አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የደምዳሚ (ድምዳሜ) ማስረጃ /conclusive evidence/ 5 የሰበር ችሎት ትርጓሜዎች

1//// የተሟላና ሙሉ ዕምነት የሚጣልበት ማስረጃ

የልዩ አዋቂ /expert/ የሚደርስበት የመጨረሻ አስተያየት ከሚኖረው ሙያዊ ዕውቀት አድማስ፣ ከሚታገዝበት መሣሪያና ከመሳሰሉት ጋር የተሟላና ሙሉ ዕምነት የሚጣልበት ማስረጃ /conclusive evidence/ ሊሆን ስለማይችል በዓይን ምስክሮች የተነገረን ፍሬ ነገር ለማስተባበል የሚያበቃ አቅም አይኖረውም፡፡
ሰ/መ/ቁ. 43453 ቅጽ 12

የትራፊክ ፖሊስ የአደጋ ፕላን ሪፖርት የባለሙያ ሙያዊ አስተያየትን በወረቀት ላይ ስዕላዊ በሆነ መንገድ የሚያስቀምጥ በባለሙያ የሚረጋገጥ ሰነድ በመሆኑ እንደ ማንኛውም የልዩ አዋቂ የምስክርነት ቃል በተገቢው መንገድ ሊመዘን የሚገባው የማስረጃ አይነት እንጅ ሁልጊዜ ድምዳሜ ማስረጃ (Conclusive Evidence) ያለመሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 92141 ቅጽ 17

2//// አሳሪ ማስረጃ

በአስተዳደር አካል የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ነው ተብሎ የምስክር ወረቀት መስጠት ማስረጃውን ደምዳሚ ወይም አሳሪ (Conclusive Evidence) የሚያደርገው አይደለም፡፡ ይልቁንም ይኸው ማስረጃ የተሰጠበት አግባብ በፍ/ህ/ህ/ቁ. 1195 ድንጋጌ ስር በተመለከቱት ሁኔታዎች መሰረት ስለመሆኑ ማስረዳት ከተቻለ በፍ/ህ/ቁ. 1195 ስር የተመለከተው ሕጋዊ ግምት ሊስተባበል የሚችል (rebuttable legal presumption) መሆኑን ከድንጋጌዎቹ ይዘትና መንፈስ የምንገነዘበው ጉዳይ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 64014 ቅጽ 13

3//// ማስተባበያ ሊቀርብበት የማይችል ወሳኝ ማስረጃ

አንድ ለማይንቀሳቀስ ንብረት የተሰጠ የባለሃብትነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ባለሃብትነትን በተመለከተ የህግ ግምት የሚያሰጥ ቢሆንም በሌላ ተቃራኒ ማስረጃ ሊስተባበል፣ በተቃራኒው ከሚቀርቡት ማስረጃዎች ጋር ሊመዘን የሚችል እንጂ እንጅ ማስተባበያ ሊቀርብበት የማይችል ወሳኝ /conclusive evidence/ ያለመሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡
ሰ/መ/ቁ. 67011 ቅጽ 13 

4//// የመጨረሻ ማስረጃ

የልጅነት ሁኔታ መኖሩን ማስረዳት ከተቻለ ፍ/ቤት ልጅ ነው ሲል የሕግ ግምት ሊወስድ የሚችል መሆኑን የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አንቀጽ 157/1/ ያመለክታል፡፡ ከአንቀፁ መረዳት እንደሚቻለው የልጅነት ሁኔታ መኖሩን ማረጋገጥ የመጨረሻ ማስረጃ (conclusive evidence) ሳይሆን የሕግ ግምት ብቻ ነው፡፡ ግምቱም ቢሆን አስገዳጅነት ያለው የሕግ ግምት አይደለም፡፡ ግምቱን የሚቃወም ወገን ማስረጃ በማቅረብ ማፍረስ እንደሚችል ንዑስ አንቀፅ 2 ይደነግጋል፡፡
ሰ/መ/ቁ. 42648 ቅጽ 10

5///// ክርክር ሊነሳበት የማይችል፣ ሙሉ እምነት ሊጣልበት የሚችል ማስረጃ

ልጅነት የሚረጋገጥበት ዋናው ማስረጃ የልደት ምስክር ወረቀት እንደሆነ በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ በአንቀጽ 154 ላይ ተመልክቷል፡፡ ይህ ማለት ግን የልደት ምስክር ወረቀት ክርክር ሊነሳበት የማይችል ሙሉ እምነት ሊጣልበት የሚችል /Conclusive/ ማስረጃ ነው ማለት ግን አይደለም፡፡
ሰ/መ/ቁ. 33440 ቅጽ 5
Federal Judges Code of Conduct and Disciplinary Procedure Regulation
Regulation Number 1/2013
link: bit.ly/40yp2Jy



📌📌Note
: This translation was undertaken by volunteer Year III students of Addis Ababa University School of Law for the benefit of fellow students who are not native Amharic speakers.
The degrees that make students cry: A look at the most challenging courses in the world

What are the hardest degrees in the world
1. Aerospace Engineering
2. Biomedical Engineering
3. Law 👈
4. Chartered Accountancy
5. Architecture
6. Medicine
7. Nursing
8. Dentistry
9. Psychology
10. Artificial Intelligence

Law 👈👈🙏 Respect for lawyers
Speak to any of  your friends who are studying law, and they might share with you a common complaint: there’s too much to read. 
https://www.studyinternational.com/news/hardest-degrees-in-the-world/

https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties #አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties
#የጥብቅና #ፈቃድ
የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ጥብቅና ፈቃድ፣

ምዝገባ እና ፈተና መቼ እንደሆነ እስከ አሁን የታወቀ ነገር የለም።
አዲስ ነገር ሲኖር የምናሳውቅ ይሆናል።
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties #አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties
የመሸሸግ ወንጀል

በንብረት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን አስምልክቶ በወንጀል ህጉ ከተደነገጉ በንብረት ላይ ከሚፈፀሙ ወንጀሎች መካከል የመሸሸግ ወንጀል አንዱ ነው፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ የመሸሸግ ወንጀልን ምንነት እና የሚያስከትለውን ተጠያቂነት እንመለከታለን፡፡

የመሸሸግ ወንጀል ምንነት

በወንጀል ህጉ አንቀፅ 682 መሰረት መሸሸግ ማለት ዕቃው የተገኘው በአንድ ንብረት ላይ በተፈፀመ ወንጀል ምክንያት መሆኑን እያወቁ ወይም ማወቅ ሲገባ ይህንኑ ዕቃ በመግዛትም ሆነ በተውሶ፣ በስጦታ፣ በመያዣነት መቀበል ወይም በማናቸውም ይህን በመሳሰለ አኳኋን መውሰድ፣ መገልገል፣ ማስቀመጥ ወይም መደበቅ፣ አሳልፎ መሸጥ ወይም በመሸጥና በመለወጥ ስምምነት ውስጥ አገናኝ በመሆን መርዳት እንዲሁም የወንጀል ተግባር ባስገኘው ፍሬ የመጣ መሆኑን እያወቁ በዚሁ በወንጀል ድርጊት በተገኘ ዕቃ ምትክ በልዋጭ የተገኘውን ወይም በሽያጭ ዋጋ የተገዛውን ሌላ አይነት ነገር ወይም ጥሬ ገንዘብ መቀበል ነው፡፡

በዚህ መሰረት የመሸሸግ ወንጀል ተፈፅሟል ለማለት
 ተሸሽጎ የተገኘው ዕቃ በአንድ ንብረት ላይ በተፈፀመ ወንጀል ምክንያት የተገኘ ወይም የወንጀሉ ተግባር ባስገኘው ፍሬ የመጣ መሆን
 ሸሻጊው ዕቃው በወንጀል ምክንያት መገኘቱን ማወቅ ወይም መገመት ሲገባው በቸልተኝነት ወንጀሉን የፈፀመ መሆን
 በወንጀል ተግባር የተገኘን ዕቃ የገዛ፣ የተቀበለ፣ የወሰደ፣ የተገለገለ ወይም በመሰል ድርጊት ውስጥ የተገኘ መሆን አለበት፡፡

የመሸሸግ ወንጀል የህግ ተጠያቂነት
ከላይ በተገለፀው ሁኔታ የመሸሸግ ወንጀል አስቦ የፈፀመ ማንም ሰው በቀላል እስራት ወይም ከባድ በሆነ ጊዜ ከአምስት አመት በማይበልጥ ፅኑ እስራትና በመቀጮ ይቀጣል፡፡ ድርጊቱ በቸልተኝነት የተፈፀመ እንደሆነ ከአንድ አመት በማይበልጥ ቀላል እስራት የሚያስቀጣ ይሆናል፡፡

ከባድ መሸሸግ

የመሸሸግ ወንጀል የተፈፀመው
 በሰዎች ወይም በንብረት ላይ ወንጀል ለመፈፀም የተቋቋመ ቡድን አባልነት እንደሆነ
 ወንጀል ፈፃሚው የተሰጠውን የሥራ ወይም የንግድ ፍቃድ በወንጀል የተገኘን ንብረት ለመሸሸግ ተገልግሎበት እንደሆነ
 ወንጀል ፈፃሚው የሸሸገው ንብረት የውንብድና፣ የዘረፋ፣ የባህር ውንብድና፣ የቅሚያ፣ የማስፈራራት ፍሬ መሆኑን ወይም ዕቃው የተገኘው ከመከላከያ ሠራዊት ንብረት ወይም በጠቅላላው ከመንግስት ሀብት ውስጥ መሆኑን እያወቀ እንደሆነ
ወንጀሉ ከባድ የመሸሸግ ወንጀል የሚሆን ሲሆን ፈፃሚውም አስራ አምስት አመት በሚደርስ ፅኑ እስራትና እስከ ብር ሀያ ሺህ በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ሊቀጣ እንደሚችል ተደንግጎ ይገኛል፡፡

ህብረተሰቡ በማወቅም ወይም በቸልተኝነት በእንድ የወንጀል ድርጊት አማካኝነት የተገኘን ንብረት መግዛት፣ መዋስ፣ በስጦታ ወይም በመያዣነት መቀበል ወዘተ በወንጀል የሚያስቀጣ መሆኑን በመገንዘብ ዕቃዎችን ሲገዛም ሆነ በተለያዩ መንገዶች ሲቀበል ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡

በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties #አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties
ጎረቤቶችን እንቅልፍ በመንሳት የተከሰሰው አውራ ዶሮ እንዲታረድ የናይጄሪያ ፍርድ ቤት ወሰነ

ናይጄሪያ ውስጥ ጉዳዩ ፍርድ ቤት የደረሰው ጩኸቱ ጎረቤቶችን ሰላም የነሳው አውራ ዶሮ በድምጽ ብክለት ምክንያት እንዲታረድ ተፈረደበት።

በአንድ አውራ ዶሮ ምክንያት እንቅልፍ አጣን ያሉት ናይጄሪያውያን ለፍርድ ቤት ባቀረቡት አቤቱታ ነው ባለቤቱ አውራ ዶሮውን እስከ መጪው አርብ ድረስ እንዲያርደው መወሰኑን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን የዘገቡት።

በሰሜናዊ ናይጄሪያ ካኖ ግዛት ውስጥ የሚገኘው ፍርድ ቤት ሁለት ሰዎች የአውራ ዶሮው የማይቋረጥ ጩኽት ሰላም አሳጣን፣ እንቅልፍ ነሳን በማለት ነበር የቀረበለትን ክስ ተከትሎ ነው ብይን የሰጠው።

በዶሮው እና በባለቤቱ ላይ ክስ ካቀረቡት ግለሰቦች መካከል አንዱ የሆነው ግለሰብ ዩሱፍ ሙሐመድ፣ የአውራ ዶሮው ጩኽት በቤቱ ውስጥ የሰላም እንቅልፍ የማግኘት እና የማረፍ መብቱን እንደጣሰበት ለፍርድ ቤቱ ተናግሯል።

የአውራ ዶሮው ባለቤት ኢሲያኩ ሹይቡ የቀረበውን ክስ ተከትሎ ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዳው ዶሮውን በአውሮፓውያኑ አቆጣጠር ነገ አርብ ለሚከበረው የስቅለት በዓል ለቤተሰቦቹ እንደገዛው እና ብዙ ጊዜ አለመቆየቱን ተናግሯል።

የአውራ ዶሮው ጩኽት ሰላም አሳጣን ያሉት ጎረቤቶቹም ዶሮው ለበዓሉ አርብ ዕለት የሚታረድ በመሆኑ ጥቂት ቀናት ብቻ እንዲታገሱት ጠይቋል።
https://bbc.in/3ZONkxY
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties #አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties
ታክስ የመጣል ሥልጣን

ለአንድ መንግስት ከታክስ የሚሰበሰብ ገቢ ለህልውና እጅግ አስፈላጊ በመሆኑ ታክስ የመጣልና የማስከፈል ሥልጣን ለመንግስት ብቻ የተሰጠ ሥልጣን ነው፡፡ ለግለሰብ ወይም ለሌላ አካል የዚህ ዓይነት ሥልጣን በየትኛውም ዓለም አይሰጥም ፡፡
ለፌደራል መንግስት በህገ መንግስቱ በተሰጠው ታክስ የመጣልና የማስከፈል ሥልጣን መሠረት ሁለት መሠረታዊ የታክስ አጣጣል ዓይነቶች አሉ፡-

1. ነዋሪነትን እና
2. የገቢ ምንጭን መሠረት ማድረግ ናቸው፡፡

እነዚህን መሠረት በማድረግ፡-

1. የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆኑ ሰዎች በዓለም ዙሪያ በሚያገኙት ገቢ እንዲሁም
2. ኢትዮጵያ ነዋሪ ያልሆኑ ሰዎች የኢትዮጵያ ምንጭ በሆነ ገቢ ላይ ታክስ የሚጣልባቸው ይሆናል፡፡

ነዋሪነት በሶስት ከፍሎች ይከፈላሉ

1. ነዋሪ የሆነ ሰው/ግለሰብ
2. ነዋሪ የሆነ ድርጅት
3. ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የመንግስት ተቋማት

አንድ ግለሰብ በኢትዮጵያ ውስጥ ነዋሪ ነው የሚባለው ፡-

1. በኢትዮጵያ ውስጥ ቋሚ የመኖሪያ አድራሻ ያለው ከሆነ
2. የኢትዮጵያ ዜግነት ያለውና ውጪ ሀገር በኮንሱላር በዲፕሎማቲክ ወይም በመሳሰሉት ስራ ተመድቦ የሚሰራ
3. በኢትዮጵያ ውስጥ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ሳያቀርጥ ወይም በመመላለስ ከ183 ቀናት በላይ ከኖረ ነው፡፡

አንድ ድርጅት ነዋሪ ነው የሚባለው፡-

1. በኢትዮጵያ ውስጥ ከተቋቋመ ወይም ከተመሠረተ
2. የድርጅቱ ወሳኝ የሆነ አመራር የሚያከናውንበት ስፍራ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው እንደሆነ ነው
ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት ፍሰት ማነቆ የሆኑ 80 ህጎች ማሻሻሏን አስታወቀች


የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን እንዳለው ለንግድ እና ኢንቨስትመንት አመቺ ያልሆኑ ህጎች መሻሻላቸውን አስታውቋል፡፡
https://am.al-ain.com/article/ethiopia-says-revises-investment-laws
Forwarded from የፍቅር ሰው
በየትኛውም ህግ ነው ተማሪዎች apparentship ወተው የተግባር ልምምድ ሳያደርግ የሚመረቁት
ከምንም በላይ የወራቤ ተማሪዎች ፍትህን ይፈልጋል።
በአሁኑ ሰዓት ተማሪዎቹ በመንከራተት ላይ ይገኛሉ
እንደሚታወቀው ይህ ወክት ተማሪዎች ለመውጫ ፈተና የሚዘጋጅበት ጊዜ ነው። በተፈጠረው አሳዛኝ ክስተት ከንባብ ሙድ እየወጡ ይገኛሉ።

ውድ የአለ ቤተሰቦች ለሚመለከተው አካል በማስተላለፍ እንድትተባበሩ እንጠይቃለን።
ስለሚታደርጉት ትብብር ከልብ እናመሰግናለን።
አባቱን ገድሏል የተባለው ተከሳሽ በእድሜ ልክ እስራት ተቀጣ።

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወላጅ አባቱን ገድሏል በተባለው አቶ መሐሩ ዮሐንስ በተባለ ተከሳሽ ላይ በዕድሜ ልክ ጽኑ እስራት ፍርድ አስተላልፏል።

ድርጊቱ የተፈጸመው በከምባታ ጠምባሮ ዞን በሀደሮ ጡንጦ ዙሪያ ወረዳ ሌሾ ማዞሪያ ቀበሌ ልዩ ስሙ ሙጉንጃ ተብሎ በሚጠራበት ቦታ ጥር 2 ቀን 2015 ዓ/ም ከምሽቱ 4 ሰዓት ላይ ነው።

የዞኑ ኮሙኒኬሽን ቢሮ እንዳስታወቀው ግለሰቡ ድርጊቱን ከመፈጸሙ በፊት "የሰበሰብከውን ንብረት አትበላም" እያለ ሲዝት እንደነበርና ምሽት ላይ ሟች ተኝቶ ባለበት በዘነዘና ጭንቅላቱን በመቀጥቀጥ ግድያውን መፈጸሙን ገልጿል።

አቃቤ ህግም በሰውና በሰነድ ማስረጃ አረጋግጦ ተከሳሽ ክሱን እንዲከላከል ቢታዘዝም መከላከያ ማስረጃ የሌለው መሆኑን በጽሑፍና በቃል ማስረጃ የለኝም ብሎ በማረጋገጡ ሚያዝያ 3 ቀን በዋለው ችሎት ተከሳሹ በዕድሜ ልክ ጽኑ እሥራት እንዲቀጣ ተወስኗል፡፡

@tikvahethmagazine
Ethiopia is the third most expensive country to live in based on cost of living .

The high cost of living is a major concern for many individuals and families around the world. It is an issue that affects people of all income levels and can significantly impact their quality of life. Several factors contribute to the high cost of living in a country, including economic policies, inflation, and the cost of essential goods and services.

One of the primary reasons for the high cost of living in a country is the state of its economy. Countries with a strong economy tend to have a higher cost of living due to the high demand for goods and services. This is because when people have more money to spend, they are willing to pay more for the things they need and want.

Inflation is another factor that contributes to the high cost of living. Inflation occurs when the general price level of goods and services increases over time. This means that people have to spend more money to buy the same goods and services they could buy for less in the past. Inflation can be caused by various factors, such as increases in the money supply, changes in government policies, or external factors like global supply chain disruptions.

Based on the analysis Ethiopia reason of higher cost of living is not due to strong economy which creates strong demand rather due to high inflation which rocken the economy badly.

Rank Country Cost of living index Local purchasing power
1. Senegal 46.4 21.7
2. Ivory Coast 42.7 7.8
3. Ethiopia 42.3 11.6
4. Mauritius 42.2 30.8
5. Zimbabwe 40.8 18.7
6. South Africa 37.8 83.9
7. Namibia 35.8 51.3
8. Botswana 34.4 63.6
9. Cameroon 33.6 18.4
10. Kenya 32.4 32.8

EII.
በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተዘጋጀ የፍትሐብሔር ክስ ለማቅረብ የሚከፈል የዳኝነት ክፍያ መጠንን ለማስላት የሚያስችል ሲስተም፡፡

👉  https://www.fsc.gov.et/Court-Services/Registry-Services/Court-Forms-and-Fees
አለአግባብ መበልጸግ በኢትዮጵያ ህግ
=============================⤵️
ያለአግባብ መበልፀግ ህግ የውል፣ የንብረት እና ከውል ውጭ ያለ ሃላፊነት ህግ ክፍል በተጨማሪ የፍታብሔር ግንኙነትን የሚገዛ የህግ ክፍል ነው፡፡ ይህ የህግ ክፍል የውል፣ የንብረት እና ከውል ውጪ ያለ ሃላፊነት ህጎች የማይገዙትን የሰው ግንኝኑነት ክፍተት ለመሙላት በስፋት ጥቅም ላይ የሚውል ህግ ሲሆን ከዚህ ባሻገር ይህ የህግ ክፍል የሰዎችን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ከመግዛት አኳያ ሰፊ ድርሻ ያለው ነው፡፡
ያለአግባብ መልፀግ ህግ በመሰረታዊነት የሚመነጨው ማንኛውም ሰው በሌላ ሰው ኪሳራ ወይም ጉዳት ምክንያት መበልፀግ የለበትም ከሚለው መርህ ነው፡፡ ስለሆነም ማንኛው ሰው በሌላ ሰው ጉዳት ወይም ኪሳራ ምክንያት ያለአግባብ የበለፀገ እንደሆነ ጉዳት ወይም ኪሳራ ለደረሰበት ሰው ካሳ የመክፈል ግዴታ እንደሚኖርበት ይህ የህግ ክፍል ያስገድዳል፡፡
አጠቃላይ መርሆዎች
የዚህ ህግ ዋንኛ አላማ ሰዎች በገንዘባቸው፣ በንብረታቸው እና በጉልበታቸው ላይ ሚኖራቸውን ህጋዊ መብት መጠበቅ ነው፡፡ ስለሆነም የፍታብሔር ህጋችን በቁጥር 2162 ስር ማንኛውም ሰው በሌላ ሰው የስራ ድካም ወይም የሌላ ሰው ሀብት በሆነ ነገር በመገልገል በቂ ባልሆነ ምክንያት ጥቅም ያገኘ እና ባለሀብቱ ላይ ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ ጥቅም ባገኘበት ልክ ለባለሀብቱ ወይም ጉልበቱ ለደከመው ሰው ካሳ የመክፈል ግዴታ እንዳለበት ያስቀምጣል፡፡ ይህ ድንጋጌ በስሩ የያዛቸው ነጥቦችን ስንመለከት ያለአግባብ የመበልጸግ ህግ ማንኛውም ሰው (ማለትም የተፈጥሮ ወይም የህግ ሰውነት ያለው ሰው) ላይ ተፈፃሚ የሚሆን ሲሆን እንደመጀመሪያ ቅድመ ሁኔታ በዚህ ህግ ተጠያቂ የሚሆን ሰው የገንዘብ ወይም የንብረት ጥቅም ሊያገኝ ይገባል፡፡ ይህም ማለት ጥቅሙ በንብት ላይ የተቋቋመ (right in rem) ወይም ከሌላ ሰው የሚጠየቅ መብት (right in personam) ወይም የነበረ እዳ የመሰረዝ፣ ግዴታ የመቅረት አይነት ወይም የኪሳራ መቅረት አይነት ጥቅም ሊሆን የሚችል ሲሆን ይህ ጥቅም ያለአግባብ የመበልፀግ የህግ ክፍል ስር ሊያስቀጣ የሚችለው ጥቅሙ የህሊና እርካታ ሊያስገኝ የሚችል ብቻ ሳይሆን በገንዘብ ሊለካ የሚችል ሲሆን ብቻ ነው፡፡ በተጨማሪም ይህ የተገኘው የገንዘብ ወይም የንብረት ጥቅም በሌላ ሰው የሚንቀሳቀስ ወይም የማይንቀሳቀስ ንብረት ወይም ስራ ምክንያት የተገኘ መሆን ያለበት ሲሆን ጥቅሙን ያገኘው ሰው ጥቅሙን ላገኘበት ምንም አይነት ህጋዊ ምክንያት የሌለው መሆን ይኖርበታል፡፡ ስለሆንም በዚህ የህግ ክፍል ተጠያቂ የሚያደርግ ክስ የቀረበበት ሰው ጥቅሙን ላገኘበት ማንኛውም ህጋዊ ምክንያት ያቀረበ እንደሆነ ካሳ መክፈል ግዴታ አይኖርበትም፡፡ ሌላው በህጉ የተቀመጠው ቅድመሁኔታ በተከሳሽ ድርጊት ምክንያት ከሳሽ የሚታወቅ ኪሳራ ወይም ድህነት ሊደርስበት ሚገባ ሲሆን የከሳሽ ጥቅም ማጣት (ኪሳራ) እና የተከሳሽ ጥቅም ማግኘት ምክንያት አንድ መሆን አለበት፡፡ ይህም ማለት በደረሰው ኪሳራ እና በተገኘው ጥቅም መካከል የውጤት እና የምክንያት ግንኝነት መኖር አለበት፡፡
ከላይ የተዘረዘሩ ሁኔታዎች ከተሟሉ በኋላ ሃላፊነትን የሚወስድ ሰው በምን ያህል መጠን ከሳሽን የመካስ ግዴታ አለበት የሚለውን በተመለከተ የተገኘው ጥቅም እና የደረሰው ኪሳራ እኩል በሚሆንበት ግዜ ምንም አይነት ችግር ሊገጥም አይችልም ምክንያቱም ተከሳሽ አለአግባብ የበለፀገበት መጠን እና ከሳሽ ላይ የደረሰው ጉዳት እኩል ስለሆነ በዚሁ ልክ ካሳ እንዲከፍ ይደረጋል፡፡ ሆኖም በአንዳንድ ሁኔታዎች ያለአግባብ የተገኘው ብልፅግና ከደረሰው ጉዳት ሊያንስ ወይም ሊበልጥ ይችላል፡፡ እንዲህ አይነት ሁኔታ በሚያጋጥምበት ግዜ ምንም እንኳን የደረሰው ጉዳት ከተገኘው ብልፅግና የሚያንስ ቢሆንም ህጉ በግልፅ ተከሳሽ መክፈል ያለበት ኪሳራ ያለአግባብ ባገኘው ብልፅግና መጠን መሆን እንደሚገባው ያስቀምጣል፡፡ በተመሳሳይ ያለአግባብ የተገኘው ብልፅግና ከደረሰው ጉዳት የሚያንስ ከሆነ ወይም ጉዳቱ ከብፅግናው የሚበልጥ በሚሆንበት ግዜ የተከሳሽ ተጠያቂነት መጠን በተገኘው ብልፅግና ልክ ብቻ በመሆኑ ካሳ እንዲከፍል የሚገደደውም በዚሁ መጠን ብቻ ይሆናል፡፡
በአጠቃላይ ያአለአግባብ መበልፀግ በመሰረታዊነት ሶስት ሁኔታዎችን ያካተተ ሲሆን አንድን ሰው በዚህ የህግ ክፍል በመክሰስ ካሳ ለማስከፈል እነዚህ ሶስት ሁኔታዎች በድምር መሟላት ይኖርባቸዋል፡፡ የመጀመሪያው ተከሳሽ በገንዘብ ሊለካ የሚችል ጥቅም ያገኘ መሆኑ ሁለተኛው ይህ ጥቅም የተገኘው በከሳሽ ኪሳራ ወይም ጉዳት ምክንያት መሆኑ እንዲሁም ሶስተኛው የተገኘበት መንገድ አለአግባብ ወይም ምንም አይነት ህጋዊ መንገድ/ምክንያት የማይቀርብበት መንገድ መሆኑ ናቸው፡፡
ያለአግባብ የመበልፅ ክሶችን ይበልጥ ለመረዳት ፌዴራል ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 34406 የሰጠውን ውሳኔ መመልከት ይቻልል፡፡ በዚህ መዝገብ በስር ፍርድ ቤት ከሳሽ የሆኑት ሰዎች ባለቤት እና አባት የሆኑት ግለሰብ መኖሪያ ቤታቸውን ያከራዩት ሰው ለተከሳሽ ቤቱን አስረክቦ ይጠፋል፡፡ የቤቱ ህጋዊ ዋራሽ ከሳሾች ቤቱን ለተረከቡት ግለሰብ ቤቱን ለቀው እንዲያስረክቧቸው ቢጠይቋቸውም ፍቃደኛ ባለመሆናቸው አለአግባብ የያዙትን ንብረት እንዲያስረክቡ እና ንብረቱን በያዙበት ወቅት ያለክራይ በመኖር ያገኙትን ያለአግባብ ብልፅግና እንዲከፍሉ ክስ አቅርበዋል፡፡ ተከሳሽም በሰጡት መልስ ቤቱን ያለአግባብ ይዛለች ከተባለ እንኳን ይህን ካወቁ 10 ዓመት በላይ ስለሆነ በይርጋ ይታገዳል፣ የደረሰባቸው የጥቅም ጉዳት ከውል ውጪ እንደመሆኑ የኪራይ ማስከፈል ጥያቄአቸው ሁለት አመት ካለፈው በይርጋ ይታገዳል በማለት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አቅርበዋል፡፡ የስር ፍርድ ቤቶች ጉዳዩን ከመረመሩ በኋላ ተከሳሽ ያለአግባብ የያዙትን ንብረት እንዲመልሱ እና ከንብረቱ ያለአግባብ የተጠቀሙትን መጠን ካሳ እንዲከፍሉ ወስነው ተከሳሽም በዚህ ውሳኔ ቅር በመሰኘት ለሰበር ሰሚ ችሎቱ አቤቱታ አቅርበዋል፡፡ የሰበር ሰሚ ችሎቱም ጉዳዩን ከመረመረ በኋላ በስር ፍርድ ቤት ከሳሽ የሆኑት ግለሰቦች ይዞታችን በሃይል ተወስዷል ወይም በይዞታችን ላይ ሁከት ተፈጥሯል በማለት ያቀረቡት ክስ የለም ክሣቸው በኪራይ የተረከቡትን ቤት ተከሳሽ መብት ሣይኖራቸው ገብተው አልወጣም ብለዋልና አለአግባብ የያዙትን ንብረት እንዲለቁ የቀረበ ክስ ስለሆነ 10 ዓመት ቢያልፈው እንኳን በይርጋ አይታገድም፡፡ በጨማሪም ተከሳሽ የቀረበው የካሣ ጥያቄም ቢሆን በይርጋ ቀሪ ይሆናል በሚል ያቀረቡት ክርክር በተመለከተ ማንኛውም በሌላ ሰው የስራ ድካም ወይም በሌላ ሰው ሃብት በሆነ ነገር በመገልገል በቂ ባልሆነ ምክንያት ጥቅም ያገኘ ሰው ጥቅም ባገኘበት መጠን ለባለሃብቱ ወይም ጉልበቱ ለደከመው ሰው ኪሣራ መክፈል እንዳለበት በፍ/ህ/ቁ. 2162 ሥር ተመልክቷል፡፡ በመሆኑም ከሳሽ በቤቱ አላግባብ በበለፀጉበት መጠን ኪሣራ እንዲከፈላቸው መጠየቃቸው ህጉን መሰረት ያደረገ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ የካሣ ጥያቄ ሊቀርብ የሚገባበት የጊዜ ገደብ በተመለከተ ክርክር ቀርቧል፡፡ ያለአግባብ ስለመበልፀግ የሚናገረው ምእራፍ የካሣ ጥያቄ የሚቀርብበትን የጊዜ ገደብ አይናገርም፡፡ ነገር ግን አላግባብ ስለመበልፀግና ከውል ውጪ ስለሚደርስ ሃላፊነት የሚናገሩት ድንጋጌዎች በአንድ አንቀጽ ውስጥ ተካትተው መገኘታቸው እንዲሁም ያለአግባብ መበልፀግም ከውል ውጪ የሚደርስ ሃላፊነት በመሆኑ ከውል ውጭ የሚደርስ ሃላፊነት ሥር የተመለከተው የይርጋ ዘመን በተመሣሣይ