አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
Follow our LinkedIn page:
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.linkedin.com/company/lawsocieties/
አቤቱቱታ ስለ ማሻሻል - የፍትሐ ብሔር ሥነ-ሥርአት ህግ ቁጥር 91

አቤቱታ ማለት ለፍርድ ቤት የሚቀርብ ክስ/መልስ/ይግባኝ/ወይም ሌላ ማንኛውም አይነት አንድ ባለ ጉዳይ ከፍ/ቤት የሆነ ዳኝነት እንዲወሰንለት በመጠየቅ የሚያቀርበው ማመልከቻ ነው፡፡

አቤቱታ ላይ ያቀረበው ሰው የሚጠየቅው ዳኝነት እና ይህንን ዳኝነት ሊያገኝ የሚገባውን ጉዳይ አብራርቶ መጠየቅ ያለበት ሲሆን ክስ ከቀረበ በኋላ ወይም ጉዳዩ ከጀመረ በኋላ በአቤቱታው ላይ መገለጽ የነበረበት እና አለመገለጹ ባለ ጉዳዩን የሚጎዳ፤ ትክክለኛ ውሳኔ እንዳይሰጥ ሊያደርግ የሚችል እና ለፍትህ አሰጣጥ የሚስቸግር ከሆነ ባለ ጉዳዩ ይህንን አቤቱታ አሻሽሎ ወይም የተጓደለውን አሟልቶ እንዲያቀርብ እንዲፈቀድለት ለፍ/ቤት ሊያመለከት ይቻላል፡፡

አቤቱታ ሲሻሻል ነገሩን በይበልጥ ወይም በተሻለ መንገድ ማብራራት እንጂ በመጀመሪያው ዳኝነት ላይ ያልተጠየቀ እና ፈጽሞ የተለየ ጉዳይ ወይም ዳኝነት ይፈጸምልኝ የሚል ጥያቄ ማቅረብ አይቻልም፡፡
ነገረ ፈጅ Negere Fej
Alternative legal enlightenment (ALE)አለ
አማራጭ የሕግ እውቀት፣
ነፃ የሕግ ምክርና ድጋፍ ሰጪ ሕግ ባለሙያዎች፣ የተለያዩ የሕግ ማብራርያ ያገኛሉ 🔴

#አለሕግ #Alehig

👉Telegram Channel 👈
https://t.me/lawsocieties

👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/

👉YouTube 👈
https://www.youtube.com/@Ale_Hig
Screenshot_20240126-171710.png
53.5 KB
የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ምድብ ችሎቶች እና አድራሻቸው
ሰ/መ/ቁጥር 211167 ሚያዝያ 28 ቀን 2014 ዓ/ም
@Abrham Yohanes
የሙና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 13 (1) እና (2) ባለማድረግ (Omission) ይልቅ በማድረግ (Comission) የተፈጸመ ወንጀልን ለመቅጣት የተደነገገ ነው።

የሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 13(2) በአንቀፅ 13(1) ከፊደል ሀ እሰከ ሐ የተመለከቱን ዝርዝር የህግ ነጥቦች መሰረት በማድረግ የከበደ የወንጀል ሀላፊነትን ለመጣል የተቀመጠ ሲሆን አንቀፅ 13(1) ከፊደል ሀ እስከ ሐ የተመለከቱትን ዝርዝር ሁኔታዎች ጥቅም መውሰድን ወይም ጥቅም የሚያስገኝን ውል መዋዋልን፤ ውል ማቋረጥን፤ የመንግስት ወይም የህዝባዊ ድርጅትን ጥቅም የሚጎዳ ተግባርን መፈፀምን ለመቅጣት የተደነገጉ መሆናቸው አንቀፅ 13 ከመነሻውም ካለማድረግ (Omission) ይልቅ ማድረግን (Comission) ለመቅጣት በህጋችን የተካተተ መሆኑን ያሳያል፡፡

ስለሆነም ተከሳሹ በስራ ሀላፊነቱ መሰረት ሊከታተለውና ሊቆጣጠረው ሲገባ ግዴታውን ባለመወጣት የደረሰ ጉዳት በአዋጁን አንቀፅ 13(2) መሰረት የወንጀል ክስ ከቀረበ የህጉን ዝርዝር ሁኔታ መሰረት ያላደረገ ክስ ነው።
በስራ መዘርዝር መሰረት የመከታተልና የመቆጣጠር ሀላፊነትን ባለመወጣት የሚፈጸም ወንጀል የሚያስጠይቀው በወ/ህ/አ.420(2) መሰረት የስራ ሀላፊነትን ባለመወጣት የወንጀል ድርጊት እንጂ በጸረ-ሙስና አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 13(2) አይደለም
የፍትሐብሔር_ጉዳዮችን_የሚመለከቱ_ፎርሞች.doc
1.2 MB
የፍትሐብሔር ጉዳዮችን የሚመለከቱ ከ180 በላይ የክስ፣ የመልስ፣ የይግባኝ፣ የአፈጻጸም፣ የሰበር፣ የውሳኔ እና የትዕዛዝ ፎርሞች፡፡
#ነገረሕግ
እሁድ እሁድ ስናካሂድ የነበረውን ከምሽቱ 2:30 የእሁድ ችሎት ነፃ ውይይት፣
Anonymous Poll
79%
እንደገና ይጀምር
3%
አሁን ጊዜው አይደለም
4%
ትንሽ ይቆይ
3%
በፍፁም አያስፈልግም
26%
መቋረጥ አልነበረበትም
ሰ/መ/ቁ/211987
ለግዴታ አፈጻጸም ዋስ የሆነ ሰው ባለዕዳው ግዴታውን ባለመፈጸሙ ምክንያት ዕዳውን ለባለገንዘቡ ሲከፍል ወለድ እና ወጪ ሊጠይቅ የሚችለው ከባለገንዘቡ ጋር ክርክር ተደርጎ ዋሱ ከዋናው ገንዘብ በተጨማሪ ወለድ እና ወጪ ጨምሮ መክፈሉ ሲረጋገጥ ነዉ፡፡ በተጨማሪም ዋሱ የኪሳራ ጥያቄ ሊያቀርብ የሚችለው ለባለዕዳው ማስጠንቀቂያ መስጠቱ እንዲሁም በባለእዳዉ በኩል የተፈጸመ ጥፋት ወይም ቸልተኝነት መኖሩን ጭምር በማስረዳት ነው።
አብርሃም ዮሀንስ
CMSPs.pdf
593 KB
የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎችን
በተመለከተ የቀረበ አጭር ማብራሪያ
መግቢያ


የኢትዮጰያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን በካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/2013 ከተሰጡት ስልጣንና ተግባራት መካከል ቁጥጥር ለደረግባቸው የሚገቡ የካፒታል ገበያ ተግባራትን መወሰን፣ ስካIta ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃደ መስጠት እና ስራቸውንም መቆጣጠር ይ7ኝበታል፡፡

በዚህም መሰረት ባለሰልጣኑ ለካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ የሚሰጥበትና የሚቆጣጠርበትን መመሪያ አዘጋጀ±ል፡፡ "phIta ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች የፈቃድ አሰጣጥና ቁጥጥር መመሪያ ቁጥር 980/2016" Πλ.6.8.6tC+oon C 9 3 2016 ዓ.ም ጀምሮ ስራ ላይ ውሏል። በዚህም መሠረት ባለስልጣኑ በቅርቡ የአገልግሎት ፈቃድ ማመልከቻዎችን መቀበል ይጀምራል፡፡

ይህን በማስመልከt በዚህ አጭር ጽሁፍ የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ምን ማለት ነው ፣ ምን ምን ተግባራትን ያከናውናሉ፣ ምን አይነት ሀላፊነቶች አስባቸው፣ ፈቃድ ለማግኘትስ ምን አይነት መሰፈርቶችንና መመዘኛዎችን ማሟላት ይጠበቅባቸዋል የሚሉት ጉዳዮች ላይ አጠር ያስ ማብራሪያ ቀርቧል፡፡
Alternative legal enlightenment (ALE)
አማራጭ የሕግ እውቀት፣
#አለሕግ #Alehig
👉Telegram Channel 👈
https://t.me/lawsocieties

👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/
በአዲስ አበባ የመሬት አገልግሎቶች ታገዱ

የመሬት አገልግሎቶች መታገዳቸውን የተናገረው የአዲስ አበባ መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ እግዱ እንከ መቼ እንደሚቆይ በግልጽ አልተናገረም፡፡

በመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ የመዋቅራዊ አደረጃጀት ጥናት ተከናውኖ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ጸድቆ ወደ ተግባር እንዲገባ የተወሰነውን ውሳኔ መሰረት በማድረግ የሠራተኞች የባህሪ እና የቴክኒክ ፈተና ተሰጥቶ ውጤቱ ይፋ መደረጉን ቢሮው አስታውሷል።

በዚህም አዲስ በተጠናው መዋቅራዊ አደረጃጀት ጥናት መሰረት የሰራተኞች ድልድል ተሰርቶ እስኪጠናቀቅ ድረስ ከዛሬ ጥር 21፣2016 ዓ.ም ጀምሮ የመሬት አገልግሎቶች በጊዜያዊነት ታግዷል ተብሏል።

ቢሮው ይህን እንዲያውቁትም ለሁሉም ክፍለ ከተሞች ደብዳቤ ጽፏል፡፡

ሸገር ከዚህ በፊት በሰራው ዘገባ ፈታና የተቀመጡ የከተማዋ የመንግሰት ሰራተኞች ደልድላቸውን ባለማወቃቸው እንደ መሬት ነክ ባሉ አገልግሎቶች ሰራተኞች በስራ ገበታቸው ላይ እንዳልነበሩ መዘገቡ ይታወሳል፡፡
በቱርክ የግል ንጽህናውን አይጠብቅም የተባለው ባል በሚስቱ ክስ ተመሰረተበት

ሚስት “ባሌ በሰባት ወይም አስር ቀናት ውስጥ አንዴ ብቻ ነው ሰውነቱን የሚታጠበው፤ ላብ ላብ ይሸታል፤ አንድ ልብስን ከአምስት ቀናት በላይ ሳይቀይር ይለብሳል፤ ጥርሱንም በሳምንት አንዴ ወይ ሁለቴ ነው የሚቦርሸው” ብላለች ከሳሽ ሚስት።

በዚህም ጤናዋም ሆነ ትዳራቸው አደጋ ላይ መውደቁን በመጥቀስ ፍቺ መጠየቋ ተሰምቷል።

ዝርዝሩን በተከታዩ ሊንክ ይመለከቱ፤ https://bit.ly/3unxbpl
ማስታወቂያ

ረቂቅ መመሪያዎች ላይ አስተያየት እንድትሰጡ ስለመጋበዝ

የትምህርት ሚኒስቴር: -
1. የአጠቃላይ ትምህርት የመምህራን የደረጃ እድገት የአፈጻጸም መመሪያ፣
2. የር/መምህራን፣ የም/ር/መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች የምልመላ መረጣና ምደባ የአፈጻጸም መመሪያ፣
3. የቅድመ አንደኛና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ዕጩ ምምህራን ምልመላና መረጣ የአፈጻጸም መመሪያ፣ የሚሉ 3 መመሪያዎችን አዘጋጅቷል።
መመሪያዎቹ በተለያየ ጊዜ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት አስተያየት ሰጥተውባቸው የዳበሩ ሲሆን የፌደራል አስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ ቁጥር 1183/2012 ክፍል 2 ንዑስ ክፍል 2 አንቀጽ 10 መሰረት የሚዘጋጁ መመሪያዎች ከመጽደቃቸው በፊት ማንኛውም ሰው የሚሳተፍበት የውይይት መድረክ ማዘጋጀትና ግብዓት መሰብሰብ እንዳለበት ስለሚደነግግ ሚኒስቴሩ የውይይት መድረከ አዘጋጀቷል።
በዚህም መሰረት ጥር 30/2016 ከጠዋቱ 3:30 ጀምሮ በትምህርት ሚኒስቴር መሰብሰቢያ አዳራሽ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችና ለባለድርሻ አካላት የገለጻና የውይይት መድረክ ስለተዘጋጀ በተጠቀሰው ጊዜና ቦታ በመገኘት አስተያየት እንድትሰጡ ተጋብዛችኋል።
Forwarded from PIN NGO
https://africafoicentre.org/access-to-information-is-an-urgent-need-in-africa/

https://t.me/PublicInformationNoble

Why Access to Information is An Urgent Need in Africa

31/01/2024
Access to Information is An Urgent Need in Africa
From the national government to the county and regional rulings, the role of transparency cannot be overemphasized. It is the cornerstone for sustainable growth and inclusive development in every country.
However, in regions where access to information is still a luxury, transparency only remains better on paper than in action. And that has been the case with most African countries.

Out of the 55 African nations, 29 have already passed laws on access to information. Yet, studies show that even with the information laws in place, many have not put effort and resources into their systematic implementation, limiting the potential benefits for citizens and governments. Many of the laws have not been implemented. Yet, AFIC’s experience has proven that when implemented, access to information laws help citizens make informed participation in government policies and programmes, resulting in better service delivery by governments. According to a research article on access to government information trends, nearly half of African countries lack Freedom of Access to Information laws while most of the existing laws have restrictive clauses, hindering citizens from accessing government information.
 
As such, it’s time Africa focuses on ensuring the unhindered free flow of information both online and offline rather than failure to adopt and effectively implement access policies. This article discusses the various ways to promote transparency by enhancing information access in Africa. You will learn the challenges facing information access, the effects of poor access, and ways to promote access to information.
https://t.me/PublicInformationNoble
208865.pdf
477.1 KB
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 208865 በማኅበር ተደራጅቶ የቤት መሥሪያ ቦታ ለማግኘት በመጠባበቅ ላይ እያሉ በሥራ ወደ ሌላ ቦታ መዘዋወር ከመኖሪያ ቤት ኅብረት ሥራ ማኅበር አባልነት የሚያሰርዝ ስላለመሆኑ የሰጠው አስገዳጅ የሕግ ትርጉም፡፡
#ethiolawreview
👎🏿#አለሕግ አካታች መሰረተ ልማት ለህዝባችን! #share #ሼር!
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
በኢትዮጵያ ውስጥ የሕጎች ሁሉ የበላይ የሆነው የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀፅ 17 በሕግ ከተደነገገው ሥርዓት ውጪ ማንኛውም ሰው ነፃነቱን እንደማያጣ ይደነግጋል።
በተጨማሪም ማንኛውም ሰው በሕግ ከተደነገገው ሥርዓት ውጪ ሊያዝ፣ ክስ ሳይቀርብበት ወይንም ሳይፈረድበት ሊታሰር እንደማይችል በግልፅ ይደነግጋል።
ኢትዮጵያ ተቀብላ ያፀደቀችው የሲቪል እና የፖለቲካ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃል ኪዳን (ICCPR) አንቀፅ 9 ማንኛውም ሰው ነፃነቱ እና ደህንነቱ ተከብሮ የመኖር መብት እንዳለው እና በዘፈቀደ ከሚደረግ እስር ሊጠበቅ እንደሚገባ ይደነግጋል።
ሕግ አስከባሪዎች ማንኛውም ሰውን በቁጥጥር ስር ከማዋላቸው በፊት የዜጎች ነፃነትን ለመጠበቅ የወጡ ሕጎች የጣሉባቸውን ግዴታዎች በሙሉ መሟላታቸውን ማረጋገጥ ይጠበቅባቸዋል።

ምስል-በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የተቀናበረ
#AHRE( Association for Human Rights in Ethiopia)

Alternative legal enlightenment (ALE)አለ
አማራጭ የሕግ እውቀት፣🔴ሕግ

#አለሕግ #Alehig

👉Telegram Channel 👈
https://t.me/lawsocieties

👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/

👉YouTube 👈
https://www.youtube.com/@Ale_Hig

ይህ ጽሁፍ ለጠቅላላ እውቀት ብቻ ነው።
ለበለጠ መረጃ የሕግ ባለሙያ/ጠበቃ ያማክሩ!
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ከመጪው ሰኞ ጀምሮ ፈቃድ መስጠት እንደሚጀመር ገለፀ

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ከየካቲት 4 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ፈቃድ መስጠት እንደሚጀምር አስታውቋል፡፡

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ ድርጅቱ ከተቋቋመ ጊዜ አንስቶ ራሱን በማደራጀት የሕግ ማዕቀፍ ሲያዘጋጅ መቆየቱን የገለፁ ሲሆን አሁን ላይ የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አሰጣጥና ቁጥጥር መመሪያ በማዘጋጀት ወደ ሥራ መግባቱን ገልፀዋል።

በዚህ መሰረትም በዘርፉ ሥራ ላይ የሚገኙ አካላት ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ መመዝገብ እንደሚችሉ የተገለፀ ሲሆን ባለስልጣኑ 15 አዳዲስ ፈቃዶች መስጠት እንደሚጀምር ተጠቁሟል።

በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ለኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ መስጠት እንደሚጀመርም የተገለፀ ሲሆን የመንግስት የልማት ድርጅቶችም በዚህ ማዕቀፍ ለመካተት ዝግጅት ማድረጋቸውን ተመላክቷል።

ሶስት ትላልቅ የውጭ ኢንቨስትመንት ባንኮች መስራት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ጥያቄ አቅርበው ምላሽ እንደተሰጣቸውም ነው የተገለፀው።
#TikvahethMagazine
https://t.me/lawsocieties