ሐሰተኛ የሕክምና ምስክር ወረቀት መስጠት
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ሐሰተኛ የሕክምና ምስክር ወረቀት መስጠት በወንጀል የሚያስቀጣ ድርጊት ነው ፡፡ ስለሆነም ማንኛውም ሐኪም ፡ የጥርስ ሐኪም ፡ የመድሀኒት ቅመማ ባለሙያ/ፋርማሲስት/ ፡ የእንስሳት ሐኪም ፡ አዋላጅ ወይም በሕክምና ሙያው ምስክር ወረቀት ለመስጠት ፍቃድ ያለው ማንኛውም ሰው የምስክር ወረቀቱ ስራ ላይ እንደሚውል እያወቀ ፡ ለተቀባዩ ሰው የማይገባ ጥቅም ለማስገኘት ወይም የሌላውን ሰው ሕጋዊ ጥቅም የሚጎዳ ሐሰተኛ የሕክምና ምስክር ወረቀት አዘጋጅቶ የሰጠ እንደሆነ በቀላል እስራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል ፡፡
ወንጀሉ በተደጋጋዊ ጊዜ የተፈፀመ ከሆነ ደግሞ ፡ የሐኪሙ የሙያ ፍቃድ ሊሻር ይችላል ፡፡ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 387 እና 123 (ሐ)
ሐሰተኛ የሕክምና ምስክር ወረቀት መስጠቱ የተከናወነው በስጦታ ፤ በስጦታ ተስፋ ወይም በሌላ ጥቅም እንደሆነ ፤ ቅጣቱ ከአስር አመት የማይበልጥ ፅኑ እስራትና ከ 50 (ሀምሳ) ሺ ብር የማይበልጥ መቀጮ ይሆናል ፡፡ በተጨማሪም ሐሰተኛውን የሕክምና ምስክር ወረቀት ያዘጋጀው የመንግስት ሠራተኛ ሆኖ ወንጀሉን የፈፀመው በዚሁ ስልጣኑ እንደሆነ የወንጀል ቅጣቱ እስከ አስራ ኣምስት አመት ሊደርስ ይችላል ፡፡ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 387 (3)
ማንም ሰው በሀሰት የተዘጋጀ የምስክር ወረቀት መሆኑን እያወቀ ሌላውን ሰው ለማታለል የተገለገለበት ከሆነ ደግሞ ፤ በቀላል እስራት ወይም በገንዘብ መቀጮ ይቀጣል ማለት ነው ፡፡
የወንጀል ሕግ አንቀፅ 387 (4)
በሳሙኤል ግርማ
https://t.me/lawsocieties
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ሐሰተኛ የሕክምና ምስክር ወረቀት መስጠት በወንጀል የሚያስቀጣ ድርጊት ነው ፡፡ ስለሆነም ማንኛውም ሐኪም ፡ የጥርስ ሐኪም ፡ የመድሀኒት ቅመማ ባለሙያ/ፋርማሲስት/ ፡ የእንስሳት ሐኪም ፡ አዋላጅ ወይም በሕክምና ሙያው ምስክር ወረቀት ለመስጠት ፍቃድ ያለው ማንኛውም ሰው የምስክር ወረቀቱ ስራ ላይ እንደሚውል እያወቀ ፡ ለተቀባዩ ሰው የማይገባ ጥቅም ለማስገኘት ወይም የሌላውን ሰው ሕጋዊ ጥቅም የሚጎዳ ሐሰተኛ የሕክምና ምስክር ወረቀት አዘጋጅቶ የሰጠ እንደሆነ በቀላል እስራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል ፡፡
ወንጀሉ በተደጋጋዊ ጊዜ የተፈፀመ ከሆነ ደግሞ ፡ የሐኪሙ የሙያ ፍቃድ ሊሻር ይችላል ፡፡ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 387 እና 123 (ሐ)
ሐሰተኛ የሕክምና ምስክር ወረቀት መስጠቱ የተከናወነው በስጦታ ፤ በስጦታ ተስፋ ወይም በሌላ ጥቅም እንደሆነ ፤ ቅጣቱ ከአስር አመት የማይበልጥ ፅኑ እስራትና ከ 50 (ሀምሳ) ሺ ብር የማይበልጥ መቀጮ ይሆናል ፡፡ በተጨማሪም ሐሰተኛውን የሕክምና ምስክር ወረቀት ያዘጋጀው የመንግስት ሠራተኛ ሆኖ ወንጀሉን የፈፀመው በዚሁ ስልጣኑ እንደሆነ የወንጀል ቅጣቱ እስከ አስራ ኣምስት አመት ሊደርስ ይችላል ፡፡ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 387 (3)
ማንም ሰው በሀሰት የተዘጋጀ የምስክር ወረቀት መሆኑን እያወቀ ሌላውን ሰው ለማታለል የተገለገለበት ከሆነ ደግሞ ፤ በቀላል እስራት ወይም በገንዘብ መቀጮ ይቀጣል ማለት ነው ፡፡
የወንጀል ሕግ አንቀፅ 387 (4)
በሳሙኤል ግርማ
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
የሰብዓዊ_መብቶች_ዓለም_አቀፍ_ቃል_ኪዳኖች_በአማርኛ፣_2001_ዓ_ም.pdf
621.5 KB
International Covenant on Civil and Political Rights (የሰብዓዊ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃል ኪዳኖች) በ2001 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን (በቀድሞ አጠራር የአትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን) በአማርኛ የተዘጋጀ
Legal Advisor
Reach Ethiopia
Addis Ababa Educational Requirements: Qualification Licensed and proven experience as a Legal Advisor in business environment; Demonstrated ability to create legal response with defensive or proactive strategies; High degree of professional ethics and integrity; Sound judgement and ability to analyze situations and information; LLM from accredited Law school; Minimum of 5 years of practical experience in providing consultancy services in the legal area for business...
Required Experience:
Not Provided https://www.greatethiopiajobs.com/jobs/job-detail/job-Legal-Advisor-job-at-Reach-Ethiopia-64134?utm_campaign=google_jobs_apply&utm_source=google_jobs_apply&utm_medium=organic
Reach Ethiopia
Addis Ababa Educational Requirements: Qualification Licensed and proven experience as a Legal Advisor in business environment; Demonstrated ability to create legal response with defensive or proactive strategies; High degree of professional ethics and integrity; Sound judgement and ability to analyze situations and information; LLM from accredited Law school; Minimum of 5 years of practical experience in providing consultancy services in the legal area for business...
Required Experience:
Not Provided https://www.greatethiopiajobs.com/jobs/job-detail/job-Legal-Advisor-job-at-Reach-Ethiopia-64134?utm_campaign=google_jobs_apply&utm_source=google_jobs_apply&utm_medium=organic
Greatethiopiajobs
greatethiopiajobs.com - greatethiopiajobs Resources and Information.
greatethiopiajobs.com is your first and best source for all of the information you’re looking for. From general topics to more of what you would expect to find here, greatethiopiajobs.com has it all. We hope you find what you are searching for!
ልጓም ያጣው የመኪና እና የቤት ንግድ
ንግድ በተለያዩ የኢኮኖሚ ተዋናዮች መካከል የሚደረግ በፍቃደኝነት ላይ የተመሠረተ ልውውጥ ነው። ንግድ እንደየአገሩ ነባራዊ ሁኔታ በሚወጡ ሕጎች የሚተዳደር ሲሆን፣ መንግሥታትም የአገራቸውን የንግድ ስርዓት በሚያወጧቸው ሕጎች መሠረት ይቆጣጠራሉ።
በኢትዮጵያም ንግድ የረዥም ጊዜ ታሪክ ያለው ሲሆን፣ ዓለም ዐቀፋዊ መልክ ባለው አሁናዊ የንግድ ስርዓትና ገበያ ውስጥ በርካታ ጥያቄዎች ሲነሱ መስማት የተለመደ ሆኗል። ከሰሞኑም የመኪና እና መኖሪያ ቤት ዋጋ ላይ የታየው ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ብዙዎችን በማነጋገር ላይ ይገኛል።
ለተጨማሪ ንባብ -> https://bit.ly/3RqBtSl
_____________________
ንግድ በተለያዩ የኢኮኖሚ ተዋናዮች መካከል የሚደረግ በፍቃደኝነት ላይ የተመሠረተ ልውውጥ ነው። ንግድ እንደየአገሩ ነባራዊ ሁኔታ በሚወጡ ሕጎች የሚተዳደር ሲሆን፣ መንግሥታትም የአገራቸውን የንግድ ስርዓት በሚያወጧቸው ሕጎች መሠረት ይቆጣጠራሉ።
በኢትዮጵያም ንግድ የረዥም ጊዜ ታሪክ ያለው ሲሆን፣ ዓለም ዐቀፋዊ መልክ ባለው አሁናዊ የንግድ ስርዓትና ገበያ ውስጥ በርካታ ጥያቄዎች ሲነሱ መስማት የተለመደ ሆኗል። ከሰሞኑም የመኪና እና መኖሪያ ቤት ዋጋ ላይ የታየው ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ብዙዎችን በማነጋገር ላይ ይገኛል።
ለተጨማሪ ንባብ -> https://bit.ly/3RqBtSl
_____________________
"ዳኛ የ8 ሰዓት ሰራተኛ ሳይሆን የ24 ሰዓት ሰራተኛ ነው። ዳኝነትን በመንግስት የስራ ሰዓት ብቻ መስራት አይቻልም።
ዳኛ ቢሮ ባለጉዳይን በማስተናገድ፣ ቤት ደግሞ የምርመራ ስራን በመስራት የሚደክም ነው። በዳኝነት ስራ ምክንያት ለረጅም ጊዜ በመቀመጥና በማቀርቀር በርካታ ዳኞች የጤና እክል እየደረሰባቸው ነው። ህብረተሰቡ የዳኞችን ድካም ሊረዳው ይገባል።"
``~~``
©ወ/ሮ እትመት አሰፋ
{የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ሰሚ ችሎት ሰብሳቢ ዳኛ}
በፋና ቴሌቪዠን
https://t.me/lawsocieties
Share👍👍👍👍👆👆👆👆
ዳኛ ቢሮ ባለጉዳይን በማስተናገድ፣ ቤት ደግሞ የምርመራ ስራን በመስራት የሚደክም ነው። በዳኝነት ስራ ምክንያት ለረጅም ጊዜ በመቀመጥና በማቀርቀር በርካታ ዳኞች የጤና እክል እየደረሰባቸው ነው። ህብረተሰቡ የዳኞችን ድካም ሊረዳው ይገባል።"
``~~``
©ወ/ሮ እትመት አሰፋ
{የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ሰሚ ችሎት ሰብሳቢ ዳኛ}
በፋና ቴሌቪዠን
https://t.me/lawsocieties
Share👍👍👍👍👆👆👆👆
#የማስረጃ_ዓይነቶች_እና_ማስረጃ_ስለማያስፈልጋቸው_ፍሬ_ነገሮች
#መግቢያ
የአንድን ፍሬ-ነገር መኖር ወይም አለመኖር ማረጋገጥ የሚቻለው ማስረጃ በማቅረብ ነው፡፡
ማስረጃ በሰው ምስክሮች፣ በዘገባ፣ በሰነድ፣ ተጨባጭነት ባላቸዉ ሊታዩና ሊዳሰሱ በሚችሉ ነገሮች እና በኤግዚቢት መልክ ሊቀርብ ይቻላል፡፡ አቀራረቡም በሕግ በተደነገገው መሰረት ነው፡፡ በክርክር ሂደት ማስረጃ የማያስፈልጋቸው ጉዳዮች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ ይህ ከፍሬ ነገሩ የተለየ ባህሪ ወይም የሚያከራክር ነገር ባለመኖሩ ምክንያት ማስረጃ ማቅረብ አስፈላጊ የማይሆንባቸዉ ሁኔታዎች ስላሉ ነዉ፡፡ በዚህ አጭር ጽሁፍ ስለ ማስረጃ ዓይነቶችና ማስረጃ ስለማያስፈልጋቸው ጉዳዮች እንመለከታለን፡፡
1. #የማስረጃ_ዓይነቶች
ማስረጃ የአንድን ፍሬ ነገር መኖር ወይም አለመኖር ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል ከሚቻልባቸው ዘዴዎች እና ማስረዳት ከሚፈለገው ፍሬ ነገር ወይም መደምደሚያ ጋር ማስረጃው የሚኖረውን ግንኙነትን መሠረት በማድረግ በተለያዩ መንገዶች ከፋፍሎ ማየት ይቻላል፡፡
ፍሬ ነገርን ለማስረዳት ከምንጠቀምበት ዘዴ አንጻር፤
ሀ. የሰው ማስረጃ
ሰዎች በአካል ፍርድ ቤት ቀርበዉ ለችሎት መረጃ የሚሰጡበት መንገድ ሲሆን ፍሬ ነገሩን ለፍርድ ቤቱ የሚገልፁት በንግግር ወይም በምልክት ነው፡፡ ይህም የምስክርነት ቃል ይባላል፡፡ የሰው ማስረጃዎች ቀጥተኛ ምስክር፣ የአከባቢ ምስክርና የባለሞያ ምስክር ሊሆኑ ይችላሉ፡፡
ለ. የሰነድ ማስረጃ
ይህ የማስረጃ ዓይነት በላዩ ላይ የተፃፈበት፣ የተሳለበት ወይም ማናቸዉም ዓይነት ምልክት የተደረገበት ሲሆን ለምሳሌ ውሎች፣ ቼኮች፣ ለፖሊስ ወይም ለፍርድ ቤት የተሰጠ የዕምነት ቃል የተመዘገበበት፣ በጽሁፍ የተገለፀ የላብራቶሪ ወይም የህክምና ምርመራ ውጤት የሰነድ ማስረጃዎች ናቸው፡፡
ሐ. ገላጭ ማስረጃ
ይህ የማስረጃ ዓይነት ፍርድ ቤት እንዲያየውና ግንዘቤ እንዲወስድበት የሚቀርብ ማስረጃ ነው፡፡ ለምሳሌ በወንጀል ድርጊት የተገኘ ንብረት ወይም ወንጀል ለመፈፀም አገልግሎት ላይ የዋለ መሣሪያ በማስረጃነት ሲቀርብ ገላጭ ማስረጃ ይባላል፡፡
ማስረዳት ከተፈለገው ፍሬ ነገር አንጻር፤
ቀጥተኛ የሆነ ማስረጃ
ማስረጃ ቀጥተኛ ነዉ የሚባለው አንድን በጭብጥነት የተያዘ ፍሬ ነገር ወይም የተወሰደን መደምደሚያ ትክክለኛነት በቀጥታ ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል የሚቀርብ ሲሆን ነዉ፡፡ ከዚህ አንፃር ምስክር ቀርቦ በጭብጥ የተያዘው ፍሬነገር መኖሩን ወይም አለመኖሩን ራሱ በስሜት ህዋሳቱ አማካኝነት በማየት፣ በማሽተት፣ በመቅመስ፣ በመስማት ወይም በመዳሰስ ያወቀ መሆኑን የሚመሰክር ሲሆን ቀጥተኛ ማስረጃ ይባላል፡፡ በሰነድ ማስረጃ በኩልም በማስረጃነት የቀረበው ሰነድ በጭብጥ የተያዘዉ ፍሬ ነገር መኖርን ወይም የተደረሰበት መደምደሚያ ትክክለኛ መሆኑን ሰነዱ ራሱ በቀጥታ ያረጋግጣል ወይም ያስተባብላል በሚል የቀረበ ከሆነ ቀጥተኛ ማስረጃ ይባላል፡፡ ለምሳሌ በቂ ስንቅ ሳይኖረው ቼክ ፈርሞ ሰጥቷል በሚል ገንዘብ እንዲከፍል በተከሳሽ ላይ ለቀረበ ክስ ከሳሽ ቼኩን በማስረጃነት ያቀረበ ቢሆን ተከሳሹ ስለመፈረም አለመፈረሙ እና ስለ ገንዘቡ ልክ ቼኩ በቀጥታ የሚናገር ስለሆነ ቀጥተኛ ማስረጃ ይባላል፡፡
ቀጥተኛ ያልሆነ ማስረጃ
ማስረጃ ቀጥተኛ ያልሆነ ነዉ የሚባለው ከሁለት ሁኔታዎች አንፃር ነዉ፡- አንደኛዉ ማስረጃ ያስረዳል የተባለዉን ፍሬ ነገር ምንጭ ማስረጃዉ ራሱ በቀጥታ ያወቀዉ ሳይሆን ከሌላ ያገኘዉ ወይም የተረዳዉ ሲሆን ነዉ፡፡ ምስክር ሌላ ሰዉ የገለፀለት መሆኑን ጠቅሶ የሚመሰክር ሲሆን ቀጥተኛ ሳይሆን የስሚ ስሚ ማስረጃ (Hearsay Evidence) ይባላል፡፡ የስሚስሚ ማስረጃን ቀጥተኛ ያልሆነ የሚያሰኘዉ ማስረጃዉ ፍሬ ነገሩን የሚገልፀዉ ራሱ በቀጥታ እንዳወቀ ሳይሆን ከሌላ ሰዉ የሰማዉ ወይም ከሰነድ ያነበበዉ በመሆኑ ነዉ፡፡ በሰነድ ማስረጃም በኩል የስሚ ስሚ የሚያሰኘዉ ማስረጃ ሆኖ የቀረበዉ ሰነድ ላይ የተገለፀዉ ፍሬ ነገር አዉቃለሁ በሚል በሌላ ሰዉ የተዘጋጀ ሲሆን ነዉ፡፡
ሁለተኛዉ ቀጥተኛ ያልሆነ ማስረጃ ነዉ የሚባልበት ሁኔታ የሚያጋጥመዉ አካባቢያዊ ማስረጃ (Circumstantial Evidence) የቀረበ እንደሆነ ነዉ፡፡ አካባቢያዊ ማስረጃ በጭብጥ ስለተያዘዉ ፍሬ ነገር መኖር አለመኖር በቀጥታ አይነግረንም፡፡ ይልቁንም የተወሰኑ ፍሬ ነገሮችን መኖር ወይም አለመኖር በማረጋገጥ ከዚህ ተነስተን በጭብጥ የተያዘዉን ፍሬ ነገር በተመለከተ አንድ ዓይነት መደምደሚያ ላይ እንድንደርስ የሚያደርግ ነዉ፡፡
የማስረጃዉ ቀጥተኛ ወይም አካባቢያዊ መሆን አለመሆኑን መለየት በማስረጃ ምዘና ጊዜ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለዉ፡፡
1. ማስረጃ ስለማያስፈልጋቸዉ ፍሬ ነገሮች
ከፍሬ ነገሮቹ የተለየ ባህሪ ወይም የሚያከራክር ነገር ባለመኖሩ ምክንያት ማስረጃ ማቅረብ አስፈላጊ የማይሆንባቸዉ ሁኔታዎች አሉ፡፡ እነሱም፡-
ሀ. ፍርድ ቤት ግንዛቤ ሊወስድባቸዉ የሚችሉ ወይም የሚገቡ ፍሬ ነገሮች፣ ለምሳሌ በአዋጅ ቁጥር 3/1987 መሠረት በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ላይ የወጡ ነገሮችን ፍርድ ቤቶች ሊቀበሏቸዉ እንደሚገባ ተደንግጓል፡፡ በነጋሪት ጋዜጣ ላይ የተገለፀ ፍሬ ነገር ለማረጋገጥ ሌላ ማስረጃ መቀበል አያስፈልግም፡፡ ጋዜጣዉን በመመልከት ብቻ ግንዛቤ ሊወሰድበት ይገባል፡፡
ለ. በፍርድ ቤት በሚደረግ የክርክር ሂደት በተከራካሪ ወገን የታመኑ ፍሬ ነገሮች፣
ሐ. ጠቅላላ እዉነታዎች (Universal Truth)፣
መ. የሕግ ግምቶች (Presumptions) ናቸዉ፡፡ ለምሳሌ በጋብቻ ውስጥ የተፀነሰ (የተወለደ) ልጅ አባቱ ባልየው እንደሆነ ህጉ ግምት ይወስዳል፡፡
በአጠቃላይ ግራ ቀኝ ተከራካሪ ወገኖች ያስረዱልናል የሚሏቸዉን ማስረጃዎች ወይም ማስረጃ ባይቀርብባቸዉም በሕግ መሠረት የሚወሰኑትን ለይቶ ለማቅረብ የማስረጃ ዓይነቶችን እና ማሰረጃ የማያስፈለጋቸዉን ፍሬነገሮች ማወቁ ተገቢ ነዉ፡፡
https://t.me/lawsocieties
ምንጭ፡- FDRE Ministry of Justice/ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር (13/01/2015 E.C)
#መግቢያ
የአንድን ፍሬ-ነገር መኖር ወይም አለመኖር ማረጋገጥ የሚቻለው ማስረጃ በማቅረብ ነው፡፡
ማስረጃ በሰው ምስክሮች፣ በዘገባ፣ በሰነድ፣ ተጨባጭነት ባላቸዉ ሊታዩና ሊዳሰሱ በሚችሉ ነገሮች እና በኤግዚቢት መልክ ሊቀርብ ይቻላል፡፡ አቀራረቡም በሕግ በተደነገገው መሰረት ነው፡፡ በክርክር ሂደት ማስረጃ የማያስፈልጋቸው ጉዳዮች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ ይህ ከፍሬ ነገሩ የተለየ ባህሪ ወይም የሚያከራክር ነገር ባለመኖሩ ምክንያት ማስረጃ ማቅረብ አስፈላጊ የማይሆንባቸዉ ሁኔታዎች ስላሉ ነዉ፡፡ በዚህ አጭር ጽሁፍ ስለ ማስረጃ ዓይነቶችና ማስረጃ ስለማያስፈልጋቸው ጉዳዮች እንመለከታለን፡፡
1. #የማስረጃ_ዓይነቶች
ማስረጃ የአንድን ፍሬ ነገር መኖር ወይም አለመኖር ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል ከሚቻልባቸው ዘዴዎች እና ማስረዳት ከሚፈለገው ፍሬ ነገር ወይም መደምደሚያ ጋር ማስረጃው የሚኖረውን ግንኙነትን መሠረት በማድረግ በተለያዩ መንገዶች ከፋፍሎ ማየት ይቻላል፡፡
ፍሬ ነገርን ለማስረዳት ከምንጠቀምበት ዘዴ አንጻር፤
ሀ. የሰው ማስረጃ
ሰዎች በአካል ፍርድ ቤት ቀርበዉ ለችሎት መረጃ የሚሰጡበት መንገድ ሲሆን ፍሬ ነገሩን ለፍርድ ቤቱ የሚገልፁት በንግግር ወይም በምልክት ነው፡፡ ይህም የምስክርነት ቃል ይባላል፡፡ የሰው ማስረጃዎች ቀጥተኛ ምስክር፣ የአከባቢ ምስክርና የባለሞያ ምስክር ሊሆኑ ይችላሉ፡፡
ለ. የሰነድ ማስረጃ
ይህ የማስረጃ ዓይነት በላዩ ላይ የተፃፈበት፣ የተሳለበት ወይም ማናቸዉም ዓይነት ምልክት የተደረገበት ሲሆን ለምሳሌ ውሎች፣ ቼኮች፣ ለፖሊስ ወይም ለፍርድ ቤት የተሰጠ የዕምነት ቃል የተመዘገበበት፣ በጽሁፍ የተገለፀ የላብራቶሪ ወይም የህክምና ምርመራ ውጤት የሰነድ ማስረጃዎች ናቸው፡፡
ሐ. ገላጭ ማስረጃ
ይህ የማስረጃ ዓይነት ፍርድ ቤት እንዲያየውና ግንዘቤ እንዲወስድበት የሚቀርብ ማስረጃ ነው፡፡ ለምሳሌ በወንጀል ድርጊት የተገኘ ንብረት ወይም ወንጀል ለመፈፀም አገልግሎት ላይ የዋለ መሣሪያ በማስረጃነት ሲቀርብ ገላጭ ማስረጃ ይባላል፡፡
ማስረዳት ከተፈለገው ፍሬ ነገር አንጻር፤
ቀጥተኛ የሆነ ማስረጃ
ማስረጃ ቀጥተኛ ነዉ የሚባለው አንድን በጭብጥነት የተያዘ ፍሬ ነገር ወይም የተወሰደን መደምደሚያ ትክክለኛነት በቀጥታ ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል የሚቀርብ ሲሆን ነዉ፡፡ ከዚህ አንፃር ምስክር ቀርቦ በጭብጥ የተያዘው ፍሬነገር መኖሩን ወይም አለመኖሩን ራሱ በስሜት ህዋሳቱ አማካኝነት በማየት፣ በማሽተት፣ በመቅመስ፣ በመስማት ወይም በመዳሰስ ያወቀ መሆኑን የሚመሰክር ሲሆን ቀጥተኛ ማስረጃ ይባላል፡፡ በሰነድ ማስረጃ በኩልም በማስረጃነት የቀረበው ሰነድ በጭብጥ የተያዘዉ ፍሬ ነገር መኖርን ወይም የተደረሰበት መደምደሚያ ትክክለኛ መሆኑን ሰነዱ ራሱ በቀጥታ ያረጋግጣል ወይም ያስተባብላል በሚል የቀረበ ከሆነ ቀጥተኛ ማስረጃ ይባላል፡፡ ለምሳሌ በቂ ስንቅ ሳይኖረው ቼክ ፈርሞ ሰጥቷል በሚል ገንዘብ እንዲከፍል በተከሳሽ ላይ ለቀረበ ክስ ከሳሽ ቼኩን በማስረጃነት ያቀረበ ቢሆን ተከሳሹ ስለመፈረም አለመፈረሙ እና ስለ ገንዘቡ ልክ ቼኩ በቀጥታ የሚናገር ስለሆነ ቀጥተኛ ማስረጃ ይባላል፡፡
ቀጥተኛ ያልሆነ ማስረጃ
ማስረጃ ቀጥተኛ ያልሆነ ነዉ የሚባለው ከሁለት ሁኔታዎች አንፃር ነዉ፡- አንደኛዉ ማስረጃ ያስረዳል የተባለዉን ፍሬ ነገር ምንጭ ማስረጃዉ ራሱ በቀጥታ ያወቀዉ ሳይሆን ከሌላ ያገኘዉ ወይም የተረዳዉ ሲሆን ነዉ፡፡ ምስክር ሌላ ሰዉ የገለፀለት መሆኑን ጠቅሶ የሚመሰክር ሲሆን ቀጥተኛ ሳይሆን የስሚ ስሚ ማስረጃ (Hearsay Evidence) ይባላል፡፡ የስሚስሚ ማስረጃን ቀጥተኛ ያልሆነ የሚያሰኘዉ ማስረጃዉ ፍሬ ነገሩን የሚገልፀዉ ራሱ በቀጥታ እንዳወቀ ሳይሆን ከሌላ ሰዉ የሰማዉ ወይም ከሰነድ ያነበበዉ በመሆኑ ነዉ፡፡ በሰነድ ማስረጃም በኩል የስሚ ስሚ የሚያሰኘዉ ማስረጃ ሆኖ የቀረበዉ ሰነድ ላይ የተገለፀዉ ፍሬ ነገር አዉቃለሁ በሚል በሌላ ሰዉ የተዘጋጀ ሲሆን ነዉ፡፡
ሁለተኛዉ ቀጥተኛ ያልሆነ ማስረጃ ነዉ የሚባልበት ሁኔታ የሚያጋጥመዉ አካባቢያዊ ማስረጃ (Circumstantial Evidence) የቀረበ እንደሆነ ነዉ፡፡ አካባቢያዊ ማስረጃ በጭብጥ ስለተያዘዉ ፍሬ ነገር መኖር አለመኖር በቀጥታ አይነግረንም፡፡ ይልቁንም የተወሰኑ ፍሬ ነገሮችን መኖር ወይም አለመኖር በማረጋገጥ ከዚህ ተነስተን በጭብጥ የተያዘዉን ፍሬ ነገር በተመለከተ አንድ ዓይነት መደምደሚያ ላይ እንድንደርስ የሚያደርግ ነዉ፡፡
የማስረጃዉ ቀጥተኛ ወይም አካባቢያዊ መሆን አለመሆኑን መለየት በማስረጃ ምዘና ጊዜ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለዉ፡፡
1. ማስረጃ ስለማያስፈልጋቸዉ ፍሬ ነገሮች
ከፍሬ ነገሮቹ የተለየ ባህሪ ወይም የሚያከራክር ነገር ባለመኖሩ ምክንያት ማስረጃ ማቅረብ አስፈላጊ የማይሆንባቸዉ ሁኔታዎች አሉ፡፡ እነሱም፡-
ሀ. ፍርድ ቤት ግንዛቤ ሊወስድባቸዉ የሚችሉ ወይም የሚገቡ ፍሬ ነገሮች፣ ለምሳሌ በአዋጅ ቁጥር 3/1987 መሠረት በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ላይ የወጡ ነገሮችን ፍርድ ቤቶች ሊቀበሏቸዉ እንደሚገባ ተደንግጓል፡፡ በነጋሪት ጋዜጣ ላይ የተገለፀ ፍሬ ነገር ለማረጋገጥ ሌላ ማስረጃ መቀበል አያስፈልግም፡፡ ጋዜጣዉን በመመልከት ብቻ ግንዛቤ ሊወሰድበት ይገባል፡፡
ለ. በፍርድ ቤት በሚደረግ የክርክር ሂደት በተከራካሪ ወገን የታመኑ ፍሬ ነገሮች፣
ሐ. ጠቅላላ እዉነታዎች (Universal Truth)፣
መ. የሕግ ግምቶች (Presumptions) ናቸዉ፡፡ ለምሳሌ በጋብቻ ውስጥ የተፀነሰ (የተወለደ) ልጅ አባቱ ባልየው እንደሆነ ህጉ ግምት ይወስዳል፡፡
በአጠቃላይ ግራ ቀኝ ተከራካሪ ወገኖች ያስረዱልናል የሚሏቸዉን ማስረጃዎች ወይም ማስረጃ ባይቀርብባቸዉም በሕግ መሠረት የሚወሰኑትን ለይቶ ለማቅረብ የማስረጃ ዓይነቶችን እና ማሰረጃ የማያስፈለጋቸዉን ፍሬነገሮች ማወቁ ተገቢ ነዉ፡፡
https://t.me/lawsocieties
ምንጭ፡- FDRE Ministry of Justice/ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር (13/01/2015 E.C)
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
Corporate Legal – Legal Advisor
Bank of Abyssinia
Addis Ababa
Full–time
Job Requirement • Education: LLB Degree in Law. • Experience: Minimum of 6 years banking experience, of which 3 years in the area of Law.
How to Apply
• Only short-listed candidates will be contacted. • Applicants should attach their educational credentials & updated work experience in PDF format Interested applicants who meet the above criteria are invited to apply within 5 consecutive days from the date of this advertisement using https://vacancy.bankofabyssinia.com Note:- In person or postal application is not accepted.
Bank of Abyssinia
Addis Ababa
Full–time
Job Requirement • Education: LLB Degree in Law. • Experience: Minimum of 6 years banking experience, of which 3 years in the area of Law.
How to Apply
• Only short-listed candidates will be contacted. • Applicants should attach their educational credentials & updated work experience in PDF format Interested applicants who meet the above criteria are invited to apply within 5 consecutive days from the date of this advertisement using https://vacancy.bankofabyssinia.com Note:- In person or postal application is not accepted.
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
Vacancy at Ethiopian Human Rights Commission (EHRC)
🔰 Position: Senior Human Rights Officer Research, Campaign & Advocacy
✅ SALARY RANGE: Gross monthly salary of ETB 22,014.00 – ETB 26,219.00 plus ETB 6,000.00 Housing allowance and ETB 1,500.00 Transport allowance
✅ MA in Human Rights Law, LL.M in Human Rights, LLM in International Law, LLM in Law (Public Law relevant to Human Rights). Candidates with Bachelor of Laws (LL.B) with 4 years of relevant experience
📌 Deadline: 12 October 2022
📌ሰለ ሰራው ሙሉ መረጃ ለማየት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ👇👇
👉 Read Detail:- https://bit.ly/3SIc748
🔰 Position: Senior Human Rights Officer Research, Campaign & Advocacy
✅ SALARY RANGE: Gross monthly salary of ETB 22,014.00 – ETB 26,219.00 plus ETB 6,000.00 Housing allowance and ETB 1,500.00 Transport allowance
✅ MA in Human Rights Law, LL.M in Human Rights, LLM in International Law, LLM in Law (Public Law relevant to Human Rights). Candidates with Bachelor of Laws (LL.B) with 4 years of relevant experience
📌 Deadline: 12 October 2022
📌ሰለ ሰራው ሙሉ መረጃ ለማየት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ👇👇
👉 Read Detail:- https://bit.ly/3SIc748
በወንጀል ጉዳዮች የእርቅ አፈፃፀም መመሪያ ቁጥር 1/2012
በእርቅ ማለቅ የሚችሉ ወንጀሎችን የወንጀል ምርመራ ከመጣራቱ በፊትም ሆነ ምርመራ ከተጣራ በኋላ ወይም ክስ ክተመሰረተ በኋላ ጉዳዩን በእርቅ መጨረሱ ወጪ ቆጣቢ፣ አስተማሪ፡ ማህበራዊ ግንኙነት ሰላማዊ ሆኖ እንዲቀጥል የሚያግዝ በመሆኑ፣
በእርቅ የሚያልቁ ጉዳዮችን በተመለከተ ወጥ አሰራር እንዲኖር፣ በእርቅ አፈፃፀም ሂደት ባለሙያዎቸ ሊከተሉት የሚገባቸዉን ስነ-ስርዓት ማስቀመጥ እና ግልፅነት ያለዉ አሰራር መዘርጋት በማስፈለጉ፣
በቀድሞዉ ፍትህ ሚኒስቴር ሲሰራበት የነበረዉ “በወንጀል ጉዳዮች የእርቅ አሰራር መመሪያ ቁጥር 14/2007 ከፌደራል ጠቅላይ ዐ/ህግ አኳያ መቃኘት እና ማሻሻል በማስፈልጉ፤ የፌዴራል ጠቅላይ ዐ/ህግ በአዋጅ ቁጥር 943/2008 አንቀፅ 21(2) መሰረት ይህንን መመሪያ አዉጥቷል፡፡
በእርቅ ማለቅ የሚችሉ ወንጀሎችን የወንጀል ምርመራ ከመጣራቱ በፊትም ሆነ ምርመራ ከተጣራ በኋላ ወይም ክስ ክተመሰረተ በኋላ ጉዳዩን በእርቅ መጨረሱ ወጪ ቆጣቢ፣ አስተማሪ፡ ማህበራዊ ግንኙነት ሰላማዊ ሆኖ እንዲቀጥል የሚያግዝ በመሆኑ፣
በእርቅ የሚያልቁ ጉዳዮችን በተመለከተ ወጥ አሰራር እንዲኖር፣ በእርቅ አፈፃፀም ሂደት ባለሙያዎቸ ሊከተሉት የሚገባቸዉን ስነ-ስርዓት ማስቀመጥ እና ግልፅነት ያለዉ አሰራር መዘርጋት በማስፈለጉ፣
በቀድሞዉ ፍትህ ሚኒስቴር ሲሰራበት የነበረዉ “በወንጀል ጉዳዮች የእርቅ አሰራር መመሪያ ቁጥር 14/2007 ከፌደራል ጠቅላይ ዐ/ህግ አኳያ መቃኘት እና ማሻሻል በማስፈልጉ፤ የፌዴራል ጠቅላይ ዐ/ህግ በአዋጅ ቁጥር 943/2008 አንቀፅ 21(2) መሰረት ይህንን መመሪያ አዉጥቷል፡፡
በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በሕግ ጥላ ስር በሚገኙት የፍትሕ ሚኒስቴር ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እና ሌሎች 2 የወንጀል ተሳታፊዎች ላይ ክስ ተመሰረተ
ዐቃቤ ሕግ ከሙስና ወንጀል ምርመራ ጋር በተያያዘ 1ኛ ተከሳሽ አቶ ፈይሳ ሾርኬ ሳፋዎ በፍትሕ ሚኒስቴር የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ፣ 2ኛ ተከሳሽ አቶ አለማየሁ ታደሰ ከበደ በፍትሕ ሚኒስቴር የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ዐቃቤ ሕግ እንዲሁም 3ኛ ተከሳሻ አቶ ፍሬው በቀለ ታየ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የታገደውን እግድ እናስነሳልሃለን፤ በዋስም እንድትወጣ እና የዐቃቤ ሕግ ምስክሮች እንዳይቀርቡ በማድረግ ክሱ እንዲቋረጥ እናደርጋለን በማለት ገንዘብ ጠይቀዋል፤ ተቀብለዋል በሚል የሙስና ወንጀል ክስ መስርቷል፡፡
የዐቃቤ ሕግ ክስ እንደሚያስረዳው ተከሳሾች በጥቅም በመመሳጠር የማይገባ ጥቅም ለራሳቸው ለማግኘትና ለሌሎች ሰዎችም ለማስገኘት በማሰብ የግል ተበዳይ አቶ አረጋይ ግርማይ በድሬደዋ ከተማ ቀበሌ 03 የሚገኝ ኤም. ኤ ሆቴል ኃ/የተ/የግ/ማ የተባለ ድርጅቱን ለ2ኛ የዐቃቤ ህግ ምስክር ለመሸጥ ፈልጎ ሆቴሉ ከሙስና ወንጀል ምርመራ ጋር በተያያዘ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የታገደ በመሆኑ ምክንያት እግዱ እንዲነሳ እናደርጋለን በማለት የግል ተበዳይ ገንዘብ እንዲከፍል ጠይቀዉት፣ የግል ተበዳይ በበኩሉ እግዱ በሌላ ክርክር በፍርድ ቤት የተነሳ በመሆኑ ለመክፈል ፈቃደኛ ሳይሆን የቀረ በመሆኑ፣ ተከሳሾች በጥቅም በመመሳጠር የተጠየቀዉን ገንዘብ እንዲከፍል በማስገደድና በማሳመን በአጠቃላይ የግል ተበዳይ በ3ኛ ተከሳሽ በኩል 7,800,000 ብር እንዲከፍል በማድረግ ብር በመቀበላቸው ሶስቱም ተከሳሾች በዋና ወንጀል አድራጊነት ተከፋይ በመሆን በፈፀሙት በስልጣን አላግባብ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸዋል፡፡
በዚሁ የክስ መዝገብ በ1ኛ ተከሳሽ ተከሳሽ ላይ በቀረበ 2ኛ ክስ ተከሳሽ የተቀበለው ገንዘብ በወንጀል የተገኘ መሆኑን እያወቀ ገንዘቡን በራሱ ስም ቢቀበልና ገቢ ቢደርግ ወንጀሉ ሊደረስበትና የህግ ተጠያቂነት እንደሚመጣበት በማሰብ በወንጀል ድርጊት ያገኘውን ገንዘብ ህገወጥ ምንጩን፣ ዝውውሩን ወይም የባለቤትነት መብቱን የደበቀ ወይም እንዳይታወቅ ያደረገ በመሆኑ በፈፀመው በወንጀል ድርጊት የተገኘን ገንዘብ ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ ወንጀል ተከሷል፡፡
ክሱ የቀረበለት ፍርድ ቤትም ተከሳሽ ቀርቦ ያቀረበውን የዋስትና ጥያቄ እና የዐቃቤ ሕግን ተቃውሞ መርምሮ ብይን ለመስጠት ለመስከረም 26 ቀን 2015 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒሰቴር የሙስና ወንጀልን ከመከላከል አንጻረ በተቋም ደረጃ ከውስጥ በመጀመር በሰራተኞች ላይ የሚስተዋልን የስነ-ምግባር ጉድለት ለመለየት የሚያስችል ጥናት ከማጥናት ጀምሮ በተለያዩ ደረጃዎች የሙስና ወንጀል ተሳትፎ ስለማድረጋቸው ጥቆማ በቀረበባቸው ዐቃቤያነ ሕግ እና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኛ ላይ ተገቢውን የወንጀል ምርመራ እና ከሶ የማስቀጣት ስራ በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ ይህንኑ እርምጃ በተለያዩ ተቋማት የመንግስት ስራ ኃላፊዎች እና ሰራተኞች ላይም ሲወስድ እንደነበረም ይታወሳል፡፡
ይህ እርምጃም የሙስና ወንጀል መከላከል ሥራ አካል ሲሆን ማህበረሰቡም በፍትሕ ሚኒስቴርም ሆነ በሌሎች የመንግስት ተቋማት የሙስና ወንጀል ተግባራት መፈጸማቸዉን ያወቀ እንደሆነ ለፖሊስ ተቋማት ወይም ለፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጄኔራል ጥቆማ ማቅረብ የሚችል ሲሆን ተቋማቱ ጥቆማውን በሚስጥር በመያዝ ተገቢውን የማጣራት ስራ ሰርተው ሕጋዊ እርምጃ ለመውሰድ ዝግጁ መሆናቸውን ያረጋግጣል፡፡
ዐቃቤ ሕግ ከሙስና ወንጀል ምርመራ ጋር በተያያዘ 1ኛ ተከሳሽ አቶ ፈይሳ ሾርኬ ሳፋዎ በፍትሕ ሚኒስቴር የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ፣ 2ኛ ተከሳሽ አቶ አለማየሁ ታደሰ ከበደ በፍትሕ ሚኒስቴር የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ዐቃቤ ሕግ እንዲሁም 3ኛ ተከሳሻ አቶ ፍሬው በቀለ ታየ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የታገደውን እግድ እናስነሳልሃለን፤ በዋስም እንድትወጣ እና የዐቃቤ ሕግ ምስክሮች እንዳይቀርቡ በማድረግ ክሱ እንዲቋረጥ እናደርጋለን በማለት ገንዘብ ጠይቀዋል፤ ተቀብለዋል በሚል የሙስና ወንጀል ክስ መስርቷል፡፡
የዐቃቤ ሕግ ክስ እንደሚያስረዳው ተከሳሾች በጥቅም በመመሳጠር የማይገባ ጥቅም ለራሳቸው ለማግኘትና ለሌሎች ሰዎችም ለማስገኘት በማሰብ የግል ተበዳይ አቶ አረጋይ ግርማይ በድሬደዋ ከተማ ቀበሌ 03 የሚገኝ ኤም. ኤ ሆቴል ኃ/የተ/የግ/ማ የተባለ ድርጅቱን ለ2ኛ የዐቃቤ ህግ ምስክር ለመሸጥ ፈልጎ ሆቴሉ ከሙስና ወንጀል ምርመራ ጋር በተያያዘ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የታገደ በመሆኑ ምክንያት እግዱ እንዲነሳ እናደርጋለን በማለት የግል ተበዳይ ገንዘብ እንዲከፍል ጠይቀዉት፣ የግል ተበዳይ በበኩሉ እግዱ በሌላ ክርክር በፍርድ ቤት የተነሳ በመሆኑ ለመክፈል ፈቃደኛ ሳይሆን የቀረ በመሆኑ፣ ተከሳሾች በጥቅም በመመሳጠር የተጠየቀዉን ገንዘብ እንዲከፍል በማስገደድና በማሳመን በአጠቃላይ የግል ተበዳይ በ3ኛ ተከሳሽ በኩል 7,800,000 ብር እንዲከፍል በማድረግ ብር በመቀበላቸው ሶስቱም ተከሳሾች በዋና ወንጀል አድራጊነት ተከፋይ በመሆን በፈፀሙት በስልጣን አላግባብ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸዋል፡፡
በዚሁ የክስ መዝገብ በ1ኛ ተከሳሽ ተከሳሽ ላይ በቀረበ 2ኛ ክስ ተከሳሽ የተቀበለው ገንዘብ በወንጀል የተገኘ መሆኑን እያወቀ ገንዘቡን በራሱ ስም ቢቀበልና ገቢ ቢደርግ ወንጀሉ ሊደረስበትና የህግ ተጠያቂነት እንደሚመጣበት በማሰብ በወንጀል ድርጊት ያገኘውን ገንዘብ ህገወጥ ምንጩን፣ ዝውውሩን ወይም የባለቤትነት መብቱን የደበቀ ወይም እንዳይታወቅ ያደረገ በመሆኑ በፈፀመው በወንጀል ድርጊት የተገኘን ገንዘብ ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ ወንጀል ተከሷል፡፡
ክሱ የቀረበለት ፍርድ ቤትም ተከሳሽ ቀርቦ ያቀረበውን የዋስትና ጥያቄ እና የዐቃቤ ሕግን ተቃውሞ መርምሮ ብይን ለመስጠት ለመስከረም 26 ቀን 2015 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒሰቴር የሙስና ወንጀልን ከመከላከል አንጻረ በተቋም ደረጃ ከውስጥ በመጀመር በሰራተኞች ላይ የሚስተዋልን የስነ-ምግባር ጉድለት ለመለየት የሚያስችል ጥናት ከማጥናት ጀምሮ በተለያዩ ደረጃዎች የሙስና ወንጀል ተሳትፎ ስለማድረጋቸው ጥቆማ በቀረበባቸው ዐቃቤያነ ሕግ እና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኛ ላይ ተገቢውን የወንጀል ምርመራ እና ከሶ የማስቀጣት ስራ በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ ይህንኑ እርምጃ በተለያዩ ተቋማት የመንግስት ስራ ኃላፊዎች እና ሰራተኞች ላይም ሲወስድ እንደነበረም ይታወሳል፡፡
ይህ እርምጃም የሙስና ወንጀል መከላከል ሥራ አካል ሲሆን ማህበረሰቡም በፍትሕ ሚኒስቴርም ሆነ በሌሎች የመንግስት ተቋማት የሙስና ወንጀል ተግባራት መፈጸማቸዉን ያወቀ እንደሆነ ለፖሊስ ተቋማት ወይም ለፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጄኔራል ጥቆማ ማቅረብ የሚችል ሲሆን ተቋማቱ ጥቆማውን በሚስጥር በመያዝ ተገቢውን የማጣራት ስራ ሰርተው ሕጋዊ እርምጃ ለመውሰድ ዝግጁ መሆናቸውን ያረጋግጣል፡፡