አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.88K photos
25 videos
1.87K files
3.58K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
And tell me how to calculate my service?
Amin Kayyoon furtuu jireenya boruuti:
Please if you have constitutional law ppt share
https://telegram.me/TransparencyEthiopia
If you have friends/colleagues from low- and middle-income countries (LMICs) interested in global surgery - please share the following application form!

With InciSioN (International Student Surgical Network), we are hosting our third annual InciSioN Global Surgery Symposium on 1-3 May 2020 in Bogota, Colombia after successful events in Rwanda (2019) and Belgium (2018) with over 700 people attending from over 60 countries in total. Every year, we *fully fund 10 students/young doctors from LMICs* to attend our meeting, so please do share!

Link: https://forms.gle/742MNPvkCNtHPMqA9
https://telegram.me/TransparencyEthiopia
Summer Exchange Program in USA 2020 (Fully Funded)

Link: https://wp.me/pagilY-A2

Duratuin: 02 Weeks


Eligibility Criteria:

Applicants must belong to India, Pakistan or USA

Applicants must be aged between 18-22 years at the time of the program

Must have a valid passport

Must be proficient in English.

From any Education background – interest: arts, humanities, sciences, and everything in between.

You don’t necessarily have to have received perfect grades in your English or literature classes, nor will we make you quote U.S., Indian, or Pakistani authors at will.
https://telegram.me/TransparencyEthiopia
Holland Scholarships 2020 - Radboud Master Scholarship

Link: https://wp.me/pagilY-13U

Holland Scholarships are aimed at helping talented and bright foreign students pursue their studies in #Netherland.
https://telegram.me/TransparencyEthiopia
Selomon Sisay:
Please can you help me by sending The new draft of the commercial code of Ethiopia?
Attorney

📌 የስራ ልምድ: 4 years of relevant Work experience
📌 የትምህርት ደረጃ: LLB Degree in Law
http://ethiopianreporterjobs.com/nb10
የቴኳንዶ ማሰልጠኛ ሊከፍት ቀበሌ ፍቃድ ሊያወጣ ሔዶ "የብቃት ማረጋገጫ አምጣ" ሲሉት
:
እንዳለ ቢሮ ውስጥ ዘረራቸው😜
Dec 15, 2019

Attorney

 Nib International Bank

 

 Addis Ababa, Ethiopia

FullTime Banking Jobs in Ethiopia Legal Jobs in Ethiopia

Job Description

Job Requirement

Educational Qualification:LLB Degree in Law

Work Experience & Required Skills:4 years of relevant Work experience

Place of work:Head Office

How to Apply

Deadline: Ten working days from this vacancy announcement.

Interested applicants should submit their CVs and non-returnable Supporting documents in person to NIB International Bank HRM Department (Dembel City Center 5th Floor) or   Mail to:

HRM Department

P.O. Box 2439

Tel. 011-5 503288

NIB International Bank

https://telegram.me/TransparencyEthiopia
Via........Rewrting ........:
የሰው መግደል ወንጀል የፈፀመው የፖሊስ አባል ጽኑ እስራት ተፈረደበት
____________

የትራፊክ አባሎች ቁም ሲሉት እንቢ ብሏል በሚል ምክንያት በቦሌ ክፍል ከተማ ወረዳ 07 አካባቢ የሰው መግደል ወንጀል የፈጸመው የፖሊስ አባል ጽኑ እስራት ተፈረደበት፡፡

ተከሳሽ ም/ሳጅን ታዘባቸው ንጋቱ የፖሊስ አባልት መተዳደሪያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 268/2005 አንቀጽ 3/2፣ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32/1/ሀ እና 539/1/ሀ ስራ ላይ የተመለከተዉን በመተላለፍ በሌላ የክስ ጉዳያቸው በመታየት ላይ ካሉት ሶስት ተከሳሾች ጋር በመሆን ተከሳሽ የፖሊስ ሰራዊት እንደመሆ የሌለውን ሰው ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነት እያለበት ስራውንም በማስተዋል፣ በትህትና እና በታጋሽነት ማከናወን እንዲሁም ከሀይል አጠቃቀም እንጻር የተለየ እንቢተኝነት ያላሳየውን ሟች ከሕግ ተገዢ እናደርጋለን በሚል ሰውን ለመጉዳት ፍፁም ፈቃደኛ በመሆን ጨካኝነቱን፣ ነውረኝነቱን እና አደጋኛነቱን በሚያሳይ ሁኔታ የግድያ ወንጀል ፈጽሟል፡፡

ተከሳሽ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 07 ልዩ ቦታው አለማየሁ ህንጻ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ሟች ወጣት ሮቤልን ጃካሮስ አደባባይ ለመንገድ ስራ ተዘግቶ የነበረን መንገድ ሟች በሚያሽከረክረው መኪና ጥሶ አልፏል የትራፊክ አባሎች ቁም ሲሉት እንቢ ብሎ አምልጧል በሚል ምክንያት ኮ/ብል ከፍያለው ደምሴ እና ኮ/ብል አብረሀም በቀለ የተባሉት በያዙት የጦር መሳሪያ ጀርባውን ደጋግመው ሲመቱት ኮ/ብል ላቃቸው ባምላክ የተባለውን በዱላ እና በጫማ በመረጋገጥ በጭቅላቱ ላይ በደረሰበት ጉዳት ህይወቱ ያለፈ በመሆኑ ተከሳሽ በወንጀል ድርጊትና በሚሰጠው ውጤት ሙሉ ተካፋይ በመሆን በዋና ወንጅል አድራጊነት በፈጸመው ከባድ የሆነ የሰው ግድያ ወንጀል ተከሶ ፍርድ ቤት መቅርቡን የክስ መዝገቡ ያስረዳል፡፡

ዐቃቤ ሕግ ተከሳሽ በፈፀመዉ ወንጀል ተጠያቂ መሆን የሚችልበትን በፖሊስ የምርምራ መዝገብ መሰረት የሰዉ እና የሰነድ ማስረጃዎችን በመያዝ ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል::ተከሳሽ በሌለበት ፍርድ ቤቱም ግራ ቀኙን መርምሮ ተከሳሹ በተከሰሰበት ወንጀል ጥፋተኛ ተብሏል::

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ ወንጀል ችሎት ተከሳሽ ወንጀል ሪከርድ የሌለበት መሆኑን በማቅለያ በመቀበል በ20 ዓመት ጽኑ እስራት አንዲቀጣ ሲል ወስኗል::
(ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ )
አለ ዜና🛑🛑🛑🛑🛑
የአጠቃላይ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና በዚህ ዓመት የሚሰጠው 12ኛ ክፍል ላይ ብቻ ነው!

የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ እንዳስታወቀው የ10ኛ ክፍል ማጠቃለያ ብሔራዊ ፈተና እንደማይሰጥ አስቀድሞ ቢነገርም አንዳንድ የግል እና የመንግስት ትምህርት ቤቶች ለ10ኛ ክፍል ፈተና ተማሪዎችን እያዘጋጁ መሆኑን መረጃ እየደረሰው ነው፡፡

የኤጄንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ አርአያ ገ/እግዚአብሔር ለኢቲቪ እንደገለፁት ለአጠቃላይ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ዝግጅት ማድረግ እንደማይገባ እና የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች መደበኛ የክፍል ፈተና ብቻ እንደሚፈተኑ ለማስታወስ ለሁሉም ክልሎች ተቋሙ ድብዳቤ ፅፏል ብለዋል፡፡ ከዚህ በኋላ ብሄራዊ ፈተና የሚወስደው 12ኛ ክፍል ላይ መሆኑን ተማሪዎችም ወላጆችም ሆነ ትምህርት ቤቶች ሊያውቁት እንደሚገባ አቶ አርአያ ተናግረዋል።
ኢትቪ via TIKVAHETH
አሰሪዋን የገደለችው የቤት ሰራተኛ በፈፀመችው ወንጀል ጽኑ እስራት ተፈረደባት
________________
ገርጂ ኮንዶሚኒየም ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ የማይገባ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ አሰሪዋን በመግደል እና በስርቆት ወንጀል የተከሰሰችው የቤት ሰራተኛ ዐቃቤ ሕግ በመሰረተው ሁለት ክስ በጽኑ እስራት ተቀጣች፡፡

በ1ኛ ክስ ተከሳሽ መሰረት ነገሰ ወንጀል ሕግ አንቀጽ 540 ስር የተደነገገውን በመተላለፍ ከምሽቱ 4 አካባቢ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ልዩ ቦታው ገርጂ ኮንዶሚኒየም ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ከሚገኘው ሉዋም ሱቅ ውስጥ ሟች እርግብ ገ/ክርስቶስ ቤት ውስጥ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ እየሰራች በነበረችበት ወቅት ለጊዜው ያልተያዘው ግብረአበሯ በተደጋጋሚ ጊዜ ስልክ በመደወል ሟችን በተኛችበት ግደያት በማለት ሲነግራት እሷም በእለቱ ሟች ወደ ተኛችበት ክፍል በመሄድ በብርድ ልብስ አፍና የጉሮሮዋ ቧንቧ እንዲደፈን በማድረግ ህይወቷ እንዲያልፍ በማድረጓ በፈጸመችው የሰው ግድያ ወንጀል ተከሳለች፡፡

በ2ኛ ክስ ወንጀል ሕግ አንቀጽ 32(1) (ለ) እና 669 (2) (መ) በመተላለፍ ተከሳሽ በ1ኛ ክስ ላይ በተጠቀሰው ቦታ ሟችን ከገደለቻት በኋላ ያልተያዘውን ግብረአበሯ ስልክ በመደወል ጠርታ ወደ ሟች ሱቅ በመግባት 6000 ብር እና ግምቱ ያልታወቀ ገንዘብ እንዲሁም የዋጋ ግምቱ ብር 1650 ብር የሆነ ስልክ ከወሰዱ በኋላ ግብረ አበሯ ለተከሳሽ 2000 እና የሟችን የእጅ ስልክ የሰጣት የወሰደች በመሆኑ በፈጸመችው የግድያና ከባድ ስርቆት ወንጀል ተከሳለች፡፡

ተከሳሽ የዐቃቤ ሕግ የክስ ዝርዝር ተነቦላት እንድትረዳው ከተደረገ በኃላ በ2ቱም ክስ ላይ የተጠቀሱትን ድርጊቶች አልፈፀምኩም በማለት የእምነት ክህደት ቃሏን ሰጥታለች፡፡ዐቃቤ ሕግም እንደክሱ አቀራረብ የምስክሮች ቃል እንዲሳማ ለፍርድ ቤቱ ያመለከተ ሲሆን ፍርድ ቤቱም ግራ ቀኙን መርምሮ ተከሳሽ በቀረበባት 2 ክስ ጥፋተኛ ተባለች::

በመጨረሻም የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 20ኛ ወንጀል ችሎት መዝገቡን መርምሮ ተከሳሽን የዘወትር ፀባይ መልካም እንደነበር እና የቤተስብን የምትረዳ መሆኑን በማቅለያ በመያዝ በ2ቱ ክስ በ11 ዓመት ጽኑ እስራት እንድትቀጣ ወስኗል፡፡
ፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ
በመምህርነት ሙያ ተቀጥሮ ከሚሰራበት ትምህርት ቤት የስርቆት ወንጀል የፈፀመው ተከሳሽ በእስራት ተቀጣ
________________

ቀዳማዊ ሰለሞን የተባለ ተከሳሽ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢፌዴሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 669/2/መ/ ላይ የተደነገገውን ድንጋጌ በመተላለፍ በፈፀመው ከባድ የስርቆት ወንጀል ተከሶ ፍርድ ቤት ቀርቧል፡፡

የክስ መዝገቡ እንደሚያስረዳው ተከሳሹ የማይገባውን ብልፅግና ለራሱ ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ ሰኔ 4 ቀን 2011 ዓ.ም በግምት ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ሲሆን በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ልዩ ቦታው ትራፊክ ሰፈር ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ በመምህርነት ሙያ ተቀጥሮ ከሚሰራበት 3A አፀደ ህፃናት ትምህርት ቤት ከተመራቂ ተማሪዎች የተሰበሰበውን የጋዋን እና የፎቶ ብር አምስት ሺህ ሰባት መቶ ብር የጠረጴዛውን መሳቢያ በመገንጠል የወሰደ እና የተሰወረ በመሆኑ በፈፀመው የከባድ ስርቆት ወንጀል ተከሷል፡፡

ዐቃቤ ህግ በበኩሉ ተከሳሹ የተከሰሰበትን የወንጀል ድርጊት እንደ ክሱ ሙሉ በሙሉ ያመኑ በመሆኑ ባመነው መሰረት በተከሳሹ ላይ የጥፋተኝነት ፍርድ ይሰጥልኝ ሲል አቅርቧል፡፡ ፍርድ ቤቱም ተከሳሹ በተከሰሰበት ድንጋጌ ስር በዝርዝር ያመነ በመሆኑ ጥፋተኛ ነህ ብሏታል፡፡

ጉዳዩን የተመለከተው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራኒዮ ምድብ 4ኛ የወንጀል ችሎት በተከሳሹ ላይ የወንጀሉን ደረጃ በደረጃ 4 እርከን 19 መነሻ ቅጣት በመያዝ ተከሳሹ የወንጀል ሪከርድ የሌለበትና ወንጀሉን በዝርዝር ያመነ በመሆኑ በ2 የቅጣት ማቅለያ ተይዞለት ዝቅ እንዲል በማድረግ በእርከን 17 ስር በማሳረፍ ተከሳሽን ያርማል ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎችን ያስተምራል ያለውን በ3 ዓመት ከ3 ወር ቀላል እስራት እንዲቀጣ ሲል ወስኖበታል፡፡
ፌ.ጠ. አ .ህ
ሞባይል ሰርቆ ለማምለጥ የሞከረዉ ግለሰብ በእስራት ተቀጣ ፡፡ ተከሳሹ ወርቁ አንዳርጌ ይባላል
________________
የ34 ዓመት ጎልማሳ ነዉ ካልተያዘዉ ግብረ አበሩ ጋር በመሆን ከመኪና ዉስጥ ሞባይል ሰርቆ ለማምለጥ ሲሞክር ተይዟል፡፡

ዐቃቤ ህግም ፈጽሞታል ባለዉ የስርቆት ወንጀል ክስ መስርቶበት ሲከራከር ቆይቷል፡፡ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የወንጀል ህግ አንቀጽ 32/1/ሀ/ እና 665/1/ ሥር የተደነገገዉን በመተላለፍ ነሐሴ 12 ቀን 2011ዓ.ም በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 05 ዲያስፖራ አደባባይ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ከቀኑ 5፡30 ሲሆን ተከሳሹ የማይገባዉን ብልጽግና ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰዉ ለማስገኘት በማሰብ ንብረትነቱ የግል ተበዳይ ልዩነሽ በሀጋን የሆነ እና የዋጋ ግምቱ 25000(ሀያ አምስት ሺህ ብር)የሚያወጣ ሳምሰንግ ሞባይል ግብረ አበሩን አሰርቋል፡፡

የግል ተበዳይን የመኪና መስኮት ከፍቶ በማዘናጋት እጇን ይዞ እያወራት ባለበት ሁኔታ ያልተያዘዉ ግብረ አበሩ ሞባይሏን ከመኪና ዉስጥ አዉጥቶ ከአካባቢዉ ተሰዉሯል፡፡ እሱም አብሮ በመሮጥ ለማምለጥ ሲሞክር ተይዟል፡፡ በመሆኑም በዋና ወንጀል አድራጊነት በፈጸመዉ የስርቆት ወንጀል ክሱ ተመስርቶበታል ሲል የዐቃቤ ህግ የክስ ሂደት ያስረዳል፡፡

ክሱ የተፈፀመዉ በየካ ክፍለ ከተማ የላምበረትና አካባቢዉ ፖሊስ ጣቢያ ሲሆን የተፈጸመዉ ወንጀልና የተመሰረተበት የክስ አይነት በመርማሪ ፖሊስ ካሳሁን በላይ አስረጅነት ተገልጾለት የእምነት ክህደት ቃሉን እንዲሰጥ ተጠይቋል፡፡ በእለቱ የግል ተበዳይ እግረኛ ለማሳለፍ መኪናዋን ስታቆም ተጠግተህ እጇን በመያዝ ያልተያዘዉ ግብረ አበርህ ሞባይሉን ነጥቆ እንዲያመልጥ አድርገሀል፡፡

አንተም ተከትለህ በመሮጥ ላይ ሳለህ በአካባቢዉ በነበሩ ሰዎች ተይዘሃል የሚል ሲሆን ተከሳሹ ግን የወንጀል ድርጊቱን አልፈጸምኩም ሲል ቃሉን ሰጥቷል፡፡ የፌደራሉ የመጀመሪ ደረጃ ፍርድ ቤት የካ ምድብ ወንጀል ችሎት የቀረቡለትን አራት ምስክሮች ዋቢ አድርጎ ተከሳሽን ጥፋተኛ ነዉ ሲል ብይን አስተላልፏል፡፡

በዚህም መሰረት ህዳር 25 ቀን 2012 ዓ.ም ባስቻለዉ 1ኛ ወንጀል ችሎት የተከሳሽን የጤና ችግር በማቅለያነት ይዞ በአራት ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል፡፡
ፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ
567..:
I'm Abush from Hu...if you have succession ppt prepared by Awet Lijalem unit 2 please share it!