አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
ታስረው እንዲቀርቡ ታዘዘ።

የፍርድ ቤት መጥሪያ ፈርመው ወስደው ሳይቀርቡ የቀሩት የአ/አ ቤቶች ኮርፖሬሽን ኃላፊ አቶ ሽመልስ ታምራት ታስረው እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ተሰጠ።

የኮንዶሚኒዬም ቤቶች ዕጣ ተጭበርብሯል ተብሎ የከባድ ሙስና ወንጀል በቀረበባቸው ተከሳሾች ላይ የዓቃቢህግ 2ኛ ምስክር ሆነው የተቆጠሩት የአ/አ ቤቶች ኮርፖሬሽን ኃላፊ አቶ ሽመልስ ታምራት መጥሪያ ፈርመው ተቀብለው ባለመቅረባቸው ምክንያት ነው ታስረው እንዲቀርቡ ዛሬ ትዕዛዝ የተሰጠው።

  ትዕዛዙን የሰጠው በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።

በአ/አ ከተማ በሀምሌ 1ቀን 2014 ዓ/ም ከኮንዶሚኒዬም ቤቶች ዕጣ አወጣጥ ጋር ተያይዞ  ዕጣው ተጭበርብሯል ተብሎ የአ/አ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቴክኖሎጂ ልማት  ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሙሉቀን ሀብቱን እና  ምክትል ቢሮ ሀላፊ የሆኑትን አቶ አብርሀም ሰርሞሌን ጨምሮ በአጠቃላይ በ 11 ተከሳሾች ላይ በየደረጃው የከባድ ሙስና ወንጀል ክስ መመስረቱ ይታወሳል።

ተከሳሾቹ  ወንጀሉን አለመፈጸማቸውንና ጥፋተኛ አለመሆናቸውን ገልጸው የሰጡትን የዕምነት ክህደት ቃል ተከትሎ ዓቃቢህግ ምስክር  እንዲሰሙለት ጠይቆ ነበር።

በዚህ መሰረት ዓቃቢህግ በሀምሌ 1 ቀን 2014 ዓ/ም በአ/አ ከተማ ወጥቶ ከነበረው የ14ኛ ዙር 20/80  እና የ3ኛ ዙር የ40/60  ከኮንዶሚኒዬም ቤቶች ዕጣ አወጣጥ  ስርዓት ጋር ተያይዞ እንዲሁም  ለምቷል የተባለው ሶፍትዌርን የሚመለከት እና የተደረገ የኦዲት ስርዓትን ላይ ያተኮረ ምስክርነት እንዲሰማለት  የምስክር ጭብጥ  ካስመዘገበ በኋላ በህዳር 22 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ ፍርድ ቤቱ የዓቃቢህግ ምስክር ቃል መሰማት ጀምሮ ነበር።

ፍርድ ቤቱ  እስካሁን የ 8 የዓቃቢህግ ምስክሮችን ቃል ያዳመጠ ሲሆን በ2ኛ የዓቃቢህግ ምስክር ሆነው የተቆጠሩት የአ/አ ቤቶች ኮርፖሬሽን ኃላፊ አቶ ሽመልስ ታምራት ግን  መጥሪያ ደርሷቸው ፈርመው የወሰዱ ቢሆንም በችሎት ሳይቀርቡ ቀርተዋል።ፍርድ ቤቱም ግለሰቡ በፖሊስ ታስረው በይደር እንዲቀርቡ ትዕዛዝ  ሰጥቷል።

Via:- Tarik Adugna
https://t.me/lawsocieties
አከፋፋይ ምረጡ ማለት እና ዋጋ ተምኜላችሁ ሽጡ ማለት ነፃ ገበያ ማለት አይደለም😝‼️

የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ፦ ከዛሬ ጀምሮ ሲሚንቶ በየትኛውም ቦታ ቁጥጥር እና ክትትል ሳይደረግበት #በነጻ_ገበያ ይካሄዳል። ስለዚህ ሲሚንቶ ፋብሪካዎች አከፋፋዮችን እና ቸርቻሪዎችን መምረጥ የፋብሪካዎቹ እድል ነው! የፋብሪካዎቹ የመሸጫ ዋጋ ለጊዜው ምርታማነት እስከሚጨምር ድረስ የፋብሪካ ዋጋ በስድስት ወር አንድ ጊዜ #በሚኒስቴሩ እንደሚወሰን ገልጿል።

#አማካይ_የሲሚንቶ_ዋጋ
- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 590.3ብር
- አሁን ፋብሪካዎች ያስገቡት የመሸጫ ዋጋ ➤ 1014.6ብር
- እንዲሸጡ የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤ 758.1ብር

ታዲያ ይህ ማለት እኮ መባል ያለበት ሲሚንቶ አምራቾች አከፋፋይ መርጣችሁ በተተመነላችሁ ዋጋ ሽጡ እንጂ በትርጉም ደረጃ #ነፃ_ገበያ ማለት አይደለም!
በዋሲሁን በላይ

https://t.me/lawsocieties
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በፓስተር ዮናታን አክሊሉ፣ በነቢይ ኢዩ ጩፋ እና የሚያገለግሉበት ቤተ ክርስቲያን ላይ ክስ መሠረተች
=======#===
ረቡዕ ታሕሳስ 12 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በፓስተር ዮናታን አክሊሉ፣ በአዲስ ኪዳን ካህናት ቤተ ክርስቲያን፣ በክራይስት አርሚ ኢንተርናሽናል ቤተ ክርስቲያን እና በነቢይ ኢዩ ጩፋ ላይ ክስ መሠረተች።

በቤተክርስቲያንቷ ሕግ አገልግሎት መምሪያ በኩል ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ዳይሬክቶሬት የተላከው ክስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ ያነጣጠረ የጥላቻ ንግግርና አደገኛ የሆነ የሃይማኖትን ክብር የሚነካ የአምልኮ ሥርዓትና እምነትን የሚያንቋሽሽ የዘለፋ እና ሐሰተኛ ንግግር በመፍጠር ለሁከትና ብጥብጥ መነሻ የሚሆን ድርጊት በፈጸሙ ግለሰቦችና ተባባሪ ተቋማት ላይ የወንጀል ምርመራ እንዲጣራ የሚጠይቅ ነው።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የክስ ዝርዝር ከሥር ተያይዟል።
https://t.me/NegereFej
220830.pdf
825.3 KB
ከባንክ ሂሳቤ ላይ ገንዘብ አላአግባብ ወጪ በመደረጉ ባንኩ ገንዘቡን እንዲመልስ የሚል ክስ ሲቀርብ የፎረንሲክ ምረመራውን ውጤት ብቻ መሠረት በማድረግ ባንኩን ለክሱ ኃላፊ ማድረግ መሰረታዊ የሕግ ስህተት ነው።

በወጪ ማዘዣው ላይ የተመለከተዉ ፊርማ በሲስተሙ ላይ ከተመለከተዉ የፊርማ ናሙና ጋር ተመሳሳይ መሆን አለመሆኑን ለማረጋገጥ የወጪ ማዘዣው ላይ የተመለከተዉ ፊርማ ከናሙና ፊርማ ጋር የሚመሳሰል መሆን አለመሆኑ ገለልተኛ በሆነ አካል ታይቶ መረጋገጥ ይኖርበታል።

በመሆኑም ክስ ከቀረበበት ባንክ ዉጪ በሌሎች ባንኮች ከወጪ ማዛዣ ክፍያ ጋር በተያያዘ ልምድ ባላቸዉ የባንክ ባለሙያዎች እንዲታይ በማድረግ ባንኩ ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ ግዴታዉን የተወጣ መሆን አለመሆኑ ማረጋገጥ ይገባል፡፡ የባለሂሳቡ ባንክ ደብተር ቀርቦ ሂሳቡ ተቀንሶ የተጻፈ መሆን አለመሆኑ ሆነ የባለሂሳቡ መታወቂያ በማየት ባንኩ ያረጋገጠ መሆን አለመሆኑ ደግሞ በሰው ማስረጃ ሆኖ የባንክ ሂሳብ ደብተሩ ካለ በማስቀረብ መረጋገጥ ይኖርበታል።

ሰ/መ/ቁ. 220830 ጥቅምት 29 ቀን 2015 ዓ/ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
#Bank #law #lawyer
#SAMUELGIRMA
Join 👈
https://t.me/lawsocieties
One_person_private_limited_Company_vs_Limited_Liability_Partnership.pdf
174.7 KB
ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (One-person private limited Company) እና ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበር (Limited Liability Partnership)
Via በአበጀ ካሣሁን
🔷Vacancy for Law office🔷
                                              
1. Junior Accountant
2. Junior Cashier and secretary
3. Accountant 1-2 year experience
4. Guday Asfetsami (ጉዳይ አስፈፃሚ)

👉 How to Apply 👈
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
lawsocieties@gmail.com
Or
consultantentrust@gmail.com
Deadline
Jan 10, 2023

Share for your friends
     👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
የወንጀል ምርመራና የፍርድ ቤቶች ሚና

በዚህ ጽሁፍ (Article) ዓላማም በኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች[2] በወንጀል የምርመራ ሂደት ውስጥ ምን ምን ዓይነተኛ ተግባርና ኃላፊነት አሉባቸው፣ ፍርድ ቤቶች ከወንጀል ምርመራ ጋር ተያይዞ ተግባርና ኃላፊነታቸውን በመወጣት ረገድ በተግባር እየተስተዋሉ ያሉ ችግሮችስ ምንድን ናቸው የሚሉትን ፍሬ ጉዳዮች ከመረመረ በኋላ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ማስቀመጥና በጉዳዬ ዙሪያ ተጨማሪ የክርክርና የውይይት መነሻ ነጥብ ለመፍጠር ነው። ጽሁፉ በሁለት ክፍሎች የተደራጀ ሲሆን በመጀመሪያው ክፍል ‹‹በኢትዮጵያ የወንጀል ፍትሕ አስተዳደር በተለይም በወንጀል የምርመራ ሂደት ውስጥ ምን ምን ዓይነተኛ ተግባርና ኃላፊነት አሉባቸው›› የሚለው የሚቀርብ በሁለተኛው ክፍል ደግሞ ‹‹የወንጀል ምርመራን ከመምራትና ከመቆጣጠር ጋር በተያያዘ በፍርድ ቤቶች በኩል ምን ምን ችግሮች ይስተዋላሉ፣ ለችግሮቹ በመፍትሔነት ሊጠቀሱ የሚችሉ ሃሳቦችን›› የሚነሱበት ይሆናል።

በስለሺ መኳንንት አንዳርጌ


https://www.abyssinialaw.com/blog/criminal-investigation-and-the-role-of-courts


https://t.me/lawsocieties
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Lawyer Mike 🔊የህግ ባለሙያ)
ሙስናን መታገል በፋሽን ወይስ በፓሺ
👇👇👇የቀጠለ..👆👆👆

የልቦና ውቅር ለውጥ‼️

The Fighting against corruption with fashion or passion?

Key Note Speaker;
Samuel Kassahun:
Director of Transparency International Ethiopia
👆👆👆👆👆👆👆👆👆

የትራንስፓረንሲ ኢንተናሽናል ኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳሙኤል ካሳሁን

እሁድ ምሽት 2:30 ቀጥታ ስርጭት

🔘 Live on Telegram 👈👈
https://t.me/lawsocieties
#በአለ_ህግ ቴሌግራም ቻናል ይጠብቁን።

ሼር በማድረግ ላልሰማ ያሰሙ ወደ ወይይቱ ይጋብዙ👆👆👆
https://t.me/lawsocieties
ቦሌ አየር ማረፊያ ውስጥ ያለው ሙስና ቅኝት ይደረግበት!

ይህን ጉዳይ ከዚህ በፊትም ብዬዋለሁ፣ አሁንም ልድገመው። በተለይ ፓስፖርታቸው ላይ የጉዞ ታሪክ የሌላቸው ዜጎች ከሀገር ለመውጣት ከ30 ሺህ እስከ 80 ሺህ ብር ገንዘብ እየተጠየቁ ነው። አልከፍልም ያሉ የንግድ ፈቃድ፣ የስራ ቅጥር ኮንትራት ወዘተ አምጡ እየተባሉ እየተሰቃዩ ነው።

የሚሄዱበት ሀገር ቪዛ ሰጥቷቸው አየር ማረፊያ ላይ የገንዘብ ድርድር ምን ማለት ነው?

ብዙዎች በዚህ ምክንያት ከጉዞ ተስተጓጉለው ከትምህርት፣ ከስብሰባ ወይም ከሌላ ያሰቡት ጉዳይ ሳይደርሱ ቀርተዋል። ግን እንዴት እንደሌሎች ሀገራት የሀገሪቱን ድንቅ መስህቦች ማስተዋወቂያ መሆን ይገባው የነበረ ተቋም ላይ እንዲህ አይነት ሙስና በፈጣጣው መጣ?

#GetReal with corruption!

Elias Meseret