አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.84K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
ጀርመን የቤት ውስጥ ጥቃት ለሚፈጽምባቸው ወንዶች መጠለያ ማዘጋጀት ጀመረች

በ"ወንዶች መጠለያዎቹ" በሴቶች አካላዊ፣ ወሲባዊ እና ስነልቦናዊ ጥቃት የደረሰባቸው ወንዶች ብሶታቸውን የሚተነፍሱበት እድል ተመቻችቶላቸዋል።

ዝርዝሩን በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ፤ https://bit.ly/4hAb8Pc
#ፀደቀ‼️
ከፍተኛ የትምህርት አቀባበል ያላቸው ተማሪዎች ወደ ቀጣይ ክፍል መሸጋገር የሚያሰችል አዋጅ ፀደቀ‼️
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 17ኛ መደበኛ ስብሰባው ከፍተኛ የትምህርት አቀባበል ያላቸው ተማሪዎች የሚገኙበትን የትምህርት ክፍል ሳያጠናቅቁ ወደ ቀጣዩ ክፍል መሸጋገር የሚያስችል የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅን አፅድቋል።

የአዋጁ መፅደቅ ብቁ የትምህርት ባለሙያ፣ አመራርና አደረጃጀት ለመፍጠር የሚያስችል ነው ተብሏል።

የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ለምክርቤት ባቀረቡት ሪፖርት እንደገለፁት፣ የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍን መሠረት አድርገው ከተቀረጹ መርሐግብሮችና ዕቅዶች አንጻር ትምህርትን ለመምራት የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ባለመኖሩ ዘርፉን በሚፈለገው ደረጃ አላደገም።

ይህንን መሰረታዊ ችግር ለመፍታት አዲስ አዋጅ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል ብለዋል። አዋጁ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና በዘርፉ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ የሚደረገውን ሪፎርም ያግዛል።

በአዋጁ ከፍተኛ የትምህርት አቀባበል ያላቸው ተማሪዎች የሚገኙበትን የትምህርት ክፍል ሳያጠናቅቁ ወደ ቀጣይ ክፍል መሸጋገር እንዲችሉ ተደርጎ መዘጋጀቱንም ተናግረዋል።

አዋጁ ብቁ የትምህርት ባለሙያ፣ አመራርና አደረጃጀት ለመፍጠር ይረዳል ያሉት ሰብሳቢው፣ በመላው ሀገሪቱ ሁሉም የአጠቃላይ ትምህርት ተቋማት የሚከናወነው የመማር ማስተማር ሂደት የሀገሪቱን እሴት ጠብቆ እንዲካሄድ ግልጽ አቅጣጫ የሚሰጥ ስለመሆኑ አስረድተዋል።
https://www.alehig.com/
206006.pdf
826.1 KB
ተከሳሽ የመከላከያ መልሱን አቅርቦ ክሱ ሊሰማ በተቀጠረበት ዕለት ባለመቅረቡ በፍ/ሥ/ሕ/ቁ 70(ሀ) መሰረት ክርክሩ በሌለበት እንዲታይ ብይን ከተሰጠ የመከላከያ ክርክር የማቅረብ መብቱን ከማሳጣት አልፎ በቀሪዎቹ የክርክር ሂደቶች ከመሳተፍ አያግደውም።
559_የኢሚግሬሽን_የሚኒስትሮች_ምክር_ቤት_ደንብ.pdf
823.9 KB
የኢሚግሬሽን የሚኒስትሮች ምክር ቤት ማሻሻያ ደንብ ቁጥር 559/2017
Council of Ministers Immigration Amendment Regulation No 559/202
560_የኢሚግሬሽንና_ዜግነት_አገልግሎት_ሠራተኞች.pdf
1.2 MB
ደንብ ቁጥር 560/2017
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የሠራተኞች መተዳደሪያ ደንብ
Regulation No. 560/2024
Immigration and Citizenship Service Employees Administration Regulatio
ካርታ ማምከን ማለት የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤትነት ማረጋገጫ ማስረጃ /ደብተር ወይም ካርታ/ በመሰረዝ ዋጋ የማሳጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ነው።
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp📱 #+251920666595
Telegram📱 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#እንድታውቁት 📣❗️🆕

የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ባለስልጣን በሽያጭ የተሽከርካሪ ስም ዝውውር ለማድረግ ሊሟሉ እሚገባቸው ጉዳዮች ብሎ የሚከተሉትን ነጥቦች አስቀምጧል።

በዚህም በሽያጭ የተሽከርካሪ ስም ዝውውር ለማድረግ፦

1. በተሽከርካሪው ላይ የተላለፈ ማንኛውም ዓይነት እዳ እና እገዳ እንዲሁም ቀረጥ ያለበት ከሆነ የስምምነት ደብዳቤ መኖሩን ማረጋገጥ፣

2. ኮድ 01 እና ኮድ 03 ከሆነ ከገቢዎች የግብር ክሊራንስ መቅረቡን

3. የዘመኑን ዓመታዊ የቴክኒክ ምርመራ/ቦሎ፤ ያደረገ መሆኑን፤

4. የጸደቀ የውልና ማስረጃ ሰነድና የስም ዝውውር 2% የከፈለበት ማስረጃ መኖሩን፣

5. የንግድ ተሽከርካሪ ከሆነ አንዱ የግምት ውጤት ለሀገር ውስጥ ገቢ ባለስልጣን ይላካል፤ ሁለተኛውን የግምት ውጤት ሁለቱ ተዋዋዮች ውል መፈፀም የሚችሉ ለመሆኑ በሸኚ ደብዳቤ ለሠነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ጽ/ቤት የተላከበት ሰነድ፤

6. የቤት ተሸከርካሪ ከሆነ የግምት ውጤቱን በቀጥታ ሰሠነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ የተላከበት ሰነድ፤

7 . የገዢ ሁለት ፎቶ ግራፍ

8. የስም ዝውውርና የአገልግሎት ለውጥ የሚያደርግ ከሆነ ተሸከርካሪው በድጋሚ ለቴክኒክ ምርመራ ብቃት ማረጋገጫ ሲቀርብ እገልግሎቱ ይሰጣል ሲል አስቀምጧል።

በተጨማሪም ቢሮው በዚሁ መረጃው ላይ በሰጠው ማሳሰቢያ፦

1. የሚገዙት ተሽከርካሪ የሻንሲና ምተር ቁጥር ትክክለኛነት የማረጋገጥ፣

2. የተሚገዙት ተሽከርካሪ ሊብሬና ተሽከርካሪ ስለያዙ እና ዉክልና ስለተሰጦት ብቻ ሀጋዊ ተሽከርካሪ ማለት ስላልሆነ የሚገዙት ተሽከርካሪ በተመዘገበበት ቅ/ጽ/ቤት ትክክለኛነቱ መረጋገጥ አለበት ሲል ገልጿል።
#tikvahethmagazine
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp📱 #+251920666595
Telegram📱 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
capital market amharic.pdf
268.2 KB
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን መግለጫ ለባለ አክስዮን ማህበሮች

ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
በሞት የተለዩ ተጠርጣሪዎችን ንብረት እንዲወረስ የሚያደርገው የንብረት ማስመለስ አዋጅ ተግባራዊ ሊደረግ ነው‼️
ምንጩ ያልታወቀ ንብረትን በተመለከተ ተጠርጣሪው በሞት ቢለይ ወይም ከሀገር የሸሸ ቢሆንም ንብረቱ  እንዲታገድና ጉዳዩ ተጣርቶ ግለሰቡ በሌለበት እንዲወረስ እንደሚደረግ ተገለፀ፡፡

በአዲሱ የንብረት ማስመለስ አዋጅ  በጥፋተኝነት ላይ ያልተመሰረተ የንብረት ማስመለስ አዋጁ እንደሚያካትት ሲገለፅ  ይህም ተጠርጣሪው በሞት ቢለይ ወይም ከሀገር የሸሸ ቢሆን ንብረቱ እንዲሁ የሚቀር ሳይሆን እንዲታገድና ጉዳዩ ተጣርቶ ግለሰቡ በሌለበት እንዲወረስ ይደረጋል ሲል ፍትህ ሚኒስትር አስታውቋል።

የጸደቀው የንብረት ማስመለስ አዋጅ ተፈጻሚ ሲሆንም  ምክንያታዊ ያልሆኑ ክሶች እንዳይመጡ ተጠርጣሪው ግለሰብ ስለ ጉዳዩ ቀርቦ እንዲያስረዳ ዕድል የሚሰጥና በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ብቻ ተፈጻሚ የሚሆን ነውም ብሏል።

አዋጁ በህገ-ወጥ መንገድ በወንጀል የተገኘ ንብረትን በአግባቡ በማስመለስ የሀገርንና የህዝብን ሀብት ከወንጀል ለመጠበቅ የሚሰራበት ነው ተብሏል።

የማይመለስ ጉዳት ማለትም ንብረቱ ከሃገር ሊሸሽና ሌሎች ተመሳሳይ ጉዳት ደርሶ ከሆነ ጊዜያዊ እግድ በራሱ በፍትህ ሚኒስቴር ያለፍርድቤት ትዕዛዝ እንደሚሰጥም ተገልጿል።

አዋጁ አንድ ግለሰብ በቅን ልቦና ባለማወቅ ንብረቱ ህገ-ወጥ መሆኑን ሳያውቅ የገዛ ቢሆን ንብረቱ እንዳይወረስ ተገቢውን ጥበቃ የሚሰጥ ነው ተብሏል።

በአዋጁ ላይ በተደነገገው መሰረትም ህገ-ወጥ ንብረት በማፍራት የተጠረጠረ ሰው ያለደረሰኝ በሰውም ሆነ ሌሎች ያስረዱልኛል ባላቸው ማስረጃዎች ጥፋተኛ አለመሆኑን ማስረዳት የሚያስችል መመሪያ እንዳለውም ተነስቷል።

አዋጁን ለማስፈጸም ከተለያዩ ሀገራት ጋር በትብብር የሚሰራ ሲሆን  ንብረቱ ኢትዮጵያ ቢሆንም በውጭ ሀገራት በህገ-ወጥ መንገድ የተገኘ መሆኑ ከተረጋገጠ ለማስመለስ የሚሰራበት ነው ተብሏል።
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
አሜሪካ በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ጥፋተኛ የተባለ ዜጋዋን አፍና ገደለች


ግለሰቡ የሁለት ልጆች እናት የሆነች ሴትን አስገድዶ ከደፈረ በኋላ ገድሏታል ተብሏል


የ14 ዓመት ታዳጊ በመድፈር ወንጀልም ጥፋተኛ ሆኖ የተገኘው ይህ አሜሪካዊ በናይትሮጅን ጋዝ ታፍኖ እንዲሞት ተደርጓል


ተጨማሪ ያንብቡ https://am.al-ain.com/article/alabama-killed-a-rapist-by-nitrogen-gas
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ውድድር ማስታወቂያ እንዲሁም የፖለቲካ ድርጅቱ የሚያሰራጨውን የአድራሻ ለውጥ፣ የስብሰባ ጥሪ እና መሰል ማስታወቂያዎችን የሚከለክል አይደለም።)እና ሌሎች በሕግ የተከለከሉ ማስታወቂያዎች፡፡

💎 ገደብ የተደረገባቸው ማስታወቂያዎች
- የአልኮል መጠኑ ከ12 በመቶ በላይ የሆነ ማንኛውንም መጠጥ የሚመለከት ማስታወቂያ ከውጭ ማስታወቂያ እና እለታዊና ሳምንታዊ ካልሆነ ጋዜጣ እና መጽሔት በስተቀር በሌሎች የማስታወቂያ ማሰራጫ መንገዶች (ማለትም በብሮድካስት አገልግሎት፣ በስልክ አገልግሎት ወይም በፖስታ አገልግሎት የማስራጫ መንገዶች) አማካኝነት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ማሰራጨት የተከለከለ ነው፡፡ ሌላው እዚህ ጋር ልብ ሊባል የሚገባው የአልኮል መጠኑ ከ12 በመቶ በላይ የሆነን መጠጥ በውጭ ማስታወቂያ ማሰራጫ መንገድ ለምሳሌ፡- በሕንጻ ወይም በማናቸውም ስትራክቸር ወይም በትራንስፖርት ተሽከርካሪ ላይ በሚፃፍ ወይም በሚለጠፍ፣ በተንጠልጣይ ነገር፣ በፖስተር፣ በስቲከር፣ በብሮሸር፣ ሊፍሌት ወይም በራሪ ወረቀት በመጠቀም ማሰራጨት ቢቻልም በሌላ በኩል ደግሞ እንደ የኤሌክትሮኒክ ስክሪን፣ በድምፅ ማጉያ፣ የድምፅ ካሴት ወይም በሌላ በምስልና በድምፅ በሚሰራጭ የውጭ ማስታወቂያ መንገዶች ማሰራጨት አይቻልም፡፡ ሌላው ማንኛውም የአልኮል መጠጥ ማስታወቂያ የአልኮል መጠጡን መውሰድ ለጤና ተስማሚ እንደሆነ፣ ግላዊ ወይም ማኅበራዊ ስኬትን እንደሚያስከትል፣ የተሻለ ሥነ ልቦናዊ ወይም አካላዊ ብቃት እንደሚያስገኝ ወይም ፈዋሽ እንደሆነ የሚገልጽ ወይም በተደጋጋሚ ወይም ከልክ በላይ እንዲጠጣ የሚገፋፋ፤ ከአልኮል ሱስ መጠበቅን የሚያጣጥል ወይም የሚቃወም፣ አካለ መጠን ያልደረሰ ልጅ ላይ ትኩረት የሚያደርግ ወይም አካለ መጠን ያልደረሰ ልጅን የማስታወቂያው ተዋናይ አድርጎ የሚጠቀም፤ ወይም ሌላ መሰል መልእክት የሚያስተላልፍ መሆን የለበትም፡፡ በተጨማሪም የአልኮል መጠጥ የውጭ ማስታወቂያ ከልጆች መዋያ ማዕከል፣ ከትምህርት ቤት፣ ከህክምና ወይም ታሪካዊ ተቋም፣ ከሲኒማ ቤት፣ ከቲያትር ቤት ወይም ከስታዲየም በመቶ ሜትር ራዲየስ ውስጥ እንዲቀመጥ መደረግ የለበትም፡፡

የሕግ ተጠያቂነት💎💎
የማስታወቂያ ስራ ሊከተለው የሚገባ ህግና ስርዓት ያለው እንደመሆኑ ህግና ስርዓቱን ባልጠበቀ መልኩ የማስታወቂያ ስራ ላይ መሰማራትም ሆነ ማሰራጨት አስተዳደራዊ፣ ፍትሀ ብሔራዊና የወንጀል ተጠያቂነትን የሚያስከትሉ ሲሆን በዚህ ፅሁፍ ከወንጀል አንፃር ሊኖር የሚችለውን የህግ ተጠያቂነት ሁኔታ እንደሚከተለው ተዳሷል፡-
- በአዋጅ ቁጥር 759/2004 አንቀፅ 34/1/ሀ/ መሰረት አንድ ሰው በአዋጁ አንቀፅ 5/1/ እና/2/ መሰረት በማስታወቂያ ስራ ላይ ለመሳተፍ የሚያስችለውን ፍቃድ ከሚመለከተው የመንግስት አካል ሳያገኝ በማስታወቂያ ስራ ላይ የተሰማራ እንደሆነ በንግድ ምዝገባና ፍቃድ አዋጅ አንቀፅ 49/2/ መሰረት ለስራው የሚጠቀምበት መሳሪያ መወረስን ጨምሮ ከብር 150ሺ እስከ 300ሺ በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ እና ከ7ዓመት እስከ 15ዓመት በሚደርስ የፅኑ እስራት ሊቀጣ ይችላል፡፡
- ከይዘትና ስርጭት አንፃር በመገናኛ ብዙሀን የሚተላለፉ ማስታወቂያዎች ከሌሎች ፕሮግራሞች የተለየ መሆኑ በግልፅ በሚታወቅ መልኩ እና በዜና መልክ ባልተዘጋጀ መልኩ መቅረብ ያለበት መሆኑን፣ የማስታወቂያ ወኪል የአንድን ሰው ምርት፣ አገልግሎት ወይም ሌላ መልእክት የሚያስተዋውቅ የንግድ ማስታወቂያ አዘጋጅቶ ባሰራጨ በሦስት ወራት ውስጥ የሌላ ሰውን ተመሳሳይ ምርት፣ አገልግሎት ወይም ሌላ መልእክት በተመሳሳይ የማስታወቂያ ተዋናይ ምስል ወይም ድምፅ አዘጋጅቶ ማሰራጨት የለበትም በማለት በአዋጁ አንቀፅ 6 ንዑስ አንቀፅ (2)(3) እና(4) የተደነገጉትን መተላለፍ፣ በአዋጁ አንቀፅ 26(3) ስር 12 በመቶ በላይ የአልኮል መጠን ያላቸውን መጠጦች የማስታወቂያ ስርጭት በተመለከተ የተቀመጡ ገደቦችን መተላለፍ ደግሞ በአዋጁ አንቀፅ 34/1/ለ/ መሰረት ከብር 10ሺ በማያንስና ከብር 100ሺ በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ እንደሚያስቀጣ ተደንግገዋል፡፡
- በአዋጁ አንቀፅ 6/1/ ስር የተዘረዘሩት የማስታወቂያ ይዘት የተመለከቱ ክልከላዎችን መተላለፍ፣ ህግን ወይም መልካም ስነምግባርን የሚፃረሩ እንዲሁም አሳሳች ወይም ተገቢ ያልሆኑ ማስታወቂያዎች ተብለው በህጉ የተደነገጉትን ማስታወቂያዎች ሰርቶ ማሰራጨት፣ በአዋጁ አንቀፅ 26(1)፣(2) እና (4) የተጠቀሱትን ክልከላዎች በመተላለፍ የአልኮል ይዘታቸው ከ12 በመቶ በላይ የሆኑ መጠጦችን ከተፈቀደው የማስታወቂያ መንገድና ቦታ ውጭ ማስተዋወቅ ከ20ሺ ብር በማያንስና ከብር 150ሺ በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ ያስቀጣል፡፡
- በአዋጁ አንቀፅ 25/1/ ስር የተመለከቱትን በህግ ክልከላ የተደረገባቸውን ማስታወቂያዎች ማሰራጨት ደግሞ ከ30ሺ ብር በማያንስና ከብር 250ሺ በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ ያስቀጣል፡፡
- በአዋጁ አንቀፅ 34/2/ መሰረት ከፍ ሲል ከተመለከተው የገንዘብ መቀጮ በተጨማሪ ጥፋተኛ የሆነው ሰው ከሕገ ወጥ ማስታወቂያ ሥራው ያገኘው ገቢ ይወረሳል፡፡
ከቅጣት ጋር በተያያዘ ሌላው ከግንዛቤ ልናስገባው የሚገባው ጉዳይ በአዋጁ ላይ በዝርዝር የተጠቀሱት ሌሎች ሁኔታዎች ማለትም የተለየ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ስለሚያስፈልገው ማስታወቂያ፣ አካለመጠን ያልደረሰ ልጅን ስለሚመለከት ማስታወቂያ፣ ስለፀረ አረም ወይም ፀረ ተባይ በተመለከተ የሚተላለፉ ማስታወቂያዎች ወዘተ በተመለከተ የተጠቀሱ ዝርዝር ሁኔታዎችን አለማሟላት በአዋጁ አንቀፅ 34 መሰረት የሚያስቀጡ መሆናቸውን መገንዘብ የሚገባ ሲሆን፡፡ በተጨማሪም ከፍ ሲል ያየናቸው በአዋጁ ላይ ተጠቅሰው የሚገኙት ቅጣቶች ተፈፃሚ የሚሆኑት ድርጎቶቹ በሌላ ህግ የበለጠ የማያስቀጡ እንደሆነ ነው፡፡ ይህም ማለት ድርጊቱ በሌላ ህግ በአዋጁ ከተገለፀው የቅጣት መጠን በላይ የሚያስቀጣ በሆነ ጊዜ ለጉዳዩ የምንጠቀመው የበለጠ የሚያስቀጣውን ህግ ይሆናል ማለት ነው፡፡ ለምሳሌ በአዋጅ ቁጥር 759/2004 አንቀፅ 8(12) መሰረት በትክክለኛ ዋጋው እየተሸጠ ያለን ምርት ወይም አገልግሎት በነጻ እየተሰጠ ወይም በቅናሽ እየተሸጠ እንደሆነ አድርጎ የሚያቀርብ ማስታወቂያ አሳሳች ወይም ተገቢ ያልሆነ ይዘት ወይም አቀራረብ እንዳለው ማስታወቂያ ይቆጠራል፡፡

በአዋጁ አንቀፅ 34(1)(ሐ) መሰረት ደግሞ መሰል አሳሳች ይዘት ያለው ማስታወቂያ ማሰራጨት ከ20ሺ ብር በማያንስና ከብር 150ሺ በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ ያስቀጣል፡፡ በሌላ በኩል በዚሁ ተመሳሳይ ጉዳይ ላይ የንግድ ስራ እና ሸማቾች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 813/2006 አንቀፅ 22(4)(5) መሰረት የንግድ እቃዎችንና አገልግሎቶችን በማስታወቂያ እንደተነገረላቸው አለመሸጥ፣ ስለዋጋ ቅናሽ አሰተኛ ወይም አሳሳች መረጃ መስተላለፍ በአዋጁ አንቀፅ43/3/ ተጠቃሎ ሲታይ ስለ ዋጋ ቅናሽ አሰተኛ ወይም የተሳሳተ መረጃ ማስተላለፍ(ማስተዋወቅ) የአመታዊ ሽያጭ ገቢውን ከ5 እስከ 10 በመቶ የገንዘብ ቅጣት እና ከ1 ዓመት እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት እንደሚያስቀጣ ይደነግጋል፡፡ ይሄም ከፍ ሲል በአዋጅ ቁጥር 759/2004 አንቀፅ 34/1/ሐ/ ከተጠቀሰው የቅጣት መጠን ከፍ የሚል በመሆኑ መሰል የዋጋ ቅናሽን በተመለከተ የሚቀርቡ ሀሰተኛ ማስታወቂያዎች ሲሰሩ ክስ ሊቀርብ የሚገባው በንግድ ስራና የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ መሰረት ሊሆን እንደሚገባ መረዳት ያስችላል፡፡
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ማጠቃለያ💎
በአጠቃላይ ከፍ ሲል አጠር ባለ መልኩ ለማቅረብ ከተሞከረው ጽሁፍ መረዳት እንደሚቻለው የማስታወቂያ ስራዎች ሊከተሏቸው የሚገቡ የሕግ ሁኔታዎች እንዳሉ መረዳት ይቻላል፡፡ ስለሆነም አሁን ላይ እየተስፋፋ ከመጣው የቴክኖሎጂ ተደራሽነት አንፃር ዜጎች በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ በማስታወቂያ ስራዎች ውስጥ የሚሳተፉበት ሁኔታ እየሰፋ በመምጣቱ በዚሁ የስራ መስክ የሚሰማሩ ሰዎች ቢያንስ መሰረታዊ የሚባሉ የማስታወቂያ ስራ ሕጎች ላይ በንባብም ሆነ በሌላ መልኩ እራሳቸውን በማብቃት ስራውን ተከትሎ ሊመጡ ከሚችሉ የሕግ ተጠያቂነቶች ራሳቸውን ሊጠብቁ ይገባል፡፡
ፍትህ ሚኒስቴር
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
https://www.alehig.com/%e1%8b%a8%e1%88%9b%e1%88%b5%e1%89%b3%e1%8b%88%e1%89%82%e1%8b%ab-%e1%88%95%e1%8c%8d/
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM