አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የተምታታው የ‹ዘር ማጥፋት ወንጀል› አረዳድ በኢትዮጵያ!
በ:- ጥበቡ ኃይሉ

በዚህ ጽሁፍ፤ በዋናነት ዓለም አቀፍ ሕጎችን በመጣስ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን ምንነት በአጭሩ በማየት፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የተምታታ የ‹ዘር ማጥፋት ወንጀል› አረዳድ መነሻ ምክንያት እና መፍትሔዎቹን ለመጠቆም ጥረት አደርጋለሁ፡፡

https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/1975-confusing-understanding-of-genocide-in-ethiopia
Calling all changemakers! Apply for OD Impact Challenge 2021.

This is a global competition that recognizes and supports the efforts of young changemakers working to bring positive change to their communities.

Apply now to win cash prizes and an all-expenses paid trip to the Netherlands for a one-week mini-MBA course sponsored by Vantage Migration.

Details: https://bit.ly/ODIC2021call
Deadline: December 31, 2020

#ODIC2021 #ODImpactChallenge
የተቋሙ አመራሮችና ባለሙያዎች ከፍ ያለ ስነ-ምግባር ተላብሰዉ መስራት ይኖርባቸዋል” ሲሉ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አቶ ተስፋዬ ዳባ ገለፁ፡፡
---------------------------------------------------------

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አቶ ተስፋዬ ዳባ ይህን ያሉት ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ከፍትህ ለሁሉም ፕሪዝን ፎሎ ሽፕ ኢትዮጵያ ጋር በጋራ ባዘጋጁትና የዐቃቤያነ ህግ ስብዕና ግንባታ ላይ ትኩረቱን አድርጎ ለመካከለኛ አመራሮች በተዘጋጀዉ ስልጠና ላይ ተገኝተዉ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ነዉ፡፡

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ በተያዘዉ በጀት አመት የለዉጥ አጀንዳዎችን በመቅረፅ ጉልህ የሆነ ተቋማዊ ለዉጥን ለመፍጠር አየተጋ እንደሚገኝ የገለፁት ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ህጉ ከእነዚህ የለዉጥ አጀንዳዎች ዉስጥ አንዱ የዓቃብያነ ህግ የሙያ ማጎልበቻ እኒሼቲቭ መሆኑን በማስታወስ ለዚህም የተቋሙ ባለሙያዎችና አመራሮችን ሞያዊ ብቃት ማጎልበት ዋነኛዉ ተግባር መሆኑን አንስተዋል፡፡

ተቋሙ በእዉነትም ለህግ፣ ለፍትህና ለርትዕ የቆመ የህዝብ አገልጋይ ተቋም እንዲሆን የተቋሙ ግንባታ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዉ ተገቢዉ የሞያ ስነ ምግባር ያላቸዉ ባለሙያዎች ኑረዉት ተዐማኒነት፣ ቅልጥፍናና ዉጤታማትን የሚያሳድጉ ስርዐቶችን ዘርግቶ ሀላፊነቱን መወጣት ይችል ዘንድ የተቋሙ ባለሙያዎችና አመራሮች ከፍ ያለ የዐቃቢያነ ህግ ስብዕናና ስነ-ምግባር ተላብሰዉ መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡

የስልጠናዉ ዋና አላማ የዐቃብያነ ህግን ስብእና ለመገንባት የሚሰራ ስራ አካል ሆኖ ስብእናና ስነ ምግባርን ለማጎልበት የሚያስችል ሲሆን ከጉዳዩ ጋር በቀጥታ የሚገናኙ አለም አቀፍና አህጉር አቀፍ ተሞክሮዎች የሚዳሰስበት መሆኑን የገለፁት አቶ ተስፋዬ ሰልጣኞች የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ አደራ በማለት ለስልጠናዉ መሳካት ድጋፍ ላደረገዉ ፍትህ ለሁሉም ፕሪዝን ፌሎ ሺፕ ኢትዮጵያ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

የፍትህ ለሁሉም ፕሪዝን ፌሎ ሽፕ ኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ፓስትር ዳንኤል ገብረስላሴ በበኩላቸዉ ፍትህ ለሁሉም ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ጋር በአቅም ግንባታ ስራዎችና በሌሎች ተግባራት ላለፉት በርካታ አመታት አብሮ መስራቱን ገልፀዉ የህግ የበላይነት ልእልና እንዲኖር በሚያስችሉ ቀጣይ ተግባራትም ድርጅታቸዉ ከተቋሙ ጋር በጋራ እንደሚሰራ በመግለፅ ለስልጠናዉ ተካፋዮች እንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡

ስልጠናዉ ለሁለት ቀናት የዐቃቤ ህግ ስብእና ምንነት፣ ስብእናዉ የተሟላ ዐቃቤ ህግ ባህሪ፣ የዐቃቤ ህግ ስነ ምግባር፣ የዐቃቤ ህግ ነፃነትና ገለልተኝነት፣ በፍትህ ስርዓት ዉስጥ የዐቃቤ ህግ ሚና እና ሰብዐዊ መብትን በማስከበር ሂደት ዉስጥ የዐቃቤ ህግ ሚና በሚሉ ነጥቦች ላይ በአሰልጣኞች ማብራራያዎች ቀርበዉ ዉይይት የሚካሄድበት ይሆናል፡፡
ቼክ ምንድን ነዉ? በቂ ስንቅ የሌለዉ ቼክ መፃፍ በወንጀል ያስጠይቃልን?
------------------------------------

በ1952 ዓ.ም የወጣው የሀገራችን የንግድ ህግ በርከት ላሉ የንግድ ሰነዶች እውቅና የሰጠ ቢሆንም በተግባር ላይ ሰፋ ባለ መልኩ አገልግሎት ላይ እየዋለ ያለው ቼክ የሚባለው የንግድ ሰነድ ነው፡፡ ቼክ ወስብስብ በሆነ የንግድ ስርአት ውሰጥ በጥሬ ገንዘብ በመገበያየት ምክንያት የሚከሰቱ ወንጀሎችንና የንብረት ጉዳቶችን በማስቀረት የተቀላጠፈ የንግድ ስርአት እንዲኖር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል፡፡

የቼክን ምንነትና ሊይዝ ስለሚገባው ዝርዝር ጉዳይ በሚመለከት የንግድ ህጋችን አንቀፅ 827 ላይ የተገለፀ ሲሆን ከዚህ አንቀፅ ጠቅላላ ይዘት ለመረዳት እንደሚቻለው ቼክ ማለት የከፋዩን ስም፣ የሚከፈልበትን ቦታ፣ቼኩ የወጣበት ቀንና ቦታ እንዲሁም የአውጪውን ፊርማ የያዘ የተገፀው ባንክ ወይም ህግ የባንክን ስራ እንዲያከናውን ስልጣን የተሰጠው መስሪያ ቤት የተወሰነ ገንዘብ ለሶስተኛ ወገን ወይም ለአምጭው ለራሱ እንዲከፍለው የሚያዝ ሐተታ የሌለበት የንግድ ሰነድ (Commercial instrument) ነው ሊባል ይችላል;; በንግድ ህግ ውስጥ አራት አይነት የቼክ አይነቶች ማለትም የስርዝ ምልክት ያለበት ቼክ (Crossed cheque)፣ ከሒሳብ ውስጥ የሚገባ ቼክ (Cheque payable in account)፣ የመንገድ ቼክ (Travellers cheque) እንዲሁም መደበኛ ቼክ የሚባሉት የቼክ አይነቶች የሚገኙ ቢሆንም የዚህ ፅሁፍ ትኩረት ግን የመጀመሪያ ሶስቱን የቼክ አይነቶች ወደጎን በመተው አራተኛው የቼክ አይነት ላይ ማለትም መደበኛ የቼክ አይነት ላይ ይሆናል፡፡

መደበኛውን የቼክ አይነት ምንነት በሚመለከት የንግድ ህጋችን አንቀጽ 827 እና በሚከተሉት አንቀጾች ላይ ተንግጎ ይገኛል፡፡ ከእነዚህ ድንጋጌዎች አጠቃላይ ይዘት ለመረዳት እንደሚቻለው መደበኛ ቼክ ማለት መጠኑ በግልፅ ተለይቶ የተጠቀሰ የገንዘብ መጠን ለአንድ ግለሰብ ወይም ሶስተኛ ወገን እንዲከፈል ለአንድ ባንክ ቤት ወይም ቼክ መከፈልን ጨምሮ በህግ የባንክ ቤት ስራን ለማከናወን ስልጣን ለተወጠዉ ተቋም ሐተታ የሌለበት ትዕዛዝ የያዘ የንግድ ሰነድ ነዉ፡፡

አንድ ቼክ ህጋዊ ነው ተብሎ ክፍያ ሊፈጸምበት የሚችለው በንግድ ህጉ አንቀጽ 827 ላይ የተገለጹትን መግለጫዎች ካሟላ ብቻ ነው;; በዚህ የህግ ድንጋጌ መሰረት አንድ ቼክ ህጋዊ ቼክ ነው እንዲባል አምስት መሰረታዊ መግለጫዎችን ሊይዝ የሚገባ ሲሆን እነዚህ መግለጫዎችም፡
-
1. የተወሰነ ገንዘብ ለመክፈል ሃተታ የሌለበት ትእዛዝ;; ይህም ሲባል በቼኩ ላይ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ወይም መሟላት ያለባቸውን ቅድመ ሁኔታዎች ሳይዘረዝር ሊከፈል የሚገባውን የገንዘብ መጠን በግልጽ ሊጻፍበት ይገባል;;
2. ከፋይ የሆነው ተቋም ስም፡፡ በንግድ ህጋችን አንቀጽ 829 መሰረት ቼክን ተቀብሎ ክፍያ ሊፈጽም የሚችለው ባንክ ቤት ወይም በህግ የባንክ ቤትን ስራ ለማከናወን ስልጣን የተሰጠው ተቋም ብቻ ነው፡፡ በመሆኑም ቼኩን ተቀብሎ በቼኩ ላይ የተገለጸውን የገንዘብ መጠን እንዲከፍል የታዘዘው ተቋም በግልጽ በቼኩ ላይ ሊኖር ይገባል;;
3. ገንዘብ የሚከፈልበት ቦታ
4. ቼኩ የወጣበት ቦታና ጊዜ
5. ቼኩን ያወጣው ሰው ፊርማ ናቸው;;

በህግ የተቀመጡትን መግለጫዎች ያላሟላ ቼክ የሚኖረው የህግ ውጤት
በመርህ ደረጃ አንድ ቼክ እንደ ህጋዊ ቼክ ተቆጥሮ ክፍያ የሚፈጸምበት ከላይ የተገለጹትን አምስት መግለጫዎች የያዘ እንደሆነ ብቻ ነው;; ነገር ግን በንግድ ህጉ አንቀጽ 828 ላይ ሁለት ልዩ ሁኔታዎች ተቀምጠዋል፡፡

በዚህ ድንጋጌ መሰረት አንድ ቼክ የሚከፈልነት ቦታ ያልገለፀ እንደሆነ በከፋዩ ስም አጠገብ የተቀመጠው ቦታ የመክፈያ ቦታ ሆኖ ይቆጠራል፡፡ ከከፋዩ ስም አጠገብ ከአንድ በላይ ቦታዎች የተገለፁ እንደሆነ በመጀመሪያ የተመለከተዉ ቦታ ቼኩ ተከፋይ ይሆናል፡፡

ነገር ግን ቼኩ ምንም አይነት ቦታ ያልገለፀ እንደሆነ የከፍዩ ዋና ስራ ማካሔጃ /ዋና መስሪያ ቤት/ የቼኩ የክፍያ ቦታ ተደርጎ ይቆጠራል፡፡
ክዚህ የህግ ግምት ውጪ የተቀሩትን ከላይ የተገለፁትን መስፈርቶችን ያላሟላ ቼክ እንደህጋዊ ቼክ የሚቆጠር ባለመሆኑ ቼክ ከፋዩ ለመክፈል አይገደድም፡፡በመሆኑም የቼክ ተከፋይ የሆነዉ ግለሰብ ቼኩ እንደ ህጋዊ ቼክ ተቆጥሮ ከፋዩ በቼኩ ላይ የተገለፀዉን የገንዘብ መጠን እንዲከፈለዉ ለማስገደድ የሚችለዉ ቼኩ በህጉ ላይ የተገለፁትን መስፈርቶች አሟልቶ የተገኘ እንደሆነ ብቻ በመሆኑ ማንኛዉም ግለሰብ አንድን ቼክ ከመቀበሉ በፊት ቼኩ ከላይ የተገለፁትን ዝርዝር መግለጫወችን የያዘ ስመሆኑ ማረጋገጥ ይኖርበተል፡፡

ከቼክ ጋር ተያይዘዉ የሚፈፀሙ ወንጀሎችና የሚያስከትሉት ቅጣት
ቼክ በርከት ያለ ጥሬ ገንዘብን ከበታ ቦታ ይዞ በመዘዋወር የሚከሰተዉን የአደጋ ተጋላጭነትና በመገበያያ ገንዘብ ላይ የሚደርሰዉን ጉዳት በማስቀረት የንግድ ስርአቱ በተቀላጠፈ መልኩ አንዲከናወን ጉልህ ሚና የሚጫወት ቢሆንም ከቼክ ጋር ተያይዘዉ የሚፈፀሙ ወንጀሎች የንግዱ ማህበረሰብ በቼክ ላይ ያለዉን እምነት በመቀነስ ቼክ ለተቀላጠፈ የንግድ ስርአት የሚያበረክተዉ ጉልህ አስተዋፅኦ ላይ ጉዳት ያደርሳል፡፡

ከቼክ ጋር በተያያዘ በዋናነት የሚፈፀመዉ የወንጀል አይነት ደረቅ ቼክ ማዉጣት ወንጀል ሲሆን ደረቅ ቼክ ወይም በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ ማዉጣት ወንጀል ማለት ቼኩ በሚወጣበት ወይም ለባንክ በሚቀርብበት ወቀት የሚያዝበት በቂ ስንቅ በሒሳብ ወስጥ ሳይኖር ቼክ ማዉጣት ወንጀል እንደሆና ይህ የወንጀል ድርጊት ተፈፅሞ ሲገኝም እስከ አስር አመት በሚደርስ ፅኑ እስራትና በገንዘብ መቀጮ የሚያስቀጣ የወንጀል ድርጊት እንደሆነ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የወንጀል ህግ አንቀፅ 693 ላይ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ሌላኛዉ ከቼክ ጋር በተያያዘ የሚፈፀመዉ የወንጀል አይነት ደግሞ ሀሰተኛ ወይም ህጋዊ ያልሆነ ቼክ የማዉጣት ወንጀል ነዉ፡፡

ሀሰተኛ ቼክ ማለት ቼክን ለማተም ስልጣን ባለዉ ባንከ ቤት ታትሞ ያልተሰጠ ወይም ታትሞ ከተሰጠዉ ጋር ተመሳስሎ የተሰራ ቼክ መሳይ ሰነድ ሲሆን ማንም ሰዉ ይህንን ሀሰተኛ ቼክ የሰራ ፣ የተገለገለ ወይም ህጋዊ አስመስሎ ለሶስተኛ ወገን ያስተላለፈ አንደሆነ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የወንጀል ህግ አንቀፅ 375ና በሚከተሉት አንቀፆች እንዲሁም በተደራቢነት በወ.ህ.ቁ 692 መሰረት በማታለል ወንጀል ተጠያቂ ይሆናል፡፡ በመሆኑም ህጋዊ ቼክ ሊኖረዉ ስለማገባ አስገዳጅ መግለጫዎችና ከቼክ ጋር በተያያዘ ስለመፈሙ ወንጀሎች በአግባቡ በመገንዘብ እራሳችንን ከአደጋ እንጠብቅ የእለቱ መልእክታችን ነዉ በሌላ ፅሁፍ እስክንገናኝ ቸር እንሰንብት፡፡
https://t.me/lawsocieties
Forwarded from አለሕግ🔵AleHig
🔴none of us truly wins until we all win🔴
@lawsocieties
#ሁከት_ይወገድልኝ

Legal Consulting Limited
የአንድ ንብረት ባለይዞታ የሆነ ሰው ይዞታውን ለመንጠቅ ወይም በይዞታው ላይ ሁከት ለመፍጠር የሚፈፀምን ማንኛውንም ድርጊት እንዲቆም ወይም ንብረቱ እንዲመለስለት የሚያቀርበው የይዞታ ክስ
በፍ/ሕ/ቁ. 1149/1/ መሰረት የሁከት ይወገድልኝ ክስ መቅረብ የሚችለው አቤቱታ አቅራቢው ለክርክሩ መነሻ በሆነው ነገር በቀጥታ ወይም በጠባቂ ይዞታ
ሲኖረው ነው፡፡ እንዲሁም የይዞታ ክስ የሚቀርበው ለክርክሩ መነሻ የሆነውን ንብረት በወቅቱ ለመያዝ ምንም ዓይነት መብት በሌለው ሰው ላይ ስለመሆኑም*የድንጋጌው መንፈስ ያስረዳል፡፡

የሁከት ይወገድልኝ አቤቱታ አቅራቢ በማስረጃ
ማረጋገጥ ያለበት ንብረቱ በይዞታው ስር የነበረና የሁከት ድርጊት ፈፃሚው የኃይል ተግባር በመጠቀም ወይም በሚስጢር ንብረቱን የወሰደበት መሆኑን
ነው፡፡ ሁከት ተፈጥሯል የሚባለው ባለይዞታ የሆነው ሰው በይዞታው ስር በሚገኘው ንብረት እንዳይገለገልበት ሌላ ሰው ጣልቃ ገብቶበት መሰናክል ሲፈጥርበት ወይም ረብሻ ሲፈጥርበት ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 80241 ቅጽ 15፣ ፍ/ህ/ቁ. 1149(1)

የሁከት ይወገድልኝ ክስ ለማቅረብ ከሳሹ ማስረዳት ያለበት ባለቤትነት ወይም የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት እንዳለው ሳይሆን ክስ ያቀረበበት ንብረት ህጋዊ ባለይዞታ መሆኑ በሌላ አነጋገር ሁከት የተፈጠረበትን ነገር በእጁ አድርጎ በእውነት ሲያዝበት እንደነበር ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 38228 ቅጽ 9

ሁከት እንዲወገድ በቀረበ ክስ ተከሳሽ የሚያነሳው የባለቤትነት ክርክር እራሱን የቻለ ባለቤትነት የመፋለም ክስ /petitory action/ በሚመለከተው ላይ አቅርቦ ከሚታይ በስተቀር ሁከት ተፈጥሯል ወይስ አልተፈጠረም ተብሎ ለሚያዘው ጭብጥ ተገቢነት የለውም፡፡
ሰ/መ/ቁ. 27506 ቅጽ 6

የሁከት ይወገድልኝ ክስ ሲቀርብ በፍርድ ቤት በጭብጥነት ተይዞ መፈታት የሚገባው ጉዳይ ሁከት አለ ወይንስ የለም? የሚለው ነው፡፡ የውሉ ተገቢውን
የአጻጻፍ ሥርዓት ተከትሎ አለመደረግ ይዞታው በተጨበረበረ መንገድ ስለመያዙ ወይንም በማናቸውም ሕገወጥ ሁኔታ ስለመያዙና ሁከት እንዲወገድለት ክስ ያቀረበው ከሳሽ በይዞታው በእውነት ሊያዝበት እንደማይችል አያረጋግጥም፡፡

በዚህ ረገድ ውሉ ጉድለት አለበት ከተባለ በፍ/ብ/ሕ/ቁ/1808(2) ላይ እንደተመለከተው ውሉ ፈራሽ ነው እንዲባል የክስ ምክንያት ከሚሆን በስተቀር
ሁከት ይወገድልኝ ተብሎ በቀረበ ክስ ላይ ሊስተናገድ የሚችል አይሆንም፡፡
ሰ/መ/ቁ 36645 ቅጽ 9

Source:-Legal Consulting Limited
via Binimos
Dear Lawyers, Good Morning‼️
Forwarded from Deleted Account
አዲስ አበባ የፈተና ጣቢያ ያደረጋችሁ የሕግ መውጫ ፈተና ተንታኞች በሙሉ የመፈተኛ ቦታው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስድስት ኪሎ FBE ካምፓሥ እሸቱ ጮሌ ህንፃ መሆኑን እንገልጻለለን። በ12/04/2013 በ 9:00 ሠዓት ገለጻ ሥለሚሠጥ እንድትገኙ
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Alemwaza Lawyer)
🔴none of us truly wins until we all win🔴
@lawsocieties
አዲስ አበባ የፈተና ጣቢያ ያደረጋችሁ የሕግ መውጫ ፈተና ተንታኞች በሙሉ የመፈተኛ ቦታው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስድስት ኪሎ FBE ካምፓሥ እሸቱ ጮሌ ህንፃ መሆኑን እንገልጻለለን። በ12/04/2013 በ 9:00 ሠዓት ገለጻ ሥለሚሠጥ እንድትገኙ እናሳስባለን
መቀሌ ፈተናው ይሰጣል በአከባቢው የምትኖሩ መውሰድ ትችላላችሁ
Forwarded from Deleted Account
መቀሌ ዩንቨርሲቲ‼️

የመቀሌ ዩንቨርስቲ የህግ ተማሪወች የመውጫ ፈተናን(exit exam) በታቀደው ጊዜ ከ ታህሳስ 13-16 ቀን 2013 አ.ም ይወስዳሉ::

የአክሱም እና አዲግራት ዩንቨርስቲ ተማሪወች ለሆናችሁ:-

♦️ትግራይ አካባቢ ለምትኖሩ ተማሪወች ፈተናውን ለመውሰድ ባስቸኳይ መቀሌ ዩንቨርስቲ በመሄድ ሪፖርት እንድታደርጉ::

♦️ ከትግራይ ውጭ ለምትኖሩ ተማሪወች በምትኖሩበት ከተማ ባለው ዩንቨርስቲ: ከሌለ ባቅራቢያችሁ በሚገኘው ዩንቨርስቲ ባስቸኳይ በመሄድ ለመፈተን ሪፖርት እንድታደርጉ::

ማሳሰቢያ- ሪፖርት ለማድረግ ስትሄዱ የዩንቨርስቲ መታወቂያ እና የአካባቢው ኗሪነት መታወቂያ መያዝ ያስፈልጋል::

በመረጃ ክፍተት ምክንያት ሪፖርት ሳያደርጉ ፈተና ያለፋቸው ተማሪወች የሚቀጥለው መውጫ ፈተናን ይወስዳሉ:: አዲስ መረጃ ካለ እናሳውቃለን::
Forwarded from Deleted Account
Hiii selam new ene 5th year law temari negn kehumera Tigray neger gn beahunu seat ketornetu bemeshesh sudan negn yalehut kene ga abrew yemimaru 5th year ye law temariwochim ke ene ga ygegnalu egna ahun mn enadrg? Sidet lay yemngegnew ye University temariwoch guday mn yetebale neger ale? Lemimeleketw akal astawukachu melsu btasawukun elalehu? Amesegnalehu
Job title:- Regional Legal Manager


ethiotelecom

Nekemte

Apply on Ethio Telecom

❤️🔴Full–time

Ethio telecom is looking for qualified applicants who meet the under mentioned requirements. Hence, if you are willing to Join this fast-growing company, please apply before closing date of the vacancy. • Vacancy Detail Vacant position: Regional Legal Manager Vacancy Code: EVA-LEG-HQ-10-2020 Term of Employment: - Permanent Place of Work: - West Region- Nekemte Salary: - As per company`s salary scale • General Mission • Protect the legal interest of the company by handling legal disputes...
https://t.me/lawsocieties

Opening date: December 14, 2020 Closing date: December 23, 2020 • Application Tips • Interested applicants shall apply online through website address;
https://www.ethiotelecom.et // and other way of application is not acceptable. • Applicants must have the required educational qualification and experience. • Applicants are required to print the application confirmation page for successful registration. Any complaints regarding registration will not be entertained otherwise. • Applicants who submit false or forged documents will be disqualified at any time confirmed. • Only short-listed applicants will be contacted. • Female applicants are strongly encouraged to apply
Ethio telecom is looking for qualified applicants who meet the under mentioned requirements. Hence, if you are willing to Join this fast-growing company, please apply before closing date of the vacancy. • Vacancy Detail Vacant position: Regional Legal Manager Vacancy Code: EVA-LEG-HQ-10-2020 Term of Employment: - Permanent Place of Work: - West Region- Nekemte Salary: - As per company`s salary scale • General Mission • Protect the legal interest of the company by handling legal disputes assist the decision making process by providing accurate legal advice and manages bad debt cases in the hands of the legal units. Main duties and tasks: • Protects the interests of the company by instituting legal actions against individuals/organizations who infringed upon the company's interests and ensures that the damages to the company are adequately redressed. • Represents the company in suits instituted against it and ensures the adequacy of the defense submitted to the judiciary, • Lodges criminal accusations to the competent public authorities on crimes committed against the interest of the company. • Assists the authorities handling such criminal cases in the gathering of evidence and information available to the company and makes a follow-up on the cases until closure. • Provides legal opinion and advice on any legal related issues to the management and work units. • Conduct problem solving researches. • Studies, organizes, files and diffuses legal or jurisprudence documents and any other legal analysis documents. • Disseminates legal information to all staffs of the company through communication kit or by conducting workshops. • Participates in the development and implementation of legal and other company policy, processes and procedures. • Participates in development and improvement of KPls. • Manage overall activity of regional and zonal legal operations. Management • Responsible for professional and personal development of his/her employees. • Implement the strategy of the department in line with the strategy of the company. • Structures, Organizes and manages the section. • Comment and distribute KPIs results of the department. • Organize and chairs weekly meetings for top-down and bottom-up information and coordination, and reports to department. • Key Responsibilities Ensures: • Optimal resolution of legal disputes through alternative dispute settlement mechanisms. • The quality and consistency of arguments on litigation process; assesses the chances of success and makes recommendations to the management on the optimum settlement of the dispute; and forward possible lessons to be taken before or after the case is disposed. Does: • Work closely with administrative bodies (Kebele, Wereda, etc) in order to Collect bad debt through pre-litigation process, and gather information/evidence about debtors for further action. • Gather necessary evidence from administrative bodies in order to bring unrecoverable debts for write-off. • Appraise the performance of his direct subordinates /reports. • Delegate the mutually agreed objectives to his/her direct reportee's. • Responsible for the implementation of processes, procedures and policies with in the department. • Develop and yearly update his/her direct reporteet s job description in collaboration with HRD. • Provide support for cross functional units. • Provide all required information to department for decision making or reporting. • Protect company interest in any circumstance. Competencies: Transversal Competency: • Ability to convince • Being open-minded • Ability to develop and improve • Integrity • Ability to communicate Professional Competency: • Labor law • Contract law • Penal law • Telecom law • Legal techniques • Minimum Qualification Master’s Degree in Law (L.L.M) with at least 5 years of experience in Legal Contract or Legal Dispute Management or Legal Advisory or Regulatory Issues activities. Degree in Law (L.L.B) with at least 7 years of experience in Legal Contract or Legal Dispute Management or Legal Advisory or Regulatory Issues activities. Date of Application