አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.84K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
ሳፋሪኮም በአዲስ አበባ የቴሌኮም አገልግሎት በይፋ አስጀመረ
****
👇👇👇👇👇👇👇👇
(ኢ ፕ ድ )

የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ የቴሌኮም አገልግሎቱን በይፋ አሰጀምሯል።

የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አንዋር ሳኡሳ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለጹት፣  ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የቴሌኮም ኩባንያ በርካታ ቅድመ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል።

በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ላይ ሳፋሪኮም ትልቅ ሚና ይኖረዋል ያሉት ስራ አስፈጻሚው፣ ከባለድርሻ አካላትና ከክልሎች ጋር በጋራ በመስራት በሁሉም ቦታ ተደራሽ ለመሆን እንሰራለን ብለዋል።

ሳፋሪኮም ለደረሰበት ደረጃ የኢትዮጵያ መንግስትና የኢትዮ ቴሌኮም እገዛ ትልቅ መሆኑን በመግልጽ አመስግነዋል። 

ኩባንያው ባለፉት ሳምንታት በድሬዳዋ፣ በባህርዳር፣ በአወዳይ፣ ጎንደር ፣ሞጆ፣ ሐረር፣ አዳማ፣ ሀረር፣ ቢሾፍቱና ደብረ ብርሃን የኔትዎርክ ሙከራ አገልግሎቱን መጀመሩ ይታወሳል።

በሞገስ ፀጋዬ
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን
https://t.me/lawsocieties
የጋብቻ ውል (አጫጭር የምልከታ ነጥቦች)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የጋብቻ ውል(Contract of marriage ) ማለት ምን ማለት ነው? ከጋብቻ ምስክር ወረቀት(Certificate of marriage) በምን ይለያል?
ጋብቻ የሁሉም መሠረት እንደመሆኑ በኢ.ፌ.ድ.ሪ ሕገ መንግሥት(constitution) እና ሌሎች ህጎች ሳይቀር ጥበቃ የተሰጠው ትልቅ ማኅበራዊ ተቋም(institution) ነው፡፡ የጋብቻ ውል(contract of marriage) ማለት ከጠቅላላው ውል ሕግ(Law of contract) ተነስተን ትርጉም የምንሰጠው አይደለም፡፡ ጋብቻ የሚፈጸመው መሃል ላይ የተለያዩ አጋጣሚዎች እንደተጠበቁ ሆነው እስከ ዕለተ ሞት ድረስ በአንድ ጣራ ስር አብሮ ለመኖር ነው፡፡ በዚሁ መሠረት የጋብቻ ውል የሚባለውም ተጋቢዎች ጋብቻቸውን በፈጸሙበት ዕለት ወይም ቀደም ብለው ጋብቻቸው እና አጠቃላይ ጋብቻቸው የሚያስከትለውን ውጤት ወስነው የሚያልፉበት ትልቅ ሰነድ ነው፡፡ በተሻሻለው የፌዴራል መንግስት የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር 213/92 አንቀጽ 42 (1) ላይ የተመለከተውም ይሄንኑ ነው፡፡

የጋብቻ ውል ጥቅም ምንድን ነው?
ምናልባት ተጋቢዎች ትኩስ ፍቅር ላይ ሆነው ወደፊት ጸብ ሊኖር እንደሚችል አይገመቱም፡፡ ፍቅር እንዳለ ጸብም አለ፡፡ እነዚህ የማይነጣጠሉ ክስተቶች ናቸው፡፡ ከዚህ በመነሣት ተጋቢዎች ንብረታቸውን በሚመለከት (የግሉን በግል፣የጋራውን በጋራ) አድርገው የሚወስኑት በዚሁ የጋብቻ ውል ስለሆነ አለመግባባት ተከስቶ የንብረት ይገባኛል ጥያቄ እና ሙግት በሚነሣበት ወቅት ማስረጃነቱ እጅግ ጠቃሚ ነው፡፡ አንዳንድ የፍርድ ቤት ጉዳዮችን ስንመለከት ይህን ባለማድረግ የሚከሰቱ ጉዳዮችም ያጋጥማሉ፡፡ ተጋቢዎች ከጋብቻ በፊት የንብረታቸውን ሁኔታ ወስነው ካላለፉ ለወደፊት ለትዳራቸው አለመስማማት እና ለፍቺ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል በመገንዘብ ቀድመው ሊያስቡበት የሚገባ ትልቅ ጉዳይ ነው፡፡
በፍርድ ቤቶች የሚታየው ክርክርም ቢሆን ባልና ሚስት የንብረታቸውን ጉዳይ የግል ንብረቶችን በግል፣የጋራውን ደግሞ በጋራ በየፈርጁ ለይተው ባለማስቀመጣቸው ምክንያት የንብረት ባለቤትነት የሚያሣጣ ባይሆንም ንብረት ያላፈራው ሰው ተጋሪ ሲሆን የምንመለከትበት ሁኔታ ያጋጥማል፡፡

በጋብቻ ውል የንብረታቸውን ጉዳይ ሳይወስኑ የተቀመጡ ተጋቢዎች ዕጣ ፈንታ ምንድንነው?
ተጋቢዎች ቢዘገይ በጋብቻቸው ዕለት ወይም ደግሞ ቀድም ብለው የንብረታቸውን ጉዳይ ወስነው ካላለፉ በትዳር ውስጥ ሆነው የንብረት ማግለል ውል ማድረግ ይችላሉ፡፡ በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 73 መሠረት ውላቸውን ፍርድ ቤት አቅርበው ሊያጸድቁ ይገባል፡፡ በትዳር ውስጥ የሚደረጉ ውሎችን ፍርድ ቤት ሊያጸድቃቸው ይገባል፡፡ (ንብረት ማግለል፣ስጦታ፣ሽያጭ፣………) ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ተጋቢዎች በመካከላቸው የሚያደርጓቸውን ውሎች ውልና ማስረጃ በመውሰድ ተመዝግቦ እንዲረጋገጥላቸው ሲጠይቁ ይስተዋላል፡፡ ውልና ማስረጃም የዚህን ዓይነት የውል ስምምነት የመዘገበበት ሁኔታ ተስተውሏል፡፡ በዚህ ላይ ማረጋገጥ እና ማፅደቅ (authentication and ratification) የሚሉትን ነጥቦች መለየት ያስፈልጋል፡፡

ከጋብቻ የምስክር ወረቀት ጋር ልዩነቱ ምንድን ነው?
የጋብቻ ምስክር ወረቀት(certificate of marriage) ምን ማለት እንደሆነ ከመግለጻችን በፊት በሀገራችን ያሉትን የጋብቻ አፈጻጸም ሥርዓቶችን ማየት ያስፈልጋል፡፡ በሀገራችን ሦስት ዓይነዋና ዋና የጋብቻ አፈጻጸም ሥርዓቶች አሉ (በባህል(Custom) ፣ በሃይማኖት(religion) እና በክብር መዝገብ ፊት(Civil status) የሚፈጸሙ የጋብቻ አፈጻጻም ሥርዓቶች ናቸው)፡፡ ጋብቻው የተፈጸመው በየትኛውም የጋብቻ አፈጻጸም ሥርዓት ቢሆንም ጋብቻን በሚመዘግበው አካል ፊት ቀርቦ መመዝገብ አለበት፡፡ ይህ ነው የጋብቻ ምስክር ወረቀት የሚባለው፡፡ የጋብቻ ምስክር ወረቀት ተጋቢዎች ባልና ሚስት መሆናቸውን የሚያሣይ ሰርቲፊኬት ነው፡፡ ይህም በተሻሻለው የፌዴራል መንግሥቱ የቤተሰብ ሕግ አዋጅ ቁጥር 213/92 አንቀጽ 28/3/ ላይ ተመልክቷል፡፡
አንዳንድ ተጋቢዎች የባልና ሚስት ማስረጃ በሚጠይቁ ግልጋሎት ላይ በሃይማኖት ተቋም የተሰጣቸውን የጋብቻ ምስክር ወረቀት ሲያቀርቡ ይስተዋላሉ፡፡ ምሳሌ፡ ውልና ማስረጃ ላይ ይህን መታዘብ ይቻላል፡፡ ይህ በሃይማኖት ተቋም የሚሰጥ የጋብቻ ምስክር ወረቀት ተጋቢዎች በሃይማኖታቸው መሠረት(ከሦስቱ የጋብቻ አፈጻጸም ሥርዓት በአንደኛው) ጋብቻ የፈጸሙ መሆኑን የሚያሣይ ነው እንጂ በሕጉ የተቀመጠው የጋብቻ ምስክር ወረቀት(certificate of marriage ) አይደለም፡፡
Source: Document Registration and Authentication Office

https://t.me/lawsocieties
#ዉሳኔ ካገኙ ጉዳዮች/ኬዞች መካከል

ሰላማዊት (ስሟ የተቀየረ) በአሶሳ ከተማ የሚገኝ ሟች እናቷ ትተውት ያለፉትና ከሌሎች 2ት ግለሰቦች ጋር የምትጋራዉ የውርስ ሃብት ነበራት፡፡ የውርስ ሃብቱ በግምት 2500 ካ.ሜ ይዞታ ላይ ያረፈና ሶስት መኝታ ቤት ፣ አንድ መታጠቢያ/ሻወር ቤት እና አምስት ክፍል ሰርቪስ ቤቶች ያሉት አንድ ቪላ/መኖሪያ ቤት እምዲሁም በግምት 100 ካ.ሜ ላይ ያረፈ ሁለት የድርጅት ቤቶች ይገኙበታል፡፡ ይህ የሰላማዊትና የሌሎች 2 ግለሰቦች የጋር ውርስ የነበረዉን ንብረት ሰላማዊት እና 2ቱ ግለሰቦች ሟች ከሞቱ በኋላም በጋራ ሲጠቀሙበት ነበር፡፡ ነገር ግን 2ቱ ግለሰቦች ሴራ በመጠንሰስ የሰላማዊትን የወራሽነት መብት ይጥሳሉ፡፡ እነኝህ ከሰላማዊት ጋር የሚጋሩ ሁለት ወራሾች የሰላማዊትን አለመማር እና በእነርሱ ላይ ያላትን ዕምነት ተጠቅመው ነበር ከውርስ ባለመብትነቷ በማታውቀው ሁኔታ እንድትገለል ያደረጓት፡፡
ይህን ጊዜ ነበር ሰላማዊት ጉዳዩን ወደ ኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር አሶሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ይዛ በመቅረብ የህግ ድጋፍ እንዲደረግላት የጠየቀችው፡፡ የማህበሩ አሶሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤትም ጠበቃ በመመደብ ጉዳዩ ውሳኔ እስካገኘበት ድረስ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ በመጨረሻም ጉዳዩ የቀረበለት ፍ/ቤት የውርስ ሃብት ከሆነው የመኖሪያ ቤት ውስጥ ድርሻዋ ከ2ቱ ግለሰቦች/ተከሳሾች እኩል ተሰልቶ እንዲሰጣት እንዲሁም ከንግድ ድርጅቶቹ በኪራይ ከሚገኘዉ ገቢ ዉስጥ ብር 925,800 (ዘጠኝ መቶ ሃያ አምስት ሺህ ስምንት መቶ ብር) 2ቱ ግለሰቦች/ተከሳሾች ለሰላማዊት እንዲከፍሏት ሲል ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
ኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር
https://t.me/lawsocieties
#Humanitarian #intervention
Humanitarian intervention is a right to use force ‘exceptionally, to avert overwhelming humanitarian catastrophe’. It envisaged the use of massive military force in a foreign State for the protection of the citizens of that State.
Opinion on the legality of that intervention was divided. Some pointed out that there is no hint of any right of humanitarian intervention in the UN Charter, and urged caution in slackening the constraints upon the unilateral use of force in international relations.
Others took the view that if the UN was unable to act in the face of outrages such as the 1995 Srebrenica Massacre and the continuing ‘ethnic cleansing’ in the Balkans, there may come a point where moral imperatives eclipse the lack of any legal foundation for unilateral intervention.
A point at which neighboring States can no longer sit by and watch the calculated slaughter of thousands of civilians, but must act in the name of elementary imperatives of humanity........👇👇👇👇👇👇
አለሕግAleHig ️
#Humanitarian #intervention Humanitarian intervention is a right to use force ‘exceptionally, to avert overwhelming humanitarian catastrophe’. It envisaged the use of massive military force in a foreign State for the protection of the citizens of that State.…
Continued...... 👆👆👆👆👆
The UK claimed to be acting on the basis of this right when it used military force in Kosovo in 1999. No such right was clearly established by State practice. States could give non-discriminatory humanitarian relief, dropping blankets and food parcels to those in need. States had also often acted to protect and rescue their own nationals abroad. But the very limited nature of the threat or use of force in those contexts is better viewed as being primarily a (defensible) infringement on the duty of non-intervention in the internal affairs of other States.
NATO States took the view that where there is an imminent humanitarian catastrophe which can be averted by the use of force and only by the use of force, and where there has been a prior determination by the Security Council of a grave crisis threatening international peace and security and an articulation by the Council of policies for the resolution of the crisis, States acting collectively through a body such as NATO are justified in intervening with the use of force even in the absence of Security Council authorization.
An argument might be made out for the view that the law should leave matters as they are, and tolerate but not condone interventions of this kind, leaving them resting on a moral rather than a legal justification.
#Global study and international Relations classical lecture
Enjoy Ethiopian 🇪🇹 coffee with butter!
https://t.me/lawsocieties
War Crime
War crime is grave breaches of the Geneva Conventions of and other serious violations of the laws and customs applicable in armed conflicts.
A war crime constitutes egregious violations of IHL & trigger individual responsibility.
States are obliged ‘to respect and ensure respect’ for the Geneva Conventions, and the inculcation of their principles is (or at least should be) a basic part of the training of all members of the armed forces.
Breaches of the laws of war are serious offences, punishable by law.
Many options exist for the prosecution of war and other international crimes: national courts, foreign courts, ad hoc tribunals, & the International Criminal Court (ICC).
International Criminal Court (ICC)
The ICC is an international tribunal established by the 1998 Rome Statute and began functioning on 1 July 2002 that sits in The Hague in the Netherlands.
The ICC has the jurisdiction to prosecute individuals for the international crimes of genocide, crimes against humanity, and war crimes.
The ICC is intended to complement existing national judicial systems and it may therefore only exercise its jurisdiction when national courts are unwilling or unable to prosecute criminals or when the UN Security Council or individual states refer investigations to the Court.
The ICC was designed to supplement rather than replace national jurisdiction over war crimes.
https://t.me/lawsocieties
Corporate Legal Senior Legal Advisor at Bank of Abyssinia

Bank of Abyssinia

Ethiopia
Education: LLM/LLB Degree in law Experience: Minimum of 6/8 years banking experience, of which 4 years in the area of Law.
Method of Application
👉 Apply here 👈..........👈
👇👇👇👇👇👇👇👇
👇👇👇
https://et.jobelk.com/jobs/21045/apply

Closing Date : 7 October. 2022
Area Legal Coordinator for North Area
VisionFund Micro-Finance Institution S.C
Debre Birhan
Job Requirements 2)

TECHNICAL AND OTHER SKILLS*

Able to communicate and good presentation skill;* Good knowledge of the court system and procedures, legal ethics;* Ability to interpret, analyse and solve problems;* Ability to act in professional and ethical manner;* Determined personality with initiative, perseverance and the ability to motivate and manage a team;* Capability and willingness to take responsibility and highly developed sense of integrity;* Proficiency in Microsoft office applications.3) Qualification and experience Requirements· LLB Degree in Law A minimum of 3 years of relevant work experience.

How to Apply

Candidates who fulfil the above requirements can submit the application letter, updated curriculum vitae with names and addresses of up to 3 references and non-returnable copies of credentials in person to:
Kombolcha, Dessie, Kemise, Debre Birhan, Efeson Branches & North Area Offices (Debre Birhan), or VFE_Vacancy@wvi.org. Women applicants are highly encouraged to apply
Report this listing
VisionFund Micro-Finance Institution
ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች ግዥን በዕውቀት ሊመሩት ይገባል ተባለ
............************
...........
የግዥን ጉዳይ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች በዕውቀት ሊመሩት ይገባል ሲሉ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ ገለፁ፡፡

በመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን አዘጋጅነት ለዳኝነት አካላት በአርባ ምንጭ ከተማ ሲሰጥ በነበረው ስልጠና ማጠቃለያ ላይ የተገኙት ምክትል ፕሬዝዳንቱ በአብዛኛው በከፍተኛ አመራሮች ላይ የሚቀርቡ የሙስና ወንጀል ክሶች ከግዥ ጋር የተያያዙ በመሆናቸው ከፍተኛ አመራሮች ግዥን በዕውቀት ሊመሩት ይገባል ብለዋል፡፡

ግዥ ሕይወት ነው ያሉት ም/ፕሬዝዳንቱ ከዕለት ዕለት የዳኝነት ስራዎቻችን ጋር የሚገናኝ በመሆኑ በተለይ ሀገራዊ ፋይዳ ባላቸው የግዥ ጉዳዮች ላይ ለሚቀርቡ ክሶችን ሀገራዊ ፋይዳውን በመረዳት በሚገባና ወቅቱን በጠበቀ መልኩ የተፋጠነ የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት በመከተል የሀገርን ኢኮኖሚ መታደግ እንደሚገባም አስምረውበታል፡፡

ክቡር ም/ፕሬዝዳንቱ እንደገለጹት ሀገራችን ካላት ውስን ሀብት 60 በመቶ የሚሆነው ለግዥ የሚውል መሆኑን መረጃዎች እንደሚጠቁሙ ገልጠዉ ዘርፉ ከፍተኛ ሀብት የሚያስተናግድ እንደመሆኑ መጠንና ለሙስና ተጋላጭ በመሆኑ በልዩ ትኩረት መታየት ይገባዋል ብለዋል፡፡

ፍርድ ቤቶች ከመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር አኳያ ድርብ ኃላፊነቶች ያሉባቸዉ እንደመሆኑ መጠን ከግዥ አኳያ ወደ ተቋሞቻችን የሚመጡ ጉዳዮችን የጉዳዮቹን ክብደት፣ ውስብስብነት፣ አስቸኳይነትና ገንዘብ ሊያስገኝ የሚችለውን ጥቅም ታሳቢ ያደረገ ውሳኔ ማስተላለፍ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

ፍርድ ቤት በሕገ መንግስቱ መሰረት የመጨረሻ ውሳኔ ሰጭ እንደመሆኑ መጠን ቀልጣፋ፣ ውጤታማና ጥራት ያለው የዳኝነት አገልግሎት መስጠትና በግዥ ዙሪያ ያሉ ሕጎች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎች እንዲሁም የአሰራር ስርዓቶች ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን በሚገባ በመመርመርና አሰራሮችን በማወቅ በዕውቀት ላይ የተመሰረተ ውሳኔ መስጠት የሚያስችል ተቋማዊ አቅም መፍጠር እንደሚገባም አስረድተዋል፡፡

ምንጭ፡- የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን
https://t.me/lawsocieties
🙏ግብር ከፋዮች ካሉባቸዉ ኃላፊነቶች ዉስጥ ዋና ዋናዎቹ፡-

👉ግብሩን በወቅቱ አሳዉቆ የመክፈል፣
👉 ተቋሙ በሚያከናዉናቹ ህገወጦችን የመከላከል ስራዎች ወይም የታክስ አስተዳደር ህጎችን በማስከበር ስራዎች ላይ ተባባሪ የመሆን፣
👉በተቋሙ ለተለያዩ የታክስ ጉዳዮች ጥሪ ሲደረግ ወይም መረጃ ሲጠየቅ በወቅቱ የመገኘትና መረጃዎችን የማቅረብ፣
👉ለአገልግሎት ጥያቄዎች መሟላት ያለባቸዉን ቅድመ ሁኔታዎች አሟልቶ የመቅረብ፣
👉ተቋሙ ተግባራዊ በሚያደርጋቸዉ የቴክኖሎጂ ዉጤቶች የመጠቀም እና
👉በታክስ አስተዳደር ህጎች ላይ የግንዛቤ መድረኮች እንዲሳተፉ ጥሪ ሲደረግ የሚመለከተዉ ሰዉ ተገኝቶ ግንዛቤ የመዉሰድ ኃላፊነቶች ያሉባቸዉ መሆኑን አሳስበዋል፡፡
ከመክፈቻዉ ንግግር በኋላ የ2014 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2015 በጀት ዓመት እቅድ እንዲሁም ለግብር ከፋዩ የዉይይት መነሻ የሚሆኑ በ2014 የግብር ዓመት የቅሬታ ምንጭ የሆኑ የታክስ ጉዳዮችና ምክረ ሀሳቦች እንዲሁም ሌሎች ለግብር ከፋዮች መቅረብ ያለባቸዉ ችግሮች የያዘ ሰነድ በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ካሳሁን ደመመ ቀርቦ ዉይይት ተደርጓል፡፡ እንደ ቅርንጫፍ ጽ/ቤትም በ2014 በጀት ዓመት ብር 4,619,449,038 ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ ብር 5,609,106,560.19 ወይም የእቅዱን 121.42 በመቶ የተሰበሰበ ሲሆን በ2015 በጀት ዓመትም 7,527,745,303.59 ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ ስራዎችን እየሰራ የሚገኝ መሆኑ በሰነዱ ተመላክቷል፡፡
በመጨረሻም በመድረኩ የተለያዩ ጥያቄዎች በግብር ከፋዩ የተነሱ ሲሆን በዉይይቱ ለተነሱ የግልጽነት ጥያቄዎችና ችግሮች በመድረኩ በተገኙ ዳይሬክተሮች እና የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ካሳሁን ደመመ ምላሽ የተሰጠባቸዉ ሲሆን ክቡር አቶ ተስፋየ ቱሉ እንደተቋም በተነሱ ጥያቄዎች ላይ ምላሻቸዉን በመስጠት እና ለመድረኩ ተሳታፊ ግብር ከፋዮችና አጋር አካላት አጋርነታቸዉን በማሳየታቸዉና በቀጣይም ይህን አጋርነታቸዉን አጠናክረዉ እንዲቀጥሉ ምስጋና በማቅረብ መድረኩ ተጠናቋል፡፡

https://t.me/lawsocieties
የወራሽነት ጥያቄ ለማቅረብ የተቀመጠ ጊዜ ገደብ

የወራሽነት ጥያቄን ለማቅረብ የተቀመጠ የጊዜ ገደብ የሚመለከቱ የሕግ ድንጋጌዎች በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1000 ላይ የተመለከተ ሲሆን ወደዚህ ነጥብ ከመግባቴ በፊት ወራሽነት ጥያቄ ማለት ምን ማለት ነው የሚለውን እደሚከተለው ለመዳሰስ እሞክራለሁ÷

በፍ/ብ/ሕ/ቁ 996(1) ላይ በተገለጸው መሰረት ወራሽ የሆነ ሰው የሟቹ ወራሽ መሆኑንና ከውርሱ ላይ የሚያገኘውን ድርሻ የሚያመለክት የወራሽነት የምስክር ወረቀት እንዲሰጠው ለፍርድ ቤት ጥያቄ ማቅረብ ይቻላል በማለት የተገለጸ ሲሆን ይህ ማለት ፍ/ቤቱ የወራሽነት ምስክር እንዲሰጠው ወራሹ ሲፈልግ የሚጠይቀው እንጂ ሟችን ለመውረስ የግድ ከፍ/ቤቱ የወራሽነት ማስረጃ ማምጣት እንዳለበት የሚያስገድድ አይደለም፡፡ ሆኖም ግን በተግባር እንደሚስተዋለው ስመ ንብረቱ ለማዛወር እና ከሌሎች የሟች መብቶች ለመጠቀምና ለመስራት በፍ/ቤቱ የተረጋገጠ የወራሽነት የምስክር ወረቀት መጠየቁ የተለመደ አሰራር ሆኗል፡፡

ከዚህ በላይ የተጠቀሰውን መሰረት በማድረግ አንድ ሰው ዋጋ ያለው የወራሽነት ማስረጃ ሳይኖረው ውርሱን ወይም ከውርሱ አንዱን ክፍል በእጁ ያደረገ እንደሆነ እውነተኛው ወራሽ ወራሽነቱን እንዲታወቅለትና የተወሰዱበት የውርስ ንብረቶች እንዲመለሱለት በዚህ ሰው ላይ የወራሽነት ጥያቄ ክስ ሊያቀብበት ይችላል በማለት በፍ/ብ/ሕ/ቁ 999 ላይ ተደንግጓል፡፡ ስለዚህ ይህን መሰል የክስ አቤቱታ አቤቱታ መቼ ሊቀርብ ይገናል ለሚለው የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1000/1/ ላይ የጊዜ ገደብ ተቀምጧል፡፡

በዚሁ መሰረት ከሳሽ መብቱንና የውርሱን ንብረት በተከሳሽ መያዛቸውን ካወቅ ሶስት ዓመት ካለፈ በኋላ ስለ ወራሽነት ጥያቄ የሚቀርበው ክስ ተቀባይነት ሊያገኝ አይችልም፡፡ በሌላ መልኩ በአንቀጽ 1000(2) ላይ እንደተገለጸው “ሟቹ ከሞተበት ወይም ከሳሹ በመብቱ ለመስራት ከቻለበት ቀን አንስቶ አስራ አምስት አመት ካለፈ በኋላ ከዘር የወረደ ርስት ካልሆነ በቀር የውርስ ጥያቄ ክስ በማናቸውም አስተያየት ቢሆን ተቀባይነት አያገኝም የሚለው ተደንግጎ ይገኛል፡፡

ከዚህ በላይ በአንቀጽ 1000(1) እና (2) ላይ የተመለከቱት የጊዜ ገደቦች ከሌሎች የውርስ ሕግ ድንጋጌዎች በተለይም 1ኛ) አንድ ወራሽ የሟች ኑዛዜ ተጠቃሚ መሆን የሚችለው ኑዛዜ በእጁ እንደሚገኝ ለውርስ አጣሪው አቅርቦ ውርስ አጣሪው ኑዛዜውን በሚነበብበት ሰዓት ራሱ ወይም ወኪሉ ካልነበረ ወራሹ ኑዛዜው ከፈሰሰበት ቀን አንስቶ በአስራ አምስት አመታት ውስጥ መቃወሚያ ካላቀረበ ከዚያ በኋላ ሊቀርብ እንደማይችል በፍ/ሕ/ቁ 974(2) የተመለከተው በፍ/ሕ/ቁ 1000(1) ካለው የጊዜ ገደብ ጋር እንዴት ተጣጥሞ ተግባራዊ ይሆናሉ ከሚለው ጋር ጥያቄ የሚያስነሳ ሲሆን በሌላ መልኩ በፍ/ሕ/ቁ 1000(1) እና (2) አተረጓጎምና አፈጻጸም እንዴት መሆን አለበት በሚል አልፎ አልፎ ጥያቄ ሲያስነሳ ይስተዋላል፡፡ ስለዚህ በእነዚህ የሕግ ማዕቀፎች ላይ የተጠቀሱት የጊዜ ገደቦች በተመለከተ መከተል የሚገባንን የሕግ ትርጓሜ እንደሚከተው ለማብራራት ተሞክሯል÷ የፍ/ብ/ሕ/ቁ 974/2/ ተፈጻሚ የሚሆነው የሟች ውርስ የሚያጣራ ፤በሕግ በኑዛዜ ወይም በፍርድ ቤት የተሾመ የውርስ አጣሪ ፤ሟች አድርጎታል የተባለው ኑዛዜ አግኝቶ የኑዛዜውን ፎርምን የኑዛዜውን ዋጋ መኖር ፤የሟች ያለኑዛዜ ወራሾች ወይም አራት አካለመጠን ያደረሱ ሰዎች ባሉበት በፍ/ብ/ሕ/ቁ 968 በተመረመረበት ሁኔታ ነው፡፡ ሆኖም ግን ኑዛዜ ያለ መሆኑን ለውርስ አጣሪው ሳያሳውቅ ቀጥታ የኑዛዜ ወራሽ መሆኑ እንዲታወቅለት ለፍ/ቤት አመልክቶ የወራሽነት የምስክር ወረቀት በመውሰድ የሟች ንብረት በእጁ ያደረገ ሰው ወይም በሀሰት የሟች ያለኑዛዜ ወራሽ ነኝ ብሎ የሟችን ንብረት ከወሰደው ሰው ለማስመለስ አግባብ የሆነው የይርጋ ገደብ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 968 የተጠቀሰው ሳይሆን በፍብ/ሕ/ቁ 1000/1/ የተመለከተው ተፈጻሚነት ሊኖረው ይገባል፡፡

በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1000/1/ እና 1000/2/ አስመልክቶ የተለያዩ አተረጓገሞች የሚስተዋሉ ሲሆን ለዚህ ጽሁፍ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት በሰ/መ/ቁ 30158 ፤26422 እና 34011 በቅጽ 7/6/6/ እንዲሁም በቅጽ 11 በሰ/መ/ቁ 52407 የሰጠውን አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ ለመዳሰስ ሞክሬያለው፡፡ በዚሁ አግባብ በፍ/ሕ/ቁ 1000/2/ ላይ ሟች ከሞተ አስራ አምስት አመት በላይ ወይም ተከሳሹ በመብቱ ሊሰራበት ከቻለበት ቀን አንስቶ አስራ አምስት ዓመት ውስጥ ክስ ካልቀረበ አስራ አምስት ዓመት ካለፈው በኋላ ክስ ሊያቀርብ የሚቻለው ከዘር የወረደ ርስት በሆነ ንብረት ላይ ነው፡፡

ርስት የሚለው ቃል በፍ/ሕ/ቁ 1130 እና ስለ ንብረቶች በሚናገረው የፍ/ብሔር የህጉ ክፍል መሬት የሚያመለክት መሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡ በኢትዮጲያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማዕከል የተዘጋጀው የአማርኛ መዝገበ ቃላት ርዕስት የሚለው መሬትን የሚመለከት መሆኑን ጠቅሶ ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡ በዚሁ አግባብ ከዘር የወረደ ርዕስት የሚለው ቤትን አያጠቃልልም የሚል መደምደሚያ ላይ መድረስ ይቻላል፡፡ በርዕስት የሚተላለፍ መሬት ብቻ ማለት ሰለሆነ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1000/2/ መሰረት ለተወላጆች የሚተላለፍ መሬት ብቻ ነው የሚል መደምደሚያ ላይ መድረስ ይቻላል፡፡

በኢፌድሪ ህገ መንግስት መሰረት መሬት የመንግስትና የህዝብ ሀብት በመሆኑ ከዘር የወረደ ርዕስት ካልሆነ በስተቀር በማለት በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1000/2/ ላይ የተገለጸው የተሻረ እና ተፈጻሚነት የሌለው ነው በማለት አስገዳጅ ውሳኔ ተሰጥቷል፡፡

የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1000/1/ አፈጻጸምን በተመለከተ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት በሰ/መ/ቁ 32407 በቅጽ 11 ላይ ትርጓሜ የሰጠ ሲሆን በዚህም መሰረት በወራሾች መካከል የሚነሳ የውርስ ንብረት ክርክር በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1000/1/ በተደነገገው አግባብ በሶስት አመት ጊዜ ውስጥ መቅረብ ያለበት ሲሆን ወራሽ በሆነ እና ወራሽ ባልሆነ ተከራካሪ ወገን መካከል የሚቀርበው የውርስ ንብረት ይገባኛል ጥያቄ በፍ/ብ/ህ/ቁ 1677 እና 1845 መሰረት በአስር አመት ጊዜ ውስጥ ካልቀረበ መብቱ በይርጋ የሚታገድ ይሆናል፡፡

የክፍፍል ጥያቄ በይርጋ የማይታገድ ስለመሆኑ

ወራሾች ተለይተው የውርስ ሀብቱ ድርሻ ታውቆ ግን ክፍፍል ሳይደረግ የቆየ የውርስ ሀብት ያለ እንደሆነ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1062 በተገለጸው መሰረት እያንዳንዱ የጋራ ወራሾች ውርሱን እንከፋፈል በማለት በማንኛውም ጊዜ ለመጠየቅ የሚችሉ በመሆኑ የክፍፍል ጥያቄ በይርጋ የማይታገድ ይሆናል፡፡
በሙሉቀን ሰኢድ
#Ethiopia #LegalService #Lawyer Samuel
https://t.me/lawsocieties
Vacancy at Rammis Bank

🔰Rammis Bank invites qualified applicants for the following job positions.

1: Board Secretary
2: Director Legal👈👈👈👈👈
3: Director Strategy and Business Development
4: Vice President Corporate Service
5: Vice President Operations

📌Deadline: October 12- 2022

📌ሰለ ሰራው ሙሉ መረጃ ለማየት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ👇👇
👉Read Detail:- https://harmeejobs.com/job/rammis-bankvacancy/