አላግባብ መበልፀግ በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ ተፈፃሚነት ሊኖረው ይገባል፡፡ በዚህ መሰረት ከውል ውጭ ሃላፊነትን በተመለከተ ተበዳዩ ክስ ማቅረብ የሚችለው ካሣ የሚጠይቅበት ጉዳት ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ እስከ 2 አመት ድረስ መሆኑ በፍ/ህ/ቁ 2143/1/ ሥር ተመልክቷል፡፡ ስለሆነም ተከሳሽ ክስ ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ ወደ ኋላ ላሉት ሁለት አመታት አላግባብ በቤቱ በተገለገሉበት መጠን እንዲከፈሉ የተጠየቁት ካሣ በይጋ የሚታገድ አይሆንም:: ሆኖም ከዛ በፊት ያሉት ግዜያት የተጠቀሙት ክፍያ ግን በይርጋ ቀሪ የሚሆኑ ናቸው በማለት ወስኗል፡፡
ሌላው መታየት ያለ ጉዳይ አንድ ሰው ያለአግባብ በልፅጓል ተብሎ ክስ በሚቀርብበት ወቅት ይህ አለመሆኑን ስለሚያሳይበት መንገድ ነው፡፡ የፍታብሔር ህጋችን በቁጥር 2163 ያለአግባብ መበልፀግ ስለሚቀርበት ሁኔታዎች የሚደነግግ ሲሆን በዚህም መሰረት ያለአግባብ በልፅገሃል ተብሎ የተከሰሰ ሰው ንብረቱን መልስ በሚባልበት ግዜ ላለመበልፀጉ ማስረጃ ያቀረበ እንደሆነ ማሰረጃ ባቀረበበት ልክ ኪሳራ እንዲከፍል አይጠበቅበትም፡፡ ይህም ማለት ምንም እንኳን ከሳሽ ተከሳሽ በእርሱ ኪሳራ መበልፀጉን ማስረዳት ቢችልም ተከሳሽ ክሱ በቀረበበት ወቅት የተገኘው ብልፅግና ከእርሱ ጋር እንደሌለ (ወይም ለሌላ ሰው የተላለፈ መሆኑን) ማስረዳት ከቻለ ካሳ መክፈል ላይኖርበት ይችላል፡፡ ሆኖም ተከሳሹ በክፉ ልቦና ተነሳስቶ ወይም መመለስ እንዳለበት እያወቀ ንብረቱን ወይም ዕቃውን ሌላ ሰው አስተላልፎ ከሆነ ምንም እንኳን የተገኘው ብልፅግና እርሱ ጋር የሌለ ቢሆንም ካሳ የመክፈል ግዴታ እንደሚኖርበት የፍታብሔር ህጉ በቁጥር 2163(2) ስር ያስቀምጣል፡፡ ነገር ግን ተከሳሽ ያለአግባብ የበለፀገበትን ሀብት ለሶስተኛ ወገን ያስተላለፈው ያለ ዋጋ እንደሆነ ከሳሽ ይህን ሶስተኛ ወገን ያለ ዋጋ የወሰደውን ንብረት እንዲመልስለት ሊጠይቀው ይችላል፡፡
መክፈል የማይገባውን ክፍያ ስለመክፈል
ማንኛውም ሰው ሊከፍል የማይገባውን ነገር የከፈለ እንደሆነ ያለአግባብ የከፈለው ክፍያ እንዲመለስለት መጠየቅ ይችላል፡፡ ይህም ማለት ማንም ሰው በስዕተት ሊከፍል የማይገባውን ክፍያ የፈፀመ እንደሆነ ይህ የከፈለው ገንዘብ እንዲመለስልት ካሳ መጠየቅ የሚችል ሲሆን ክፍያውን የተቀበለው ሰው በእምነት ማጉደል ሀሳብ ተነሳስቶ የተቀበለ እንደሆነ ክፍያውን የፈፀመው ሰው ክፍያው ከተፈፀመበት ቀን አንስቶ የከፈለው ነገር የሰጠውን ፍሬ ወይም ህጋዊ ወለድ ጨምሮ መጠየቅ እንደሚችል ህጉ ይደነግጋል፡፡ ሆኖም ሰውየው የከፈለው መክፈል የማይጠበቅበትን ክፍያ ቢሆንም እንኳን በሚከተሉት ሁኔታዎች የከፈለው ክፍያ እንዲመለስለት መጠየቅ አይችልም፡-
• ክፍያውን የፈፀመው ዕዳ እንደሌለበት እያወቀ ወይም ይህን ሁኔታ በግልፅ እየተረዳ በፍቃደኝነት ከሆነ፤
• ግለሰቡ የሚከፈለውን ነገር ያለዋጋ የመስጠት የህግ ችሎታ ያለው ሆኖ ክፍያውን የፈፀመው በይርጋ የታገደውን ዕዳውን ወይም የሕሊና ግዴታውን እና የበጎ አድራጎት መንፈሱን ተከትሎ እንደሆነ፤
ክፍያውን ከፈፀመለት ሰው የከፈለው እንዲመለስለት መጠየቅ እንደማይችል የፍታብሔር ህጉ በቁጥር 2165 እና 2166 ስር ያስቀምጣል፡፡
በሌላ በኩል ያለአግባብ የተከፈለውን ክፍያ የተቀበለ ሰው የተከፈለውን ነገር ከመመለስ የሚድንበት መንገድ ህጉ በቁጥር 2168 ስር ያስቀመጠ ሲሆን በዚህም መሰረት የማይገባውን ገንዘብ የተቀበለ ሰው በሌላ ሰው ላይ ያለው ገንዘቡ የተከፈለው መስሎት በቅን ልቦና የብድሩን ሰነድ አበላሽቶ ወይም ዋሶቹን ከዕዳው ነፃ አድርጎ ወይም ከእውነተኛ ባለዕዳ ሊቀበል የሚገባውን ገንዘብ በይርጋ አሳልፎ እንደሆነ፤ ያለአግባብ የተቀበለውን ገንዘብ የመመለስ ግዴታ ማይኖርበት ሲሆን እንዲህ ባለው ሁኔታ ክፍያውን ያለአግባብ የከፈለው ግለሰብ ክፍያው እንዲመለስለት ለመጠየቅ የሚችለው ከዋናው ባለዕዳ ብቻ ነው፡፡
በሌላ ሰው ንብረት ላይ የወጣ ወጪን ስለማስመለስ
ይህ የህግ ክፍል የሌላ ሰው ንብረት ያየዘ ሰው ንብረቱ በሚመልስበት ግዜ ንብረቱን ለመጠበቅ ያወጣውን ወጪ እንዲመለስለት ስለሚጠይቅበት አግባብ ወይም ንብረቱ በግለሰቡ ቁጥጥር በነበረበት ወቅት ያስገኘውን ጥቅም የራሱ ስለሚያደርግበት መንገድ የሚደነግግ የህግ ክፍል ነው፡፡ ዋናው ያለአግባብ መበልፀግ ህግ አላማ ማንኛውም ሰው መክፈል የማይገባውን ክፍያ እንዳይከፍል ወይም ማውጣት የሌለበትን ወጪ እንዳያወጣ ይህን ካደረገም ተገቢው ካሳ ተከፍሎት ፍትሀዊነት እንዲሰፍን ማድረግ ነው፡፡ ስለሆነም ማንኛውም ሰው የራሱ ባልሆነ ንብረት ላይ በቀና ልቦና ያወጣው ወጪ ሳይቀናነስ ንብረቱን ለባለቤቱ መልስ መባሉ ተገቢ አይደለም፡፡ የፍታብሔር ህጉ በቁጥር 2168 ስር አንድ ሰው ለተወሰነ ግዜ በእጁ የቆየውን ዕቃ እንዲመለስ የተገደደ እንደሆነ የሕግ ወይም የውል ተቃራኒ የሚሆን ድንጋጌ ከሌለ በቀር ይህ ሰው የተባለውን ዕቃ ከመለዋወጥ የተነሳ ያሉት መብቶችና ግዴታዎች በዚህ የህግ ክፍል እንደሚገዛ ያደነግጋል፡፡
በዚህም መሰረት ማንኛውም ሰው በእጁ የነበረውን የሌላ ሰው ንብረት እንዲመልስ በሚገደድበት ወቅት ዕቃው እንዳይጠፋ ወይም እንዳይበላሽ ለማድረግ ያወጣውን ወጪ እንዲመለስለት ለመጠየቅ እንደሚችል በቁጥር 2168 ስር ተቀምጧል፡፡ ሆኖም ይህ ወጪ የወጣው ዕቃውን እንዲመልስ በተገደደው ሰው ወይም እርሱ ሃላፊነትን በሚወስድለት ሰው ጥፋት ምክንያት ከሆነ ወጪው እንዲመለስለት ለመጠየቅ አይችልም፡፡ በመሆኑም አንድ ሰው በውል ህግ መሰረት በተቃራኒው ካልተዋዋሉ ወይም ወጪው አላስፈላጊ ካልሆነ ወይም ወጪው ዕቃውን እንዲመልስ በተገደደው ሰው ጥፋት ምክንያት የተፈፀመ እስካልሆነ ድረስ የሌላን ሰው ንብረት እንዳይጠፋ ወይም እንዳይበላሽ ለማድረግ ያወጣው ወጪ እንዲመለስለት የመጠየቅ መብት እንዳለው ህጉ ያስቀምጣል፡፡
ነገርግን ይህ የሌላ ሰው ንብረት እንዲመልስ የተገደደ ሰው በውል በሌላ መልኩ ካልተዋዋሉ በስተቀር በማንኛውም መልኩ ለዕቃው አጠባበቅ ያወጣው ወጪ ወይም በንብረቱ ይዞታ ምክንያት የከፈለው ግብር እንዲመለስለት ለመጠየቅ አይችልም፡፡ ይህ መርህ መሰረት ያደረገው ህጉ የሌላ ሰው ንብረትን የያዘ ሰው ንብረቱን በእጁ በሚያስገባበት ወቅት ምንም አይነት መብት የሌለው መሆኑን የሚያውቅ ካልሆነ በስተቀር ንብረቱ ከሚያፈራው ፍሬ እንዲጠቀም መብት የሚሰጥ በመሆኑ ይህ ግለሰብ ፍሬ ያፈራለትን ንብረት ለመጠበቅ ያወጣው ወጪ ይመለሰልኝ ብሎ መጠየቅ ተገቢ ካለመሆኑ ጋር ተያይዞ ነው፡፡ ስለሆነም በእጁ ያለው ዕቃ እንዲመልስ የተገደደ ሰው የተቀበለው ዕቃ ያፈራውን ፍሬ የማስቀረት ህጋዊ መብት ያለው ሲሆን ዕቃውን በይዞታው ስር ባደረገበት ወቅት በዕቃው ላይ ምንም ዓይነት የውልም ሆነ የህግ መብት እንደሌለው እያወቀ ድርጊቱን ከፈፀመ ግን ይህን የንብረቱን ፍሬ ለራሱ የማስቀረት መብቱ ቀርቶ ለትክክለኛው የንብረቱ ባለቤት ዕቃው በእሱ ይዞታ ስር በነበረበት ወቅት ያፈራው ፍሬ ግምት ልክ የመክፈል ግዴታ ይኖርበታል፡፡
ሌላው የሌላ ሰው ንብረት እንዲመልስ ከተገደደ ሰው መብት ጋር ተያይዞ የሚነሳው ይህ ግለሰብ ንብረቱ በእጁ በነበረበት ወቅት በቅን ልቦና በመነሳሳት ወጪ አውጥቶ የዕቃውን ዋጋ ከፍ በሚያደርግበት ግዜ ስለሚኖረው ህጋዊ መብት ነው፡፡ የፍታብሔር ህጉም በቁጥር 2171 ስር በሌላ ሰው ዕቃ ላይ የተደረገ ወጪ የዕቃውን ግምት ከፍ አድርጎት ከሆነ ዕቃውን እንዲመልስ የተገደደው ሰው ለዚሁ ጉዳይ ያወጣው ወጪ የዕቃውን ዋጋ ከፍ ባደረገው መጠን ብቻ ሊመለስለት እንደሚገባ ያስቀምጣል፡፡
ሌላው መታየት ያለ ጉዳይ አንድ ሰው ያለአግባብ በልፅጓል ተብሎ ክስ በሚቀርብበት ወቅት ይህ አለመሆኑን ስለሚያሳይበት መንገድ ነው፡፡ የፍታብሔር ህጋችን በቁጥር 2163 ያለአግባብ መበልፀግ ስለሚቀርበት ሁኔታዎች የሚደነግግ ሲሆን በዚህም መሰረት ያለአግባብ በልፅገሃል ተብሎ የተከሰሰ ሰው ንብረቱን መልስ በሚባልበት ግዜ ላለመበልፀጉ ማስረጃ ያቀረበ እንደሆነ ማሰረጃ ባቀረበበት ልክ ኪሳራ እንዲከፍል አይጠበቅበትም፡፡ ይህም ማለት ምንም እንኳን ከሳሽ ተከሳሽ በእርሱ ኪሳራ መበልፀጉን ማስረዳት ቢችልም ተከሳሽ ክሱ በቀረበበት ወቅት የተገኘው ብልፅግና ከእርሱ ጋር እንደሌለ (ወይም ለሌላ ሰው የተላለፈ መሆኑን) ማስረዳት ከቻለ ካሳ መክፈል ላይኖርበት ይችላል፡፡ ሆኖም ተከሳሹ በክፉ ልቦና ተነሳስቶ ወይም መመለስ እንዳለበት እያወቀ ንብረቱን ወይም ዕቃውን ሌላ ሰው አስተላልፎ ከሆነ ምንም እንኳን የተገኘው ብልፅግና እርሱ ጋር የሌለ ቢሆንም ካሳ የመክፈል ግዴታ እንደሚኖርበት የፍታብሔር ህጉ በቁጥር 2163(2) ስር ያስቀምጣል፡፡ ነገር ግን ተከሳሽ ያለአግባብ የበለፀገበትን ሀብት ለሶስተኛ ወገን ያስተላለፈው ያለ ዋጋ እንደሆነ ከሳሽ ይህን ሶስተኛ ወገን ያለ ዋጋ የወሰደውን ንብረት እንዲመልስለት ሊጠይቀው ይችላል፡፡
መክፈል የማይገባውን ክፍያ ስለመክፈል
ማንኛውም ሰው ሊከፍል የማይገባውን ነገር የከፈለ እንደሆነ ያለአግባብ የከፈለው ክፍያ እንዲመለስለት መጠየቅ ይችላል፡፡ ይህም ማለት ማንም ሰው በስዕተት ሊከፍል የማይገባውን ክፍያ የፈፀመ እንደሆነ ይህ የከፈለው ገንዘብ እንዲመለስልት ካሳ መጠየቅ የሚችል ሲሆን ክፍያውን የተቀበለው ሰው በእምነት ማጉደል ሀሳብ ተነሳስቶ የተቀበለ እንደሆነ ክፍያውን የፈፀመው ሰው ክፍያው ከተፈፀመበት ቀን አንስቶ የከፈለው ነገር የሰጠውን ፍሬ ወይም ህጋዊ ወለድ ጨምሮ መጠየቅ እንደሚችል ህጉ ይደነግጋል፡፡ ሆኖም ሰውየው የከፈለው መክፈል የማይጠበቅበትን ክፍያ ቢሆንም እንኳን በሚከተሉት ሁኔታዎች የከፈለው ክፍያ እንዲመለስለት መጠየቅ አይችልም፡-
• ክፍያውን የፈፀመው ዕዳ እንደሌለበት እያወቀ ወይም ይህን ሁኔታ በግልፅ እየተረዳ በፍቃደኝነት ከሆነ፤
• ግለሰቡ የሚከፈለውን ነገር ያለዋጋ የመስጠት የህግ ችሎታ ያለው ሆኖ ክፍያውን የፈፀመው በይርጋ የታገደውን ዕዳውን ወይም የሕሊና ግዴታውን እና የበጎ አድራጎት መንፈሱን ተከትሎ እንደሆነ፤
ክፍያውን ከፈፀመለት ሰው የከፈለው እንዲመለስለት መጠየቅ እንደማይችል የፍታብሔር ህጉ በቁጥር 2165 እና 2166 ስር ያስቀምጣል፡፡
በሌላ በኩል ያለአግባብ የተከፈለውን ክፍያ የተቀበለ ሰው የተከፈለውን ነገር ከመመለስ የሚድንበት መንገድ ህጉ በቁጥር 2168 ስር ያስቀመጠ ሲሆን በዚህም መሰረት የማይገባውን ገንዘብ የተቀበለ ሰው በሌላ ሰው ላይ ያለው ገንዘቡ የተከፈለው መስሎት በቅን ልቦና የብድሩን ሰነድ አበላሽቶ ወይም ዋሶቹን ከዕዳው ነፃ አድርጎ ወይም ከእውነተኛ ባለዕዳ ሊቀበል የሚገባውን ገንዘብ በይርጋ አሳልፎ እንደሆነ፤ ያለአግባብ የተቀበለውን ገንዘብ የመመለስ ግዴታ ማይኖርበት ሲሆን እንዲህ ባለው ሁኔታ ክፍያውን ያለአግባብ የከፈለው ግለሰብ ክፍያው እንዲመለስለት ለመጠየቅ የሚችለው ከዋናው ባለዕዳ ብቻ ነው፡፡
በሌላ ሰው ንብረት ላይ የወጣ ወጪን ስለማስመለስ
ይህ የህግ ክፍል የሌላ ሰው ንብረት ያየዘ ሰው ንብረቱ በሚመልስበት ግዜ ንብረቱን ለመጠበቅ ያወጣውን ወጪ እንዲመለስለት ስለሚጠይቅበት አግባብ ወይም ንብረቱ በግለሰቡ ቁጥጥር በነበረበት ወቅት ያስገኘውን ጥቅም የራሱ ስለሚያደርግበት መንገድ የሚደነግግ የህግ ክፍል ነው፡፡ ዋናው ያለአግባብ መበልፀግ ህግ አላማ ማንኛውም ሰው መክፈል የማይገባውን ክፍያ እንዳይከፍል ወይም ማውጣት የሌለበትን ወጪ እንዳያወጣ ይህን ካደረገም ተገቢው ካሳ ተከፍሎት ፍትሀዊነት እንዲሰፍን ማድረግ ነው፡፡ ስለሆነም ማንኛውም ሰው የራሱ ባልሆነ ንብረት ላይ በቀና ልቦና ያወጣው ወጪ ሳይቀናነስ ንብረቱን ለባለቤቱ መልስ መባሉ ተገቢ አይደለም፡፡ የፍታብሔር ህጉ በቁጥር 2168 ስር አንድ ሰው ለተወሰነ ግዜ በእጁ የቆየውን ዕቃ እንዲመለስ የተገደደ እንደሆነ የሕግ ወይም የውል ተቃራኒ የሚሆን ድንጋጌ ከሌለ በቀር ይህ ሰው የተባለውን ዕቃ ከመለዋወጥ የተነሳ ያሉት መብቶችና ግዴታዎች በዚህ የህግ ክፍል እንደሚገዛ ያደነግጋል፡፡
በዚህም መሰረት ማንኛውም ሰው በእጁ የነበረውን የሌላ ሰው ንብረት እንዲመልስ በሚገደድበት ወቅት ዕቃው እንዳይጠፋ ወይም እንዳይበላሽ ለማድረግ ያወጣውን ወጪ እንዲመለስለት ለመጠየቅ እንደሚችል በቁጥር 2168 ስር ተቀምጧል፡፡ ሆኖም ይህ ወጪ የወጣው ዕቃውን እንዲመልስ በተገደደው ሰው ወይም እርሱ ሃላፊነትን በሚወስድለት ሰው ጥፋት ምክንያት ከሆነ ወጪው እንዲመለስለት ለመጠየቅ አይችልም፡፡ በመሆኑም አንድ ሰው በውል ህግ መሰረት በተቃራኒው ካልተዋዋሉ ወይም ወጪው አላስፈላጊ ካልሆነ ወይም ወጪው ዕቃውን እንዲመልስ በተገደደው ሰው ጥፋት ምክንያት የተፈፀመ እስካልሆነ ድረስ የሌላን ሰው ንብረት እንዳይጠፋ ወይም እንዳይበላሽ ለማድረግ ያወጣው ወጪ እንዲመለስለት የመጠየቅ መብት እንዳለው ህጉ ያስቀምጣል፡፡
ነገርግን ይህ የሌላ ሰው ንብረት እንዲመልስ የተገደደ ሰው በውል በሌላ መልኩ ካልተዋዋሉ በስተቀር በማንኛውም መልኩ ለዕቃው አጠባበቅ ያወጣው ወጪ ወይም በንብረቱ ይዞታ ምክንያት የከፈለው ግብር እንዲመለስለት ለመጠየቅ አይችልም፡፡ ይህ መርህ መሰረት ያደረገው ህጉ የሌላ ሰው ንብረትን የያዘ ሰው ንብረቱን በእጁ በሚያስገባበት ወቅት ምንም አይነት መብት የሌለው መሆኑን የሚያውቅ ካልሆነ በስተቀር ንብረቱ ከሚያፈራው ፍሬ እንዲጠቀም መብት የሚሰጥ በመሆኑ ይህ ግለሰብ ፍሬ ያፈራለትን ንብረት ለመጠበቅ ያወጣው ወጪ ይመለሰልኝ ብሎ መጠየቅ ተገቢ ካለመሆኑ ጋር ተያይዞ ነው፡፡ ስለሆነም በእጁ ያለው ዕቃ እንዲመልስ የተገደደ ሰው የተቀበለው ዕቃ ያፈራውን ፍሬ የማስቀረት ህጋዊ መብት ያለው ሲሆን ዕቃውን በይዞታው ስር ባደረገበት ወቅት በዕቃው ላይ ምንም ዓይነት የውልም ሆነ የህግ መብት እንደሌለው እያወቀ ድርጊቱን ከፈፀመ ግን ይህን የንብረቱን ፍሬ ለራሱ የማስቀረት መብቱ ቀርቶ ለትክክለኛው የንብረቱ ባለቤት ዕቃው በእሱ ይዞታ ስር በነበረበት ወቅት ያፈራው ፍሬ ግምት ልክ የመክፈል ግዴታ ይኖርበታል፡፡
ሌላው የሌላ ሰው ንብረት እንዲመልስ ከተገደደ ሰው መብት ጋር ተያይዞ የሚነሳው ይህ ግለሰብ ንብረቱ በእጁ በነበረበት ወቅት በቅን ልቦና በመነሳሳት ወጪ አውጥቶ የዕቃውን ዋጋ ከፍ በሚያደርግበት ግዜ ስለሚኖረው ህጋዊ መብት ነው፡፡ የፍታብሔር ህጉም በቁጥር 2171 ስር በሌላ ሰው ዕቃ ላይ የተደረገ ወጪ የዕቃውን ግምት ከፍ አድርጎት ከሆነ ዕቃውን እንዲመልስ የተገደደው ሰው ለዚሁ ጉዳይ ያወጣው ወጪ የዕቃውን ዋጋ ከፍ ባደረገው መጠን ብቻ ሊመለስለት እንደሚገባ ያስቀምጣል፡፡
በዚህም መሰረት ይህ ንብረቱን እንዲመልስ የተገደደ ሰው የዕቃውን ዋጋ ከፍ ለማድረግ ያወጣው ወጪ እንዲመለስለት የሚከተሉትን ነገሮች ማስረዳት ይጠበቅበታል፡-
• በዕቃው ላይ ወጪ ያወጣ መሆኑን፤
• የዕቃውን ዋጋ መጨመሩን እና የዕቃው ዋጋ የጨመረው እሱ ባወጣው ወጪ ምክንያት መሆኑን፤
• የዕቃው ዋጋ መጨመር ንብረቱ እንዲመለስ በተጠየቀመት ግዜ የሚታይ መሆኑን፡፡
ነገር ግን እነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች ተሟሉ ማለት ሰውየው በዕቃው ላይ ያወጣው ወጪ በእርግጠኝነት ይመለስለታል ማለት አይደለም፡ ከነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች በተጨማሪ የቅን ልቦና መኖር አስፈላጊ ነው፡፡ ምንም እንኳን ወጪውን በማውጣት ሂደት ቅን ልቦና አለ የሚለው ግምት የሚወሰድበት ቢሆንም ይህ ግን ተቃራኒ ማስረጃ ሊቀርብበት የሚችል ነው፡፡ የፍታብሔር ህጉም በቁጥር 2172 ስር ወጪው በተፈፀመበት ግዜ ዕቃውን እንዲመልስ የተገደደው ሰው ዕቃውን የመመለስ ግዴታ ያለበት መሆኑን ያውቅ እንደነበር ወይም የማወቅ ግዴታ ያለበት መሆኑን ማስረዳት ከተቻለ የወጪው ኪሳራ እንዳይከፈል ወይም የንብረቱ ባለቤት ኪሳራውን የመክፈያ እስከ ሁለት ዓመት የሚደርስ ግዜ እንዲሰጠው ዳኞች ለመወሰን እንደሚችሉ አስቀምጧል፡፡
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties #አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties
• በዕቃው ላይ ወጪ ያወጣ መሆኑን፤
• የዕቃውን ዋጋ መጨመሩን እና የዕቃው ዋጋ የጨመረው እሱ ባወጣው ወጪ ምክንያት መሆኑን፤
• የዕቃው ዋጋ መጨመር ንብረቱ እንዲመለስ በተጠየቀመት ግዜ የሚታይ መሆኑን፡፡
ነገር ግን እነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች ተሟሉ ማለት ሰውየው በዕቃው ላይ ያወጣው ወጪ በእርግጠኝነት ይመለስለታል ማለት አይደለም፡ ከነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች በተጨማሪ የቅን ልቦና መኖር አስፈላጊ ነው፡፡ ምንም እንኳን ወጪውን በማውጣት ሂደት ቅን ልቦና አለ የሚለው ግምት የሚወሰድበት ቢሆንም ይህ ግን ተቃራኒ ማስረጃ ሊቀርብበት የሚችል ነው፡፡ የፍታብሔር ህጉም በቁጥር 2172 ስር ወጪው በተፈፀመበት ግዜ ዕቃውን እንዲመልስ የተገደደው ሰው ዕቃውን የመመለስ ግዴታ ያለበት መሆኑን ያውቅ እንደነበር ወይም የማወቅ ግዴታ ያለበት መሆኑን ማስረዳት ከተቻለ የወጪው ኪሳራ እንዳይከፈል ወይም የንብረቱ ባለቤት ኪሳራውን የመክፈያ እስከ ሁለት ዓመት የሚደርስ ግዜ እንዲሰጠው ዳኞች ለመወሰን እንደሚችሉ አስቀምጧል፡፡
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties #አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
የታክስ አይነቶች
ቀጥታ ታክስ
የደመወዝ ገቢ ግብር
የኪራይ ገቢ ግብር
የንግድ ሥራ ገቢ ግብር
የሌሎች ገቢዎች ግብር
ቀጥታ ያልሆኑ ታክሶች
የተጨማሪ እሴት ታክስ ( Value Added Tax )
ኤክሳይዝ ታክስ ( Excise Tax )
ተርን ኦቨር ታክስ ( Turnover Tax )
የቴምብር ቀረጥ ( Stamp Duty )
የጉምሩክ ቀረጥ ( Customs Duty )
ሱር ታክስ ( Surtax )
ገቢዎችን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በድረ ገጽ፦ www.mor.gov.et
በፌስቡክ፡- ministryofrevenuesofethiopia/የገቢዎች ሚኒስቴር/
በዩትዩብ፦ ministryofrevenuesofethiopia
በቴሌቪዥን ፕሮግራሞቻችን ፡- ዋልታ ቴሌቪዥን ሰኞ ማታ ከ 2፡30 ጀምሮ
ፋና ቴሌቪዥን ሐሙስ ማታ ከ2፡00 ዜና በኃላ
ኢቲዮጵያ ቴሌቪዥን /ኢ.ቢ.ሲ/ ቅዳሜ ማታ ከ2፡00 ዜና በኋላ
በሬድዮ ፕሮግራሞቻችን፡- ፋና ኤፍ ኤም ሬድዮ 98.1 ሐሙስ ማታ ከ2፡30 ጀምሮ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሬድዮ 93.1 ማክሰኞ ጠዋት ከ2፡30 ጀምሮ
በወርሃዊ ጋዜጣችን፡- ገቢያችን ህልውናችን
እንዲሁም በነጻ ጥሪ አገልግሎታችን፡ - 8199 በመደወል መረጃዎችን በመጠየቅ
ስለሚከታተሉን እናመሰግናለን!
ቀጥታ ታክስ
የደመወዝ ገቢ ግብር
የኪራይ ገቢ ግብር
የንግድ ሥራ ገቢ ግብር
የሌሎች ገቢዎች ግብር
ቀጥታ ያልሆኑ ታክሶች
የተጨማሪ እሴት ታክስ ( Value Added Tax )
ኤክሳይዝ ታክስ ( Excise Tax )
ተርን ኦቨር ታክስ ( Turnover Tax )
የቴምብር ቀረጥ ( Stamp Duty )
የጉምሩክ ቀረጥ ( Customs Duty )
ሱር ታክስ ( Surtax )
ገቢዎችን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በድረ ገጽ፦ www.mor.gov.et
በፌስቡክ፡- ministryofrevenuesofethiopia/የገቢዎች ሚኒስቴር/
በዩትዩብ፦ ministryofrevenuesofethiopia
በቴሌቪዥን ፕሮግራሞቻችን ፡- ዋልታ ቴሌቪዥን ሰኞ ማታ ከ 2፡30 ጀምሮ
ፋና ቴሌቪዥን ሐሙስ ማታ ከ2፡00 ዜና በኃላ
ኢቲዮጵያ ቴሌቪዥን /ኢ.ቢ.ሲ/ ቅዳሜ ማታ ከ2፡00 ዜና በኋላ
በሬድዮ ፕሮግራሞቻችን፡- ፋና ኤፍ ኤም ሬድዮ 98.1 ሐሙስ ማታ ከ2፡30 ጀምሮ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሬድዮ 93.1 ማክሰኞ ጠዋት ከ2፡30 ጀምሮ
በወርሃዊ ጋዜጣችን፡- ገቢያችን ህልውናችን
እንዲሁም በነጻ ጥሪ አገልግሎታችን፡ - 8199 በመደወል መረጃዎችን በመጠየቅ
ስለሚከታተሉን እናመሰግናለን!
scd17.pdf
1 MB
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ሥነ-ሥርዓት መመሪያ ቁጥር 17/2015 አውጥቷል።
መመሪያው ተፈጻሚ የሚሆነው ከሚያዚያ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ነው። ይህንን መመሪያ ከ https://www.pocketlaw.abyssinialaw.com/ ማግኘት ይችላሉ። በነጋሪ መተግበሪያም በቅርቡ እናካትታለን።
መመሪያው ተፈጻሚ የሚሆነው ከሚያዚያ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ነው። ይህንን መመሪያ ከ https://www.pocketlaw.abyssinialaw.com/ ማግኘት ይችላሉ። በነጋሪ መተግበሪያም በቅርቡ እናካትታለን።
በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተዘጋጀ የፍትሐብሔር ክስ ለማቅረብ የሚከፈል የዳኝነት ክፍያ መጠንን ለማስላት የሚያስችል ሲስተም፡፡
👉 https://www.fsc.gov.et/Court-Services/Registry-Services/Court-Forms-and-Fees
👉 https://www.fsc.gov.et/Court-Services/Registry-Services/Court-Forms-and-Fees
www.fsc.gov.et
Federal Supreme Court of Ethiopia > Court Services > Registry Services > Court Forms and Fees
The Federal Supreme Court of Ethiopia has enjoyed a rich history as an institution since it was established on 1934 E.C. The Federal Supreme Court has evolved through the decades, starting from the Emperor regime throughout the Derg regime.
ንፋስ አመጣሽ ትርፍ
1. “ንፋስ አመጣሽ ትርፍ” ያለልፋት (ያለጥረት፣ ያለተጨማሪ ወጪ ወዘተ) የሚገኝ ያልተጠበቀ ወይም ሌላ ተደጋግሞ የማይገኝ ትርፍ ነው፡፡
2. የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትሩ በሚያወጣው መመሪያ ከተመለከቱት የንግድ ስራዎች በሚገኝ ንፋስ አመጣሽ ትርፍ ላይ በመመሪያው በተመለከተው የማስከፈያ መጣኔ (ልክ) ግብር ይከፈልበታል፡፡
3. ሚኒስትሩ በሚያወጣው መመሪያ፡
ሀ. ነፋስ አመጣሽ ትርፍ ነው ሊባል የሚችለውን የገቢ መጠን፣
ለ. ግብሩ የሚመለከታቸውን የንግድ ስራዎች አይነት፣
ሐ. ግብሩን ለማስከፈል የወጣው መመሪያ ስራ ላይ የሚውልበትን ቀን፣
መ. የግብር አወሳሰኑን ዘዴና ለግብሩ አወሳሰን መሰረት የሚሆኑ ታሳቢዎችን ይወሰናል፡፡
4. ለተለያዩ የንግድ ስራዎች የሚወሰነው የነፋስ አመጣሽ ትርፍ መጠንና የግብር ማስከፈያ መጣኔውም የተለያየ እንዲሆን ሚኒስትሩ ሊወሰን ይችላል፡፡
1. “ንፋስ አመጣሽ ትርፍ” ያለልፋት (ያለጥረት፣ ያለተጨማሪ ወጪ ወዘተ) የሚገኝ ያልተጠበቀ ወይም ሌላ ተደጋግሞ የማይገኝ ትርፍ ነው፡፡
2. የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትሩ በሚያወጣው መመሪያ ከተመለከቱት የንግድ ስራዎች በሚገኝ ንፋስ አመጣሽ ትርፍ ላይ በመመሪያው በተመለከተው የማስከፈያ መጣኔ (ልክ) ግብር ይከፈልበታል፡፡
3. ሚኒስትሩ በሚያወጣው መመሪያ፡
ሀ. ነፋስ አመጣሽ ትርፍ ነው ሊባል የሚችለውን የገቢ መጠን፣
ለ. ግብሩ የሚመለከታቸውን የንግድ ስራዎች አይነት፣
ሐ. ግብሩን ለማስከፈል የወጣው መመሪያ ስራ ላይ የሚውልበትን ቀን፣
መ. የግብር አወሳሰኑን ዘዴና ለግብሩ አወሳሰን መሰረት የሚሆኑ ታሳቢዎችን ይወሰናል፡፡
4. ለተለያዩ የንግድ ስራዎች የሚወሰነው የነፋስ አመጣሽ ትርፍ መጠንና የግብር ማስከፈያ መጣኔውም የተለያየ እንዲሆን ሚኒስትሩ ሊወሰን ይችላል፡፡
ቅድመ ታክስ ክፍያ /Withholding/
አብዛኛውን ጊዜ እንደ አንድ የታክስ አይነት ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ሆኖም ዊዝሆልዲንግ ታክስ ማለት አንድ ግብር ከፋይ ሊያገኝ የሚችለውን ገቢ መሠረት በማድረግ የግብር ሰብሳቢው ተቋም ከገቢ ማስታወቂያ ጊዜ አስቀድሞ ግብር የሚሰበስብበት ሥርአት ነው፡፡ በዚህም የተነሳ ዊዝሆልዲንግ ወይንም ከክፍያ ላይ የሚሰበሰብ ቅድመ ታክስ እየተባለ ይጠራል፡፡ ዊዝሆልዲንግ በግዢና ሽያጭ ወይም የአገልግሎት ክፍያ በሚፈፀምበት ወቅትም ተሰልቶ ተከፋይ የሚሆንበት ሁኔታ አለ፡፡ ዊዝሆልዲንግ ገቢ በማግኘት የታክስ ግዴታቸውን ሳይወጡ የሚሰወሩትን በቀላሉ አነስተኛውን ምጣኔ እንዲከፍሉ ለማድረግ ስለሚያሰችል ለግብር አሰባሰቡ የመቆጣጠሪያ ዘዴ (Controlling mechanism) ነው፡፡
ቅድመ ታክስ በሁለት መልኩ ይከናወናል፡¬
1. ወደ አገር ውስጥ ለሚገቡ እቃዎች በሚከፈል የመድህን አረቦን (Insurance Premium) እና የመጓጓዣ ወጪ (Fright) ላይ ታስቦ አስመጪው 3 በመቶ እንዲከፍል ይደረጋል፡፡ ይህ ክፍያ ግብር ከፋዩ ለዓመቱ መክፈል ከሚኖርበት ግብር ይታሰብለታል፡፡ በዊዝሆልዲንግ የከፈለው በልጦ ከተገኘ ትርፉ ክፍያ በተረጋገጠ በዘጠና ቀናት ውስጥ ለግብር ከፋዩ ተመላሽ ይደረግለታል፡፡ በዘጠና ቀናት ውስጥ ካልተመለሰለት ባለፈው ሩብ ዓመት በንግድ ባንኮች ስራ ላይ በዋለው በከፍተኛው የማበደሪያ ልክ ላይ 15% ተጨምሮበት ወለድ ይከፈለዋል፡፡
አብዛኛውን ጊዜ እንደ አንድ የታክስ አይነት ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ሆኖም ዊዝሆልዲንግ ታክስ ማለት አንድ ግብር ከፋይ ሊያገኝ የሚችለውን ገቢ መሠረት በማድረግ የግብር ሰብሳቢው ተቋም ከገቢ ማስታወቂያ ጊዜ አስቀድሞ ግብር የሚሰበስብበት ሥርአት ነው፡፡ በዚህም የተነሳ ዊዝሆልዲንግ ወይንም ከክፍያ ላይ የሚሰበሰብ ቅድመ ታክስ እየተባለ ይጠራል፡፡ ዊዝሆልዲንግ በግዢና ሽያጭ ወይም የአገልግሎት ክፍያ በሚፈፀምበት ወቅትም ተሰልቶ ተከፋይ የሚሆንበት ሁኔታ አለ፡፡ ዊዝሆልዲንግ ገቢ በማግኘት የታክስ ግዴታቸውን ሳይወጡ የሚሰወሩትን በቀላሉ አነስተኛውን ምጣኔ እንዲከፍሉ ለማድረግ ስለሚያሰችል ለግብር አሰባሰቡ የመቆጣጠሪያ ዘዴ (Controlling mechanism) ነው፡፡
ቅድመ ታክስ በሁለት መልኩ ይከናወናል፡¬
1. ወደ አገር ውስጥ ለሚገቡ እቃዎች በሚከፈል የመድህን አረቦን (Insurance Premium) እና የመጓጓዣ ወጪ (Fright) ላይ ታስቦ አስመጪው 3 በመቶ እንዲከፍል ይደረጋል፡፡ ይህ ክፍያ ግብር ከፋዩ ለዓመቱ መክፈል ከሚኖርበት ግብር ይታሰብለታል፡፡ በዊዝሆልዲንግ የከፈለው በልጦ ከተገኘ ትርፉ ክፍያ በተረጋገጠ በዘጠና ቀናት ውስጥ ለግብር ከፋዩ ተመላሽ ይደረግለታል፡፡ በዘጠና ቀናት ውስጥ ካልተመለሰለት ባለፈው ሩብ ዓመት በንግድ ባንኮች ስራ ላይ በዋለው በከፍተኛው የማበደሪያ ልክ ላይ 15% ተጨምሮበት ወለድ ይከፈለዋል፡፡
2. በአንድ ጊዜ ግዥ ወይም በአንድ የእቃ አቅርቦት ከብር 10,000 በላይ ለሆነ ክፍያ ወይም በተለያዩ አገልግሎቶች በአንድ ጊዜ ግዥ ወይም በአንድ አገልግሎት ውል ከብር 3,000 በላይ ከሚፈፀም ክፍያ ላይ 2% ዊዝሆልድ ይደረጋል፡፡ ይህ ተቀናሽ ተደርጎ የሚያዘው በዊዝሆልዲንግ ኤጀንቶች ነው፡፡ ዊዝሆልድ የተደረገው መጠን ግብር ከፋዩ በዓመት ከሚከፍለው የበለጠ እንደሆነ በቁጥር አንድ በተገለፀው መልኩ ይፈፀማል፡፡ ከሚከፈላቸው ክፍያ ላይ 2 በመቶ ዊዝሆልድ የሚደረግባቸው የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና ንግድ ፈቃድ ማቅረብ ለሚችሉ ሲሆን ማቅረብ የማይችሉ ከሆነ ግን 30 በመቶ ዊዝሆልድ ይደረግባቸዋል፡፡
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
Directive_ Property Registration & Compensation_EPSS.pdf
671.8 KB
Directive (Amend) No. 960/2023.
961-2023 Directive.pdf
194.9 KB
A Directive to Provide for the Repeal of Tax and Duty Exemption for Vehicles
Rendering Taxi Transport Services No. 961/2023
Rendering Taxi Transport Services No. 961/2023
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#Yegna Microfinance Institution S.C#
▪️1 - Branch Cashier
▪️2 - Accountant II
▪️3 - Branch Manager
▪️4 - Senior Auditor
▪️5 - Attorney👈
▪️6 - Marketing & Promotion Officer
▪️Find More Details here
💧💧💧💧💧
https://bit.ly/3L5sI0h
▪️Deadline: April 24/2023
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties #አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties
▪️1 - Branch Cashier
▪️2 - Accountant II
▪️3 - Branch Manager
▪️4 - Senior Auditor
▪️5 - Attorney👈
▪️6 - Marketing & Promotion Officer
▪️Find More Details here
💧💧💧💧💧
https://bit.ly/3L5sI0h
▪️Deadline: April 24/2023
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties #አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties
All jobs in one place
Yegna Microfinance Institution S.C - All jobs in one place
Yegna Microfinance Institution S.C is engaged to make contribution towards the economic development of the country by providing professional and quality financial service
https://entrustconsult.com/
one stop government services
one stop government services
Entrust Consulting – Save your time, information matters.
https://entrustconsult.com/
https://entrustconsult.com/
ከመቀጠር የሚገኝ ገቢን አስመልከቶ የአመት ፍቃድ በገንዘብ ተቀይሮ ከሚገኝ ገቢ ላይ የሚከፈል ታክስ
።።።።።።።።።።።።።።።
የዓመት ፍቃድን በተመለከተ አንድ ዓመት ያገለገለ የግል ድርጅት ሠራተኛ 16 ቀን የዓመት ፍቃድ የሚሰጠው ሲሆን ከአንድ ዓመት በላይ ያገለገለ ሠራተኛ በየሁለት ዓመቱ አንድ የሥራ ቀን እየታከለበት የዓመት እረፍት ፈቃድ ያገኛል፡፡
ምሳሌ፡- አቶ አበበ በXYZ ካምፓኒ በድርጅቱ ተቀጥረው የሚሰሩ ሲሆኑ በድርጅቱ 28 ዓመት ያገለገሉ ሲሆን 10,500 ብር ደመወዝ ይከፈላቸዋል፡፡ አቶ አበበ በ2011 ዓ.ም ያልተጠቀሙት 30 ቀናት የአመት ፍቃድ በገንዘብ ተቀይሮ እንዲሰጣቸው በጠየቁት መሰረት በመጨረሻው ዓመት ሂሳቡ ተሰልቶ ተሰጣቸው፤
የአመት ፍቃዳቸው በገንዘብ ተቀይሮ ከተሰጣቸው ገንዘብ ላይ የሚከፍሉት የስራ ግብር፡-
1. 10,500/12= 875
2. 875+10,500=11,375.00
3. 11,375.00*35/100-1500 = 2481.25
4. 10,500*30/100-955=2,195
5. 2,481.25-2,195= 286.25
6. 286.25*12 = 3,435 ብር
ተከፋይ የስራ ግብር ይሆናል፡፡
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties #አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties
።።።።።።።።።።።።።።።
የዓመት ፍቃድን በተመለከተ አንድ ዓመት ያገለገለ የግል ድርጅት ሠራተኛ 16 ቀን የዓመት ፍቃድ የሚሰጠው ሲሆን ከአንድ ዓመት በላይ ያገለገለ ሠራተኛ በየሁለት ዓመቱ አንድ የሥራ ቀን እየታከለበት የዓመት እረፍት ፈቃድ ያገኛል፡፡
ምሳሌ፡- አቶ አበበ በXYZ ካምፓኒ በድርጅቱ ተቀጥረው የሚሰሩ ሲሆኑ በድርጅቱ 28 ዓመት ያገለገሉ ሲሆን 10,500 ብር ደመወዝ ይከፈላቸዋል፡፡ አቶ አበበ በ2011 ዓ.ም ያልተጠቀሙት 30 ቀናት የአመት ፍቃድ በገንዘብ ተቀይሮ እንዲሰጣቸው በጠየቁት መሰረት በመጨረሻው ዓመት ሂሳቡ ተሰልቶ ተሰጣቸው፤
የአመት ፍቃዳቸው በገንዘብ ተቀይሮ ከተሰጣቸው ገንዘብ ላይ የሚከፍሉት የስራ ግብር፡-
1. 10,500/12= 875
2. 875+10,500=11,375.00
3. 11,375.00*35/100-1500 = 2481.25
4. 10,500*30/100-955=2,195
5. 2,481.25-2,195= 286.25
6. 286.25*12 = 3,435 ብር
ተከፋይ የስራ ግብር ይሆናል፡፡
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties #አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
መንግስት መስሪያቤቶች የሚሰጡትን አገልግሎት ከነ መስፈርታቸው ትክክለኛው የ Website አድራሻ እና አጠቃላይ መረጃ ለማግኘት ከፈለጉ
Save your time, information matters.
ለማነኛውም የመንግስት አገልገወሎት እና አስፈላጊ ሰነዶችና እና መረጃዎች
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://entrustconsult.com/
ይህን ድህረገጽ ይወዱታል ለወዳጅ ዘመድ ይጋብዙ።
One stop Government services
https://entrustconsult.com/
Save your time, information matters.
ለማነኛውም የመንግስት አገልገወሎት እና አስፈላጊ ሰነዶችና እና መረጃዎች
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://entrustconsult.com/
ይህን ድህረገጽ ይወዱታል ለወዳጅ ዘመድ ይጋብዙ።
One stop Government services
https://entrustconsult.com/
Forwarded from Entrust Consult 📗ኢንትረስት
ENTRUST
With a one-stop government services website we provide CONVENIENCE and TRANSPARENCY. Individuals and businesses can access all necessary government services in one place without having to visit multiple government offices or websites. A one-stop government services website can increase transparency by providing a clear overview of government services and their requirements. SAVE YOUR TIME INFORMATION MATTERS!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://entrustconsult.com/
https://entrustconsult.com/
With a one-stop government services website we provide CONVENIENCE and TRANSPARENCY. Individuals and businesses can access all necessary government services in one place without having to visit multiple government offices or websites. A one-stop government services website can increase transparency by providing a clear overview of government services and their requirements. SAVE YOUR TIME INFORMATION MATTERS!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://entrustconsult.com/
https://entrustconsult.com/