም ይሆናል፣
በሳሙኤል ግርማ
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
*BALANCE SHEET Of LIFE*
Birth is your
*Opening Stock.*
What comes to you
is
*Credit.*
What goes from you
is
*Debit*
Death is your
*Closing Stock.*
Your friends are your
*Assets.*
Your bad habits are
your *Liabilities.*
Your happiness is
your
*Profit.*
Your sorrow is your
*Loss.*
Your heart is your
*Goodwill.*
Your soul is your
*fixed Asset*
Your character is
your
*Capital.*
Your knowledge is
your
*Investment*
Your age is your
*Depreciation.*
And finally :
*ALWAYS REMEMBER,*
*MORAL IS YOUR AUDITOR*
*Have a nice balance sheet of Life*
#happy #Sunday!
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
Birth is your
*Opening Stock.*
What comes to you
is
*Credit.*
What goes from you
is
*Debit*
Death is your
*Closing Stock.*
Your friends are your
*Assets.*
Your bad habits are
your *Liabilities.*
Your happiness is
your
*Profit.*
Your sorrow is your
*Loss.*
Your heart is your
*Goodwill.*
Your soul is your
*fixed Asset*
Your character is
your
*Capital.*
Your knowledge is
your
*Investment*
Your age is your
*Depreciation.*
And finally :
*ALWAYS REMEMBER,*
*MORAL IS YOUR AUDITOR*
*Have a nice balance sheet of Life*
#happy #Sunday!
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
በኢትዮጵያ የህግ ማሻሻያ ሰነድ ዝግጅት ሂደትን የሚያሳይ መጽሐፍ ተመርቆ ለንባብ በቃ
______________________
መጽሐፉ የዝግጅት ምዕራፉን አጠናቆ ለንባብ መብቃቱ በኢትዮጵያ ሲደረግ የነበረውን የህግ ማሻሻያ ሂደት ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ እና የህግ ጥናትና ምርምር ሥራዎችን ለመደገፍ ከፍተኛ እገዛ እንደሚኖረው ተገልጿል፡፡
በመጽሐፉ የምረቃ ሥነ-ስርዓት ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የፍትሐብሄርና ልዩ ልዩ ወንጀሎች ዘርፍ ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አቶ ገለታ ስዩም ሲሆኑ በንግግራቸዉም የመጽሐፉ መዘጋጀት በሕግ ዘርፍ አገልግሎት አሰጣጥ እና ወቅቱ የሚጠይቀውን ፍትህ የማስፈን ሂደት ለመደገፍ ብሎም በዘርፉ ዙሪያ ለሚደረጉ የጥናትና ምርምር ሥራዎች እንዲሁም ቀጣዩ ትውልድ በአሁኑ ወቅት ሲደረጉ የነበሩ የሕግ ማሻሻያ ሥራዎችን በአግባቡ እንዲረዳ ከማድረግ አንፃር ከፍተኛ እገዛ አለው ብለዋል፡፡
አቶ ገለታ አያይዘውም መጽሐፉ ተዘጋጅቶ ለንባብ እንዲበቃ የገንዘብና የሙያ ድጋፍ ላበረከቱ አካላት ማለትም ለUSAIDና በኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ለሕግ ጥናት ማርቀቅና ማጠቃለል ዳይሬክቶሬት ጀነራል በተለይም በመጽሐፉ ዝግጅት ወቅት የጎላ ድርሻ ለነበራቸው ለዶ/ር ኤልያስ ኑር እና ለአቶ በላይሁን ይርጋ ያላቸውን አድናቆት ገልጸው ምስጋናም አቅርበዋል፡፡
በመድረኩ ዶ/ር ኤልያስና አቶ በላይሁን በመጽሐፉ ይዘት ዙሪያ ሰፋ ያለ ማብራሪያና ገለጻ ያደረጉ ሲሆን በዋናነትም መጽሐፉ የሽብር፣የበጎ አድራጎት ማህበራት፣ የመገናኛ ብዙኃን ፣ የጦር መሣሪያ አስተዳደር እና ሌሎች ስምንት አዋጆችን እንዲሁም ሁለት የህግ መድብሎችን ማለትም የወንጀል ሰነ-ሥርዓትና የማስረጃ ህግ እንዲሁም የንግድ ህግን በተመለከተ ለማሻሻል መንግስት የወሰደውን እርምጃ አብራርተዋል፡፡
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
______________________
መጽሐፉ የዝግጅት ምዕራፉን አጠናቆ ለንባብ መብቃቱ በኢትዮጵያ ሲደረግ የነበረውን የህግ ማሻሻያ ሂደት ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ እና የህግ ጥናትና ምርምር ሥራዎችን ለመደገፍ ከፍተኛ እገዛ እንደሚኖረው ተገልጿል፡፡
በመጽሐፉ የምረቃ ሥነ-ስርዓት ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የፍትሐብሄርና ልዩ ልዩ ወንጀሎች ዘርፍ ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አቶ ገለታ ስዩም ሲሆኑ በንግግራቸዉም የመጽሐፉ መዘጋጀት በሕግ ዘርፍ አገልግሎት አሰጣጥ እና ወቅቱ የሚጠይቀውን ፍትህ የማስፈን ሂደት ለመደገፍ ብሎም በዘርፉ ዙሪያ ለሚደረጉ የጥናትና ምርምር ሥራዎች እንዲሁም ቀጣዩ ትውልድ በአሁኑ ወቅት ሲደረጉ የነበሩ የሕግ ማሻሻያ ሥራዎችን በአግባቡ እንዲረዳ ከማድረግ አንፃር ከፍተኛ እገዛ አለው ብለዋል፡፡
አቶ ገለታ አያይዘውም መጽሐፉ ተዘጋጅቶ ለንባብ እንዲበቃ የገንዘብና የሙያ ድጋፍ ላበረከቱ አካላት ማለትም ለUSAIDና በኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ለሕግ ጥናት ማርቀቅና ማጠቃለል ዳይሬክቶሬት ጀነራል በተለይም በመጽሐፉ ዝግጅት ወቅት የጎላ ድርሻ ለነበራቸው ለዶ/ር ኤልያስ ኑር እና ለአቶ በላይሁን ይርጋ ያላቸውን አድናቆት ገልጸው ምስጋናም አቅርበዋል፡፡
በመድረኩ ዶ/ር ኤልያስና አቶ በላይሁን በመጽሐፉ ይዘት ዙሪያ ሰፋ ያለ ማብራሪያና ገለጻ ያደረጉ ሲሆን በዋናነትም መጽሐፉ የሽብር፣የበጎ አድራጎት ማህበራት፣ የመገናኛ ብዙኃን ፣ የጦር መሣሪያ አስተዳደር እና ሌሎች ስምንት አዋጆችን እንዲሁም ሁለት የህግ መድብሎችን ማለትም የወንጀል ሰነ-ሥርዓትና የማስረጃ ህግ እንዲሁም የንግድ ህግን በተመለከተ ለማሻሻል መንግስት የወሰደውን እርምጃ አብራርተዋል፡፡
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
Respect your efforts, respect yourself. Self-respect leads to self-discipline. When you have both firmly under your belt, that's real power.
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
Each Of Us Has A Finite Amount Of Time, Energy, And Money;
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
ALE (አለ) law societies 🔴
ALE (Alternative Legal Education)
All in one, for all.🔴
አለ (አማራጭ የሕግ ትምህርት)
ሁሉም በአንድ፣ ለሁሉም።🔴
There is free legal aid. ነፃ የሕግ ድጋፍ አለ።
For discussion @ALE_lawsocieties
For more Contact us: @LawsocietiesBot
https://t.me/lawsocieties
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
ALE (አለ) law societies 🔴
ALE (Alternative Legal Education)
All in one, for all.🔴
አለ (አማራጭ የሕግ ትምህርት)
ሁሉም በአንድ፣ ለሁሉም።🔴
There is free legal aid. ነፃ የሕግ ድጋፍ አለ።
For discussion @ALE_lawsocieties
For more Contact us: @LawsocietiesBot
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
በይርጋ የማይታገዱ የፍትሀብሄር ጉዳዬች
=======//////========
የይርጋ መሰረታዊ ዓላማ ማንኛውም በህግ በግልፅ የተደነገገ መብትና ግዴታ በህጉ በተወሰነው ወይም በተገደበው ጊዜ ውስጥ ስልጣን ላለው አካል እንዲቀርቡ ግዴታን በማስቀመጥ መብቴ ተጣሰብኝ የሚል ወገን ዳተኛ ሳይሆን በትጋት መብቱን እንዲጠይቅ ለማስቻል መሆኑ ይታወቃል።
ነገር ግን አንዳንድ ጉዳዬች ከንብረቶቹ ልዩ ባህሪና የመንግስት ፖሊሲ አንፃር ህግ አውጪው በይርጋ እንዳይታገዱ አድርጎ ያስቀመጣቸው የፍትሀብሄር ጉዳዬች አሉ። ከእነዚህ መካከል፦
#የመፋለም ክስ ( petitory action)
~~××××××~~~~~
ለባለሀብቱ የባለቤትነት መብት ከሚሰጣቸው መብቶች መካከል ንብረቱ ያለ እርሱ ፈቃድ ከህግ ውጪ በሌላ ሰው ወይም ሀይል ከተወሰደ ንብረቱን ካለበት ድረስ በመከታተል የማስመለስ ወይም የመፋለም መብት አንዱ ስለመሆኑ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1206 ድንጋጌ ያስረዳል፡፡
ባለሀብትነትን የሚያስቀር የይርጋ ዘመን” በሚል ርዕስ ስር በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1192 የተመለከተው በሚንቀሳቀስ ንብረት ላይ ያለውን መብት በአስር ዓመት የጊዜ ወሰን /ይርጋ/ ቀሪ የሚሆንበትን አግባብ ያመላከተ ሲሆን የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሀብትነት በይርጋ ቀሪ እንደሚሆን ግን አያሳይም፡፡
ድንጋጌው የሚንቀሳቀስ ንብረትን የባለሀብትነት ጥያቄ የጊዜ ገደብ ካስቀመጠ በኋላ ስለማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሀብትነት ቀሪ መሆን በዝምታ ያለፈው ለጉዳዩ ቀጥተኛ ተፈፃሚነት በሌለው በፍ/ብ/ህግ አንቀፅ 1845 ስር የተመለከተው ተመሳሳይ የ10 ዓመት የይርጋ ጊዜ ተፈፃሚ እንደሆን ተፈልጎ ካለመሆኑ በላይ የማይንቀሳቀስ ንብረት ከሚንቀሳቀስ ንብረት በተለየ ሁኔታ የዘላቂነት ባህሪ ያለው እና ከትውልው ወደ ትውልድ የሚተላለፍ በመሆኑ የባለሀብትነቱ መብት ቀሪ የሚሆነው በይርጋ ሳይሆን በሌሎች ሁኔታዎች( አንቀፅ 1168....) ይሆን ዘንድ ተፈልጎ የተቀመጠ ድንጋጌ መሆኑን እንገነዘባለን።
በመሆኑም የማይንቀሳቀስ ንብረት የመፋለም ክስ (petitory action) በይርጋ ቀሪ አይሆንም። (የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰ/መዝ/ቁ 43600)
N.B= ይህ ሲባል ግን ከውርስ፣ ከሽያጭ፣ ከስጦታና ከሌሎች ውሎች በመነጨ በማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ የሚደረግ ክርክር ይርጋ የለውም ማለት የሚቻል ሳይሆን ለጉዳዩ አግባብነት ባላቸው ህጎች በተቀመጡ የይርጋ ጊዜዎች የሚስተናገዱ ይሆናል።
#ህገ ወጥ ውል (unlawful contrat)
~~~×××××~~~~~~
እንድ ውል የፀና ውል ለመሆን መሟላት ከሚገባው አንዱ ነጥብ ውሉ ህጋዊ በሆነ ጉዳይ ላይ የተመሰረተ መሆን የሚገባው እንደሆነ የፍ/ብ/ህግ 1678 ይደነግጋል። አንድ ውል ህገ ወጥ ውል ነው የሚባለው ደግሞ ተዋዋዬቹ የተዋዋሉበት መሰረታዊ ጉዳይ ዓላማ በመሰረታዊና ሞራላዊ ይዘቱ ተዋዋይ ወገኖች ስምምነት በማድረግ መብትና ግዴታ እንዲፈጥሩበት በህግ ያልተፈቀደ ወይም በህግ ክልከላ የተደረገበት ሆኖ ሲገኝ ነው።
አንድ ውል የተመሰረተበት መሰረታዊ ጉዳይ (object of contract) በህግ ክልከላ የተደረረበት በሆነ ጊዜ ውሉ በህግ ፊት እንደሌለና ምንም አይነት ህጋዊ ውጤት የማያስከትል (null and void contrat) እንዲሁም ችግሩን በማስተካከል ህጋዊ ውጤት እንዲኖረው ማድረግ የማይቻል ነው። ለምሳሌ፦ የመሬት ሽያጭ ውል፣ በሰው ለመነገድ የተደረግ ውል፣ ወንጀል ለመፈፀም የተደረገ ውል......
ህገ ወጥ የሆነውን ውል ውድቅ ለማድረግ ደግሞ በህጉ የተደነገገው የይርጋ ጊዜ ገደብ መቃወሚያ ሊቀርብ የማይችልና ተቀባይነት የሌለው በመሆኑ በይርጋ የሚታገዱ አይደሉም። (የፌ/ጠ/ፍ/ቤት/ሰ/መዝ/ቁ 43226)
N.B= ይህ ሲባል ግን የህጉን መስፈርት ያላሟሉ ውሎች (illegal contract) ከህገ ወጥ ውል በተለየ ሁኔታ ታይተው የይርጋ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ የሚሆንባቸው መሆኑን መረዳት ይገባል።
#የመንግስትን መሬት የማስመለስ ክስ
~××××××~~~~~~
ግለሰቦች በፌደራሉ እና በክልሉ መንግስት በወጡ የገጠር መሬት አጠቃቀም እና አስተዳደር አዋጅ በሚደነግጉት መሰረት በህጋዊ መንገድ ሳይሰጣቸው ከህግ ውጪ የወል ወይም የመንግስትን መሬት ይዘው መቆየታቸው እና የመሬቱ ባለይዞታ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ማግኘታቸው የመሬቱ ህጋዊ ባለይዞታ ሊያደርጋቸው አይችልም። በወረራ የተያዘ የመንግስት መሬትም ይርጋ የሌለው መሆኑን የአብክመ የገጠር መሬት አዋጅ ቁጥር 252/2009 አንቀፅ 55 በግልፅ ያስቀምጣል።
በመሆኑም ከህግ ውጭ በህገ ወጥ መንገድ የተያዙ መሬቶችን መኖራቸውን ሲረዳ መሬት አስተዳደርም ሆነ የመንግስት ወኪል የሆነ አካል መሬቶቹን ለማስመለስ የሚያቀርበው ክስ በይርጋ የሚታገድ አይደለም። (የፌ/ጠ/ፍ/ቤት/ሰ/መዝ/ቁ 93013 እና 96203 ያልታተሙ)
#በህገ ወጥ መንገድ የተያዘ የግለሰብ ይዞ መሬት
~~××××××~~~~~~
ከላይ እንደተመለከትነው ህገ ወጥ ውልን መሰረት አድርጎ የግለሰብን መሬት በያዘ ሰው ላይ የሚቀርብ ክስ ይርጋ የሌለው መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በአብክመ የገጠር መሬት አዋጅ ቁጥር 252/2009 አንቀፅ 55 መሰረት ህጉ በማይፈቅድበት መንገድ በሀይልም ሆነ በህገ ወጥ አግባብ የገጠር መሬትን ይዞ የተገኘ ግለሰብ ላይ የሚቀርብ ክስ ይርጋ የለውም።
N.B= በህገ ወጥ መንገድ የሚለው ሀሳብ በህግ ተቀባይነት በሌለው አኳኋን የያዘን በሚመለከት እንጂ የህጉን መስፈርት ባላሟላ ውል ወይም ተግባር (illegal contrat) አማካኝነት የተያዘን መሬት የሚመለከት አይደለም። ምክንያቱም መሬቱን የያዘው በህጉ በተፈቀደ የውል ተግባር ሆኖ የሚፈለገውን ፎርማሊቲ ወይም መስፈርት አለማለቱ ብቻ አያያዙ ህገ ወጥ ነው የሚያስብል ስላልሆነ ነው።
#የአደራ ውል
~×××
አደራ ተቀባይ በአደራ የሚጠብቀውን ዕቃ የሚመልስበት የጊዜ ገደብ በውል ተመልክቶ ከሆነ ይህ ጊዜ ሲያበቃ ዕቃውን መመለስ ያለበት ስለመሆኑ በፍ/ብ/ህ/ቁ 2781(1) የተመለከተ ሲሆን በውል ላይ የተቀመጠ የጊዜ ገደብ ከሌለ ግን አደራ ሰጪው እንደጠየቀ ወዲያውኑ እንደሚመለስ በፍ/ብ/ህ/ቁ 2989(1) ስር ተመላክቷል።
ከእነዚህ ድንጋጌዎች ለመረዳት የሚቻለው አደራ ተቀባይ ዕቃውን የሚመልስበት የጊዜ ገደብ ከሌለ በቀር አደራ ሰጪው በአደራ እንዲቀመጥ የሰጠው ዕቃ ያለምንም የጊዜ ገደብ በማንኛውም ጊዜ እንዲመለስለት መጠየቅ የሚችል መሆኑን ነው።
#የውርስ ሀብት ክፍፍል
~~~~××××~~~~
ወራሾች ተለይተው እና የውርስ ሀብቱ ድርሻ ታውቆ ነገር ግን ክፍፍል ሳይደረግ የቆየን የውርስ ሀብት በማናቸውም ጊዜ መጠየቅ እንደሚችልና በይርጋ የሚታገድ እንዳልሆነ ከፍ/ብ/ህ/ቁ 1060 እና ተከታዬቹ ድንጋጌዎች መረዳት ይቻላል።
እንዲሁም ከውርስ ሀብት ጥያቄ ጋር በተያያዘ የውርስ ሀብቱን በእጁ አድርጎ በመገልገል ላይ ያለ ተከራካሪ የሆነ ወራሽ ለክርክሩ ምክንያት የሆነውን የውርስ ንብረት በጋራ ይዞ ከቆየ ሰው ላይ የውርስ ድርሻዬን ልወቅ ወይም ይለይልኝ ጥያቄ በይርጋ ይታገዳል የሚባልበት አግባብ የለም።
#የድምፅ ብክለት
~×××~~
=======//////========
የይርጋ መሰረታዊ ዓላማ ማንኛውም በህግ በግልፅ የተደነገገ መብትና ግዴታ በህጉ በተወሰነው ወይም በተገደበው ጊዜ ውስጥ ስልጣን ላለው አካል እንዲቀርቡ ግዴታን በማስቀመጥ መብቴ ተጣሰብኝ የሚል ወገን ዳተኛ ሳይሆን በትጋት መብቱን እንዲጠይቅ ለማስቻል መሆኑ ይታወቃል።
ነገር ግን አንዳንድ ጉዳዬች ከንብረቶቹ ልዩ ባህሪና የመንግስት ፖሊሲ አንፃር ህግ አውጪው በይርጋ እንዳይታገዱ አድርጎ ያስቀመጣቸው የፍትሀብሄር ጉዳዬች አሉ። ከእነዚህ መካከል፦
#የመፋለም ክስ ( petitory action)
ለባለሀብቱ የባለቤትነት መብት ከሚሰጣቸው መብቶች መካከል ንብረቱ ያለ እርሱ ፈቃድ ከህግ ውጪ በሌላ ሰው ወይም ሀይል ከተወሰደ ንብረቱን ካለበት ድረስ በመከታተል የማስመለስ ወይም የመፋለም መብት አንዱ ስለመሆኑ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1206 ድንጋጌ ያስረዳል፡፡
ባለሀብትነትን የሚያስቀር የይርጋ ዘመን” በሚል ርዕስ ስር በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1192 የተመለከተው በሚንቀሳቀስ ንብረት ላይ ያለውን መብት በአስር ዓመት የጊዜ ወሰን /ይርጋ/ ቀሪ የሚሆንበትን አግባብ ያመላከተ ሲሆን የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሀብትነት በይርጋ ቀሪ እንደሚሆን ግን አያሳይም፡፡
ድንጋጌው የሚንቀሳቀስ ንብረትን የባለሀብትነት ጥያቄ የጊዜ ገደብ ካስቀመጠ በኋላ ስለማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሀብትነት ቀሪ መሆን በዝምታ ያለፈው ለጉዳዩ ቀጥተኛ ተፈፃሚነት በሌለው በፍ/ብ/ህግ አንቀፅ 1845 ስር የተመለከተው ተመሳሳይ የ10 ዓመት የይርጋ ጊዜ ተፈፃሚ እንደሆን ተፈልጎ ካለመሆኑ በላይ የማይንቀሳቀስ ንብረት ከሚንቀሳቀስ ንብረት በተለየ ሁኔታ የዘላቂነት ባህሪ ያለው እና ከትውልው ወደ ትውልድ የሚተላለፍ በመሆኑ የባለሀብትነቱ መብት ቀሪ የሚሆነው በይርጋ ሳይሆን በሌሎች ሁኔታዎች( አንቀፅ 1168....) ይሆን ዘንድ ተፈልጎ የተቀመጠ ድንጋጌ መሆኑን እንገነዘባለን።
በመሆኑም የማይንቀሳቀስ ንብረት የመፋለም ክስ (petitory action) በይርጋ ቀሪ አይሆንም። (የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰ/መዝ/ቁ 43600)
N.B= ይህ ሲባል ግን ከውርስ፣ ከሽያጭ፣ ከስጦታና ከሌሎች ውሎች በመነጨ በማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ የሚደረግ ክርክር ይርጋ የለውም ማለት የሚቻል ሳይሆን ለጉዳዩ አግባብነት ባላቸው ህጎች በተቀመጡ የይርጋ ጊዜዎች የሚስተናገዱ ይሆናል።
#ህገ ወጥ ውል (unlawful contrat)
እንድ ውል የፀና ውል ለመሆን መሟላት ከሚገባው አንዱ ነጥብ ውሉ ህጋዊ በሆነ ጉዳይ ላይ የተመሰረተ መሆን የሚገባው እንደሆነ የፍ/ብ/ህግ 1678 ይደነግጋል። አንድ ውል ህገ ወጥ ውል ነው የሚባለው ደግሞ ተዋዋዬቹ የተዋዋሉበት መሰረታዊ ጉዳይ ዓላማ በመሰረታዊና ሞራላዊ ይዘቱ ተዋዋይ ወገኖች ስምምነት በማድረግ መብትና ግዴታ እንዲፈጥሩበት በህግ ያልተፈቀደ ወይም በህግ ክልከላ የተደረገበት ሆኖ ሲገኝ ነው።
አንድ ውል የተመሰረተበት መሰረታዊ ጉዳይ (object of contract) በህግ ክልከላ የተደረረበት በሆነ ጊዜ ውሉ በህግ ፊት እንደሌለና ምንም አይነት ህጋዊ ውጤት የማያስከትል (null and void contrat) እንዲሁም ችግሩን በማስተካከል ህጋዊ ውጤት እንዲኖረው ማድረግ የማይቻል ነው። ለምሳሌ፦ የመሬት ሽያጭ ውል፣ በሰው ለመነገድ የተደረግ ውል፣ ወንጀል ለመፈፀም የተደረገ ውል......
ህገ ወጥ የሆነውን ውል ውድቅ ለማድረግ ደግሞ በህጉ የተደነገገው የይርጋ ጊዜ ገደብ መቃወሚያ ሊቀርብ የማይችልና ተቀባይነት የሌለው በመሆኑ በይርጋ የሚታገዱ አይደሉም። (የፌ/ጠ/ፍ/ቤት/ሰ/መዝ/ቁ 43226)
N.B= ይህ ሲባል ግን የህጉን መስፈርት ያላሟሉ ውሎች (illegal contract) ከህገ ወጥ ውል በተለየ ሁኔታ ታይተው የይርጋ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ የሚሆንባቸው መሆኑን መረዳት ይገባል።
#የመንግስትን መሬት የማስመለስ ክስ
ግለሰቦች በፌደራሉ እና በክልሉ መንግስት በወጡ የገጠር መሬት አጠቃቀም እና አስተዳደር አዋጅ በሚደነግጉት መሰረት በህጋዊ መንገድ ሳይሰጣቸው ከህግ ውጪ የወል ወይም የመንግስትን መሬት ይዘው መቆየታቸው እና የመሬቱ ባለይዞታ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ማግኘታቸው የመሬቱ ህጋዊ ባለይዞታ ሊያደርጋቸው አይችልም። በወረራ የተያዘ የመንግስት መሬትም ይርጋ የሌለው መሆኑን የአብክመ የገጠር መሬት አዋጅ ቁጥር 252/2009 አንቀፅ 55 በግልፅ ያስቀምጣል።
በመሆኑም ከህግ ውጭ በህገ ወጥ መንገድ የተያዙ መሬቶችን መኖራቸውን ሲረዳ መሬት አስተዳደርም ሆነ የመንግስት ወኪል የሆነ አካል መሬቶቹን ለማስመለስ የሚያቀርበው ክስ በይርጋ የሚታገድ አይደለም። (የፌ/ጠ/ፍ/ቤት/ሰ/መዝ/ቁ 93013 እና 96203 ያልታተሙ)
#በህገ ወጥ መንገድ የተያዘ የግለሰብ ይዞ መሬት
ከላይ እንደተመለከትነው ህገ ወጥ ውልን መሰረት አድርጎ የግለሰብን መሬት በያዘ ሰው ላይ የሚቀርብ ክስ ይርጋ የሌለው መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በአብክመ የገጠር መሬት አዋጅ ቁጥር 252/2009 አንቀፅ 55 መሰረት ህጉ በማይፈቅድበት መንገድ በሀይልም ሆነ በህገ ወጥ አግባብ የገጠር መሬትን ይዞ የተገኘ ግለሰብ ላይ የሚቀርብ ክስ ይርጋ የለውም።
N.B= በህገ ወጥ መንገድ የሚለው ሀሳብ በህግ ተቀባይነት በሌለው አኳኋን የያዘን በሚመለከት እንጂ የህጉን መስፈርት ባላሟላ ውል ወይም ተግባር (illegal contrat) አማካኝነት የተያዘን መሬት የሚመለከት አይደለም። ምክንያቱም መሬቱን የያዘው በህጉ በተፈቀደ የውል ተግባር ሆኖ የሚፈለገውን ፎርማሊቲ ወይም መስፈርት አለማለቱ ብቻ አያያዙ ህገ ወጥ ነው የሚያስብል ስላልሆነ ነው።
#የአደራ ውል
አደራ ተቀባይ በአደራ የሚጠብቀውን ዕቃ የሚመልስበት የጊዜ ገደብ በውል ተመልክቶ ከሆነ ይህ ጊዜ ሲያበቃ ዕቃውን መመለስ ያለበት ስለመሆኑ በፍ/ብ/ህ/ቁ 2781(1) የተመለከተ ሲሆን በውል ላይ የተቀመጠ የጊዜ ገደብ ከሌለ ግን አደራ ሰጪው እንደጠየቀ ወዲያውኑ እንደሚመለስ በፍ/ብ/ህ/ቁ 2989(1) ስር ተመላክቷል።
ከእነዚህ ድንጋጌዎች ለመረዳት የሚቻለው አደራ ተቀባይ ዕቃውን የሚመልስበት የጊዜ ገደብ ከሌለ በቀር አደራ ሰጪው በአደራ እንዲቀመጥ የሰጠው ዕቃ ያለምንም የጊዜ ገደብ በማንኛውም ጊዜ እንዲመለስለት መጠየቅ የሚችል መሆኑን ነው።
#የውርስ ሀብት ክፍፍል
~~~~××××~~~~
ወራሾች ተለይተው እና የውርስ ሀብቱ ድርሻ ታውቆ ነገር ግን ክፍፍል ሳይደረግ የቆየን የውርስ ሀብት በማናቸውም ጊዜ መጠየቅ እንደሚችልና በይርጋ የሚታገድ እንዳልሆነ ከፍ/ብ/ህ/ቁ 1060 እና ተከታዬቹ ድንጋጌዎች መረዳት ይቻላል።
እንዲሁም ከውርስ ሀብት ጥያቄ ጋር በተያያዘ የውርስ ሀብቱን በእጁ አድርጎ በመገልገል ላይ ያለ ተከራካሪ የሆነ ወራሽ ለክርክሩ ምክንያት የሆነውን የውርስ ንብረት በጋራ ይዞ ከቆየ ሰው ላይ የውርስ ድርሻዬን ልወቅ ወይም ይለይልኝ ጥያቄ በይርጋ ይታገዳል የሚባልበት አግባብ የለም።
#የድምፅ ብክለት
የድምፅ ብክለት ክልከላ ባለቤቱ ስራውን የሚፈፅመው በራሱ ንብረት ወይም ቤት ውስጥ ቢሆንም ድርጊቱ ሌላውን ጎረቤት እንዳይረብሽ፣ እንዳያውክ፣ ወይም ችግር እንዳያስከትል በማድረግ መብቱን ይጠቀም ዘንድ ህጉ ያበጀው የባለቤትነት መብት አጠቃቀምን አድማስ የሚወስን ስርዓት መሆኑን ከአንቀፅ 1226 እና ተከታዬቹ ድንጋጌዎች መረዳት ይቻላል።
ይህን ችግር ለማስወገድ የሚቀርበው አቤቱታ ከፍ/ብ/ህ/ቁ 1149 ስር ከተመለከተው በይዞታ ላይ ሁከት መፍጠር ተግባር የሚለይ ሲሆን አንዴ የተፈጠረ የድምፅ ብክለት እንዲቀጥል የሚደረግበት አግባብ ስለሌለ በይርጋ የሚታገድ አይደለም።
Source:- The Voice of Justice page
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
ይህን ችግር ለማስወገድ የሚቀርበው አቤቱታ ከፍ/ብ/ህ/ቁ 1149 ስር ከተመለከተው በይዞታ ላይ ሁከት መፍጠር ተግባር የሚለይ ሲሆን አንዴ የተፈጠረ የድምፅ ብክለት እንዲቀጥል የሚደረግበት አግባብ ስለሌለ በይርጋ የሚታገድ አይደለም።
Source:- The Voice of Justice page
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
የአ/አ/ከ/አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ በሚሰጠው የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ላይ ካርታው ‹‹በህጋዊ መንገድ ስልጣን ከተሰጠው አካል ፈቃድ ውጭ ለመያዣነት አያገለግልም›› የሚል ማሳሰቢያ ማስቀመጡ ከንብረት መብት አንፃር ያለው ህጋዊነትና ፋይዳው
*******************************************
ውድ የፌስ ቡክ ገጻችን ተከታታዮች በኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የፌዴራል ህጎች ተፈጻሚነት መከታተያ ዳይሬክቶሬት ጥናት ካደረገባቸው ጉዳዮች መካከል ከላይ በርዕሱ ላይ በተመለከተው ጉዳይ ዙሪያ የስራ ክፍሉ ያዘጋጀውን አጭር ሀተታ እንደሚከተለው አቅርበንላችኋል፡፡
የአ/አ/ከ/አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ የነባር ባለ ይዞታነትና የቤት ባለቤትነት ማረጋገጫ፣ የነባር ይዞታ ተነጻጻሪ ካርታ፣ ግንባታው የተጠናቀቀ የሊዝ ይዞታና የቤት ባለቤትነት ማረጋገጫ (አረንጓዴ ቀለም ያለው)፣ የሊዝ ተነጻጻሪ ባለይዞታና የቤት ባለቤትነት ካርታ እና ግንባታው ለተጀመረ የሊዝ ባለይዞታነትና የቤት ባለቤትነት ካርታ (ቢጫ ቀለም ያለው) ተራ ቁጥር ላይ ለተዘረዘሩት የካርታ አይነቶች በጀርባቸው ላይ የተቀመጠው ማሳሰቢያ ‹‹በዚህ ካርታ ላይ የሰፈረው ቦታ/ይዞታ በህጋዊ መንገድ ስልጣን ከተሰጠው አካል ፍቃድ ውጭ ለመያዣነት አያገለግልም›› ሲል በነባር ይዞታ ተነጻጻሪ ካርታ ላይ ግን ‹‹በዚህ ካርታ ላይ የሚገኝ ንብረትን በህጋዊ መንገድ ስልጣን ከተሰጠው አካል እውቅና ውጭ ለመያዣነት አያገለግልም የሚል ይዘትን አስቀምጧል፡፡ ይህም ካርታን ለመያዣ ለመጠቀም የሚመለከተውን አካል ፍቃድ ማግኝት ወይስ ማሳወቅ ብቻ በቂ ነው? ይህ የሚያስፈልገውስ ለይዞታው ብቻ ወይስ ካርታው ላይ ለሰፈረው ለማንኛውም ንብረት ነውን ? ለሚለው ጥያቄ ወጥ በሆነ መልኩ ምላሽ የማይመልስ፣ የተለያየ ይዘት ያለው ማሳሰቢያ በተለያየ ጊዜ በካርታዎች ላይ የሚቀመጥና በተጠቃሚዎች ላይም የተለያየ ግዴታ እና መብት የሚጥል መሆኑን ያመላክታል፡፡
የዚህን ማሳሰቢያ ህጋዊነትና አላማን በተመለከተ የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫ ምዝገባ ጽ/ቤት ህጋዊ አስተያየት እንዲሰጠበት በጠየቀው መሰረት ካርታውን የሚያዘጋጀው የአ/አ/ከ/አስ/መ/ል/ማ/ቢሮ በቀን 27/02/2011 በቁጥር ይአሰ/45/2011 ማብራሪያ ሲሰጥ ካርታን እንደመያዣ መጠቀም የሚችሉት ከብሄራዊ ባንክ በኩል እውቅና ያገኙ የፋይናንስ ተቋማት ብቻ መሆናቸውን፤ ከግለሰብ ጋር ለሚደረግ የብድር ውል ግንኙነት ካርታን ማስያዝ እንደማይቻል፤ ለዚህ የህግ መሰረቱም የይዞታ አስተዳደር አገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 12/2004 አንቀጽ 33 መሆኑን፤ ‹‹በህጋዊ መንገድ ስልጣን ከተሰጠው አካል ፍቃድ ውጭ ለመያዣነት አያገለግልም›› በሚለው ማሳሰቢያ ውስጥ ስልጣን የተሰጠው አካል ማለት የይዞታ አስተዳደር የሽግግር ጊዜ አገ/ፕ/ጽ/ቤት እንደሆነና ከዚህ አካል ፍቃድና እውቅና ውጭ ለየትኛውም አገልግሎት ካርታን መጠቀም እንደማይችል፤ የማሳሰቢያው አላማም ብሄራዊ ባንክ እውቅና ከሰጣቸው ተቋማት ውጭ ንብረትን በመያዣነት እየያዙ ብድርን ለመስጠት የሚንቀሰቀቀሱ ተቋማትንና አራጣን ለመከላከል የተቀመጠ አሰራር እንደሆነ አብራርቷል፡:
በየካርታዎች ላይ የተቀመጠው ማሳሰቢያ ይዘትና የተሰጠውን ማብራሪያ ይህ ሲሆን የማይንቀሳቀስ ንብረትን አጠቃቀም ከሚደነግጉ አለማቀፋው እና ሃገራዊ ህጎች ጋር ያለው ተስማሚነት እስከ ምን ድረስ ነው?፤ የማሳሰቢያውና የአሰራሩ ምንጭ በትክክልስ መመሪያ ቁ.12/2004 ሊሆን ይችላል? በንብረት የመጠቀም መብት ላይ ገደብ የሚያስቀምጥ ከመሆኑ አንጻር በህጎች ላይ የተቀመጠውን የገደብ አጣጣል መርህ የተከተለ ነው? ፤ በማብራሪያው እንደተቀመጠው ማሳሰቢያውና አሰራሩ አራጣን የመከላከል ሚና አለው? ይህስ ተግባር የሚያከናውን ሌላ ተቋም የለምን? የመመሪያ ቁ.12/2004 አንቀጽ 33 ድንጋጌ ይዘት ፈቃጅ ወይስ ከልካይ? ይህ አንቀጽስ በውል የሚቋቋም የማይንቀሳቀስ ንብረት መያዣ መለከታል? የሚለውን መመርመር አስፈላጊ ነው፡፡ የንብረት መብት ህገ-መንግስታዊ እውቅና ሊሰጣቸው ከሚገባ መብቶች አንዱ እንደመሆኑ መጠን የ1987ቱ የኢትዮጲያ ህገ-መንግስትም በምዕራፍ ሶስት ለሰብአዊ መብቶችና መሰረታዊ ነጻነቶችን እውቅና የሰጠ ሲሆን ማንኛውም የኢትዮጲያ ዜጋ ጉልበቱን ፤ የመፍጠር ችሎታውን እና ካፒታሉን ፈሰስ አድርጎ ያገኘው ንብረት ላይ የግል ባለቤትነት መብቱ የተጠበቀና የመሽጥ፤የማውረስና በማንኛውም መልኩ የማስተላለፍ (በዋስትና የማሳዝ) መብት ያለው መሆኑን ደንግጓል፡፡ ይህ መብቱ ሊገደብ የሚችለው የሌሎችን መብት ከተቃረነ ወይም መገደቡ የህዝብ ጥቅምን ለመጠበቅ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝና ባለ መብቱ ለሚደርስበት መጉላላት በቂ ካሳ ከተከፈለው እንደሆነ ያስቀምጣል፡፡
መሬትን በተመለከተ የባለቤትነት መብቱ የመንግስትና የህዝብ ሲሆን ከገጠርና ከኢንቨስትመንት መሬት በተቃራኒ የከተማ መሬትን እንዴት ማግኝት ይቻላል? ይህ ህገ-መንግስት ከመውጣቱ በፊትም ሆነ በኋላ የከተማ መሬት የያዙ ሰዎች መብት እስከምን ድረስ ነው? የሚለውን ግን ሳይመልስ አልፎታል፡፡ የ1952ቱ የፍትሐብሄር ሕግ ህገ-መንግስቱ ከመወጣቱ በፊት እንደመውጣቱ መጠን የማይንቀሳቀስ ንብረትን (መሬትን ጨምሮ) መሸጥ፤ መለወጥ፤ማከራየት እና ለብደርም ሆነ ለሌላ እዳ እንደመያዣ መጠቀም እንደሚቻል በዝርዝር ደንግጓል፡፡ የማይንቀሳቀስ ንብረት መያዣ በሶስት መልኩ ማለትም በህግ፤ በፍርድ ቤትና በውል ሊቋቋም ይችላል፡፡ ከህግ የሚመነጭ መያዣ ከተዋዋይ ወገኖች መካከል አንዱ ወገን ግዴታውን ባይወጣ ሌላው ወገን ጥቅሙን ስለሚያስከብርበት መንገድ ሳይዋዋሉ በቀሩ ጊዜ ህጉ ክፍቱን ለመሙላት ያሰቀመጣቸው ሁኔታዎች ሲሆኑ ለምሳሌ አንድ የማይንቀሳቀስ ንብረት የሸጠ ሰው ላልተከፈለው የብር መጠንና በውሉ ላይ ላሉት መብቶች የሸጠው የማይንቀሰቀስ ንብረት እንደ መያዣ ሆኖ ያገለግለዋል ሲል ህጉ ደንግጎ ይገኛል፡፡ በፍርድ ቤት ከሚሰጡ ትዕዛዞችና ውሳኔዎች የሚመነጭ መያዣ የሚቋቋመው ከፍርድ በፊትም ሆነ በኋላ በራሱ በፍርድ ቤቱ አነሳሽነት ወይም በከሳሹ (በፍርድ በለመብቱ) ጠያቂነት ለክርክሩ መነሻ የሆነው የማይንቀሳቀስ ንብረት ክርክሩ እስከሚያልቅ ድረስ ወይም ለፍርድ አፈጻጸም ሲባል እንደመያዣ ሆኖ ተከብሮ እንዲቆይ ሲል ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ በሚሰጥበት ጊዜ ነው፡፡ በውል የሚቋቋም የማይንቀሳቀስ ንብረት መያዣ በሁለት ወይም ከዚያ በላይ በሆኑ ተዋዋይ ወገኖች ነጻ ፍቃድና ስምምነት መሰረት በተደረገ ወይም ለወደፊቱ በሚደረግ ውል ለሚደርስ /ይደርሳል/ ተብሎ ለሚጠበቅ የብር መጠን ልክ የማይንቀሳቀስ ንብረት እንደ መያዣ የሚያዝበት ተጨማሪ ውል ነው፡፡
ስለውል በጠቅላላው በሚደነግገው ክፍል የተቀመጡ የችሎታ ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆነው ባለእዳው አንድን የማይንቀሳቅስ ንብረት ለገንዘብ ጠያቂው በውል በመያዣነት ለመስጠት የሚችለው ንብረቱን የመሸጥ የመለወጥ መብት ካለው ወይም ሶስተኛ ወገንም ከሆነም ንብረቱን ስለባለዕዳው ለማሲያዝ የሚችለው ንብረቱን በስጦታ የመስጠት ችሎታ ያለው ከሆነ ብቻ ነው፡፡
*******************************************
ውድ የፌስ ቡክ ገጻችን ተከታታዮች በኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የፌዴራል ህጎች ተፈጻሚነት መከታተያ ዳይሬክቶሬት ጥናት ካደረገባቸው ጉዳዮች መካከል ከላይ በርዕሱ ላይ በተመለከተው ጉዳይ ዙሪያ የስራ ክፍሉ ያዘጋጀውን አጭር ሀተታ እንደሚከተለው አቅርበንላችኋል፡፡
የአ/አ/ከ/አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ የነባር ባለ ይዞታነትና የቤት ባለቤትነት ማረጋገጫ፣ የነባር ይዞታ ተነጻጻሪ ካርታ፣ ግንባታው የተጠናቀቀ የሊዝ ይዞታና የቤት ባለቤትነት ማረጋገጫ (አረንጓዴ ቀለም ያለው)፣ የሊዝ ተነጻጻሪ ባለይዞታና የቤት ባለቤትነት ካርታ እና ግንባታው ለተጀመረ የሊዝ ባለይዞታነትና የቤት ባለቤትነት ካርታ (ቢጫ ቀለም ያለው) ተራ ቁጥር ላይ ለተዘረዘሩት የካርታ አይነቶች በጀርባቸው ላይ የተቀመጠው ማሳሰቢያ ‹‹በዚህ ካርታ ላይ የሰፈረው ቦታ/ይዞታ በህጋዊ መንገድ ስልጣን ከተሰጠው አካል ፍቃድ ውጭ ለመያዣነት አያገለግልም›› ሲል በነባር ይዞታ ተነጻጻሪ ካርታ ላይ ግን ‹‹በዚህ ካርታ ላይ የሚገኝ ንብረትን በህጋዊ መንገድ ስልጣን ከተሰጠው አካል እውቅና ውጭ ለመያዣነት አያገለግልም የሚል ይዘትን አስቀምጧል፡፡ ይህም ካርታን ለመያዣ ለመጠቀም የሚመለከተውን አካል ፍቃድ ማግኝት ወይስ ማሳወቅ ብቻ በቂ ነው? ይህ የሚያስፈልገውስ ለይዞታው ብቻ ወይስ ካርታው ላይ ለሰፈረው ለማንኛውም ንብረት ነውን ? ለሚለው ጥያቄ ወጥ በሆነ መልኩ ምላሽ የማይመልስ፣ የተለያየ ይዘት ያለው ማሳሰቢያ በተለያየ ጊዜ በካርታዎች ላይ የሚቀመጥና በተጠቃሚዎች ላይም የተለያየ ግዴታ እና መብት የሚጥል መሆኑን ያመላክታል፡፡
የዚህን ማሳሰቢያ ህጋዊነትና አላማን በተመለከተ የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫ ምዝገባ ጽ/ቤት ህጋዊ አስተያየት እንዲሰጠበት በጠየቀው መሰረት ካርታውን የሚያዘጋጀው የአ/አ/ከ/አስ/መ/ል/ማ/ቢሮ በቀን 27/02/2011 በቁጥር ይአሰ/45/2011 ማብራሪያ ሲሰጥ ካርታን እንደመያዣ መጠቀም የሚችሉት ከብሄራዊ ባንክ በኩል እውቅና ያገኙ የፋይናንስ ተቋማት ብቻ መሆናቸውን፤ ከግለሰብ ጋር ለሚደረግ የብድር ውል ግንኙነት ካርታን ማስያዝ እንደማይቻል፤ ለዚህ የህግ መሰረቱም የይዞታ አስተዳደር አገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 12/2004 አንቀጽ 33 መሆኑን፤ ‹‹በህጋዊ መንገድ ስልጣን ከተሰጠው አካል ፍቃድ ውጭ ለመያዣነት አያገለግልም›› በሚለው ማሳሰቢያ ውስጥ ስልጣን የተሰጠው አካል ማለት የይዞታ አስተዳደር የሽግግር ጊዜ አገ/ፕ/ጽ/ቤት እንደሆነና ከዚህ አካል ፍቃድና እውቅና ውጭ ለየትኛውም አገልግሎት ካርታን መጠቀም እንደማይችል፤ የማሳሰቢያው አላማም ብሄራዊ ባንክ እውቅና ከሰጣቸው ተቋማት ውጭ ንብረትን በመያዣነት እየያዙ ብድርን ለመስጠት የሚንቀሰቀቀሱ ተቋማትንና አራጣን ለመከላከል የተቀመጠ አሰራር እንደሆነ አብራርቷል፡:
በየካርታዎች ላይ የተቀመጠው ማሳሰቢያ ይዘትና የተሰጠውን ማብራሪያ ይህ ሲሆን የማይንቀሳቀስ ንብረትን አጠቃቀም ከሚደነግጉ አለማቀፋው እና ሃገራዊ ህጎች ጋር ያለው ተስማሚነት እስከ ምን ድረስ ነው?፤ የማሳሰቢያውና የአሰራሩ ምንጭ በትክክልስ መመሪያ ቁ.12/2004 ሊሆን ይችላል? በንብረት የመጠቀም መብት ላይ ገደብ የሚያስቀምጥ ከመሆኑ አንጻር በህጎች ላይ የተቀመጠውን የገደብ አጣጣል መርህ የተከተለ ነው? ፤ በማብራሪያው እንደተቀመጠው ማሳሰቢያውና አሰራሩ አራጣን የመከላከል ሚና አለው? ይህስ ተግባር የሚያከናውን ሌላ ተቋም የለምን? የመመሪያ ቁ.12/2004 አንቀጽ 33 ድንጋጌ ይዘት ፈቃጅ ወይስ ከልካይ? ይህ አንቀጽስ በውል የሚቋቋም የማይንቀሳቀስ ንብረት መያዣ መለከታል? የሚለውን መመርመር አስፈላጊ ነው፡፡ የንብረት መብት ህገ-መንግስታዊ እውቅና ሊሰጣቸው ከሚገባ መብቶች አንዱ እንደመሆኑ መጠን የ1987ቱ የኢትዮጲያ ህገ-መንግስትም በምዕራፍ ሶስት ለሰብአዊ መብቶችና መሰረታዊ ነጻነቶችን እውቅና የሰጠ ሲሆን ማንኛውም የኢትዮጲያ ዜጋ ጉልበቱን ፤ የመፍጠር ችሎታውን እና ካፒታሉን ፈሰስ አድርጎ ያገኘው ንብረት ላይ የግል ባለቤትነት መብቱ የተጠበቀና የመሽጥ፤የማውረስና በማንኛውም መልኩ የማስተላለፍ (በዋስትና የማሳዝ) መብት ያለው መሆኑን ደንግጓል፡፡ ይህ መብቱ ሊገደብ የሚችለው የሌሎችን መብት ከተቃረነ ወይም መገደቡ የህዝብ ጥቅምን ለመጠበቅ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝና ባለ መብቱ ለሚደርስበት መጉላላት በቂ ካሳ ከተከፈለው እንደሆነ ያስቀምጣል፡፡
መሬትን በተመለከተ የባለቤትነት መብቱ የመንግስትና የህዝብ ሲሆን ከገጠርና ከኢንቨስትመንት መሬት በተቃራኒ የከተማ መሬትን እንዴት ማግኝት ይቻላል? ይህ ህገ-መንግስት ከመውጣቱ በፊትም ሆነ በኋላ የከተማ መሬት የያዙ ሰዎች መብት እስከምን ድረስ ነው? የሚለውን ግን ሳይመልስ አልፎታል፡፡ የ1952ቱ የፍትሐብሄር ሕግ ህገ-መንግስቱ ከመወጣቱ በፊት እንደመውጣቱ መጠን የማይንቀሳቀስ ንብረትን (መሬትን ጨምሮ) መሸጥ፤ መለወጥ፤ማከራየት እና ለብደርም ሆነ ለሌላ እዳ እንደመያዣ መጠቀም እንደሚቻል በዝርዝር ደንግጓል፡፡ የማይንቀሳቀስ ንብረት መያዣ በሶስት መልኩ ማለትም በህግ፤ በፍርድ ቤትና በውል ሊቋቋም ይችላል፡፡ ከህግ የሚመነጭ መያዣ ከተዋዋይ ወገኖች መካከል አንዱ ወገን ግዴታውን ባይወጣ ሌላው ወገን ጥቅሙን ስለሚያስከብርበት መንገድ ሳይዋዋሉ በቀሩ ጊዜ ህጉ ክፍቱን ለመሙላት ያሰቀመጣቸው ሁኔታዎች ሲሆኑ ለምሳሌ አንድ የማይንቀሳቀስ ንብረት የሸጠ ሰው ላልተከፈለው የብር መጠንና በውሉ ላይ ላሉት መብቶች የሸጠው የማይንቀሰቀስ ንብረት እንደ መያዣ ሆኖ ያገለግለዋል ሲል ህጉ ደንግጎ ይገኛል፡፡ በፍርድ ቤት ከሚሰጡ ትዕዛዞችና ውሳኔዎች የሚመነጭ መያዣ የሚቋቋመው ከፍርድ በፊትም ሆነ በኋላ በራሱ በፍርድ ቤቱ አነሳሽነት ወይም በከሳሹ (በፍርድ በለመብቱ) ጠያቂነት ለክርክሩ መነሻ የሆነው የማይንቀሳቀስ ንብረት ክርክሩ እስከሚያልቅ ድረስ ወይም ለፍርድ አፈጻጸም ሲባል እንደመያዣ ሆኖ ተከብሮ እንዲቆይ ሲል ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ በሚሰጥበት ጊዜ ነው፡፡ በውል የሚቋቋም የማይንቀሳቀስ ንብረት መያዣ በሁለት ወይም ከዚያ በላይ በሆኑ ተዋዋይ ወገኖች ነጻ ፍቃድና ስምምነት መሰረት በተደረገ ወይም ለወደፊቱ በሚደረግ ውል ለሚደርስ /ይደርሳል/ ተብሎ ለሚጠበቅ የብር መጠን ልክ የማይንቀሳቀስ ንብረት እንደ መያዣ የሚያዝበት ተጨማሪ ውል ነው፡፡
ስለውል በጠቅላላው በሚደነግገው ክፍል የተቀመጡ የችሎታ ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆነው ባለእዳው አንድን የማይንቀሳቅስ ንብረት ለገንዘብ ጠያቂው በውል በመያዣነት ለመስጠት የሚችለው ንብረቱን የመሸጥ የመለወጥ መብት ካለው ወይም ሶስተኛ ወገንም ከሆነም ንብረቱን ስለባለዕዳው ለማሲያዝ የሚችለው ንብረቱን በስጦታ የመስጠት ችሎታ ያለው ከሆነ ብቻ ነው፡፡
የፍትሐብሄር ህጉ የማይንቀሳቀስ ንብረት የመያዣ ውል የሚቋቋምባቸው ንብረቶች በህግ እንደማይንቀሳቀስ ንብረት የሚቆጠሩ ተንቀሳቃሽ ንብረቶች እንደተጠበቁ ሆነው መሬትና ቤት ናቸው ቢልም አሁን መሬት የህዝብና የመንግስት ከመሆኑ አንጻር በቀጥታ ያለምንም ገደበ መሽጥ ወይም መለወጥ አይቻልም፡፡ ሆኖም ግን የከተማ ቦታን በሊዝ ያገኘ ግለሰብ ለቦታው በከፈለው የሊዝ ዋጋ ልክና የሊዝ ዘመን ድረስ ቦታውን ወይም ቤቱን ለውል ማሳዣ መጠቀም እንደሚችል በሊዚ አዋጅ 721/04 ተደንግጓል፡፡ ይህንንም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ሊዝ አፈጻጸም ደንብ ቁ.49/2004 እና መመሪያ ቁ.11/2004 በተመሳሳይ በግለጽ ደንግገውት ይገኛል፡፡
ለብድር ሆነ ለሌላ ውል ማስያዣ የማይንቀሳቀስ ንብረት ሲያዝ ውል ለማረጋገጥና ለመመዝገብ ስልጣን በተሰጠው አካል (በአዲስ አበባ ደረጃ የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኢጀንሲ) ቀርቦ በጹሁፍ ሆኖ መመዝገብ ይኖርበታል፡፡ ይህ ያስፈለገበት ምክንያት በዋናነት የዜጎችን የግል ንብረት የማፍራት፣ የመጠቀም እና በሕጋዊ መንገድ የማስተላለፍ መብትን በማስከበር የፍትሕ ሥርዓቱን ለማገዝ የሕግ የበላይነትን ለማስጠበቅ፤ የመልካም አስተዳደርን እና የነጻ ገበያ ሥርዓት ግንባታን ለማሳለጥ እንደሆነ ተደንግጓል፡፡ ሰነድ አረጋጋጩም ሰነድ ከማረጋገጡና ከመመዝገቡ በፊት የሰነዱ ይዘት ሕግን እና ሞራልን የማይቃረን መሆኑን የማረጋገጥ ስልጣንና ተግባር ያለው ሲሆን የማይንቀሳቀስ ንብረት የመያዣ ውል በአዋጁ መሠረት ሲመዘግብ በሕግ አግባብ የተዘጋጀ የመያዣ ውል ሰነድና የማይንቀሳቀስ ንብረት ከሆነ ሁለት የሰው ምስክር መቅረቡን፤ እዳና እገዳ አለመኖሩን፣ ተዋዋዮች ከህግ ወይም ከውል የመነጨ ስልጣን ያላቸው ስለመሆኑ፣ የተዋዋዮች መታወቂያና ያላገባ ወይም ያገባ ማስረጃ፤ የትዳር አጋር የፈቃድ ስምምነት፣ በመያዣነት የቀረበው ንብረት የባለቤትነት ማረጋገጫ ማስረጃ አስቀርቦና መርምሮ መሆን እንዳለበት ተደንግጓል፡፡ ይህም ተበዳሪውም ሆነ አበዳሪው እንዳይታልልና ህግ-ወጥ ተግባር ውስጥ እንዳይሳተፍ የሚያደርግ ነው፡፡
ከህግና ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ የሚመነጭ የማይንቀሳቀስ ንብረት መያዣ በውልና ማስረጃ ቀርቦ መረጋገጥና መመዝገብ አይጠበቅበትም ምክኒያቱም ከህግ ከሆነ ህጉን ጠቅሶ መብትን ማስከበር ስለሚቻል እንዲሁም ከፍርድ የመነጨ ከሆነም የማይንቀሳቀስ ንብረት አስተዳዳሪ ለሆነ አካል ንብረቱ እንዲታገድና ተከብሮ እንዲቆ ትዕዛዝ እንዲሰጥ ማድረግ ብቻ በቂ ስለሆነ ነው፡፡ በተመሳሳይም ከባንክ ወይም ከፋይናንስ ተቋማት ጋር ለሚደረግ የብደር ውል የማይንቀሳቀስ ንብረቱን እንደመያዣ የሰጠ ተበዳሪ በሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ ጽ/ቤት ሄዶ መዋዋልና ማስመዝገብ ሳያስፈልገው ንብረት አስተዳደር ለሆነው (በአዲስ አበባ ደረጃ ለመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ) አካል የብድር ስምምነቱና የመያዣ ውሉ በባለንብረቱ የግል ማህደር ተመዝግቦ እንዲቀመጥ መድረጉ ብቻ በቂ መሆኑ በህጎች ላይ እና በቃለ -መጠየቅ ከሰበሰብነው መረጃ ማረጋገጥ ተችሏል፡፡
በዚህም ምክኒያት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ይህንና ሌሎች አገልግሎቶችን የሚጠይቁ ባለጉዳዮችን ከሊዚ አዋጁ፤ ከደንቡና ከአፈጻጸም መመሪያው ጋር የተጣጣመና ወጥ የሆነ አገልግሎት ለመስጠጥ ያስችለው ዘንድ የይዞታ አገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ ቁ.12/2004 ያወጣ ሲሆን ይህ መመሪያም በከተማ አስተዳደሩ የሚኖሩ ነዋሪዎች የካርታ ይሰራልኝ፤ የስም ይዛወርልኝ፤ ይዞታ ይከፈልልኝ እና ተያያዥ አገልግሎትን ምን ሲያሟሉ ያገኛሉ የሚለውን አስከ አንቀጽ 32 ድረስ ካስቀመጠ በኋል ዋስትናና እገዳ ይመዝገብልኝና ይሰረዝልኝ አገልግሎት እንዴት ይሰጣል? የሚለውን በአንቀጽ 33 ምላሽ የሰጠ ሲሆን የዚህ አገልግሎት ጥያቄ ቀጥታ ከነማን ሊቀርብ ይችላል የሚለውን በማሳያ መልኩ ሲደነግግ ‹‹የዋስትናና ዕገዳ ምዝገባ አገልገሎት ጥያቄ ከፍርድ ቤት፣ ከባንክ፣ ከኢንሹራንስና ሌሎች በሕግ አግባብ ስልጣን ከተሰጣቸው አካላት ሊቀርብ ይችላል።
“ዋስትናና ዕገዳ ምዝገባና ስረዛውም እንደሚከተለው ይፈጸማል›› በማለት አስቀምጦ እናገኝዋለን፡፡ በየካርታዎች ላይ እየተቀመጠ ያለው ማሳሰቢያና ካርታን እንደማስያዣ በመጠቀም ከግለሰብ መበደርን የሚከለክለው አሰራር የህግ መሰረቱ መመሪያ ቁ.12/2004 ነውን? የሚለውን ጉዳይ ስንመረምረው ከላይ ከተቀመጡት አለማቀፍ ህጎች፤ የ1987ቱ ህገ-መንግስት፤ የፍትሃብሄር ህጉ፤ የሊዚ አዋጁና በአዲስ አበባ ደረጃ የወጡ የሊዚ አፈጻጸም ደንብና መመሪያም ሆነ ራሱ መመሪያ ቁ.12/2004 በነባር ይዞታ ሆነ በሊዚ ለተገኘ ቦታ የተሰጠን ካርታ ባለይዞታው ለብደርም ሆነ ለሌላ ውል እንደማሳዣ ለመጠቀም የሚችለው በህግ ስልጣን የተሰጠው አካል ሲፈቅድና ውሉም (የብደር ውልን ጨምሮ) ከብሄራዊ ባንክ እውቅና ካገኘ የፋይናንስ ተቋም ጋር ከተደረገ ብቻ ነው የሚል ቅድመ-ሁኔታን ያዘለ ገደብ /ክልከላን/ አላስቀመጡም፡፡ ይልቁንም ከላይ እንዳየነው በአለማቀፍ ህጎችና ስምምነቶች ላይ የተቀመጡ የሰብአዊ መብት (የንብረት መብትን ጨምሮ) ድንጋጌዎች ሲተረጎሙ መንግስትም ቢሆን መብቶችን በሚያጣብብና በሚያፈርስ መልኩ ሊተረጉሟቸው እንደማይገባ ተደንግጓል፡፡
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ-መንግስትም ኢትዮጵያ ያጸደቀቻቸው የአለማቀፍ የሰብአዊ መብት የስምምነት ሰነዶች ልክ እንደ ሀገሪቱ ህግ የሚቆጠሩ ሲሆን ሶስቱ የመንግስት መዋቅሮችም እነዚህን መብቶች የማክበር፣ የማስከበርና የማሳደግ (የማሟላት) ግዴታ ተጥሎባቸዋል፡፡ ህገ-መንግስቱ በዚህ መልክ ለንብረት መብት ጥበቃ የሚያደርግለት ከሆነ በየደረጃው የሚገኝ ህግ አውጭ፤ ህግ አስፈጻሚና ህግ ተርጓሚ ለአሰራር አመችነት ሲል ወይም በቸልተኝነት በግልጽ የህገ-መንግሰት ወይም ህገ-መንግስቱን መሰረት አድርገው የወጡ ህጎችን መሰረት (ድጋፍ) ያላደረገ ህግ በማውጣት፣ የህግ መሰረት የሌለው አሰራር በማስቀመጥና በአግባቡ የወጡ ህጎችንም ከወጡበት አላማ ውጭ በመተርጎም መብቶችን መገደብ ወይም ማስቀረት የህግ ውጤት የሌለውና እንዳልተደረገ የሚቆጠር ተግባር እንደሆነ ህገ-መንግስቱ ደንግጓል፡፡
የፌዴራሉ የሊዚ አዋጅም ሆነ የአ/አ/ከ/አስተዳደር ያወጣው የሊዚ አፈጻጸም ደንብና መመሪያ ካርታን ለማሳዣነት ለመጠቀም በህግ ስልጣን የተሰጠው አካል ፍቃድ ያስፈልጋል፤ ይህ ስልጣን የተሰጠው አካልም የአ/አ/ከ/አስ/የይ/ጊ/ሽ/አገ/ፕሮጀክት ዴስክ ስለመሆኑም ሆነ የማይንቀሳቀስ ንብረት ማረጋገጫ ካርታን ከግለሰብ ጋር ለሚደረግ የብድር ውል መጠቀም አይቻልም የሚል የህግ ድንጋጌ አላስቀመጡም፡፡ የአግልግሎት አሰጣጥ መመሪያ ቁ.12/2004 በመግቢያው ላይ ‹‹ሰነድ ያላቸው ህጋዊ ባለይዞታዎችና በህግ የከተማ ቦታ የሚፈቀድላቸው ሰዎች የሚጠይቋቸውን የተለያዩ መስተንግዶዎች ከሊዚ አዋጁና ደንቡ ጋር በተጣጣመ መልኩ ለመስጠት እንዲቻል›› በማለት ያስቀመጠውን አለማ ስናይም የሊዚ አዋጁን፣ የአፈጻጸም ደንብና መመሪያውን ሳይከተል ለተቀመጠ ማሳሰቢያና አሰራር የህግ መሰረቱ ነው ማለት አይቻልም፡፡ ይልቁንስ ከመመሪያው ስያሜ ማለትም (የአገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ) ከሚለው ጀምሮ ከአንቀጽ 1 አስከ 32 ያሉ የህግ ድንጋጌዎች የካርታ አሰጣጥ፤የስም ዝውውር፤ የቦታ ክፍፍል የመሳሰሉት አገልግቶች በተገልጋዩ በሚጠየቁ ጊዜ እንዴት ይስተናገዱ የሚለውን እንደሚመልሱት ሁሉ አንቀጽ 33 ትም ከላይ እንዳየነው ፍርድ ቤቶች፤ባንኮች እና የኢንሹራንስ ተቋማት የማይንቀሳቀስ ንብረትን (ካርታን) ለፍርድ አፈጻጸምም ሆነ ለእዳ
ለብድር ሆነ ለሌላ ውል ማስያዣ የማይንቀሳቀስ ንብረት ሲያዝ ውል ለማረጋገጥና ለመመዝገብ ስልጣን በተሰጠው አካል (በአዲስ አበባ ደረጃ የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኢጀንሲ) ቀርቦ በጹሁፍ ሆኖ መመዝገብ ይኖርበታል፡፡ ይህ ያስፈለገበት ምክንያት በዋናነት የዜጎችን የግል ንብረት የማፍራት፣ የመጠቀም እና በሕጋዊ መንገድ የማስተላለፍ መብትን በማስከበር የፍትሕ ሥርዓቱን ለማገዝ የሕግ የበላይነትን ለማስጠበቅ፤ የመልካም አስተዳደርን እና የነጻ ገበያ ሥርዓት ግንባታን ለማሳለጥ እንደሆነ ተደንግጓል፡፡ ሰነድ አረጋጋጩም ሰነድ ከማረጋገጡና ከመመዝገቡ በፊት የሰነዱ ይዘት ሕግን እና ሞራልን የማይቃረን መሆኑን የማረጋገጥ ስልጣንና ተግባር ያለው ሲሆን የማይንቀሳቀስ ንብረት የመያዣ ውል በአዋጁ መሠረት ሲመዘግብ በሕግ አግባብ የተዘጋጀ የመያዣ ውል ሰነድና የማይንቀሳቀስ ንብረት ከሆነ ሁለት የሰው ምስክር መቅረቡን፤ እዳና እገዳ አለመኖሩን፣ ተዋዋዮች ከህግ ወይም ከውል የመነጨ ስልጣን ያላቸው ስለመሆኑ፣ የተዋዋዮች መታወቂያና ያላገባ ወይም ያገባ ማስረጃ፤ የትዳር አጋር የፈቃድ ስምምነት፣ በመያዣነት የቀረበው ንብረት የባለቤትነት ማረጋገጫ ማስረጃ አስቀርቦና መርምሮ መሆን እንዳለበት ተደንግጓል፡፡ ይህም ተበዳሪውም ሆነ አበዳሪው እንዳይታልልና ህግ-ወጥ ተግባር ውስጥ እንዳይሳተፍ የሚያደርግ ነው፡፡
ከህግና ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ የሚመነጭ የማይንቀሳቀስ ንብረት መያዣ በውልና ማስረጃ ቀርቦ መረጋገጥና መመዝገብ አይጠበቅበትም ምክኒያቱም ከህግ ከሆነ ህጉን ጠቅሶ መብትን ማስከበር ስለሚቻል እንዲሁም ከፍርድ የመነጨ ከሆነም የማይንቀሳቀስ ንብረት አስተዳዳሪ ለሆነ አካል ንብረቱ እንዲታገድና ተከብሮ እንዲቆ ትዕዛዝ እንዲሰጥ ማድረግ ብቻ በቂ ስለሆነ ነው፡፡ በተመሳሳይም ከባንክ ወይም ከፋይናንስ ተቋማት ጋር ለሚደረግ የብደር ውል የማይንቀሳቀስ ንብረቱን እንደመያዣ የሰጠ ተበዳሪ በሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ ጽ/ቤት ሄዶ መዋዋልና ማስመዝገብ ሳያስፈልገው ንብረት አስተዳደር ለሆነው (በአዲስ አበባ ደረጃ ለመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ) አካል የብድር ስምምነቱና የመያዣ ውሉ በባለንብረቱ የግል ማህደር ተመዝግቦ እንዲቀመጥ መድረጉ ብቻ በቂ መሆኑ በህጎች ላይ እና በቃለ -መጠየቅ ከሰበሰብነው መረጃ ማረጋገጥ ተችሏል፡፡
በዚህም ምክኒያት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ይህንና ሌሎች አገልግሎቶችን የሚጠይቁ ባለጉዳዮችን ከሊዚ አዋጁ፤ ከደንቡና ከአፈጻጸም መመሪያው ጋር የተጣጣመና ወጥ የሆነ አገልግሎት ለመስጠጥ ያስችለው ዘንድ የይዞታ አገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ ቁ.12/2004 ያወጣ ሲሆን ይህ መመሪያም በከተማ አስተዳደሩ የሚኖሩ ነዋሪዎች የካርታ ይሰራልኝ፤ የስም ይዛወርልኝ፤ ይዞታ ይከፈልልኝ እና ተያያዥ አገልግሎትን ምን ሲያሟሉ ያገኛሉ የሚለውን አስከ አንቀጽ 32 ድረስ ካስቀመጠ በኋል ዋስትናና እገዳ ይመዝገብልኝና ይሰረዝልኝ አገልግሎት እንዴት ይሰጣል? የሚለውን በአንቀጽ 33 ምላሽ የሰጠ ሲሆን የዚህ አገልግሎት ጥያቄ ቀጥታ ከነማን ሊቀርብ ይችላል የሚለውን በማሳያ መልኩ ሲደነግግ ‹‹የዋስትናና ዕገዳ ምዝገባ አገልገሎት ጥያቄ ከፍርድ ቤት፣ ከባንክ፣ ከኢንሹራንስና ሌሎች በሕግ አግባብ ስልጣን ከተሰጣቸው አካላት ሊቀርብ ይችላል።
“ዋስትናና ዕገዳ ምዝገባና ስረዛውም እንደሚከተለው ይፈጸማል›› በማለት አስቀምጦ እናገኝዋለን፡፡ በየካርታዎች ላይ እየተቀመጠ ያለው ማሳሰቢያና ካርታን እንደማስያዣ በመጠቀም ከግለሰብ መበደርን የሚከለክለው አሰራር የህግ መሰረቱ መመሪያ ቁ.12/2004 ነውን? የሚለውን ጉዳይ ስንመረምረው ከላይ ከተቀመጡት አለማቀፍ ህጎች፤ የ1987ቱ ህገ-መንግስት፤ የፍትሃብሄር ህጉ፤ የሊዚ አዋጁና በአዲስ አበባ ደረጃ የወጡ የሊዚ አፈጻጸም ደንብና መመሪያም ሆነ ራሱ መመሪያ ቁ.12/2004 በነባር ይዞታ ሆነ በሊዚ ለተገኘ ቦታ የተሰጠን ካርታ ባለይዞታው ለብደርም ሆነ ለሌላ ውል እንደማሳዣ ለመጠቀም የሚችለው በህግ ስልጣን የተሰጠው አካል ሲፈቅድና ውሉም (የብደር ውልን ጨምሮ) ከብሄራዊ ባንክ እውቅና ካገኘ የፋይናንስ ተቋም ጋር ከተደረገ ብቻ ነው የሚል ቅድመ-ሁኔታን ያዘለ ገደብ /ክልከላን/ አላስቀመጡም፡፡ ይልቁንም ከላይ እንዳየነው በአለማቀፍ ህጎችና ስምምነቶች ላይ የተቀመጡ የሰብአዊ መብት (የንብረት መብትን ጨምሮ) ድንጋጌዎች ሲተረጎሙ መንግስትም ቢሆን መብቶችን በሚያጣብብና በሚያፈርስ መልኩ ሊተረጉሟቸው እንደማይገባ ተደንግጓል፡፡
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ-መንግስትም ኢትዮጵያ ያጸደቀቻቸው የአለማቀፍ የሰብአዊ መብት የስምምነት ሰነዶች ልክ እንደ ሀገሪቱ ህግ የሚቆጠሩ ሲሆን ሶስቱ የመንግስት መዋቅሮችም እነዚህን መብቶች የማክበር፣ የማስከበርና የማሳደግ (የማሟላት) ግዴታ ተጥሎባቸዋል፡፡ ህገ-መንግስቱ በዚህ መልክ ለንብረት መብት ጥበቃ የሚያደርግለት ከሆነ በየደረጃው የሚገኝ ህግ አውጭ፤ ህግ አስፈጻሚና ህግ ተርጓሚ ለአሰራር አመችነት ሲል ወይም በቸልተኝነት በግልጽ የህገ-መንግሰት ወይም ህገ-መንግስቱን መሰረት አድርገው የወጡ ህጎችን መሰረት (ድጋፍ) ያላደረገ ህግ በማውጣት፣ የህግ መሰረት የሌለው አሰራር በማስቀመጥና በአግባቡ የወጡ ህጎችንም ከወጡበት አላማ ውጭ በመተርጎም መብቶችን መገደብ ወይም ማስቀረት የህግ ውጤት የሌለውና እንዳልተደረገ የሚቆጠር ተግባር እንደሆነ ህገ-መንግስቱ ደንግጓል፡፡
የፌዴራሉ የሊዚ አዋጅም ሆነ የአ/አ/ከ/አስተዳደር ያወጣው የሊዚ አፈጻጸም ደንብና መመሪያ ካርታን ለማሳዣነት ለመጠቀም በህግ ስልጣን የተሰጠው አካል ፍቃድ ያስፈልጋል፤ ይህ ስልጣን የተሰጠው አካልም የአ/አ/ከ/አስ/የይ/ጊ/ሽ/አገ/ፕሮጀክት ዴስክ ስለመሆኑም ሆነ የማይንቀሳቀስ ንብረት ማረጋገጫ ካርታን ከግለሰብ ጋር ለሚደረግ የብድር ውል መጠቀም አይቻልም የሚል የህግ ድንጋጌ አላስቀመጡም፡፡ የአግልግሎት አሰጣጥ መመሪያ ቁ.12/2004 በመግቢያው ላይ ‹‹ሰነድ ያላቸው ህጋዊ ባለይዞታዎችና በህግ የከተማ ቦታ የሚፈቀድላቸው ሰዎች የሚጠይቋቸውን የተለያዩ መስተንግዶዎች ከሊዚ አዋጁና ደንቡ ጋር በተጣጣመ መልኩ ለመስጠት እንዲቻል›› በማለት ያስቀመጠውን አለማ ስናይም የሊዚ አዋጁን፣ የአፈጻጸም ደንብና መመሪያውን ሳይከተል ለተቀመጠ ማሳሰቢያና አሰራር የህግ መሰረቱ ነው ማለት አይቻልም፡፡ ይልቁንስ ከመመሪያው ስያሜ ማለትም (የአገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ) ከሚለው ጀምሮ ከአንቀጽ 1 አስከ 32 ያሉ የህግ ድንጋጌዎች የካርታ አሰጣጥ፤የስም ዝውውር፤ የቦታ ክፍፍል የመሳሰሉት አገልግቶች በተገልጋዩ በሚጠየቁ ጊዜ እንዴት ይስተናገዱ የሚለውን እንደሚመልሱት ሁሉ አንቀጽ 33 ትም ከላይ እንዳየነው ፍርድ ቤቶች፤ባንኮች እና የኢንሹራንስ ተቋማት የማይንቀሳቀስ ንብረትን (ካርታን) ለፍርድ አፈጻጸምም ሆነ ለእዳ
ማስከበሪያ ሲይዙ በውልና ማስረጃ መዋዋልና ማስመዝገብ ስለማያስፈልጋቸው ቀጥታ ንብረቱን ለሚያስተዳድረው የአዲስ አበባ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ እግዱ ወይም የዋስትና ሰነዱ በባለ እዳው የግል የንብረት ማህደር እንዲቀመጥ ወይም እዳና እገዳው እንዲነሳ አግልግሎት በሚጠይቁበት ጊዜ አግልግሎቱ እንዴት ይሰጣል? የሚለውን ለመመለስና ይህን አገልግሎትስ እነማን ያገኛሉ ለሚለው በአብነት መልክ ያስቀመጠ እንጅ ካርታን የሚይዙት እነዚህ አካላት ብቻ ናቸው ባላለበት፣ መመሪያ እንደመሆኑ መጠን የፍትሃብሄር ህጉንና የሰነዶች ማረጋገጫ ምዝገባ አዋጅን መሻር በማይችልበትና በነዚህ ህጎች መሰረት በግለሰቦች መካከል ለሚቋቋም የብደር ውል ማስከበሪያ የማይንቀሳቀስ ንብረት መያዣን በግልጽ ባልከለከለበት፤ የማይንቀሳቀስ ንብረት ማረጋገጫ ካርታን ከመጠቀም ጋር ተያይዞ ለአ/አ/ከ/አስ/የይ/ጊ/አገ/ፕ/ዴስክ ስልጣን ባልሰጠበት ሁኔታ የመመሪያው አንቀጽ 33 በካርታዎች ላይ ለሚቀመጠው መብት ገዳቢ ማሳሰቢያና ከግለሰብ ጋር ለሚደረግ የብድር ውል ካርታን እንደ ማሳዣ መጠቀምን ለሚከለክለው አሰራር የህግ መሰረት የሚሆንበት አግባብ የለም፡፡
የማሳሰቢያውና የክልከላው አላማም ባለይዞታዎችን በብድር ስም ካርታን እንደመያዣ እየያዙ የአራጣን ስራ ከሚሰሩ ግለሰቦች ለመጠበቅና አራጣን ለመከላከል ነው ይባል እንጅ አራጣ ማለት አንድ ሰው የሌላውን ሰው ችግረኛነት፤ የበታችነት፤ ወይም ደካማነቱን አይቶ በህግ ከተፈቀደው ወለድ በላይ ገንዘብ ካበደረው ወይም ተመጣጣኝነት የሌለውን ንብረት በምትኩ እንዲሰጠው ቃል(ውል) ያስገባው እንደሆነ ነው፡፡ ከጉዳያችን ጋር የሚያያዘው ተመጣጣኝ ያለሆነ (ከእዳው የበለጠ) ንብረት በመያዣ መያዝ ሲሆን ይህ ድርጊት በወንጀል የሚያስቀጣና በቀጥታ የፍትህ አካለት (የፖሊስ፤ የዓቃቤ ህግ መሰሪያ ቤትና የፍርድ ቤትን) የሚመለከት ከመሆኑ በተጫማሪ አበዳሪው ተመጣጣኝ ያልሆነ ንብረትን (መሬትና ቤት ሲሆን) በምትኩ እንዲሰጠው የሚያደርግ አሰገዳጅ ቃል (ውል) ተበዳሪውን ለማሰገባት ከላይ እንደተመለከትነው ይህ የተገባው ቃል ወይም ውል በውልና ማስረጃ መመዝገብ ይጠበቅበታል፡፡ መዝጋቢው አካልም (በአ/አ/ ደረጃ የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኢጀንሲ) ከተሰጠው ስልጣንና ሃላፊነት መካከል የተዋዋዮችን ችሎታ ፤ ንብረቱን ወይም ካርታውን የሚያስዘው ግለሰብ ህጋዊ ባለቤትነትን፤ ንብረቱ ለምን ያህል የገንዘብ መጠን እንደተያዘ በውሉ መቀመጡን፤ ይህን ብቻ ሳይሆን በጠቅላላው ከህግና /ለምሳሌ አራጣን ከሚከለክለው የወንጀል ህግ/ ከሞራል አንጻር የማይቃረን መሆኑን የማረጋገጥና የመመዝገብ ነው፡፡
ወንጀልን የመከላከል የሁሉም ግለሰብና ተቋም ድርሻ ቢሆንም በዋናነት ከላይ የጠቀስናቸው ተቋማት ሃላፊነት ሆኖ እያለ በህግ በግልጽ ይህን ወንጀል እንዲከላከል ግዴታ ባልተጣለበትና በካርታ አጠቃቀም መብት ላይ ገደብ የማስቀመጥ ስልጣን ባልተሰጠበት ሁኔታ አራጣን ለመከላከል ነው በሚል የዜጎችን በንብረት የመጠቀም ሰብአዊ መብት የሚገድብ የህግ መሰረት የሌለው ማሳሰቢያና ከልካይ አሰራር ማስቀመጡ አግባብ አይደለም፡፡
ውድ የፌስ ቡክ ገጻችን ተከታታዮች ከማብራሪያው ጥሩ ግንዛቤ እንደጨበጣችሁ እየተማመንን በቀጣይ በዚሁ የስራ ክፍል ጥናት የተደረገባቸው ጉዳዮች ላይ የቀረቡ ሀተታዎችን ይዘን የምንቀርብ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ቸር ቆዩን!
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
የማሳሰቢያውና የክልከላው አላማም ባለይዞታዎችን በብድር ስም ካርታን እንደመያዣ እየያዙ የአራጣን ስራ ከሚሰሩ ግለሰቦች ለመጠበቅና አራጣን ለመከላከል ነው ይባል እንጅ አራጣ ማለት አንድ ሰው የሌላውን ሰው ችግረኛነት፤ የበታችነት፤ ወይም ደካማነቱን አይቶ በህግ ከተፈቀደው ወለድ በላይ ገንዘብ ካበደረው ወይም ተመጣጣኝነት የሌለውን ንብረት በምትኩ እንዲሰጠው ቃል(ውል) ያስገባው እንደሆነ ነው፡፡ ከጉዳያችን ጋር የሚያያዘው ተመጣጣኝ ያለሆነ (ከእዳው የበለጠ) ንብረት በመያዣ መያዝ ሲሆን ይህ ድርጊት በወንጀል የሚያስቀጣና በቀጥታ የፍትህ አካለት (የፖሊስ፤ የዓቃቤ ህግ መሰሪያ ቤትና የፍርድ ቤትን) የሚመለከት ከመሆኑ በተጫማሪ አበዳሪው ተመጣጣኝ ያልሆነ ንብረትን (መሬትና ቤት ሲሆን) በምትኩ እንዲሰጠው የሚያደርግ አሰገዳጅ ቃል (ውል) ተበዳሪውን ለማሰገባት ከላይ እንደተመለከትነው ይህ የተገባው ቃል ወይም ውል በውልና ማስረጃ መመዝገብ ይጠበቅበታል፡፡ መዝጋቢው አካልም (በአ/አ/ ደረጃ የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኢጀንሲ) ከተሰጠው ስልጣንና ሃላፊነት መካከል የተዋዋዮችን ችሎታ ፤ ንብረቱን ወይም ካርታውን የሚያስዘው ግለሰብ ህጋዊ ባለቤትነትን፤ ንብረቱ ለምን ያህል የገንዘብ መጠን እንደተያዘ በውሉ መቀመጡን፤ ይህን ብቻ ሳይሆን በጠቅላላው ከህግና /ለምሳሌ አራጣን ከሚከለክለው የወንጀል ህግ/ ከሞራል አንጻር የማይቃረን መሆኑን የማረጋገጥና የመመዝገብ ነው፡፡
ወንጀልን የመከላከል የሁሉም ግለሰብና ተቋም ድርሻ ቢሆንም በዋናነት ከላይ የጠቀስናቸው ተቋማት ሃላፊነት ሆኖ እያለ በህግ በግልጽ ይህን ወንጀል እንዲከላከል ግዴታ ባልተጣለበትና በካርታ አጠቃቀም መብት ላይ ገደብ የማስቀመጥ ስልጣን ባልተሰጠበት ሁኔታ አራጣን ለመከላከል ነው በሚል የዜጎችን በንብረት የመጠቀም ሰብአዊ መብት የሚገድብ የህግ መሰረት የሌለው ማሳሰቢያና ከልካይ አሰራር ማስቀመጡ አግባብ አይደለም፡፡
ውድ የፌስ ቡክ ገጻችን ተከታታዮች ከማብራሪያው ጥሩ ግንዛቤ እንደጨበጣችሁ እየተማመንን በቀጣይ በዚሁ የስራ ክፍል ጥናት የተደረገባቸው ጉዳዮች ላይ የቀረቡ ሀተታዎችን ይዘን የምንቀርብ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ቸር ቆዩን!
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Alemwaza Lawyer)
Exit Exam ውጤት #በትንሽ ነጥብ ልዩነት ያልመጣላችሁ ውድ የህግ ቤተሰቦች ውጤት በወጣ በ15 ቀን ውስጥ remark (እንደገና ይታረምልኝ) ጥያቄ በህግ ት/ቤታችሁ በኩል በፅሁፍ በማመልከት መጠየቅ ትችላላችሁ። ለበለጠ መረጃ የህግ ት/ቤታችሁን ሄድ ፤ ዲን ወይም ሀላፊ በመጠየቅ እንደገና ለማሳረም መስፈርቱን የምታሟሉ ከሆነ ብቻ ሂደቱን ጠብቃችሁ እንድታመለክቱ እናበረታታችኋለን።
የመረጃው ምንጭ @lawsocieties #አለ #ALE
We go together‼️
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
የመረጃው ምንጭ @lawsocieties #አለ #ALE
We go together‼️
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties