አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
*“አትግደሉን ትንሿ የመብት ጥያቄ ናት‼️*
#አለ_ህግ #Ale_Hig, ነፃ የህግ የማማከር አገልግሎት፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎች፣ ክሶች፣ የውል ፎርሞች፤ መፅሐፍቶች https://www.youtube.com/@Lawsocieties ሁሉንም ሕጎችና ባለሙያዎች እዚሁ ያገኛሉ🔴 All in one, for All. መሰረታዊ የህግ መረጃ እውቀት፤ ሀብት እና ሀይል ነው @LawsocietiesBot / lawsocieties@gmail.com
https://t.me/lawsocieties
አንድ ሰው "መንግስት በጣም አዋጪ ለሆኑ ፕሮጀክቶቹ ገንዘብ በብዛት አትሞ በፍጥነት ቢሰራበት ችግሩ ምንድን ነው?"
ለጠየቀው ጥያቄ፣ ከኢኮኖሚ #ህግ አንፃር የተሰጠ ማብራሪያ፡፡

ገንዘብ #እንደፈለጉ በማተም የሚያስፈልጉ ወጪዎችን መሸፈን ይቻላል!
ነገር ግን አዲስ የሚታተመው ገንዘብ ኢኮኖሚው ከሚሸከመው የገንዘብ መጠን በላይ ከሆነ (መታተም ካለበት ዝቅተኛ መጠን ከበለጠ) እና ገንዘቡ ታትሞ የሚያርፍበት ሴክተር እና የአዲሱ ገንዘብ የስርጭት ሂደት ያልተጠና ሲሆን ነው አዲስ የሚታተመው ገንዘብ ችግር መሆን የሚጀምረው፡፡
.........................
በኢኮኖሚክስ አስተምሮት ገንዘብ በዘፈቀደ ሊታተም እና ሊሰራጭ አይችልም (በኢኮኖሚ እና በፖለቲካ አስተዳደር ደካማነት ብዙ ገንዘብ ማተም የፈለገ ሀገር መብቱ ነው! ነገር ግን በዋጋ ንረት ዋጋ የሚከፍለው ኢኮኖሚው ነው)፡፡ ገንዘብ ለአንድ ኢኮኖሚ አስፈላጊም አደጋም ነው! ለዚህም ሲባል የገንዘብ ፖሊሲ (Monetary policy) በጠንካራ ተቋማት (በዋናነት በብሄራዊ ባንክ) በከፍተኛ ክትትል እንቅስቃሴው እንዲመራ ይደረጋል፡፡

በኢኮኖሚክስ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት የተቀበለው ድንቁ ኢኮኖሚስት Milton Friedman በአንድ ሀገር የኢኮኖሚ ስርዓት ውስጥ የገንዘብ አቅርቦት ማደግ ያለበት በየዓመቱ ከጠቅላላው ምርት GDP ጋር ተመጣጣኝ በሆነ መጠን ወይም ፐርሰንት ነው (ስርዓቱ K-Percent Rule ይባላል) ስለዚህ የገንዘብ ኖት መጠን የሚወሰነው ጠቅላላ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ከሚኖረው እድገት እና እንቅስቃሴ አንጻር ከ3 ከመቶ ያልበለጠ ህትመት እንዲሆን ይመክራል፡፡

ጥያቄውን ያነሳልኝ ልጅ ኢኮኖሚክስን የተማረ ስላልነበር ለጠየቀው ጥያቄ መልስ መስጠት አለብኝ (እንዲሁም ኢኮኖሚክስን ላልተማራችሁ ሰዎች የሚረዳ ከሆነ) ጥያቄውን ለመመለስ ያህል…….....

የኢትዮጲያ ኢኮኖሚ በገበያው ያለው የቁሳቁስ እና የአገልግሎት አቅርቦት ከሰዎች የመግዛት ፍላጎት እና አቅም ጋር እየመዘነ ኢኮኖሚው በፈጠረው ሃብት አንጻር ተጨማሪ ገንዘብ ወደ ገበያው በተለያየ መንገድ መልቀቅ አለበት፡፡

ነገር ግን በተለይ የዋጋ ንረት ላለበት ኢኮኖሚ (ነባሩ የዋጋ ንረት ከገንዘብ ፈሰስ አንጻር የተባባሰ ከሆነ) ተጨማሪ ገንዘብ ተጨማሪ የሸማች አቅም በመጨመር ምርት በሚፈለገው ፍጥነት ወደ ገበያ ሳይመጣ ፉክክር እና ፍላጎትን በመፍጠር ያለው ምርት ላይ ዋጋ እንዲጨመር ሊያደርግ ይችላል (የዚህ አይነቱ አጋጣሚ በአንደኛው እና በሁለተኛው ጦርነት ወቅት በተወሰኑ የአውሮፓ ሀገራት፤ አፍሪካ ውስጥም በዝምባብዌ፤ በላይቤሪያ፤ ወዘተ ሆኖ ያውቃል)፡፡


#ለምሳሌ፡- መንግስት ግዙፍ የመስኖ ግድብን በመስራት 200ሺ ሄክታር የስንዴ ማሳን እስከማልማት የሚደርስን የፕሮጀክቱን ወጪ 20ቢሊየን ብር አትሞ ቢያዘጋጅ ብለን እናስብ፡፡ ቀጥታ ለመስኖ ግንባታ (ሲሚንቶ (የተወሰነ ግብዓት)፤ ብረት (የተወሰነ ግብዓት)፤ የግንባታ ማሽነሪ፤ ወዘተ) እና ለሰብል ዝግጅት (ምርጥ ዘር፤ የአፈር ማዳበሪያ፤ ለማጓጓዣ ነዳጅ፤ ጸረ-ሰብል መድሃኒት፤ ወዘተ) ኢኮኖሚው በብር ገዝቶ ማቅረብ ይችላል?

ስለዚህ ብር የሚያገለግለው ለሀገር ውስጥ ግብዓት (የውጪ ምንዛሬ ለማይጠይቁ ግብዓት ፍጆታ ካላቸው) እና የባለሙያ ክፍያ/የአገልግሎት ክፍያ ለመፈጸም ነው፡፡ ምክንያቱም የውጪ ምንዛሬ ለሚጠይቁ የፕሮጀክት ወጪዎች ብርን በቀጥታ መጠቀም ስለማይቻል ማለት ነው፡፡ ይህ ማለት በቂ የውጪ ምንዛሬ በሌለበት ብርን በማተም ብቻ ፕሮጀክቶችን ፋይናንስ በማድረግ ለማጠናቀቅ ከባድ ነው፡፡

ፕሮጀክቶች ለመጠናቀቅ ረጅም ጊዜ የመውሰድ ልምድ ስላላቸው እና አሁን በሀገራችን የሰዎች ቀጥተኛ ተሳትፎ በማሽኖች ስላልተተካ በየፕሮጀክቶቹ እና ለፕሮጀክቱ ግብዓት የሚያቀርቡ ተቋማት ከፍተኛ የሰው ሃይል ስለሆነ የሚጠቀሙት ከፍተኛ ክፍያ (በደሞዝ እና በስራ ማስኬጃ) በጠቅላላ ሂደቱ በሙሉ ይወጣል፡፡

ስለዚህ ለረጅም ጊዜ ለስራ ማስኬጃ የሚወጣው ወጪ ገበያ ውስጥ ለሸመታ በሚል ስለሚወጣ አቅርቦት እስካልተሻሻለ ያለው አነስተኛ አቅርቦት ላይ ገንዘብ ያላቸው ሸማቾች ሲጨመሩ ፉክክሩ እቃዎችን ከእጥረት የተነሳ ውድ እንዲሆኑ ያደርጋል፡፡

#ለምሳሌ- ይህ ፕሮጀክት እስኪጠናቀቅ ድረስ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ 10ሺ በቤታቸው/በቤተሰቦቻቸው ድጋፍ በቤት ያለስራ ተቀምጠው የነበሩ ወጣቶችን በወር የ5ሺ ብር ደሞዝተኛ ቢያድርግ፡ እነዚህ ሰዎች በየወሩ የ5ሺ ብር የአገልግሎትም ሆነ የቁሳቁስ ሸመታ ላይ ሊሳተፉ ይችላሉ! ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ምርት ወደ ገበያ ከማምጣቱ በፊት ወጣቶቹ ወደ ሸመታ በመግባታቸው ፉክክሩን በመጨመር ዋጋዎችን ከፍላጎት በተነሳ ምክንያት (Demand Pull Inflation) ውድ ሊያደርጉት ይችላሉ፡፡

በሌላ ጎን እነዚህ የ5ሺ ብር አዳዲስ ደሞዝተኞች የባንክ ደብተር አውጥተው በወር አንድ አንድ ሺ ብር ማስቀመጥ ቢጀምሩ ባንኮች የተቀበሉትን ቁጠባ በኢንቨስትመንት መልኩ ቢያበድሩት ድጋሚ ገንዘብ ወደ ገበያው ፈሰስ ሆኖ ተመሳሳይ ችግር ሊፈጥር ይችላል፡፡ በተለይ ገንዘብን በጥሬ ገንዘብነት መያዝ ለለመደ ማህበረሰብ ከባንኩ ቁጥጥር ውጪ የሚውለውን ገንዘብ መጠን ስለሚጨምረው የማክሮ ኢኮኖሚ ሚዛን መዛባቱ ሲባባስ በተለያዩ የMonetary ዘዴዎች ገንዘቡን ወደ ማዕከላዊ ባንኩ ለመሰብሰብ አስቸጋሪ ነው፡፡


አስተውሉ የታተመው ገንዘቡ ወደ ገበያ ሳይሰራጭ ለፕሮጀክት ብቻ ማዋል የሚባል አመክንዬ ሊኖር አይችልም! እንዲሁም የማክሮ ኢኮኖሚ ጉዳይ ሲወራ ስለጥቂት ሰዎች ሳይሆን ስለድምር ተጽዕኖው ነው የሚወራው፡፡ ምን ማለቴ ነው ? በቀላሉ ከላይኛው ምሳሌ በመነሳት ፕሮጀክቱ ሊኖር የሚችለው አንድ ቦታ ላይ ነው፡ ሰዎቹም 10ሺ ናቸው የሚል ክርክር ቢነሳ ጠንካራ አይደለም! ምክንያቱም የማክሮ ኢኮኖሚውም ሆነ የዋጋ ንረት የሚሰላው የየአካባቢዎቹን አማካይ ጥቅል ውጤት ተወስዶ ነው፡፡
#WaseAlpha
by Wase Belay
https://t.me/lawsocieties
#የወንጀል #ምስክሮችና ጠቋሚዎች #ጥበቃ
........
የወንጀል ድርጊትን ለመቆጣጥር እና ለመከላከል እንዲሁም ወንጀለኞች የወንጀል ድርጊት ከፈፀሙ በኋላ ተደብቀው እንዳይቀሩና ህግ ፊት ቀርበው ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ የወንጀል ምስክሮች እና ጠቋሚዎች የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ ነው፡፡ የወንጀል ምስክሮችና ጠቋሚዎች ይህን ሚናቸውን በአግባቡ እንዲወጡ በምስክርነታቸው ወይም በጠቋሚነታቸው ምክንያት በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ ከሚደርስባቸው አደጋና ጥቃት መከላከል አስፈላጊ ነው፡፡ ሀገራችንም ይህንኑ በመረዳት የወንጀል ምስክሮችና ጠቋሚዎች ጥበቃ ህግ አውጥታ ሥራ ላይ ውሏል፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ የምስክር እና የጠቋሚዎች ምንነት፣ በአዋጁ የተካተቱ የጥበቃ እርምጃ ዓይነቶችን እና የጥበቃ ስምምነት እንዳስሳለን፡፡

የምስክር እና ጠቋሚዎች ምንነት

ጠቋሚ ወይም ምስክር ማለት በወንጀል ምርመራ፣ በወንጀል ክስ ወይም በወንጀል ማጣራት ሒደት መረጃ ወይም ምስክርነት የሰጠ ወይም ለመስጠት የተስማማ ሰው እንደሆነ በአዋጅ ቁጥር 699/2003 አንቀፅ 2(1) ላይ ትርጓሜ ተሰጥቶታል፡፡

የጥበቃ ተጠቃሚነት እና ተፈፃሚነቱ

በአዋጁ አንቀፅ 2(2) የጥበቃ ተጠቃሚ ማለት ከፍትህ ሚኒስቴር ጋር የጥበቃ ስምምነት የተፈራረመ ምስክር፣ ጠቋሚ ወይም የምስክር ወይም የጠቋሚ ቤተሰብ አባል ነው፡፡ በዚህ መልኩ ስምምነት የገባ ምስክር ወይም ጠቋሚ በአዋጅ ላይ የተቀመጡት የጥበቃ እና የጥንቃቄ እርምጃዎች ይደረጉለታል፡፡ ሆኖም እነዚህ የጥበቃ እና የጥንቃቄ እርምጃዎች ከፍተኛ የሰለጠነ የሰው ሀይል፣ ጊዜ፣ ገንዘብ እና ወጪን የሚጠይቁ በመሆኑ ከአገራችን እድገት እና የኢኮኖሚ አቅም አኳያ ለሁሉም ምስክሮች እና የወንጀል ጠቋሚዎች ከለላ እና ጥበቃ ማድረግ አይቻልም፡፡ በመሆኑም የጥበቃ እና የጥንቃቄ እርምጃዎች ማግኘት የሚቻለው በአዋጁ ላይ የተቀመጡት መስፈርቶች ተሟልተው ሲገኙ እንደሆነ በአዋጁ አንቀፅ 3 ስር ተደንግጎ ይገኛል፡፡ በዚህ አዋጅ መሠረት የሚደረጉ የጥበቃ እና ጥንቃቄ እርምጃዎች ተፈፃሚ የሚሆኑት፡-

 በሕግ የተደነገገው የፅኑ እስራት መነሻ ከግምት ሳይገባ አስር ዓመትና ከዚያ በላይ በሆነ ፅኑ እስራት ወይም በሞት ሊያስቀጣ በሚችል የወንጀል ድርጊት ተጠርጣሪ ላይ የሚሰጥ ምስክርነትን ወይም ጥቆማን ወይም የሚካሄድ ምርመራን በሚመለከት ሆኖ:-

 የወንጀል ድርጊቱ ያለምስክሩ ወይም ያለጠቋሚው ምስክርነት ወይም ጥቆማ በሌላ ማናቸውም መንገድ ሊረጋገጥ ወይም ሊደረስበት የማይችል ሲሆን እና

 በምስክሩ፣ በጠቋሚው ወይም በምስክሩ ወይም በጠቋሚው ቤተሰብ ህይወት፣ አካላዊ ደህንነት፣ ነጻነት ወይም ንብረት ላይ ከባድ አደጋ ይደርሳል ተብሎ ሲታመን ነው፡፡
ነገር ግን አዋጁ ይህንን መስፈርት ቢያስቀምጥም ፍትህ ሚኒስቴር እና የፌዴራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የጥበቃ ተጠቃሚ ላልሆኑ ምስክሮችና ጠቋሚዎችም በአዋጁ አንቀፅ 4 ስር የተቀመጡ አንዳንድ ጥበቃዎችን እንደአስፈላጊነቱ ሊያደርግ እንደሚችል ይገልፃል፡፡

ይህም በሚስጥር መያዝ ያለበት ካልሆነ በስተቀር ለጠቋሚ ጥቆማ ባቀረበበት ጉዳይ ላይ ወቅታዊ መረጃና ምክር መስጠት እንዲመሰክር ለተጠራ ምስክር የጉዞና የውሎ አበል መስጠት
በበቀል የተወሰደ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲታገድ ወይም እንዲሻር ማድረግ ወይም ተመጣጣኝ የሆነ የማካካሻ እርምጃ መውሰድ በበቀል እርምጃ ለደረሰ ጉዳት የህክምና አገልግሎት በመንግሥት ሆስፒታል በነፃ መስጠት ለምስክሩ ወይም ለጠቋሚው የምክር አገልግሎት መስጠት ወይም እንዲያገኝ ማድረግን የሚያካትት ነው፡፡

የጥበቃ እርምጃ ዓይነቶች

ለወንጀል ምስክሮችና ጠቋሚዎች የሚደረጉ የጥበቃ እና የጥንቃቄ እርምጃዎች በአዋጁ አንቀፅ 4 ስር ተዘርዝረው ይገኛሉ፡፡ የጥበቃ እና የጥንቃቄ እርምጃዎች እንደ ሁኔታው በተናጠል ወይም በጣምራ ለጥበቃ ተጠቃሚ ተፈጻሚ የሚደረጉ ሲሆን ይህም ፡-

 የአካልና ንብረት ደህንነት ጥበቃ

 የመኖሪያ ስፍራ መቀየርን ጨምሮ ደህንነቱ የተጠበቀ የመኖሪያ ቦታ መስጠት

 ማንነትንና ባለንብረትነትን መደበቅ

 ማንነትን መቀየር

 ለራስ መጠበቂያ የነፍስ ወከፍ መሳሪያ መስጠት

 መረጃ በተሰጠበት የወንጀል ድርጊት ያለመከሰስ

 መረጃ በሚሰጥበት የወንጀል ጉዳይ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊትም ሆነ በኋላ ተከሳሽ በጥበቃ ተጠቃሚው መኖሪያ ወይም የሥራ ቦታ ወይም ትምህርት ቤት አካባቢ እንዳይደርስ ማገድ

 የፍርድ ሂደት ተጀምሮ ምስክርነት እስከሚሰጥ ድረስ የምስክር ማንነት እንዳይገለጽ ማድረግ

 ምስክርነት በዝግ ችሎት እንዲሰጥ ማድረግ

 ምስክርነት በአካል ሳይታይ ከመጋረጃ በስተጀርባ ሆኖ ወይም ማንነትን በመሸፈን እንዲሰጥ ማድረግ

 ማስረጃ በኤሌክትሮኒክስ ወይም በሌላ የተለየ ዘዴ እንዲቀርብ ማድረግ

 በሚስጥር መያዝ ያለበት ካልሆነ በስተቀር ለጠቋሚ ጥቆማ ባቀረበበት ጉዳይ ላይ ወቅታዊ መረጃና ምክር መስጠት

 እንዲመሰክር ለተጠራ ምስክር የጉዞና የውሎ አበል መስጠት

 የጥበቃ እርምጃው የመኖሪያ ስፍራን ለውጥ ካስከተለ የጓዝ ማንሻ ወጪን መሸፈን

 በበቀል የተወሰደ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲታገድ ወይም እንዲሻር ማድረግ ወይም
ተመጣጣኝ የሆነ የማካካሻ እርምጃ መውሰድ

 በበቀል እርምጃ ለደረሰ ጉዳት የህክምና አገልግሎት በመንግሥት ሆስፒታል በነጻ መስጠት

 በጥበቃ እርምጃው ምክንያት ለደረሰ የገቢ ማጣት ወይም በበቀል እርምጃ ለደረሰ የመሥራት ችሎታ ማጣት የመሠረታዊ ፍላጎት ማሟያ ወጪን መሸፈን

 በጥበቃ ሥር እያለ ለደረሰ ሞት የቀብር ማስፈጸሚያ ወጪ መሸፈንና ለቤተሰብ የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ

 የጥበቃ ተጠቃሚው የሥራና የትምህርት ዕድል እንዲያገኝ መርዳት

 ለምስክሩ ወይም ለጠቋሚው የምክር አገልግሎት መስጠት ወይም እንዲያገኝ ማድረግን እንደሚያካትት በአዋጁ ላይ ተዘርዝሮ ይገኛል፡፡

የጥበቃ ስምምነት

በአዋጁ አንቀፅ 2(2) መሰረት የጥበቃ ተጠቃሚ ከፍትህ ሚኒስቴር ጋር የጥበቃ ስምምነት የተፈራረመ ምስክር፣ ጠቋሚ ወይም የምስክር ወይም የጠቋሚ ቤተሰብ አባል ሲሆን በአዋጁ አንቀፅ 8 መሰረት የአካልና ንብረት ደህንነት ጥበቃ፣ የመኖሪያ ስፍራ መቀየርን ጨምሮ ደህንነቱ የተጠበቀ የመኖሪያ ቦታ መስጠት፣ ማንነትንና ባለንብረትነትን መደበቅ እና ማንነትን መቀየር ከተመለከቱት የጥበቃ ዓይነቶች አንዱን ወይም ከአንድ በላይ ተግባራዊ ለማድረግ በሚኒስቴሩ እና በጥበቃ ተጠቃሚው መካከል የጥበቃ ስምምነት መፈረም አለበት፡፡ የጥበቃ ተጠቃሚው አካለ መጠን ያላደረሰ ወይም በፍርድ የተከለከለ ሰው ከሆነ የጥበቃ ስምምነቱ ከወላጆቹ ወይም ከአሳዳሪው ጋር የሚፈረም ሲሆን ጥበቃው የጥበቃ ተጠቃሚው አካለ መጠን ከደረሰ ወይም የህግ ችሎታውን መልሶ ካገኘ በኋላ የሚቀጥል ከሆነ ስምምነቱን የጥበቃ ተጠቃሚው ራሱ መፈረም እንዳለበት በህጉ ተደንግጎ ይገኛል፡፡

የጥበቃ ተጠቃሚ የሆነው አካለ መጠን ያላደረሰ ልጅ መረጃ ወይም ምስክርነት የሚሰጠው በወላጁ ወይም በአሳዳሪው ላይ ሲሆን፣ ወላጅ ወይም አሳዳሪ የሌለው ሲሆን፣ አስፈላጊው ጥረት ተደርጎ ወላጁን ወይም አሳዳሪውን ማግኘት ያልተቻለ እንደሆነ፣ ወላጁ ወይም አሳዳሪው በቂ ባልሆነ ምክንያት ፈቃዱን ሳይሰጥ ሲቀር ወይም በማናቸውም ምክንያት ፈቃዱን መስጠት ሳይችል ሲቀር ሚኒስቴሩ በአንቀፅ 9 መሰረት ከልጁ ጋር ልዩ የጥበቃ ስምምነት ሊፈራረም ይችላል፡፡.....................
............ ነገር ግን አካለ መጠን ካላደረሰ ልጅ ጋር የተደረገ ልዩ የጥበቃ ስምምነት ከተፈረመበት ዕለት ጀምሮ ባሉት አስር ቀናት ውስጥ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርቦ መፅደቅ አለበት፡፡ ፍርድ ቤቱም አካለ መጠን ያላደረሰው ልጅ ጥቅምና ደህንነት ይበልጥ ሊረጋገጥ የሚችልበትን ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት የጥበቃ ስምምነቱን መሻር፣ ማፅደቅ ወይም ማሻሻል ይችላል፡፡

በጠቋሚዎችና በምስክሮች ላይ ወንጀል መፈፀም የሚያስከትለው ተጠያቂነት

ምስክሮች እና ወንጀል ጠቋሚዎች ከላይ የተጠቀሱ ጥበቃዎች የሚደረግላቸው ከመሆኑም በተጨማሪ ምስክሮች በመሆናቸው ወይም ወንጀል በመጠቆማቸው ጉዳት የሚያደርስባቸው ማንኛውም ሰው በወንጀል ይጠየቃል፡፡ በ1996 በወጣው የወንጀል ህግ አንቀፅ 444 መሰረት ማንኛውም ሰው ወንጀልን በሚመለከት ለፍትህ አካለት ጥቋማ ወይም መረጃ የሰጠ ሰው ላይ ወይም በምስክርነት በቀረበ ሰው ላይ ማናቸውንም ጥቃት፣ ተፅኖ ወይም ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ በቀላል እስራት ወይም በመቀጮ የሚቀጣ ከመሆኑም በላይ የተፈፀመው ድርጊት በምስክሩ ላይ ከባድ የአካል ወይም የጤና ጉዳት ወይም ሞት አስከትሎ ከሆነ ላስከተለው ጉዳት አግባብ ባለው የወንጀል ድንጋጌ ተጠያቂ ይሆናል፡፡

ማጠቃለያ

ወንጀል ጠቋሚዎች እና ምስክሮች ለፍትህ ተባባሪ በመሆናቸው ጥቃት እንዳይደርስባቸው ጥበቃ ማድረግ ህብረተሰቡ ወንጀልን መካላከል ሂደት ያለስጋት ተሳታፊ እንዲሆን የሚያደርግ በመሆኑ ለህጉ ለተግባራዊነት ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል፡፡

በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
https://t.me/lawsocieties
unpublished cassation V. 8 - Reduced - Reduced.pdf
5.2 MB
[ File : Unpublished Cassation V.8.pdf ]
ያልታተሙ የሰበር ውሳኔዎች

ቅፅ - 8

በዳንኤል ፍቃዱ ( ጠበቃና የህግ አማካሪ) ተሰብስበው የተዘጋጁ

ውሳኔዎቹ ሁሉም በ2014 ዓ.ም. የተወሰኑ ናቸው።
ቀጣሪ ድርጅቶች ከግል የትምህርት ተቋማት የተመረቁ ተቀጣሪዎችን የትምህርት ማስረጃዎች ሕጋዊነት እንዲያረጋግጡ ተጠየቁ ----------------------------------------------------
የመንግሥትም ሆነ የግል ቀጣሪ ድርጅቶች ከግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተመረቁ ሠራተኞቻቸውን እና አዲስ ሠራተኞችን ከመቅጠራቸው በፊት የተቀጣሪዎቹን የትምህርት ማስረጃዎች ሕጋዊነት እና ትክክለኛነት መረጋገጥ እንደሚገባቸው የኢፌዴሪ ትምህርት እና ሥልጠና ባለሥልጣን አሳሰበ።
.....
ተገልጋዮች ወይም ሕጋዊ ወኪሎች የማረጋገጫ አገልግሎት ለማግኘት ወደ ባለሥልጣኑ ከመሔዳቸው በፊት የሚከተሉትን መስፈርቶች በማሟላት አገልግሎቱን ማግኝት እንደሚችሉም ገልጿል።

መስፈርቶቹም፦

1. በጀርባው ላይ የኮሌጁ ኃላፊ እና ሬጅስትራር ፊርማ እና ማህተም ያለበት ኦሪጅናል ዲግሪ ከኮፒ ጋር በማያያዝ፤
2. በጀርባው ላይ የኮሌጁ ኃላፊ እና ሬጅስትራር ፊርማ እና ማህተም ያለበት ኦሪጅናል ትራንስክሪፕት/Student Copy/ ከኮፒ ጋር በማያያዝ፤
3. ዲግሪውን ለመማር በመግቢያነት የተያዘ ኦሪጅናል ዲፕሎማ ወይም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሰርቲፊኬት ከኮፒ ጋር በማያያዝ፤
4. ዲግሪውን ለመማር በመግቢያነት የተያዘው የ12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት ከሆነ በትምህርት ምዘናዎች እና ፈተናዎች አገልግሎት ድርጅት ትክክለኛነቱ የተረጋገጠ ከኮፒ ጋር በማያያዝ፤
5. ዲግሪውን ለመማር በመግቢያነት የተያዘው ዲፕሎማ ከሆነ ዲፕሎማው በተገኘበት ክልል የቴክኒክ እና ሙያ ኤጀንሲ ወይም የዞን/የከተማ መስተዳደር የሥራ እና ሥልጠና ቢሮ ትክክለኛነቱ የተረጋገጠ እንዲሁም የደረጃ 4 ብቃት ማረጋገጫ(COC) ካገኙበት ማዕከል የተረጋገጠ መሆን አለበት ከኮፒ ጋር በማያያዝ እና
6. የስም ለውጥ ካለ የፍርድቤት ውሳኔ ከኮፒ ጋር በማያያዝ ናቸው።

ከዚህ በተጨማሪ የማስተርስ ዲግሪ ለማረጋገጥ በቅድሚያ የመጀመሪያው ዲግሪ ከላይ በተገለጸው መንገድ መረጋገጥ እንዳለበት የኢፌዴሪ ትምህርት እና ስልጣና ባለሥልጣን አሳስቧል
EBC
https://t.me/lawsocieties
አለሕግAleHig ️
Photo
ከህገወጦች እራሳችንንና ህብረተሰባችንን ልንከላከል ይገባል!
============ https://t.me/lawsocieties
በህገወጥ መንገድ የሚንቀሳቀሱ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የራሳቸውን ማህበራዊ ሚዲያ ገጽ በመጠቀም እንዲሁም በአንዳንድ አካባቢዎች በተሽከርካሪ ከቦታ ቦታ በመዟዟር እና ቅስቀሳ በማድረግ ከባለሥልጣኑ የማስተማር ፈቃድ ያገኙ በማስመሰል ህብረተሰቡን በማሳሳት ላይ ይገኛሉ፡፡
ስለሆነም በከፍተኛ የትምህርት ተቋም ተመዝግቦ ለመማር የፈለገ አንድ ተማሪ ለመማር ከመወሰኑና ከመመዝገቡ በፊት ሊማርበት ያሰበው ተቋም፡-
* ለመማር የፈለገው የትምህርት ዓይነት በመረጠው ካምፓስ ፈቃድ ያለው መሆኑን ማጣራት፤
* በመረጠው በተቋሙ ሊማር ያሰበው የትምህርት ዓይነት ያገኘው ፈቃድ ከመቼ እስከ መቼ እንደተሰጠው ወይም የፈቃድ እድሳት የተደረገለትን ጊዜ ማጣራት ፤
* ያገኝው ፈቃድ በትምህርት አሰጣጥ ዘዴ(መደበኛ፣ የርቀት እና ድንበር ተሸጋሪ እና ኦንላይን ) መሆኑን ማጣራት እና
* የተፈቀደለት ተማሪ ብዛት በቁጥር ስንት እንደሆነ ማጣራት ናቸው፡፡
ህብረተሰቡም ስለትምህርት ጥራት እውን መሆን በያግባኛል፣ በባለቤትነት ስሜት በየአካባቢው እንቅስቃሴ ሲያደርግ ህገ-ወጥ የትምህርት ተቋማትን በማጋለጥ ዘብ ሊቆም ይገባል፡፡ ከባለሥላጣኑ ጋር በቅርበት እጅ እና ጓንት በመሆን ይህን ማድረግ ከተቻለ ህገ-ወጥ ተቋማት በተማሪው፣ በወላጆች እንዲሁም በሀገር ላይ የሚያደርሱት ኪሳራ መቀነስ ይቻላል፡፡ህግ የጣሱትንም በፍትሀብሄር እና በወንጀል ተጠያቂ እንዲሆኑና ቅጣታቸውን እንዲያገኙ ለማድረግም ምቹ ሁኔታዎችን ይፈጥራል፡፡
መላው የሀገራችን የህብረተሰብ ክፍል የትምህርት ጥራትን ማረጋግጥ ለአንድ አካል ብቻ የሚተው አለመሆኑን በመረዳት እገዛቸውን አጠናክረው መቀጠል ተገቢ ነው፡፡ እንዲሁም በተለያዩ መዋቅሮች ላይ የሚገኙ የመንግስት አካላትም ከባለሥልጣኑ ጎን በመሆን የትምህርት ጥራትን ለመጠበቅ በተጀመሩ አበረታች ስራዎች ላይ ትብብራቸው ከመቼውም ጊዜ በላቀ መልኩ አጠናክረው መቀጠል ይጠበቅባቸዋል፡፡ጥራት ያለው የትምህርት ስርዓት እውን መሆን የአንድ ሀገር እድገት እውን ሆነ ማለት ነውና ሁላችንም የበኩላችንን አስተዋጽኦ በማበርከት የዜግነት ግዴታችንን ልንወጣ ይገባል፡፡
በኢፊዲሪ ትምህርትና ስልጣና ባለሥልጣን
ታህሳስ 27 ቀን 2015 ዓ.ም፤ አዲስ አበባ
https://t.me/lawsocieties
በፌደራል ማናቸውም ፍርድ ቤት የወንጀል ክስ ተመስርቶቦት ጠበቃ ለማቆም የገንዘብ አቅም ከሌሎት ፈፅሞ አይጨነቁ የፌደራል ፍርድ ቤቶች የተከላካይ ጠበቆች ፅህፈት ቤት በነፃ ሙሉ የጥብቅና አገልግሎት በትጉህ ባለሙያዎቹ ይሰጥዎታል ከእርሶ የሚጠበቀው ለተከሰሱበት የወንጀል ችሎት የመንግስት ጠበቃ ይመደብልኝ በማለት መጠየቅ ብቻ ነው።
https://t.me/lawsocieties
ሃሰተኛ ማስረጃን ለማረጋገጥ የሞከሩ ሶስት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
.......................
ታህሳስ 27/2015 (ኢዜአ) በኤጀንሲው ዋና መስርያ ቤት ቀርበው ሃሰተኛ የልደት ፣ ፍቺ እና ያላገባ ማስረጃ ለማረጋገጥ የሞከሩ ሶስት ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአዲስ አበባ የወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ ገለጸ።

1ኛው ግለሰብ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማው ወረዳ 3 ጽህፈት ቤት የተሰጠ የፍቺ ምዝገባ ሰርተፍኬት አስመስሎ በማሰራት በጥብቅና ውክልና ለማረጋገጥ ታህሳስ 26 ቀን 2015 የቀረበ ሲሆን በተደረገ ማጣራት በእጁ የተገኘው የግለሰቡ የነዋሪነት መታወቂያ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ወረዳ 12 የተሰራ ሃሰተኛና ተመሳስሎ የተሰራ መሆኑ መረጋገጡ ተገለጿል።

2ኛዋ ግለሰብ በየካ ክፍለ ክተማ ወረዳ 1 ጽህፈት ቤት የተሰጠ የልደት እና ያላገባ ማስረጃ እንዲሁም ይህን የነዋሪነት መታወቂያ ተመሳስሎ የተሰራ ታህሳስ 25 ቀን 2015 ይዛ በመቅረብ ለማረጋገጥ ስትሞክር በቁጥጥር የዋለች መሆኑ ተመላክቷል።

3ኛው ግለሰብ በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ጽህፈት ቤት በተመሳሳይ ሁኔታ የተሰራ የልደት ማስረጃ ዛሬ ታህሳስ 27 ይዞ በመቅረብ ለማረጋገጥ ሲሞክር በተደረገ የሰነድ ማጣራት ሃሰተኛ መሆናቸው በመረጋገጡ የኤጀንሲው ስነ-ምግባር እና ፀረ ሙስና ክፍል በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ የተደረገ ሲሆን በሁሉም ተጠርጣሪዎች ላይ ተጨማሪ ምርመራ እየተደረገ እንደሚገኝ ኤጀንሲው አስታውቋል።

በከተማችን ከግዜ ወደ ግዜ ተመሳስለው የሚሰሩ ሃሰተኛ ሰነዶች እየተበራከቱ የመጡና ከፍተኛ የዘርፉ ስጋት እየሆኑ የመጡ መሆኑ መምታጣቸውን ገልጾ ህብረተስቡ ከመሰል ወንጀል ተግባራት ራሱን እንዲጠብቅና ሃሰተኛ ሰነድ ሲያዘጋጅ ሲመለከተ ጥቆማ እንዲሰጥ ተቋሙ አሳስቧል።
ሰነዶች ማረጋገጫ
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
በኑዛዜ የሚከናወኑት ተግባሮች ስጦታ (legacy) ወይንም የክፍያ ደንብ (Rule of partition) ሊሆኑ ይችላሉ፡፡
ሰበር መዝገብ ቁጥር 201100
በመርህ ደረጃ አንድ ሰው ከውርስ ሀብቱ መካከል አንድን ንብረት ለወራሾቹ መስጠቱ የኑዛዜ ስጦታ የማያሰኘው ሲሆን ፣ ይልቁንም ይህ ዓይነቱን ኑዛዜ ሕጉ የሚቀበለው እንደ አንድ የክፍያ ደንብ በመሆኑ አንድ አውራሻ ለወራሹ አንድን ንብረት ቢናዘዝለት የኑዛዜ አፈፃፀም ስጦታ(legacy) አፈፃፀምን መከተል ሳይሆን የክፍያ ደንብ (Rule of partition) በመከተል የሚከናወን ይሆናል፡፡

ሆኖም በኑዛዜው ላይ የሚሰጠው የክፍያ መጠን በመገለፁ ብቻ ሁል ጊዜ የክፍያ ደንብ ሊባል የሚችል ሊሆን አይችልም፡፡ በመሆኑም የተሰጠው የንብረት መጠን ከሟቹ የውርስ ንብረት ጋር ታይቶ ውጤቱም በዚሁ ረገድ መታየት አለበት፡፡
https://t.me/lawsocieties
ከደረሰኝ ጋር የተገናኙ ወንጀሎች እና ቅጣታቸው
https://t.me/lawsocieties
I. ማንኛውም ደረሰኝ የመስጠት ግዴታ ያለበት ታክስ ከፋይ ያለደረሰኝ ግብይት ያከናወነ እንደሆነ ከብር 25ሺ (ሃያ አምስት ሺ ብር) እስከ ብር 50ሺ (ሃምሳ ሺ ብር) የገንዘብ መቀጫ እና ከሦስት እስከ አምስት ዓመት በሚደርስ ጽኑ እሥራት ይቀጣል፡፡

II. በአንድ ግብይት በተሰጡ ተመሳሳይ የደረሰኝ ኮፒዎች ላይ የተለያዩ ዋጋዎችን በመመዝገብ የሽያጭ ዋጋን ያሳነሰ ማንኛውም ሰው ብር 100ሺ (አንድ መቶ ሺ ብር) እና ከአምስት ዓመት እስከ ሰባት ዓመት በሚደርስ ጽኑ እሥራት ይቀጣል፡፡

III. የሽያጩ ትክክለኛ ዋጋ ከብር 100ሺ (አንድ መቶ ሺ ብር) የሚበልጥ ከሆነ በዚህ ተራ ቁጥር (||) መሠረት የሚጣለው ቅጣት በደረሰኞቹ ላይ ከተመለከቱት ከፍተኛው የገንዘብ መጠን እና ከሰባት ዓመት እስከ አስር ዓመት የሚደርስ ጽኑ እሥራት ይቀጣል፡፡

IV. ግብይት ሳይፈጸም ደረሰኝ የሰጠ ወይም የተቀበለ ሰው ከብር 100ሺ (አንድ መቶ ሺ ብር) እስከ ብር 200ሺ (ሁለት መቶ ሺ ብር) በሚደርስ የገንዘብ ቅጣት እና ከሰባት ዓመት እስከ አስር ዓመት በሚደርስ ጽኑ እሥራት ይቀጣል፡፡

V. በዚህ ተራ ቁጥር (IV) የተመለከተው ደረሰኝ ከብር 200ሺ (ሁለት መቶ ሺ ብር) የሚበልጥ የገንዘብ መጠን የያዘ እንደሆነ በዚህ ተራ ቁጥር (|) መሠረት የሚጣለው ቅጣት በደረሰኙ ከተገለጸው የገንዘብ መጠን ጋር እኩል በሆነ የገንዘብ ቅጣት እና ከአስር ዓመት እስከ አስራ አምስት ዓመት የሚደረስ ጽኑ እሥራት ይቀጣል፡፡

VI. ባለሥልጣኑ ሳይፈቅድለት የታክስ ደረሰኝ ያተመ ሰው ከብር 300ሺ (ሦስት መቶ ሺ ብር) እስከ ብር 500ሺ (አምስት መቶ ሺ ብር) በሚደርስ የገንዘብ ቅጣት እና ከሁለት ዓመት እስከ አምስት ዓመት በሚደርስ ጽኑ እሥራት ይቀጣል፡፡

VII. በዚህ ተራ ቁጥር (VI) መሠረት ጥፋተኛ የተባለ ሰው ወንጀሉን ለሁለተኛ ጊዜ ፈጽሞ ጥፋተኛ መሆኑ ከተረጋገጠ የህትመት መሣሪያው እና የማተሚያ ድርጅቱ ይወረሳል፣ የንግድ ፈቃዱም ይሰረዛል፡፡
(የገቢዎች ሚኒስቴር)
https://t.me/lawsocieties