አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.86K photos
25 videos
1.86K files
3.58K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
አለሕግAleHig ️
Photo
Stay Connected with AleHig!
https://linktr.ee/alehig
AleHig is active across multiple social media platforms, ensuring easy access to legal information, updates, and services for everyone.
Whether you’re looking for insights on legal issues or want to stay informed about the latest developments, our dynamic online presence keeps you in the loop. 🌍

alehig.com
Follow us for real-time updates and empower yourself with knowledge to navigate the legal landscape in Ethiopia!
አማራጭ የሕግ እውቀት አለ
Alternative legal enlightenment/ALE
#የሕግአማካሪ #Attorney Mikias Melak Birhanie WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak #DailyAdvice የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ የሕግ መረጃና መሰረታዊ የሕግ እውቀት ያገኛሉ::
Telegram
https://t.me/AleHig

Telegram_Group
https://t.me/AleHig_Group

Facebook Page
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

LinkedIn
https://www.linkedin.com/company/alehig/

YouTube
https://www.youtube.com/@Ale_Hig

TikTok
https://www.tiktok.com/@alehigofficial

Instagram https://www.instagram.com/alehigofficial

Twitter /X
https://x.com/AlehigOfficial?t=yFRauAZ7v70Je2MEPIGGsQ&s=09

official website
https://www.alehig.com

#LegalAwareness #AleHig #LegalUpdates #AccessToJustice
October 5, 2024
የኢፌዲሪ ህገ መንግስት ስለ ሪፐብሊኩ ፕሬዝዳንት ስልጣንና ተግባር ምን ይላል ?

(የኢፌዴሪ ህገ መንግስት)

ምዕራፍ ሰባት
ስለ ሪፐብሊኩ ኘሬዚዳንት
አንቀጽ 69
ስለ ኘሬዚዳንቱ

ኘሬዚዳንቱ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ርዕሰ ብሔር ነው፡፡


አንቀጽ 70
የፕሬዜዳንቱ አሰያየም
1. ለፕሬዜዳንትነት ዕጩ የማቅረብ ሥልጣን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው።
2. የቀረበው ዕጩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብሰባ በሁለት ሦስተኛ ድምጽ ከተደገፈ ፕሬዜዳንት ይሆናል።
3. የምክር ቤት አባል ፕሬዜዳንት ሆኖ ከተመረጠ የተወከለበትን ምክር ቤት ወንበር ይለቃል።
4. የፕሬዜዳንቱ የሥራ ዘመን 6 ዓመት ነው። አንድ ሰው ከሁለት ጊዜ በላይ ለፕሬዜዳንትነት ሊመረጥ አይችልም።

አንቀጽ 71
የኘሬዚዳንቱ ሥልጣንና ተግባር
1. የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽኑን ምክር ቤት ዓመታዊ የጋራ ስብሰበባ ይከፍታል፡፡
2. በዚህ ሕገ መንግሥት መሰረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያጸደቃቸው ሕጐችና ዓለምአቀፍ ስምምነቶች በነጋሪት ጋዜጣ ያውጀል፡፡
3. ሀገሪቷን በውጭ ሀገሮች የሚወክሉትን አምባሳደሮችና ሌሎች መልክተኞች በጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅራቢነት ይሾማል፡፡
4. የውጭ ሀገር አምሳደሮችንና የልዩ መልዕክተኞችን የሹመት ደብዳቤ ይቀበላል፡፡
5. በሕግ መሰረት ኒሻኖች እና ሽልማቶችን ይሰጣል፡፡
6. በጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅራቢነት በሕግ በተወሰነው መሰረት ከፍተኛ የውትድርና ማዕረጐችን ይሰጣል፡፡
7. በሕግ መሰረት ይቅርታ ያደርጋል፡፡
#TikvahEthiopia
Telegram
https://t.me/AleHig

Telegram_Group
https://t.me/AleHig_Group

Facebook Page
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

LinkedIn
https://www.linkedin.com/company/alehig/

YouTube
https://www.youtube.com/@Ale_Hig

TikTok
https://www.tiktok.com/@alehigofficial

Instagram https://www.instagram.com/alehigofficial

Twitter /X
https://x.com/AlehigOfficial?t=yFRauAZ7v70Je2MEPIGGsQ&s=09

official website
https://www.alehig.com

#LegalAwareness #AleHig #LegalUpdates #AccessToJustice
October 5, 2024
Forwarded from ሕግ ቤት
ከህግ ትምህርት ቤት መሠረታዊ ትሩፋቶች ጥቂቶቹ
*****
ምን
ጭ ወ/ሮ ትብለጥ ቡሽራ Tiblet Bushra
**
የህግ
ትምህርት ቤት በአንድ ወገን ብቻ የተነገረ ታሪክ ወይም ፍሬ ነገር ሁሌም ጎዶሎ እንደሆነ ያስተምርሀል፡፡ በምንም ጉዳይ አቋም ከመውሰድህ፣ ከመፍረድህ፣ አስተያየት ከመስጠትህ በፊት ሙሉ ታሪኩን ማወቅ በመርህ ደረጃ እንደቅድመ ሁኔታ ያስቀምጥብሀል ”There is always the other side of a story” ብለህ እንድታስብ ያስገድድሀል፡፡ ከዛ ውጪ የሚደረስ ድምዳሜ ትክክለኛ ያልሆነ ወይም የተዛባ፣ ያዳለ፣ ፍትሀዊነት የጎደለው ነው፡፡ ይህ አይነት አስተሳሰብ እንዲኖርህ የሚጠበቀው ደግሞ እጅህ ላይ በመጡ የህግ ጉዳዮች ብቻ ሳይሆን በአገራዊ ጉዳዮች፣ በግለሰቦች ጉዳዮች በምትሰማቸው ከአንድ ወገን የሚነገሩ ታሪኮች፣ ውሳኔዎችም ጭምር ነው፡፡

የህግ ትምህርት ቤት ለሀሳቦች ክፍት መሆንን (Open mindedness) ያስተምርሀል፡፡ እውነት ወይም ሀሰት ፈተና ቀርቦልህ ለአንድ ጥያቄ እውነትም ብለህ 10/10 ሀሰትም ብለህ 10/10 ልታገኝ ትችላለህ ልታጣም ትችላለህ፡፡ ለመልስህ እንዳቀረብከው የክርክር ነጥብ ጥንካሬ እና ምክኒያታዊነት፡፡ በዚህ አንተ ከያዝከው ሀሳብ የተለየ ሀሳብ ይዞ አሳማኝ ምክኒያት ለሚያቀርብልህ እጅ መስጠት እና የራስን ሀሳብ በምክኒያት መተው ሽንፈት እንዳልሆነ ያስተምርሀል፡፡

የህግ ትምህርት ቤት የሀሳብ ነጻነት ጠቀሜታን፣ የሀሳብ ነጻነት ማክበርን ወይም ለሌሎች እይታ ዋጋ መስጠትን ያስተምርሀል፡፡ በአንድ አከራካሪ ጉዳይ ላይ አስተማሪህ የያዘውን አቋም እያወክ ይህን ጉዳይ በፈተና መልክ ሲያመጣው ካስተማሪው የተለየው የራስህን አቋም በምክኒያት አስደግፈህ ካቀረብክ ከኔ አቋም ውጪ አቋም ኖረው ብሎ ዜሮ አይሰጥህም፡፡ ካንተ ጋር ባይስማማም እንደ መከራከሪያ ነጥቦችህ ጥንካሬ እና ምኪኒያታዊነት ከፍ ያለ ማርክ ሊሰጥህም ይችላል፡፡ ይህን ሲያረግ ከኔ ብትለይም ያንተን ሀሳብ አከብራለሁ፣ ዋጋ እሰጠዋለሁ፣ አቋሜን እያወክ የራስህን አቋም ማስቀመጥህን እንደንቀት አላየውም እንደጥንካሬ፣ እንደ እሴት ጭማሪ አየዋለሁ እንጂ የሚል ትምህርት ያስተምርሀል፡፡

የህግ ትምህርት ቤት ስለ “ጥርጣሬ ተጠቃሚ” “benefit of doubt” ጽንሰ ሀሳብ ሲያስተምርህ ይህን ጽንሰ ሀሳብ ከወንጀል ጉዳዮች በዘለለ በሌሎች ጉዳዮችም እንድትተገብረው ጥበብን (wisdom) ያስተምርሀል፡፡ ስለሆነ ሰው ወይም ጉዳይ የማትገምተው አይነት ነገር ስትሰማ “እውነት ላይሆን ይችላል” “ከሚመስለው ውጪ ሊሆን ይችላል እውነቱ” “ምናልባት ይሄን እንዲያደርግ ያስቻለው አስገዳጅ ሁኔታ ሊኖር እኮ ይችላል” እና የመሳሰሉ ሌላ ከሚኖሩ አጠራጣሪ ነገሮች ለመጠቀም የሚያስችለው ሁኔታዎችን ከግምት ማስገባትን ሊጨምር ይችላል፡፡

የህግ ትምህርት ቤት በመርህ ደረጃ በጭፍን መታዘዝ (blind obedience) ልክ አለመሆኑን ያስተምራል፡፡ ለአለቃ መታዘዝ አንደኛው የስነ-ምግባር ግዴታ ቢሆንም ህገ-ወጥ የሆነ ትእዛዝን አለመቀበል መብትህ ሳይሆን ግዴታህ አርጎ ያስተምርሀል፡፡ ይህ ትምህርት እና አመክኒዮው ደሞ ለሌሎች ጉዳዮችም እንድትጠቀመው ትምህርት ይሆንሀል፡፡

የህግ ትምህርት ቤት ስለሰው ልጆች ክቡርነት፣ እኩልነት፣ ነጻነት… እያስተማረህ ትህትናን/ humility፣ በምንም ሁኔታ ላይ ብትሆን አንተ ከማንም እንደማታንስ ከማንም እንደማትበልጥም ያስተምርሀል ወይ ደግሞ ያስታውስሀል።

የህግ ትምህርት ቤት ባህል፣ ወግ፣ ሀይማኖት፣ ማንነት በአንድ ማህበረሰብ ውስጥ ወይም በግለሰቦች ውስጥ ያለውን ቦታ ያንን ችላ ያለ ምንም ነገር ዘለቄታ እንደማይኖረው ያስተምራል፡፡ በዛው ልክ ጎጂ የሆኑ ባህላዊ ድርጊቶችን ለመቀየር ወይም አዲስ ባህልን ለመፍጠር (to set Norm or standards) ሕግ ያለውን ኃይል ያሳይሀል

የህግ ትምህርት ቤት የህግ የበላይነትን መጠበቅ ወይም ማስጠበቅ ለሁላችንም የጋራ ሰላም፣ ደህንነት እና ጥቅም፣ ዋስትና መሆኑን ፈትፍቶ ያስተምርሀል፡፡
Lawyer_Henok Taye⚖️Ethio Law🥇ኢትዮ ሕግ
October 6, 2024
ቸርቹ ና ጠጅ ቤቱ ፊት ለፊት ናቸው።
ጠጪዎች እየተሳለቁ እየተሳሳቁ ይጠጣሉ: ገበያ ለጉድ ነው።

ቸርቹም የዋዛ አይደለም: የመጠጥ ሀጢዓትነት ቢያንስ አንዴ ይሰበካል: ስም ሳይጠቀስ ‘ወጋሁ ይባላል’
ቀስ በቀስ ነገሩ እየተጋጋለ ወደ next level ተሸጋገረ።
የ ቸርቹ ፓስተር ‘ጠጅ ቤቱ ብን ብሎ እንዲጠፋ: እንዲከስም በገሀድ መፀለይ ጀመረ።
ይባስ ብሎ ትንቢት ተናገረ:
እና ትንቢቱ ደረሰና ጠጅ ቤቱ በእሳት ጋየ ወደመ።

የጠጅ ቤቱ ባለቤት የዋዛ አይደለም: ብቀጥንም ጠጅ ነኝ አለና በህግ አምላክ’ ብሎ ተነሳ። ቸርቹንና ፓስተሩን ከውል ውጭ ሀላፊነት በአንድነት ና በነጠላ ተጠያቂ ናቸው ሲል ፍርድ ቤት ገተራቸው።
ቸርቹ ና ፓስተሩ መቃወሚያ ና በፍሬ ነገሩ መልስ ሰጡ።
“ፀሎት ሆነ ትንቢት የእሳቱ መንስዔ ስለመሆኑ ማስረጃ የለም። እኔ ስለፀለይኩና ትንቢት ስለተናገርኩ ጠጅ ቤቱ በእሳት አይወድምም። እንደዚህ ዓይነት ሀይል ና ስልጣንም የለኝም”

የጠጅ ቤቱ ባለቤት ግን “ጠጅ ቤቱ በእሳት የወደመው በተከሳሽ ፀሎት የተነሳ ነው። ባይፀልይ ና ትንቢት ባይናገር ኖሮ ስንት ጥሬ ግሬ ያፈራሁት ጥሪት አይወድምም ነበር” ሲል ወጥሮ ተከራከረ።

የችሎቱ ዳኛ የግራ ቀኙን ክርክር ና ማስረጃ መርምረው ብይን ሰጡ።
ብይን
በፀሎት ና ትንቢት በሚያምን የጠጅ ቤት ባለቤት እና
በፀሎት ና ትንቢት በማያምን ፓስተር መካከል የሚደረግ ክርክር መፍታት ከፍርድ ቤቱ አቅም በላይ ነው።
መዝገቡ ተዘግቷል: ወጪ ና ኪሳራ ይቻቻሉ።
Abrham Yohanes Law Corner
https://t.me/NegereFej
October 6, 2024
የግብር/የታክስ አይነቶች

መስከረም 27/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

ቀጥታ ታክስ


🟠የደመወዝ ገቢ ግብር
🟠የኪራይ ገቢ ግብር
🟠የንግድ ሥራ ገቢ ግብር

የሌሎች ገቢዎች ግብር

🔵ቀጥታ ያልሆኑ ታክሶች

የተጨማሪ እሴት ታክስ ( Value Added Tax )
ኤክሳይዝ ታክስ ( Excise Tax )
ተርን ኦቨር ታክስ ( Turnover Tax )
የቴምብር ቀረጥ ( Stamp Duty )
የጉምሩክ ቀረጥ (Customs Duty )
ሱር ታክስ ( Surtax )

በድረ ገጽ፦ www.mor.gov.et ገቢያች
Telegram
https://t.me/AleHig

Telegram_Group
https://t.me/AleHig_Group

Facebook Page
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

LinkedIn
https://www.linkedin.com/company/alehig/

YouTube
https://www.youtube.com/@Ale_Hig

TikTok
https://www.tiktok.com/@alehigofficial

Instagram https://www.instagram.com/alehigofficial

Twitter /X
https://x.com/AlehigOfficial?t=yFRauAZ7v70Je2MEPIGGsQ&s=09

official website
https://www.alehig.com

#LegalAwareness #AleHig #LegalUpdates #AccessToJustice
October 7, 2024
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የዋቢ የምዝገባ ሂደት

ጠበቃ ኖት? አሁኑኑ ይመዝገቡ፤ ዋቢን መጠቀም ይጀምሩ!

ዋቢ ላይ መመዝገብ ቀላል ነው! የዋቢ ድህረ ገፅ ላይ በመሄድ እነዚህን ቅደም ተከተሎች ይከተሉ:

በመጀመሪያ ወደ ዋቢ የምዝገባ ገጽ ይሂዱ: https://wabilaws.com/am/users/sign_up

1. ባለ ሶስት መስመር ማውጫውን ይጫኑ
2. ይግቡ የሚለውን ይጫኑ
3. እንደ ጠበቃ ይመዝገቡ
4. መረጃዎትን ያስገቡ - ይመዝገቡ
5. በኢሜይል የተላከውን የአካውንት ማረጋገጫ ሊንክ ይጫኑ

ዋቢን ይጎብኙ!
Wabilaws.com

የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችን ይከታተሉ!

Facebook:
https://www.facebook.com/profile.php?id=61562959684020
Instagram:
https://www.instagram.com/wabi_laws?igsh=aWR0M3ZqMWZnemcx&utm_source=qr
LinkedIn:
https://www.linkedin.com/company/wabilaws/
Telegram:
https://t.me/WABI_laws

ማሳሰቢያ:
ይሄ ድህረ-ገፅ የአዋጅ 1249/2021 መሠረት በማድረግ የተቋቋመ ሲሆን በአዋጁ የተከለከለውን በአገናኝ የሚደረግ የጥብቅና አገልግሎት በማይፃር መልኩ ይሰራል። ዋቢ ከጠበቃውም ሆነ ከደንበኛው እንደ አገናኝ ምንም አይነት ክፍያ አይቀበልም ።
October 7, 2024
Forwarded from ስለፍትሕ (Licensed Lawyer Mikias Melak 🔊 ጠበቃና የሕግ አማካሪ ሚኪያስ መላክ)
ከንግድ አሰራር ጋር በተያዘ  የሚደረጉ ለውጦች 


መመርያ  143/2011  አንቀጽ 4  መሰረት 
ለውጦችን  ማሳወቅ 
4 ታክስ ከፋዩ የሚያሳውቃቸው ለውጦች


1/ ማንኛውውም  ታክስ ከፋይ ከዚህ በታች የተመለከቱትን  ለውጥ ሲያደርግ ለውጡ በተደረገ  በ30 (በሰላሳ) ቀናት ውስጥ ለሚኒስቴሩ በጽሁፍ  ማሳወቅ አለበት፡ 
ሀ) በንግድ ድርጅት ስያሚ የተደረገ ለውጥ
ለ) በድርጅት ስም የተመዘገበ
  (1) ቋሚ የንግድ ስራ ፣የቢሮ እና የመኖርያ ቤት አድራሻ ለውጥ ፣
(2) በማምረቻ ቦታ  ወይም ታክስ ከፋዩ በሚጠቀምበት መጋዘን ላይ ተደረገ የአድራሻ ለውጥ
(3)በፖስታ ወይም በመደበኛ እና በተንቀሳቃሽ ስልክ ፣ፋክስ ወይም ኢ-ሜይል አድራሻ ላይ የተደረገ ለውጥ
ሐ) በዋንኛ የስራ እንቅስቃሴው ወይም  በቅርንጫፍ ወይም በንግድ ሥራው ዘርፍ ወይም መስክ ላይ የተደረገ ለውጥ
መ) በድርጅቱ መተዳደርያ ደንብ ወይም የመመስረቻ ጽሑፍ የሽርክና ስምምነት  ላይ የተደረገ ለውጥ
ሠ) በአክስዮን ባለድርሻ  አባላት ላይ የተደረገ ለውጥ ፣
ረ) በድርጅቱ  ወይም በታክስ አንደራሴው የባንክ ሂሳብ ወይም የባንክ ቅርጫፍ አድራሻ ላይ የተደረገ ለውጥ
ሰ) በታክስ እንደራሴው እና ከሚንስቴሩ ጋር ግንኙነት በሚደረግበት የኤሌክትሮኒክስ አድራሻ ላይ  የተደረገ ለውጥ
ሸ በተመዘገበና በተከፈለ ካፒታል ላይ የተደረገ ለውጥ
ቀ) የንግድ ስራው በከፊል  ወይም በሙሉ በማቋረጥ  በሽያጭ ወይም በስጦታ በማስተላለፍ ወይም በመለወጥ ወይም በዋስትና በማስያዝ በድርጅቱ ላይ የተደረገ ለውጦች 
በ )የንግድ ስራ ወኪል በታክስ አንደራሴው የተደረገ ለውጥ ፣
ተ) የአክስዮን ትረፍ ድርሻ ለካፒታል ማሳደጊያ ሲውል ፣
ቸ የገቢ ምንጭ መቋረጥን ወይም መሻሻልን በተመለከተ
(1)  የቤት ወይም የህንጻ ወይም ወይም የመጋዘን ኪራይ ውል ሲቋረጥ ወይም ሲሻሻል ፣
(2)   በተሸከርካሪ ወይም በኮንስትራክሽን መሳርያዎች ወይም ሌሎች  የካፒታል ወይም የንግድ ስራ እቃዎች የተደረገ የኪራይ ውል መቋረጥ ወይም መሻልሻ ፣

(3)  በራስ ገቢውን የሚስታወቅ ተቀጣሪ ስራውን ሲለቅ ወይም ሲቀየር ወይም የደሞዝ ለውጥ ሲኖር
(4)  የንግድ ስራ አንቅስቃሴው በጊዚያውነት ወይም በቋሚነት ሲቋረጥ ወይም ሲሻሻል ፣
ኃ) ታክስ ከፋዩ ሰራተኛ ሲጨምር ወይም ሲቀንስ ወይም የሰራተኞች የደሞዝ ለውጥ ሲያደርግ ፣
2/ ታክስ ከፋዩ በዚህ አንቀጽ  ንዑስ አንቀጽ (1) ከተዘረዘሩት ለውጦች የተለየ ለውጥ ማሳወቅ ያለበት ሆኖ ሲገኝ  ሚኒስቴሩ የለውጡን አይነት በሰርኩላር ያሳውቃል ፡፡
ለተጨማሪ ሙሉ መመሪያውን ይመልከቱ” ከንግድ አሰራር ጋር በተያዘ  የሚደረጉ ለውጦች  ” መመርያ  143/2011  ያንብቡ
 
Ministry of Revenues, Addis Ababa. @AboutJustices
https://t.me/AboutJustices
October 7, 2024
ከጠበቃ እና የሕግ አማካሪ የሕግ ምክር እና አማራጭ የሕግ እውቀት መረጃ፣ በቴሌግራም ቤተሰብ ይሁኑ👇 https://t.me/AleHig
ለተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ እና  ማብራሪያዎች ያገኛሉ +251920666595
alehig.com
ወይም
https://linktr.ee/alehig
October 8, 2024
ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሬጅስትራሮችን ለመቅጠር ማስታወቂያ አውጥቶ ምዝገባ ያካሄደ መሆኑ ይታወቃል፡፡
ስለሆነም ከዚህ በታች ስማችሁ የተዘረዘረው ተመዝጋቢዎች ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም የጽሁፍ ፈተና ስለሚሰጥ ማንነታችሁን የሚገለጽ መታወቂያ በመያዝ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ግቢ ውስጥ ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት ላይ ተገኝታችሁ ፈተናውን እንድተወስዱ እያሳወቅን በፈተናው ወቅት የኤሌክትሮኒክስ መሣሪያዎችን መጠቀም የማይቻል መሆኑን እንገልጻለን፡፡
Telegram
https://t.me/AleHig

Telegram_Group
https://t.me/AleHig_Group

Facebook Page
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

LinkedIn
https://www.linkedin.com/company/alehig/

YouTube
https://www.youtube.com/@Ale_Hig

TikTok
https://www.tiktok.com/@alehigofficial

Instagram https://www.instagram.com/alehigofficial

Twitter /X
https://x.com/AlehigOfficial?t=yFRauAZ7v70Je2MEPIGGsQ&s=09

official website
https://www.alehig.com

#LegalAwareness #AleHig #LegalUpdates #AccessToJustice
October 9, 2024
የሞት ቅጣት በአለም አቀፍ ደረጃ እንዲወገድ ጥሪ ቀረበ።

የአውሮፓ ህብረት እና የአውሮጳ ምክር ቤት በጋራ በሰጡት መግለጫ ሁለቱ ተቋማት በሁሉም ጉዳዮች ላይ የሞት ቅጣትን እንደሚቃወሙ አረጋግጠዋል።

ድርጊቱን ኢሰብአዊ እና የሰብአዊ ክብር ጥሰት ሲሉ አውግዘው የሞት ቅጣት በአለም አቀፍ ደረጃ እንዲወገድ ጠይቀዋል።

አሁንም የሞት ቅጣት እየፈጸሙ ያሉ ጥቂት የማይባሉ ሃገራት ቅጣቱን በማስቀረት እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

የአውሮፓ ህብረት ከፍተኛ ተወካይ ጆሴፕ ቦረል እና የአውሮፓ ምክር ቤት ዋና ፀሃፊ አላይን ቤርሴት የሞት ቅጣት የመቀነስ አለም አቀፋዊ አዝማሚያ ቢታይበትም አሁንም በተለያዩ ሀገራት ቅጣቱ መቀጠሉ እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል።

በ2023 የሞት ቅጣት የፈጸሙ ሀገራት ቁጥር ዝቅ ማለቱን ጠቅሰው "ከሁለት ሶስተኛ በላይ የሚሆኑት ሀገራት የሞት ቅጣትን በህግ ወይም በተግባር ሰርዘዋል" ብለዋል።

ይሁን እንጂ መግለጫው አምስት አገሮች ማለትም ቻይና፣ ኢራን፣ ሳዑዲ አረቢያ፣ ሶማሊያ እና ዩናይትድ ስቴትስ በሞት በመቅጣት ከቀዳሚዎቹ  ሃገራት መካከል እንደቀጠሉ አመልክቷል።

ከተላለፉ እና ተፈጻሚ ከሆኑ የሞት ቅጣቶች ውስጥ 74 በመቶ የተፈጸሙት በኢራን ነው።

የአውሮፓ ህብረት እና የአውሮፓ ምክር ቤት በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ አዲስ እና አወዛጋቢ የሞት ቅጣት መፈጸሚያ የሆነውን የናይትሮጅን ሃይፖክሲያ አጠቃቀምን በተመለከተ ስጋታቸውን ገልጸዋል።

መግለጫው አሁንም የሞት ቅጣት የሚቀጣባት ብቸኛዋ አውሮፓዊት ሀገር ቤላሩስ መሆኗን አመልክቷል።

የሞት ቅጣት ወንጀልን እንደሚከላከል የሚያምኑ በርካታ ሃገራት ቢኖሩም የአውሮፓ ህብረት እና የአውሮፓ ምክር ቤት አደረኩት ባሉት ጥናት የሞት ቅጣት በወንጀል ቅነሳ ላይ የሚያመጣው ለውጥ አነስተኛ ወይም ምንም ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ የሞት ቅጣት ፍርድን በህጋቸው ከሚያስተናግዱ ሀገራት አንዷ ናት። ሞት ቅጣት ፍርድ ተገቢ ነው ብለው ያምናሉ?


@tikvahethmagazine
October 10, 2024
#ሪልስቴት

ያልተገነባ ቤት / ግንባታ ከማከናወናቸው በፊት ቤት የሚሸጡ ሪል ስቴት አልሚዎች የሚሰበስቡትን ገንዘብ በዝግ አካውንት እንዲያስቀምጡ ሊገደዱ ነው ፤ በተጨማሪ ግንባታው 80 በመቶ ላይ ያልደረሰን ቤት ለደንበኞች እንዳያስተላልፉ ሊከለከሉ ነው።

ይህንም የሚመለከት ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ ቀርቧል።

አዲሱ ረቂቅ አዋጅ ምን ይላል ?

ቤት ለመገንባት የመሬት የይዞታ ማረጋገጫ እና የግንባታ ፈቃድ ያላገኙ የሪል ስቴት አልሚዎች ደንበኞችን #እንዳይመዘግቡ እና #ቅድመ_ክፍያ እንዳይሰበስቡ ይከለክላል።

በአሁኑ ጊዜ ባለው አሠራር መሠረት የንግድ ፈቃድ በማውጣት ብቻ ወደ ሪል ስቴት ገበያው ሲቀላቀሉ የነበሩት አልሚዎች፤ በአዲሱ ረቂቅ አዋጅ " የብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ " የማውጣት ግዴታ ተጥሎባቸዋል። የአገር ውስጥም ሆነ የውጭ ባለሀብት ሪል ስቴት አልሚዎች ይህንን ፈቃድ ለማግኘት ቢያንስ 50 ቤቶችን ገንብተው የሚያስከረክቡ መሆን አለባቸው።

የአገር ውስጥ እና የውጭ አልሚዎች ግንባታውን ለማከናወን የሚያስፈልገውን " የፋይናንስ አቅርቦት ምንጭ " የማቅረብ ቅድመ ሁኔታ ተቀምጦባቸዋል። ይሁንና ረቂቁ፤ " የቅድሚያ ቤት ሽያጭ ተጠቃሚነት " መብትን ከቅድመ ሁኔታ ጋር ለአገር ውስጥ ባለሀብቶች ሰጥቷል።

ይህ አሠራር የሪል ስቴት አልሚዎች የቤት ግንባታውን ሳያከናውኑ ወይም በሂደት ላይ እያለ ለግንባታው የሚውልን ፋይናንስ የሚያሰባስቡበት እና ገንዘቡብ ለግንባታው የሚያውሉበት መንገድ ነው።

የቤት ግንባታው ሳይከናወን በፊት ከገዢዎች ጋር ውል ማሰር እና ክፍያ መፈጸም ኢትዮጵያ ውስጥ በሪል ስቴት ልማት ላይ በተሰማሩ አልሚዎች በኩል የተለመደ አሰራር ነው።

አዲሱ ረቂቅ አዋጅ፤ በዚህ ዓይነት መልኩ ለግንባታ የሚውለውን ሀብት ማሰባሰብ የሚፈልጉ አልሚዎች " አግባብ ካለዉ አካል ፈቃድ ማቅረብ " ይጠበቅባቸዋል። ይህም ግዴታ ነው።

የቅድመ ሽያጭ ዘዴን መጠቀም የሚፈልጉት ሪል ስቴት አልሚዎች፤ ከቤት ገዢዎች የሚሰበስቡት ገንዘብ የሚቀመጥበት የባንክ ሂሳብ እና የገንዘብ አወጣጥ ላይም አስገዳጅ አሠራር በረቂቅ አዋጁ ተጥሎባቸዋል።

አልሚዎቹ ከቤት ገዢዎች የሚሰበስቡትን ገንዘብ " የዝግ የባንክ ሂሳብ ገቢ ማደረግ ወይም ማስያዝ " እንዳለባቸው ረቂቅ ሕጉ ላይ ሰፍሯል።

አዲሱ ሕግ፤ ገንዘቡ የሚቀመጥበት ዝግ የባንክ አካውንት የሚከፈተው " አግባብ ባለው አካል ፈቃድ መሠረት " እንደሆነም ያስረዳል።

በዝግ የባንክ ሂሳብ ገቢ የተደረገው ገንዘብ የሚለቀቅበት ሁኔታ ከረቂቅ አዋጁ መፅደቅ በኋላ በሚወጣ ደንብ ይወሠናል።

ከዚህም ባሻገር በቅድሚያ የተሸጠው ቤት ተገንብቶ ለተጠቃሚዎች እስከሚተላለፍ ድረስ የቤት የመሥሪያ ቦታው የይዞታ ማስረጃ " በሚመለከተው አካል እንዳይሸጥ፣ እንዳይለወጥ " እንደሚታገድ ረቂቁ ይገልጻል።

ቤት ቀድመው በሚሸጡ ሪል ስቴት አልሚዎች ላይ እነዚህ አስገዳጅ አሠራሮች የተቀመጡት " ደንበኞች የሚደርስባቸውን እንግልት እና ኪሳራ ለመቀነስ በማሰብ " እንደሆነ የአዋጁ ማብራሪያ ያስረዳል።

ረቂቅ አዋጁ በሪል ስቴት አልሚዎች ላይ ሌሎችንም ግዴታዎች ጥሏል።

በረቂቁ መሠረት፤ የሪል ስቴት አልሚዎች ግንባታው 80 በመቶ ላይ ያልደረሰን ቤት ለደንበኞች እንዳያስተላልፉ ተከልክለዋል።

" ያለደንበኛው ፍላጎት እና ፈቃድ አጠቃላይ ግንባታው ቢያንስ 80 በመቶ ያልተጠናቀቀ ቤት ለደንበኞች ሊያስተላልፍ አይችልም " ይህንን ለማድረግ በቅድሚያ ደንበኛው መስማማት እንዳለበት ያመለክታል።

ሪል ስቴት አልሚዎች ቤት ገዢዎችን መመመዝገብ እና ቅድመ ክፍያ መሰብሰብ የሚችሉበት ጊዜም ቅድመ ሁኔታ ተቀምጦበታል።

አልሚዎች ምዝገባ ማድረግ እና ክፍያ መሰብሰብ የሚችሉት " የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ እና የግንባታ ፈቃድ ከሚመለከተው አካል ከተረከቡ " በኋላ ነው።

" በሕጋዊ መንገድ የተረከበው መሬት ሊያስተናግድ ከሚችለዉ የቤት ደንበኛ በላይ መመዝገብ አይችልም " የሚለውም ሪል ስቴት አልሚዎች ላይ ከተቀመጡት ግዴታዎች መካከል ነው።

ለሪል ስቴት ልማት አሠራር የሚዘረጋው አዲሱ አዋጅ፤ ከግዴታዎች ባሻገር አልሚዎች ከመንግሥት " መሬት በስፋት " ማግኘት የሚችሉበትን ሂደትም ያስቀመጠ ነው።

ከመንግሥት መሬት " በስፋት " የሚቀርብላቸው አልሚዎች ረቂቁ ላይ ከተጠቀሱ ሦስት ቅድመ ሁኔታዎች ውስጥ ቢያንስ አንዱን ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።

ከእነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች መካከል በብዛት ቤቶችን መገንባት እና ከእነዚህ ቤቶች ውስጥ " 40 በመቶውን ዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ላላቸው የማኅበረሰብ ክፍል ተደራሽ " ማድረግ የሚለው አንዱ ነው።

ይህንን ቅድመ ሁኔታ የሚከተሉ አልሚዎች የሚገነቡበት ቤት ብዛት " እንደ ከተሞች ደረጃ በአንድ ጊዜ ከ500 እስከ 5 ሺህ " ሊሆን እንደሚችል በረቂቁ ላይ ተጠቅሷል።

መንግሥት በአዲስ አበባ ከተማ መሬት " በስፋት " የሚያቀርበው " በአዲስ አበባ ከ5 ሺ በላይ ቤት ለሚገነባ እና ለሚያስተላልፍ " አልሚ እንደሆነ ረቂቁ ላይ ሰፍሯል።

በሌሎች ከተሞች መሬት " በስፋት " የሚቀርበው እደሚኖራቸው " ተጨባጭ የቤት ፍላጎት " ሲሆን፣ " ኢንዱስትሪ ፓርክ ያለበት አካባቢ ባሉ ከተሞች " ደግሞ ከአንድ ሺህ በላይ ቤቶችን ለሚገነቡ አልሚዎች እንደሚቀርብላቸው ረቂቁ ያስረዳል።

ከመንግሥት መሬት " በስፋት " ማግኘት የሚፈልጉ አልሚዎች የተቀመጠባቸው ሌሎች ቅድመ ሁኔታዎች ከውጭ ምንዛሬ ጋር የተገናኙ ናቸው።

በአገር ውስጥ " በጥራት እና በብዛት የማይገኙ " ግብአቶችን በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ (ፍራንኮ ቫሉታ) የሚያስገቡ እንዲሁም የሚያገኙትን ትርፍ እስከ አስር ዓመት ከአገር ሳያወጡ አገር ውስጥ መልሰው የሚጠቀሙ አልሚዎች የዚህ አሠራር ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ረቂቁ ላይ ሰፍሯል።

" የሪል ስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይት እና ግመታ " የተሰኘው ይህ ረቂቅ አዋጅ የቀረበለት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለተጨማሪ ዕይታ ወደ ከተማ፣ መሠረተ ልማት እና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምፅ መርቶታል።

መረጃው ከቢቢሲ አማርኛ የተወሰደ ነው።

@tikvahethiopia
October 10, 2024
#NewsUpdate: የፌደራል ፍርድ ቤቶች የ2017 ዓ/ም የዳኝነት የስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በ6 ኪሎ ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተካሂዷል።

ፍርድ ቤቶች ከነሀሴ 1/ 2016 ዓ/ም ጀምሮ እስከ መከረም 30/ 2017 ዓ/ም ለሁለት ወራት በከፊል ዝግ ሆነው የቆዩ ሲሆን ዛሬ ጥቅምት 1 በይፋ መከፈታቸው ተበስሯል።
#tikvahethmagazine
Telegram
https://t.me/AleHig

Telegram_Group
https://t.me/AleHig_Group

Facebook Page
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

LinkedIn
https://www.linkedin.com/company/alehig/

YouTube
https://www.youtube.com/@Ale_Hig

TikTok
https://www.tiktok.com/@alehigofficial

Instagram https://www.instagram.com/alehigofficial

Twitter /X
https://x.com/AlehigOfficial?t=yFRauAZ7v70Je2MEPIGGsQ&s=09

official website
https://www.alehig.com

#LegalAwareness #AleHig #LegalUpdates #AccessToJustice
October 11, 2024
Forwarded from ሕግ ቤት
International Organization for Migration(IOM) would like to invite qualified and competent applicants to apply for the following vacant post

Position: 1. Project Associate

Position: 2. National Officer

https://g.co/kgs/C1SvG96
October 11, 2024
#Passport
የፖስፖርት የግዜ ቆይታ ከ5 ዓመት ወደ 10 ዓመት ከፍ ሊል ነው.....
October 12, 2024