አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
Forwarded from Yoseph Mesele
Selam bro esit sile special mitigating and special aggravating circumstances yemyawera note kalehe asichukay nw ke yikrta gar
Forwarded from Deleted Account
ሰላም ሰላም.. የወንጀልም የፍታብሔርም የስነስርዓት ህግ ማብራሪያ ካለህ እስቲ ላክልኝ...
ረቂቅ የንግድ ሕግ ላይ ግብዓት የማሰባሰብ ውይይት ከባለድርሻ አካለት ጋር ተካሄደ
***

ታህሳስ 23/ 2013 ዓ.ም ለኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተመራው ረቂቅ የንግድ ሕግ ላይ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች እና የተለያዩ የባለድርሻ አካለት በተገኙበት ግብዓት የማሰባሰብ ውይይት ተካሄዷል።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዶ/ር ጌዲዬን ጢሞቲወስ በውይይት መድረኩ ባደረጉት ንግግር ረቂቅ የንግድ ሕጉን ለማዘጋጀት የአገራችን የሕግ ባለሙያዎች እና ሙህራን ጊዜያቸውንና ጉልበታቸውን አፍስሰው ከብዙ ጥረት በኃላ የተዘጋጀ መድብል መሆኑን ጠቁመው በስራው ሂደት ከፍተኛ ሚና ለነበራቸው ባለሙያዎችና ተቋማትን ምስጋና አቅርበዋል።

ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ አክለውም ረቂቅ የንግድ ሕጉ ዘመናዊ የሆነ የንግድ ስራ እንቅስቃሴን ቀልጣፋ እንዲሆን ለማድረግ እና አነስተኛ እንዲሁም ከፍተኛ ሀብት የሚያንቀሳቅሱ የሀገር ውስጥ ብሎም የውጭ ባለሀብቶች ምቹ የሆነ የንግድ ስራ እንቅስቃሴ የሚደረግበትን መደላድል በማመቻቸት ንግድ እና ኢንቨስትመንትን ማሰደግም የመንግስት አላማ መሆኑን ተናግረዋል።

ዶ/ር ጌዱዬን አያይዘውም አንድን ሀገር ከድህነት ማውጣት እና ሀብት መፍጠር የሚቻለው በምኞት፡ በንግግር ሳይሆን በስራ፣ ምርትና አገልግሎትን በመሸጥ፣ በንግድ ስራ በመሳተፍ ሲሆን ዜጎች በንግድ ስራ እንዲሳተፉ መንግስት የተለያዩ የሕግ ማሻሻያዎችን እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።

በረቂቅ ሕጉ የግል ድርጅቶች አመሰራረትና አደረጃጀት አስመልክቶ ዘመናዊ ፣ ቀልጣፋ እና ቀላል ያሉ ሕግ ድንጋጌዎችን እንዲኖሩ፣ አነስተኛ አክስዮን ድርሻ ያላቸውን ባለአክሲዮኖች በሚሳተፉበት ድርጅትና ማህበር መብታቸው እና ጥቅማቸው የሚከበርበት ሥርዓት እና ከኪሳራ እንዲሁም ከኪስራ ሂደት ጋር በተያያዘ ሥርዓቱን ቀልጣፉ፣ ወጪ ቆጣቢ በማድረግ መብት፣ ጥቅምና ፍላጎትን ለማስጠበቅ የሚረዱ ድንጋጌዎች የተካተቱ መሆኑን እና ረቂቅ ሕጉ ከ50- 60 ዓመታት እንዲያገለግል ጥራት ያለው ተጨባጭ የሆነ ውጤትና ለውጥ የሚያመጣ እንዲሆን አስተዋጽኦ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

በመድረኩ ረቂቅ የንግድ ሕጉን በማዘጋጀት ከፍተኛ ሚና ያላቸው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የሕግ ጥናት፣ ማርቀቅና ማጠቃለል ዳይሬክተር ጀኔራል አቶ በላይሁን ይርጋ እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህራን የሆኑት ዶ/ር ስዩም ዩሐንስ እና ዶ/ር ታደሰ ሌጮ ከ1952 ዓ.ት ጀምሮ ያገለገለውን የንግድ ሕግ ድንጋጌ ክፍተቶች፣ የአዲሱን ሕግ መሰረታዊ እሳቤዎች እና ከኪስራ ንግድ ጋር በተያያዘ በሕጉ ውስጥ የተጠቀሱ ድንጋጌዎችን መሰረት በማድረግ አጠቃላይ ገለፃ አድርገዋል።

በመጨረሻም የውይይት መድረኩ ተሳታፊዎች በረቂቅ የንግድ ሕጉንለማዳበር በጥንካሬ እንዲሁም ሊሻሻሉ ይገባቸዋል ያለቸውን ሀሳቦች እና ጥያቄዎችን በማንሳት ዉይይት በማድረግ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
Forwarded from Kira Abigaro
ዓይነ ስውሩ የሕግ ተመራቂ ስለምን ራሱን በእሳት አቃጠለ?
***


የዛሬ ሳምንት አርብ ታኅሳስ 16/2013 ዓ.ም አንድ ዓይነ ሥውር የሕግ ተማሪ ራሱን በእሳት አቃጥሎ በደረሰበት ከባድ ጉዳት ህክምና ላይ ሳለ ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል።

አብርሃም ዱሬሳ ከዲላ ዩኒቨርሲቲ በሕግ ትምህርት ቤት የመጀመሪያ ዲግሪውን እንዳገኘ እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት የመውጫ ፈተና በመውሰድ ላይ እንደነበር ጓደኛው ጣሰው ሃብታሙ ለቢቢሲ ተናግሯል።

ፈተናው ባለፈው ዓመት በ2012 ዓ.ም ይሰጥ የነበረ ቢሆንም በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት ምክንያት በመራዘሙ ለረጅም ጊዜ ለፈተናው ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን ያስታውሳል።

ከአብርሃም ጋር በአንድ ግቢ ውስጥ ተከራይተው መኖር ከጀመሩ አምስት ዓመት እንደሆናቸው የሚያስታውሰው ጣሰው፣ ሲዘጋጅበት የነበረውን የመውጫ ፈተና ማክሰኞ ዕለት መውሰድ መጀመሩን ይናገራል።

የመውጫ ፈተናውን ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ፣ ረቡዕ እና ሐሙስ በሰላም ተፈትኖ እንደነበር የሚናገረው ጣሰው ደስተኛም እንደነበር ለቢቢሲ ያስረዳል።

የመጨረሻው የፈተና ዕለት፣ ማለትም አርብ፣ ረፍዶበት ስለነበር የመፈተኛ ኮዱን [የመለያ ቁጥሩን] ረስቶ በችኮላ ፈተናው ወደ ሚሰጥበት ወደ ስድስት ኪሎ ግቢ መሄዱን ያስታውሳል።
ፈተናው የሚሰጠው ስድስት ኪሎ ኤፍ ቢ ተብሎ በሚታወቀው ካምፓስ ስለነበር ወደ ውስጥ ዘልቆ መፈተኛ ኮዱን መርሳቱን እና ይፈትኑት እንደሆነ ቢጠይቅም፣ "ያለእርሱ አይሆንም፣ ሄደህ አምጣ" በመባሉ ወደ ቤቱ መመለሱን ጓደኛው ጣሰው ያስረዳል።

ካለመፈተኛ ኮዱ መግባት ስለማይችል ወደ ቤቱ ሽሮ ሜዳ ተመልሶ፣ ከትራንስፖርት ከወረደ በኋላ ወደ ቤቱ የሚያቀናውን የእግር መንገድን አቋርጦ፣ የመፈተኛ ኮዱን በመያዝ ስድስት ኪሎ ዩኒቨርስቲ ሲደርስ ፈተናው መሰጠት ከጀመረ የተወሰኑ ደቂቃዎች ማለፉን ጣሰው ለቢቢሲ ተናግሯል።

"ፈተናው አላለቀም ተማሪዎች አልወጡም ቢያንስ ከ20 ደቂቃ በላይ ይቀር ነበር" ብሎኛል ሲል የሟች አብርሃም የቅርብ ወዳጅ ጣሰው ለቢቢሲ የነበረውን ሁኔቴ አስረድቷል።

የፈተና ተቆጣጣሪዎችን ለማሳመን እና ልባቸውን ለማራራት ያልፈነቀለው ድንጋይ አልነበረም የሚለው ጣሰው፤ ነገር ግን ምንም ፍሬ እንዳላፈራለት ይናገራል።

"መግባት እንደማይችል ሲነግረው ስላረፈደበት ምክንያት ሊያስረዳ ቢሞክርም፤ "በቀረችው 20 ደቂቃ አብቃቅቼ እሰራለሁ" እያለ ዓይነ ስውር መሆኑን ታሳቢ አድርገው እንዲተባበሩት ቢለምንም፣ ቢያለቅስም፣ ፈተናውን እንዲወስድ ግን አልተፈቀደለትም።"

የሟች አብርሃም ጓደኛ ጣሰው፣ ፈተናውን መፈተን ባለመቻሉ ሲያለቅስ፣ ሲበሳጭ መዋሉን ያስታውሳል።

ጓደኞቹ ሊያጽናኑት ቢሞክርም "በቃ የእድሌ መጨረሻ ነው፣ ዓይነ ስውር ካልተማረ ውጤታማ አይሆንም" እያለ ያለቅስ እነደነበር ይናገራል።

ምሽት ላይ ወደ ቤቱ ሲገባ ወዳጆቹ የመሰላቸው እረፍት ሊያደርግ ቢሆንም፣ እርሱ ግን ቤቱን ዘግቶ፣ በራሱ ላይ ጋዝ አርከፍክፎ፣ በዙሪያዎቹ ተቀጣጣይ ነገር በማኖር ራሱ ላይ እሳት መለኮሱን ጣሰው ገልጿል።

ግቢ ውስጥ ያሉ ሰዎች ተረባርበው የቤቱን በር በመገንጠል እሳቱን አጥፍተው፣ ወደ የካቲት 12 ሆስፒታል ተወስዶ ሕክምና ቢያገኝም ቃጠሎው ከፍተኛ ስለነበር ቅዳሜ ማለዳ 3፡00 ላይ ህይወቱ አልፋለች።

የአብርሃም ቤተሰብ

አብርሃም ዱሬሳ ባለትዳር ሲሆን ባለቤቱ ነፍሰጡር በመሆኗ መስከረም ወር ላይ ለመውለድ ትግራይ ወደ ሚገኙት ቤተሰቦቿ መሄዷን ጓደኛው ጣሰው ለቢቢሲ ተናግሯል።

አብርሃም ብቻውን ለመኖር የተገደደው በተፈጠረው ችግር ምክንያት በረራ ተቋርጦ ስለነበር ባለቤቱ ልጃቸውን ክርስትና አስነስታ መምጣት ስላልቻለች በመዘግየቷ ነበር።

"ለብቻው የሆነው ለዚህ ነው እንጂ ከሚስቱ ጋር ነበር የሚኖረው" የሚለው ጣሰው በጓደኛው ሞት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ይገልጻል።

በየካቲት 12 ሆስፒታል አብረውት የነበሩት አቶ አሸብር ገብረ ሕይወትም ቅዳሜ ዕለት ሆስፒታል ሲደርሱ አብርሃም ነፍሱ እንደነበረችና ሙሉ በሙሉ በእሳት ተቃጥሎ ማየታቸውን ይናገራሉ።

በኢትዮጵያ ዓይነ ስውራን ማኅበር ፕሬዚደንት አቶ ወሰን አለሙ፣ በማኅበሩ ሦስት ዓመታትን አንዳገለገሉ ገልፀው፤ ከዚህ ቀደም በድሬደዋ ከተማ ከኮቪድ-19 የጥንቃቄ እርምጃዎች የተሳሳተ ግንዛቤ ጋር በተያያዘ አንድ ዓይነ ስውር በተመሳሳይ ሁኔታ ራሱን አቃጥሎ መሞቱን ያስታውሳሉ።

አቶ ወሰን፣ "በአብርሃም ዱሬሳ አርፍዶ በመምጣቱ ወደ ፈተና ክፍል መግባት አትችልም መባሉ ሕግን ካለማወቅ የመጣ ነው" ይላሉ።

"የዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች ኮንቬንሽን ተመጣጣኝ ሁኔታን ማመቻቸት ይላል" በማለትም ይህ ማለት የሰዓት፣ የቦታ ማስተካከያ ማድረግ ሊሆን እንደሚችል ያብራራሉ።

አብርሃም ቀደም ባሉት ሦስት የፈተና ቀናት በሰዓቱ ተገኝቶ መፈተኑን ከግንዛቤ በማስገባት፣ ያለ ኮድ ማስተናገድንም ሊያካትት እንደሚችል ያስረዳሉ።

"ይህ በግልጽ ስህተት ነው" የሚሉት ፕሬዝዳንቱ "ፈተናውን የሚያከናውነው አካል እንዲህ አይነት ሥርዓቶችን መዘርጋት ነበረበት" ብለዋል።

የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ፌደሬሽን ትናንት ባወጣው መግለጫ ላይ በተማሪ አብርሃም ዱሬሳ ላይ የተፈጸመዉ ክልከላ "ሰብአዊነት የጎደለዉ በመሆኑ መንግሥት ክትትል አድርጎ እርምጃ እንዲወስድ" ሲል ጠይቋል።

ቢቢሲ ስለጉዳዩ ተጨማሪ መረጃን ለማግኘት ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ክፍል ቢደውልም ጉዳዩ እነርሱን እንደማይመለከት ገልፀዋል።

በተጨማሪም ይመለከተዋል የተባለው የፈተናዎች ኤጀንሲም ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነም።

# BBC Amharic
የሰ/መ/ቁ 22891 - በጋብቻ ወቅት በአንደኛው ተጋቢ ምክንያት የተፈጠረ ዕዳ ለጋራ ጥቅም መዋሉ በተረጋገጠ ጊዜ የዕዳው ወደ የጋራ ንብረት ወይም ወደ ሌላኛው ተጋቢ የግል ንብረት በመሄድ ሊከፈል የሚችለው በፍርድ አፈፃፀም ላይ ስለመሆኑና ከዚህ ጋር በተያያዘ በሌላኛው ተጋቢ ላይ ዕዳውን መሠረት በማድረግ ክስ ሊመሰረትበትም ሆነ ፍርድ ሊሰጥበት የማይገባ ስለመሆኑ በጋብቻ ወቅት ለጋራ ጥቅም የዋለ እዳ ከግል ወይም ከጋራ ንብረት ሊከፈል የሚችልበት ሁኔታ እና ክስ ሊመሰረት የማይቻልበት አግባብ
http://negari.abyssinialaw.com/judgments?id=1148
ጥብቅና የተከበረ ሙያ ነው። የዛሬ ችሎት ውሎዬና ትዝብቴ:-

ጠበቃ - ውሉ ህገወጥ ነው

ዳኛ -ህገወጥነቱን ያስረዱ

ጠበቃ- ሁሉም ነገር ህገወጥ ነው

ዳኛ -ለምሳሌ

ጠበቃ - ከመጀመሪያው ጀምሮ እስከ መጨረሻው
ህገወጥ ነው።
ዳኛ - እስቲ አንዱን እንኳ ይጥቀሱ ? ክቡር ጠበቃ
ውሉ የህግ ጉድለት ነው ያለበት ወይስ ዋጋ
አልባ ውል ነው የሚሉት ?

ጠበቃ - ሁለቱም ። በህገመንግስቱ መሰረት
ህገፕወጥ ነው

(ችሎት ውስጥ ቁጭ ብለን እስክንጠራ የምንጠባበቅ ጠበቆች አጉረመረምን፣ ተንሾካሸክን)

ዳኛ - ፀጥታ አሉና ይቀጥሉ ክቡር ጠበቃ አሉ

ጠበቃ- ያው ቀደም ሲል እንዳልኩት ህገወጥ ነው
ውል ክፍል አልተፈረመም
ዳኛ - ውል ክፍል ባይፈረምስ? ለመሆኑ ምንድን
ነው ውል ክፍል ማለት ?

ጠበቃ - እኛ የምንለው ውሉ ህገወጥ ነው ብለን
ነው የምንፋለመው ?

ዳኛ - ክርክራችሁ መፋለም ነው ወይስ ውል
ይፍረስልኝ ነው ?
ጠበቃ - ሁለቱንም ። እንፋለማለንም ውልም
ይፍረስልን
ዳኛ - ክቡር ጠበቃ የይዞታው ባለቤት እኛ ነን ነው
የምትሉት ወይስ ውሉ ህገ ወጥ ነው
የሚሉት ?
ጠበቃ - (ከጀርባቸው ቁጭ ያከው የችሎት ታዳሚ
ጠበቆች ጉርምርምታና ሹክሽክታ
ያሳቀቃቸው ይመስላል ። ) እኛ እንግዲህ
በህገ መንግስቱ መሰረት ንብረት የማፍራት
መብት አለን።

ዳኛ - ታዲያ ማን ንብረት እንዳታፈሩ ከለከላችሁ ?
(ሙድ የያዙ ይመስላሉ)

ጠበቃ - ተከሳሽ ?
ዳኛ - እንዴት?
ጠበቃ - ህገወጥ ውል ይዘው ____ ብለው ዝም
አሉ።
ዳኛ - ጨረሱ ?

ጠበቃ - አዎ ጨርሻለሁ ክቡር ፍ/ቤት አሉ ። ወደ
ኃላ እኛን ዞር ብለው እየተመለከቱ

ዳኛ - ተከሳሽ ይቀጥሉ

የተከሳሽ ጠበቃ - ገልበው ገልበው ልክ አስገቡልኝ።

NB - *** ለካ
ሁሉም ሰው ጠበቃ መሆን ይችላል ።
By: Birhanu Assefa
ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት
@LawsocietiesBot
Forwarded from Abrham Tadesse
With regard to Abrhama Deressa's suicide case, What kind of code is that ? As far as I know it was only 4digit code and also it was posted on each exam room no need to go back to home even there was nothing given to the examinee in hard copy code so what kind of code was that???
I was one of the examinee there
Forwarded from Deleted Account
በዐ/ሕግ ሙያ 13 ዓመት አገልግያለው በታናሽ ወንድማችን የሕግ ባለሙያ አብርሃም ዱሬሳ ምናልባትም ከኔ በተሻለ የለበስኩትን ጥቁር በቀይ ጋወን ተረክቦኝ ፍትሕ ሊያስከብር የሚችለውን ጀግናችንን በደረሰበት አሰቃቂ በደል አተነዋል...እጅግ..ያንገበግበኛል...ይህ አልበቃ ብሎ በሱ ዙሪያ የተሰ ምላሾችም እጅግ ደካማ መሆናቸው ደግሞ ይበልጥ ያስቆጫል...ግን ጥቁር በቀይ ጋዎን ለብሼ በምከራከርበት ችሎት በቆምኩበት ለጀግናው ወንድማችን የሕግ ባለሙያ አብርሃም ዱሬሳ ልዩ ክብር አለኝ......"ፍትሕ ለጀግናው ወንድማችን አብርሃም ዱሬሳ"......ዐ/ሕግ
አእምሮ አልባ ዳኛ

በክፉ ህሊና እድልህን ዘግቶ በጉዳት ያጠቃህ፣
ታታሪውን ወጣት የነገን ተስፈኛ ለህልፈት ያበቃህ፤
ማን ይሆን ያ ክፉ ርህራሄ ያጣ?
ለምን ፈቀድክለት ደንብን ተከልሎ በጉዳተኛ ላይ ቂሙን እንዲወጣ?
እንዴት ዘነጋሃው አብራሃም ወንድሜ ግብግብ መሆኑን የኔና ያንተ እጣ?
ልብህ እያወቀው በምቀኞች መንደር በክፎዎች አንባ ልንኖር ተወልደን፣
ኮረኮንቹን መንገድ የጉዞን ጋሬጣ እሾሁን ተራምደን፣
የህብረተሰብ ሸጋታ አስተሳሰብ የሚቆልለውን የመከራ ቋጥኝ በጀግንነ አልፈን፣
በየህይወት ዘርፉ በትምህርት በስራ የገፉንን ሁሉ በወኔ አሸንፈን፤
ለድል የምንበቃ የእድሜልክ ታጋዮች መሆናችንን ልብህ እያመነው፣
አብራሃም ወንድሜ በክፉዎች ወጥመድ በእኩያኑ ሴራ መውደቅህ ለምነው?
ዳገት ቁልቁለቱን ያን ሁሉ መከራ አልፈኸው በብርታት፣
በአንዲት እርጉም አፍታ በከፋ ሰው ድርጊት በድንገት መረታት?

እስቲ ይሁን በቃ፣
በእውቀት አቅምህ ሳይሰንፍ አእምሮህ ጎልብቶ ሙሉ ሆኖ ልብህ፣
ማየት ብቃት ሆኖ ህሊና አልባ ዳኛ ሞት አስፈረደብህ።
ግን አይዞህ አልሞትክም ቃል ገብተንልሃል ሞትክን ላለመርሳት፣
በልባችን ነዷል ያቃጠለህ እሳት።

አይን አእምሮ በሚመስላቸው የእውቀትና ህሊና ድሆች ፍርደገምድል ፍርድ ራሱን ላጠፋው አይነስውር ወንድሜ አብራሃም ዱሬሳ የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን ለመግለፅ ብዬ የፃፍኩት።

የህግ ባለሙያ እና የቀድሞው የፍሪካ እንዲሁም የኢትዮጵያ የአይነ ስውራን ፌደሬሽን ፕሬዘዳንት #አቶ ካሳሁን ይበልጣል።
ፍትህ የየሚመጣው በሁላችን ተሳትፎ ነው።
Ethical and corruption free society that upholds integrity and accountability
Contact Us via
@Transparency_Ethiopia_Bot
and
ethiopiatransparency@gmail.com
ከመድሎ የፀዳች አገርን እንፍጠር‼️‼️
ኢትዮጵያ ለ50 ዓመታት የተጠቀመችበትን የንግድ ሕግ ልትቀይር ነው፡፡
ባሕር ዳር፡ ታኅሣሥ 25/2013 ዓ.ም (አብመድ) ኢትዮጵያ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ስትጠቀምበት የነበረውን የንግድ ሕግ ከዘመነ ቴክኖሎጂ ጋር የተናበበና ነባራዊ ሁኔታዎችን ባገናዘበ አዲስ ሕግ ልትቀይር መሆኑ ተገልጿል።
አገሪቷ ከምትጠቀምባቸው መድኃኒቶች ውስጥ 80 ከመቶ የሚሆነው በውጭ ምንዛሪ ተገዝቶ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባ መሆኑም ተጠቁሟል።
የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ድኤታ ምስጋኑ አረጋ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት፤ ኢትዮጵያ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ስትጠቀምበት የነበረው የንግድ ሕግ ከዘመነ ቴክኖሎጂ ጋር የተናበበና ነባራዊ ሁኔታዎችን ባገናዘበ መልኩ በአዲስ ሕግ ልትተካ ነው።
አገሪቷ እያካሄደች ያለው የምጣኔ ሀብት ማሻሻያ መርህ በዋናነት በማክሮ ኢኮኖሚ፣ መዋቅራዊ እና የዘርፍ ማሻሻያ ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑን ጠቁመው ፣ በዚህም በአሁኑ ወቅት ሁለንተናዊ ለውጦችን ለማምጣት ከመቼውም በላይ እየተንቀሳቀሰች መሆኑን አብራርተዋል።
እንደ ሚኒስትር ድኤታው ገለፃ፤ እየተደረጉ ካሉ ማሻሻያዎች መካከል 50 ዓመታትን በሥራ ላይ የነበረው የንግድ ሕግ ዘመኑ የደረሰበትን የዕድገት ደረጃ ባገናዘበ መልኩ የማሻሻል እና ሕግ ሆኖ የማውጣት ሂደቱ ከጫፍ መድረሱን አብራርተዋል።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
Forwarded from Cozet
Selam Ale...pls share to me if u have cassation bench decisions regarding legality n sufficiency of modes of civil case summons through e-mail, telegram, fax, tv or in any electronic media
New vacancy
Legal Officer
Berhan Insurance S.C

Addis Ababa (+1 other)

Apply


Job Requirement • Educational Qualification: LLB Degree from a recognized University or College • Experience: Minimum 2 years of relevant work experience Place of work: Addis Ababa How to Apply NB: Only short listed candidates will be communicated. Interested and qualified applicants may submit their application letter, curriculum vitae and other credentials in person or through the following addresses within 7 (seven) working days from the date of this announcement. Address: Berhan Insurance S.C. at Beklo Bet Yeshitam Building 4th floor, around Global Hotel near Garad Mall. P.O.Box 9266, Addis Ababa. Email: hr@berhaninsurance.com

Join..........

❤️Via Telegram channel❤️ https://t.me/lawsocieties
የሕግ የበላይነት እንዲከበር ዜጎች ለሕግ ተገዥ መሆን እንዳለባቸው ተገለጸ
__________________

የሕግ የበላይነትና የሕግ ተገዥነት በሚል ርዕስ እና ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን በሚመለከት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የአራዳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለክፍለ ከተማው የተለያዩ የህብረተስብ አባላት የንቃተ ህግ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

የፌዴራል ዐቃቤ ሕግ አቶ ሹመት ጌትነት ስልጠናውን በሰጡበት ወቅት እንደተናገሩት ሕግ የሰው ልጆችን መብትና ግዴታዎች ዘርዝሮ የሚያቀርብ ሁሉንም ዜጎች ያለ ልዩነት የሚመራና የሚዳኝ እንደሆነ እና ሕጎች ሲወጡ ለረዥም ጊዜ ተብለው ቢሆንም ከህብረተሰቡ የኑሮ ሁኔታ ለውጦች ጋር ተያይዞ ሊሻሻሉ እንደሚችሉ ገልጸው የፍትሀ-ብሄርና ወንጀል ህጎችን በዝርዝር ለሰልጣኞቹ አብራርተዋል፡፡

ዐቃቤ ሕጉ በገለጻቸው ሕጎች አለም አቀፍና ብሄራዊ በሚል ተፈጻሚነት እንዳላቸው እና ማንም ሰው ከህግ በታችና በህግ ፊት እኩል በመሆኑ የተቀመጡ የህግ ስርዓቶችን ለማስፈን ስልጣን በመገደብና የስልጣን ክፍፍል እንዲኖር በማድረግ የህግ የበላይነት እንደሚረጋገጥ ገልጸዋል፡፡

የሕግ ተገዥነት የሚፈጸመው በተግባራችን ሕጉ የሚፈቅደውን ስናደርግ፣ ሕግ አክብረን መብታችን ማስከበር ስንችል የሌሎችን መብት ሳንገፋ ሕግ አስከባሪዎችን ማክበር ስንችል ነው ያሉት ዐቃቤ ሕጉ የሰዎች ተግባር ከሕጉ ጋር አለመገናኘትና አለመፈጸም የሕግ ተገዥ አለመሆን የሚያስከትል ስለሆነ መብትና ግዴታዎችን የሚያውቅ ዜጋ ለመፍጠር ስልጠናው አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡

ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡት ዐቃቤ ህግ አቶ ሳሙኤል ገዳሙ በአንድ ሀገር ላይ የዲሞክራሲ መገለጫ የሚሆነው ሰብዓዊ መብቶች ሲከበሩ በመሆኑ ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ህገ-መንግስቱ እንዲቆም ያደረጉ መሰረታዊ መብቶች ናቸው ብለዋል፡፡

አቶ ሳሙኤል አክለውም ሰብዓዊ መብቶች ሰዎች ሰው በመሆናቸው ያለ ልዩነት የሚሰጣቸው መብቶች መሆናቸውን እና ዲሞክራያዊ መብቶች ደግሞ ህዝቦች ያላቸውን ተሳትፎ የሚያሳዩበት እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡

የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው በሀገራችን ያሉ ህጎች መልካም ቢሆኑም ህብረተሰቡ ህጉን አውቆ ተጠያቂ እዲሆን የህግ አካላት ተቀራርበው መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
Jan 03, 2021
Manager, Legal Division
Zemen Insurance SC Addis Ababa, Ethiopia
FULL_TIME Insurance Jobs in Ethiopia Legal Jobs in Ethiopia
Job Description
Job Requirement
Education Qualifications: LLB in Law
Work Experience: 8.5 years of relevant work Experience
Place of work: Addis Ababa

How to Apply
Dead line for Application: 6 working days from the date of this Vacancy Announcement

Place of application: Zemen Insurance Share Company Bole Road, Alem Building second Floor.

Interested Applicants should apply in person, post office and email Address along with non-returnable updated CV and copies of relevant credentials from the date of this vacancy announcement until January 9/2021. Post office

Address: Zemen Insurance S.C.

PO.Box 23029 Addis Ababa, Ethiopia