የሕብረት ሽርክና ማሕበር መፍረስ (አን. 205-206)፡-
የሕብረት ሽርክና ማሕበር በተለያዩ ምክንያቶች ሊፈርስ የሚችል ሲሆን የሚከተሉት ምክንያቶች ለመፍረስ ያሚያበቁ ናቸው ተብለው በሕጉ ተቀምጠዋል፡- ማኅበሩ የተቋቋመው ላልተወሰነ ጊዜ ወይም ከማኅበሩ ሸሪክ በአንዱ እድሜ ልክ ድረስ ከሆነ ወይም በመመስረቻ ጽሁፉ ውስጥ የማፍረስ መብት ተጠቅሶ እንደሆነ ማንኛውም ሸሪክ በቅን ልቦና የስድስት ወራት የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ በመስጠት እንዲፈርስ ሲጠይቅ፣ ከማኅበሩ ሸሪኮች አንዱ በአካል ጉዳት ወይም በሕመም ወይም በማንኛውም ሌላ ምክንያት የማኅበሩን ሥራ ለማከናወን ያልቻለ እንደሆነ፣ በማኅበሩ ሸሪኮች መካከል አብሮ ለመሥራት የማያስችል አለመግባባት ሲፈጠር፣ ከማኅበሩ ሸሪኮች አንዱ ሲሞት ወይም የማህበርተኛው መክሰር በፍርድ ሲወሰን ወይም ሸሪክ ለመሆን ችሎታ ሲያጣ፣ ከማኅበሩ ሸሪክ የግል ገንዘብ ጠያቂዎች ያለውን ድርሻ በሙሉ ሲወስዱ ወይም በቀሪው ድርሻ እንዲቀጥል ሌሎች የማኀበሩ ሸሪኮች የማይስማሙ ከሆነ ማሕበሩ ሊፈርስ ይችላል፡፡
ከላይ የተጠቀሰው ሀሳብ ቢኖርም ቀጥሎ በተጠቀሱት ምክንያቶች ማኅበሩ ሳይፈርስ ሊቀጥል ይችላል፡- ከሸሪኮች አንዱ ማኅበሩ እንዲፈርስ ጥያቄ ሲያቀርብና ቀሪዎቹ ሸሪኮች የሸሪኩን ድርሻ ከፍለው ማኅበሩ እንዲቀጥል ሲስማሙ፤ ወይም ለሞተው ሸሪክ ወራሾች ወይም ችሎታ ላጣው ሸሪክ ሞግዚት ወይም ለከሰረው ሸሪክ ንብረት ጠባቂ የሟችን ወይም ችሎታ ያጣውን ሸሪክ ወይም የከሰረውን ሸሪክ ድርሻ በመክፈል ማኅበሩ እንዲቀጥል ስምምነት ሲደረግ ማሕበሩ ሊቀጥል ይችላል፡፡
ሒሳብ ስለማጣራት (አን. 207-209)፡-
በማሕበሩ የመመስረቻ ፅሑፍ፣ በሸሪኮች ስምምነት ወይም በፍርድ ቤት የሒሳብ አጣሪ እስከሚመደብ ድረስ ሥራ አስኪያጆች የነበራቸውን ስልጣን እንደያዙ የሚቆዩ ሲሆን ለሒሳብ አጣሪዎች የማህበሩን ንብረትና ማንኛውንም አስፈላጊ ሰነድ ማስረከብና እስከ ርክክቡ ቀን ድረስ ያከናወኑትን ሥራ ማስረዳት አለባቸው፡፡
ሒሳብ አጣሪዎች የማኅበሩ የመጨረሻ ሂሳብ እንዲጣራ አስፈረላጊ የሆኑትን ተግባሮች ሁሉ ይፈጽማሉ፡፡ በዚህም መሰረት ተጀምረው የነበሩ ሥራዎችን የማገባደድ፣ የማኅበሩን የሃብትና ዕዳ መግለጫ የማዘጋጀት፣ የማኅበሩን ሃብት የመሰብሰብ፤ የማኅበሩን ንብረት የመሸጥ፤ የማኅበሩን ዕዳ ከማኅበሩ ሃብት ወይም እንዳስፈላጊነቱ ከሸሪኮች ሌላ ገንዘብ ሰብስቦ ለገንዘብ ጠያቂዎች የመክፈል፣ በማኅበሩ ስም በፍርድ ቤት፣ በአስተዳደር አካላት ወይም በግልግል ዳኝነት የመከራከርና ጉዳዮችን የማስፈጸም፣ የማኅበሩን ሃብት ለሸሪኮች የማከፋፈል፣ ማኅበሩን ለማፍረስ አስፈላጊ የሆኑ ሌሎች ተግባራትን የማከናወን ሥልጣን አላቸው፡፡ የሥራ አስኪያጆችን ተጠያቂነት የሚመለከቱት የሕግ ድንጋጌዎች በሒሳብ አጣሪዎች ላይም ተፈጻሚነት አላቸው፡፡
ስለ ክፍፍል (አን. 211-212)፡-
የማኅበሩ ዕዳዎች ከተከፈሉና እያንዳንዱ ሸሪክ የከፈለው መዋጮ ከተመለሰ በኋላ ትርፍ ካለ በአባለቱ መካከልየሚከፋፈል ይሆናል፡፡ የማኅበሩ ገንዘብ ለሸሪኮች የሚመለሰውን መዋጮ ለመክፈል የማይበቃ ከሆነ ኪሳራው በሸሪኮች መካከል ይከፋፈላል፡፡ በመመስረቻ ጽሑፉ ሌላ የአከፋፈል ሁኔታ ካልተወሰነ በስተቀር ትርፍና ኪሳራው በሸሪኮች መካከል እኩል ይከፋፈላል፡፡
በንቃተ ህግ፣ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
የሕብረት ሽርክና ማሕበር በተለያዩ ምክንያቶች ሊፈርስ የሚችል ሲሆን የሚከተሉት ምክንያቶች ለመፍረስ ያሚያበቁ ናቸው ተብለው በሕጉ ተቀምጠዋል፡- ማኅበሩ የተቋቋመው ላልተወሰነ ጊዜ ወይም ከማኅበሩ ሸሪክ በአንዱ እድሜ ልክ ድረስ ከሆነ ወይም በመመስረቻ ጽሁፉ ውስጥ የማፍረስ መብት ተጠቅሶ እንደሆነ ማንኛውም ሸሪክ በቅን ልቦና የስድስት ወራት የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ በመስጠት እንዲፈርስ ሲጠይቅ፣ ከማኅበሩ ሸሪኮች አንዱ በአካል ጉዳት ወይም በሕመም ወይም በማንኛውም ሌላ ምክንያት የማኅበሩን ሥራ ለማከናወን ያልቻለ እንደሆነ፣ በማኅበሩ ሸሪኮች መካከል አብሮ ለመሥራት የማያስችል አለመግባባት ሲፈጠር፣ ከማኅበሩ ሸሪኮች አንዱ ሲሞት ወይም የማህበርተኛው መክሰር በፍርድ ሲወሰን ወይም ሸሪክ ለመሆን ችሎታ ሲያጣ፣ ከማኅበሩ ሸሪክ የግል ገንዘብ ጠያቂዎች ያለውን ድርሻ በሙሉ ሲወስዱ ወይም በቀሪው ድርሻ እንዲቀጥል ሌሎች የማኀበሩ ሸሪኮች የማይስማሙ ከሆነ ማሕበሩ ሊፈርስ ይችላል፡፡
ከላይ የተጠቀሰው ሀሳብ ቢኖርም ቀጥሎ በተጠቀሱት ምክንያቶች ማኅበሩ ሳይፈርስ ሊቀጥል ይችላል፡- ከሸሪኮች አንዱ ማኅበሩ እንዲፈርስ ጥያቄ ሲያቀርብና ቀሪዎቹ ሸሪኮች የሸሪኩን ድርሻ ከፍለው ማኅበሩ እንዲቀጥል ሲስማሙ፤ ወይም ለሞተው ሸሪክ ወራሾች ወይም ችሎታ ላጣው ሸሪክ ሞግዚት ወይም ለከሰረው ሸሪክ ንብረት ጠባቂ የሟችን ወይም ችሎታ ያጣውን ሸሪክ ወይም የከሰረውን ሸሪክ ድርሻ በመክፈል ማኅበሩ እንዲቀጥል ስምምነት ሲደረግ ማሕበሩ ሊቀጥል ይችላል፡፡
ሒሳብ ስለማጣራት (አን. 207-209)፡-
በማሕበሩ የመመስረቻ ፅሑፍ፣ በሸሪኮች ስምምነት ወይም በፍርድ ቤት የሒሳብ አጣሪ እስከሚመደብ ድረስ ሥራ አስኪያጆች የነበራቸውን ስልጣን እንደያዙ የሚቆዩ ሲሆን ለሒሳብ አጣሪዎች የማህበሩን ንብረትና ማንኛውንም አስፈላጊ ሰነድ ማስረከብና እስከ ርክክቡ ቀን ድረስ ያከናወኑትን ሥራ ማስረዳት አለባቸው፡፡
ሒሳብ አጣሪዎች የማኅበሩ የመጨረሻ ሂሳብ እንዲጣራ አስፈረላጊ የሆኑትን ተግባሮች ሁሉ ይፈጽማሉ፡፡ በዚህም መሰረት ተጀምረው የነበሩ ሥራዎችን የማገባደድ፣ የማኅበሩን የሃብትና ዕዳ መግለጫ የማዘጋጀት፣ የማኅበሩን ሃብት የመሰብሰብ፤ የማኅበሩን ንብረት የመሸጥ፤ የማኅበሩን ዕዳ ከማኅበሩ ሃብት ወይም እንዳስፈላጊነቱ ከሸሪኮች ሌላ ገንዘብ ሰብስቦ ለገንዘብ ጠያቂዎች የመክፈል፣ በማኅበሩ ስም በፍርድ ቤት፣ በአስተዳደር አካላት ወይም በግልግል ዳኝነት የመከራከርና ጉዳዮችን የማስፈጸም፣ የማኅበሩን ሃብት ለሸሪኮች የማከፋፈል፣ ማኅበሩን ለማፍረስ አስፈላጊ የሆኑ ሌሎች ተግባራትን የማከናወን ሥልጣን አላቸው፡፡ የሥራ አስኪያጆችን ተጠያቂነት የሚመለከቱት የሕግ ድንጋጌዎች በሒሳብ አጣሪዎች ላይም ተፈጻሚነት አላቸው፡፡
ስለ ክፍፍል (አን. 211-212)፡-
የማኅበሩ ዕዳዎች ከተከፈሉና እያንዳንዱ ሸሪክ የከፈለው መዋጮ ከተመለሰ በኋላ ትርፍ ካለ በአባለቱ መካከልየሚከፋፈል ይሆናል፡፡ የማኅበሩ ገንዘብ ለሸሪኮች የሚመለሰውን መዋጮ ለመክፈል የማይበቃ ከሆነ ኪሳራው በሸሪኮች መካከል ይከፋፈላል፡፡ በመመስረቻ ጽሑፉ ሌላ የአከፋፈል ሁኔታ ካልተወሰነ በስተቀር ትርፍና ኪሳራው በሸሪኮች መካከል እኩል ይከፋፈላል፡፡
በንቃተ ህግ፣ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
Legal Officer I
Tsehay Insurance S.C
Addis Ababa
Apply
1 day agoFull–time
Job Description Tsehay Insurance S.C is one the Private Companies Operating in the Country. It was established in March 2012 and engaged in all types of general insurance business. the Company,s head Office is located at Bole, in Front Of Brass Hospital. Our Company therefore invites interested and qualified Candidates to fill the Following Vacant Positions. Job Requirements LLB Work Experience -------1 years Of relevant experience Required No------One /1/ How to Apply NB:- For No 1, 2 3, 4 Insurance Experience is Mandatory. Terms Of Employment --------Permanent Place Of Work:------For all Positions Addis Ababa Salary:---------As per the Scale Of the Company with Other benefit Packages Interested applicants, who Fulfill the minimum requirements, can send their non-returnable application with CV and Copies of relevant documents within 7 Working days from the First date of this announcement to Tsehay Insurance S.C Manager, HR & Property Administration P.O.Box 56144 Addis Ababa
Tsehay Insurance S.C
Addis Ababa
Apply
1 day agoFull–time
Job Description Tsehay Insurance S.C is one the Private Companies Operating in the Country. It was established in March 2012 and engaged in all types of general insurance business. the Company,s head Office is located at Bole, in Front Of Brass Hospital. Our Company therefore invites interested and qualified Candidates to fill the Following Vacant Positions. Job Requirements LLB Work Experience -------1 years Of relevant experience Required No------One /1/ How to Apply NB:- For No 1, 2 3, 4 Insurance Experience is Mandatory. Terms Of Employment --------Permanent Place Of Work:------For all Positions Addis Ababa Salary:---------As per the Scale Of the Company with Other benefit Packages Interested applicants, who Fulfill the minimum requirements, can send their non-returnable application with CV and Copies of relevant documents within 7 Working days from the First date of this announcement to Tsehay Insurance S.C Manager, HR & Property Administration P.O.Box 56144 Addis Ababa
It seems Activism on the Rights of Women in this country doesn’t engage more on substantive issues critical to women. I haven’t seen anyone in this sphere talking about the talk of the town i.e the upcoming national dialogue. What about the Ministry of Women? Is it making preparation in letting women participate in the Dialogue? Do they even have checked the law in the making? What about other stakeholders?
Dear fellow women, please be informed that such a process may become an important moment that determines the future of the country. So, please don’t leave your country only to the dictates, judgment, and decisions of your brothers. Remember how they led us through until now. So, be active on this.
Women's participation, as they may come with a different opinion, may also facilitate concessions and break any potential deadlock in the negotiation process. But for this, women need to have a defined evaluation of the situation of the country, a defined interest about the future of the country, and an organized body to coordinate this.
Dear fellow women, please be informed that such a process may become an important moment that determines the future of the country. So, please don’t leave your country only to the dictates, judgment, and decisions of your brothers. Remember how they led us through until now. So, be active on this.
Women's participation, as they may come with a different opinion, may also facilitate concessions and break any potential deadlock in the negotiation process. But for this, women need to have a defined evaluation of the situation of the country, a defined interest about the future of the country, and an organized body to coordinate this.
Forwarded from 🇪🇹የሕግ ጉዳይ
አራጣ
አራጣ ማለት በሕግ ከተፈቀደዉ በላይ በሆነ የወለድ ምጣኔ ገንዘብ ማበደር ማለት ነዉ፡፡ የአራጣ ብድር ተግባር በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ የወንጀል ተጠያቂነትን የሚያስከትል መሆኑ በግልጽ ተደንግጓል፡፡
የወንጀል ሕግ አንቀጽ 712 ላይ ተደንግጓል
“ማንም ሰዉ የተበዳዩን ችግረኛነት፣ የበታችነቱን፣ ወይም የገንዘብ ችግሩን ወይም መንፈሰ ደካማነቱን ወይም ልምድ ወይም ችሎታ የሌለዉ መሆኑን መሰረት በማድረግ በሕግ ከተፈቀደዉ ወለድ በላይ ገንዘብ ያበደረዉ እንደሆነ ወይም ካበደረዉ ገንዘብ ጋር በግልጽ ተመጣጣኝነት የሌለዉን ንብረት በምትኩ እንዲሰጠዉ ያደረገ ወይም ቃል ያስገባዉ እንደሆነ በቀላል እስራት ወይም እንደነገሩ ሁኔታ ከ5 ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት እና በመቀጮ ይቀጣል፡፡"
ሕጋዊ በሆነ አካል ፊት ማለትም በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ በግለሰቦች ወይም በድርጅቶች መካከል የሚደረግ የገንዘብ ብድር ውልን ለማከናወን (በፍ/ብ/ህ/ቁ/ 2471 መሠረት) የሚከተሉትን ቅድመ ሁኔታዎች ተዋዋይ ወገኖች ማሟላት ይገባቸዋል ፡፡
1. በሕግ አግባብ የተዘጋጀ የውል ሰነድ፤
2. ተዋዋዮች ከሕግ ወይም ከውል የመነጨ ስልጣን ያላቸው መሆኑን ማስረጃ ፤
3. የተዋዋዮች መታወቂያ ፤
4 የተዋዋዮች ያላገባ ወይም ያገባ ከሆኑ የጋብቻ ማስረጃ እና የትዳር አጋር የፈቃድ ስምምነት፤
5. ተበዳሪው የንግድ ማህበር ከሆነ መመስረቻ ጽሑፍ፣ መተዳደሪያ ደንብ፣ የንግድ ዋና ምዝገባ እና እንደ አስፈላጊነቱ ቃለጉባኤ አስፈላጊ ናቸው፡፡
|ተዋዋይ ወገኖች በተቋሙ የሚዋዋሉት የገንዘብ ብድር ውል ከሕግና ከማህበረሰብ ሞራል አንጻር በማይጻረር መልኩ አግባብ ባላቸው ሕጎች መሰረት ተረገጋግጦ ይጸድቃል፡፡
በጠበቃ ሳሙኤል
https://t.me/LawyerEthiopia
አራጣ ማለት በሕግ ከተፈቀደዉ በላይ በሆነ የወለድ ምጣኔ ገንዘብ ማበደር ማለት ነዉ፡፡ የአራጣ ብድር ተግባር በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ የወንጀል ተጠያቂነትን የሚያስከትል መሆኑ በግልጽ ተደንግጓል፡፡
የወንጀል ሕግ አንቀጽ 712 ላይ ተደንግጓል
“ማንም ሰዉ የተበዳዩን ችግረኛነት፣ የበታችነቱን፣ ወይም የገንዘብ ችግሩን ወይም መንፈሰ ደካማነቱን ወይም ልምድ ወይም ችሎታ የሌለዉ መሆኑን መሰረት በማድረግ በሕግ ከተፈቀደዉ ወለድ በላይ ገንዘብ ያበደረዉ እንደሆነ ወይም ካበደረዉ ገንዘብ ጋር በግልጽ ተመጣጣኝነት የሌለዉን ንብረት በምትኩ እንዲሰጠዉ ያደረገ ወይም ቃል ያስገባዉ እንደሆነ በቀላል እስራት ወይም እንደነገሩ ሁኔታ ከ5 ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት እና በመቀጮ ይቀጣል፡፡"
ሕጋዊ በሆነ አካል ፊት ማለትም በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ በግለሰቦች ወይም በድርጅቶች መካከል የሚደረግ የገንዘብ ብድር ውልን ለማከናወን (በፍ/ብ/ህ/ቁ/ 2471 መሠረት) የሚከተሉትን ቅድመ ሁኔታዎች ተዋዋይ ወገኖች ማሟላት ይገባቸዋል ፡፡
1. በሕግ አግባብ የተዘጋጀ የውል ሰነድ፤
2. ተዋዋዮች ከሕግ ወይም ከውል የመነጨ ስልጣን ያላቸው መሆኑን ማስረጃ ፤
3. የተዋዋዮች መታወቂያ ፤
4 የተዋዋዮች ያላገባ ወይም ያገባ ከሆኑ የጋብቻ ማስረጃ እና የትዳር አጋር የፈቃድ ስምምነት፤
5. ተበዳሪው የንግድ ማህበር ከሆነ መመስረቻ ጽሑፍ፣ መተዳደሪያ ደንብ፣ የንግድ ዋና ምዝገባ እና እንደ አስፈላጊነቱ ቃለጉባኤ አስፈላጊ ናቸው፡፡
|ተዋዋይ ወገኖች በተቋሙ የሚዋዋሉት የገንዘብ ብድር ውል ከሕግና ከማህበረሰብ ሞራል አንጻር በማይጻረር መልኩ አግባብ ባላቸው ሕጎች መሰረት ተረገጋግጦ ይጸድቃል፡፡
በጠበቃ ሳሙኤል
https://t.me/LawyerEthiopia
ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የፌዴራል ፍርድ ቤት መር አስማሚነት መመሪያ አወጣ
**************
በፍትሃብሔር ጉዳዮ በተከታካሪ ወገኖች መካከል የሚነሱ አለመግባባቶችን በስምምነት መፍታት የሚሰጠው ጥቅምና ለፍትሕ ሥርዓቱ መጎልበት ያለውን አስተዋጽኦ በተለይም በተከራካሪዎ መካከል ቀጣይነት ያለው መልካም ግንኙነት እንዲኖር ለማስቻል ተከራካሪዎቹ ራሳቸው አለመግባባቶቻቸውን ለመፍታት በስምምነት መጨረስ ያለውን አስተዋጽኦ ከግምት በማስገባት፤
በፍርድ ቤቶች ላይ የሚኖር የመዝገብ መደራረብ ምክንያት ጉዳዮች እልባት ሳያገኙ የሚዘገዩበትን ሁኔታ ለመቀነስ አንዳንድ የፍትሐብሔር ጉዳዮችን በስምምነት መፍታት ለባለጉዳዮች አማራጭ የሙግት መፍቻ ሥርዓትን የበለጠ ተደራሽ በማድረግ፣ ፈጣን የሆነ የፍትሕ ስርዓትን ለማስፈን ስለሚያስችል፤
አስማሚዎች መብቶቻቸውን እና ሃላፊነታቸውን ተረድተው የማስማማት ተግባራቸውን በጥራት፣ በብቃት እና ምክንያታዊ በሆነ አጭር ጊዜ ውስጥ እንዲያከናውኑ የስነ-ምግባር መርሆች እና ዲስፕሊን ስነ-ስርዓቶችን መደንገግ አስፈላጊ በመሆኑ፤
የፍርድ ቤት መር አስማሚነትን የሚያግዝ የአስማሚዎችን የዲሲፕሊን ጉዳዮች የሚመረምር ኮሚቴ በፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 45(7) መሰረት መቋቋም ስለሚያስፈልገው እና የኮሚቴውንም ዝርዝር ሃላፊነት፤ አወቃቀር እና የተጠያቂነት ወሰን መደንገግ ስለሚያስፈልግ፤
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 45(8) እና 48(4) በተሰጠው ስልጣን መሰረት የፍርድ ቤት መር የአስማሚነት መመሪያ ወጥቷል፡፡
ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ያወጣው መመሪያ የፌዴራል ፍርድ ቤት መር አስማሚነት መመሪያ ቁጥር 12/2014 በሚል ስያሜ ይጠራል፡፡
የመመሪያውን ዲጂታል (ፒዲኤፍ) ቅጂ በጠቅላይ ፍርድ ቤት ድረ-ገጽ እና ቴሌግራም ቻናል ወይም ከታች በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ ያገኙታል፡፡
http://196.189.91.203/News-Media/ArtMID/1170/ArticleID/993/%e1%8c%a0%e1%89%85%e1%88%8b%e1%8b%ad-%e1%8d%8d%e1%88%ad%e1%8b%b5-%e1%89%a4%e1%89%b1-%e1%8b%a8%e1%8d%8c%e1%8b%b4%e1%88%ab%e1%88%8d-%e1%8d%8d%e1%88%ad%e1%8b%b5-%e1%89%a4%e1%89%b5-%e1%88%98%e1%88%ad-%e1%8a%a0%e1%88%b5%e1%88%9b%e1%88%9a%e1%8a%90%e1%89%b5-%e1%88%98%e1%88%98%e1%88%aa%e1%8b%ab-%e1%8a%a0%e1%8b%88%e1%8c%a3
https://t.me/fscethiopiaPR/74
ነጻና ገለልተኛ ፍ/ቤት ለህግ የበላይነት!
የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
**************
በፍትሃብሔር ጉዳዮ በተከታካሪ ወገኖች መካከል የሚነሱ አለመግባባቶችን በስምምነት መፍታት የሚሰጠው ጥቅምና ለፍትሕ ሥርዓቱ መጎልበት ያለውን አስተዋጽኦ በተለይም በተከራካሪዎ መካከል ቀጣይነት ያለው መልካም ግንኙነት እንዲኖር ለማስቻል ተከራካሪዎቹ ራሳቸው አለመግባባቶቻቸውን ለመፍታት በስምምነት መጨረስ ያለውን አስተዋጽኦ ከግምት በማስገባት፤
በፍርድ ቤቶች ላይ የሚኖር የመዝገብ መደራረብ ምክንያት ጉዳዮች እልባት ሳያገኙ የሚዘገዩበትን ሁኔታ ለመቀነስ አንዳንድ የፍትሐብሔር ጉዳዮችን በስምምነት መፍታት ለባለጉዳዮች አማራጭ የሙግት መፍቻ ሥርዓትን የበለጠ ተደራሽ በማድረግ፣ ፈጣን የሆነ የፍትሕ ስርዓትን ለማስፈን ስለሚያስችል፤
አስማሚዎች መብቶቻቸውን እና ሃላፊነታቸውን ተረድተው የማስማማት ተግባራቸውን በጥራት፣ በብቃት እና ምክንያታዊ በሆነ አጭር ጊዜ ውስጥ እንዲያከናውኑ የስነ-ምግባር መርሆች እና ዲስፕሊን ስነ-ስርዓቶችን መደንገግ አስፈላጊ በመሆኑ፤
የፍርድ ቤት መር አስማሚነትን የሚያግዝ የአስማሚዎችን የዲሲፕሊን ጉዳዮች የሚመረምር ኮሚቴ በፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 45(7) መሰረት መቋቋም ስለሚያስፈልገው እና የኮሚቴውንም ዝርዝር ሃላፊነት፤ አወቃቀር እና የተጠያቂነት ወሰን መደንገግ ስለሚያስፈልግ፤
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 45(8) እና 48(4) በተሰጠው ስልጣን መሰረት የፍርድ ቤት መር የአስማሚነት መመሪያ ወጥቷል፡፡
ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ያወጣው መመሪያ የፌዴራል ፍርድ ቤት መር አስማሚነት መመሪያ ቁጥር 12/2014 በሚል ስያሜ ይጠራል፡፡
የመመሪያውን ዲጂታል (ፒዲኤፍ) ቅጂ በጠቅላይ ፍርድ ቤት ድረ-ገጽ እና ቴሌግራም ቻናል ወይም ከታች በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ ያገኙታል፡፡
http://196.189.91.203/News-Media/ArtMID/1170/ArticleID/993/%e1%8c%a0%e1%89%85%e1%88%8b%e1%8b%ad-%e1%8d%8d%e1%88%ad%e1%8b%b5-%e1%89%a4%e1%89%b1-%e1%8b%a8%e1%8d%8c%e1%8b%b4%e1%88%ab%e1%88%8d-%e1%8d%8d%e1%88%ad%e1%8b%b5-%e1%89%a4%e1%89%b5-%e1%88%98%e1%88%ad-%e1%8a%a0%e1%88%b5%e1%88%9b%e1%88%9a%e1%8a%90%e1%89%b5-%e1%88%98%e1%88%98%e1%88%aa%e1%8b%ab-%e1%8a%a0%e1%8b%88%e1%8c%a3
https://t.me/fscethiopiaPR/74
ነጻና ገለልተኛ ፍ/ቤት ለህግ የበላይነት!
የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
Telegram
The Federal Supreme Court of Ethiopia
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥ 1234/2013 አንቀጽ 45(8) እና 48(4) በተሰጠው ስልጣን መሰረት የፌዴራል ፍርድ ቤት መር አስማሚነት መመሪያ ቁጥር 12/2012 አወጥቷል፡፡ የመመሪያውን ዲጂታል (ፒዲኤፍ) ቅጂ እነሆ ብለናል፡፡ http://196.189.91.203/News-Media/ArtMID/1170/ArticleID/993/%e1%8c%a0%e1%89%85%e1%88%8b%e1%8b%ad…
የሀገር ክህደት ወንጀል (Treason) እና የሚያስከትለዉ ተጠያቂነት
ሀገር ለብዙዎች በቃል ከሚነገረው በላይ ከስሜት ጋር ጥልቅ ቁርኝት ያለው ነገር ነው፡፡ ሰዎች ለሀገራቸው ካላቸው ፍቅር በመነጨም ሀገራቸው ከሌሎች የተሻለች ትሆን ዘንድ ሲጥሩ እና አልፎም ችግር ሲገጥም ለሀገራቸው መስዋዕትነት ሲከፍሉ ማየት የነባራዊ አለም እውነታ ነው፡፡ በአንፃሩ ጥቂቶች በተለያየ ምክንያት የሀገራቸው ጥቅም ተፃራሪ ሆነው የሚገኙበትም ሁኔታ አለ፡፡ ሁሉም በሚባል ደረጃ ሀገራት መሰል ድርጊቶችን ከወንጀሎች ሁሉ በበለጠ ክብደት ሰጥተው የሚያወግዟቸውና ተፈፅመውም ሲገኙ ከባድ ቅጣት የሚያስከትሉ ናቸው፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ በሀገር ላይ ከሚፈፀሙ ወንጀሎች በጉልህ የሚነሳው የሀገር ክህደት ወንጀል ምንነት፣ ታሪካዊ አመጣጥ እና በሀገራችን ያለውን የህግ ማዕቀፍ የምንመለከት ይሆናል፡፡
የሀገር ክህደት (Treason) ምንነት እና ታሪካዊ አመጣጥ
የሀገር ክህደት ወንጀል በታሪክ በጉልህ የሚታወቅና አሁን ባለበት ደረጃ ለመድረስ ተለያዩ የታሪክ ሂደቶችን ያለፈ ነው፡፡ "Treason" የሚለው ቃል “tradere” ከሚለው የላቲን ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም አሳልፎ መስጠት እንደማለት ነው፡፡(free encyclopedia) በጥንት የሮም ታሪክ የሀገር ክህደት ትርጉም ሰፋ ተደርጎ የሚተረጎም ነበር፡፡ “ይኸውም ማንኛውም ሮማዊ በማንኛውም ሁኔታ ለሀገሩ ተቃራኒ ከሆነ በተለይም ከውጪ ጠላት ጋር ከተባበረ የክህደት ወንጀል እንደፈፀመ የሚቆጠር ሲሆን ፈፃሚው “Perduelli” ጠላት ይባል ነበር፡፡ በሂደት ቀድሞ “Perduelli” በሚል ይታወቅ የነበረው “crimen mnajestatis” የተተካ ሲሆን የሮማን ህዝብና ንጉሰነገስት ክብር መንካትን ያካትት ነበር፡፡ ይሁንና በኋላኛው ሂደት ውስጥ የተከሳሹን መብት ለመጠበቅ ጥረት ይደረግ ነበር፡፡ ለአብነትም ተከሳሹ በአንድ ሰው ምስክርነት ብቻ እንዳይቀጣ የማድረግና ጥፋተኛ ቢባል እንኳን ከሀገር እንዲወጣ እድል እስከመስጠት ይደርስ ነበር፡፡((1959) "Historical Concept of Treason: English, American," Indiana Law Journal: Vol. 35)
በቀደመው የእንግሊዝ ታሪክ ውስጥ ተጠቃሽ በሆነው ንጉስ ኤድዋርድ ሶስተኛ (Edward III, 1312- 1377) የሀገር ክህደት (Treason) በአግባቡ ትርጉም ያልተሰጠው እና ንጉሳዊ አስተዳደሩን ለማስደሰት በዘፈቀደ የሚተረጎም (constructive treasons) የነበረ በመሆኑ ግለሰቦች የተከለከለውን ድርጊት አውቀው ከመፈፀም ለመታቀብ ግራ የሚጋቡበት ሁኔታ ነበር፡፡ ከዚህም አልፎ ለወንጀሉ ግልፅ ትርጉም አለመኖሩ የንጉሳዊው አስተዳደር አገልጋዮች ሰዎችን እየያዙ ለመፍታት ገንዘብ እስከመጠየቅ እንዲደርሱ እድል የፈጠረ ነበር፡፡ ይህንን በዘፈቀደ የሚደረግ ትርጉምን ለመከላከል ይቻል ዘንድም ፓርላማው ህግ (Statute of 25 Edward III or Treason Act of 1351) ለማውጣት በቅቷል:: (McConkie, J. Taylor (2013) "State Treason: The History and Validity of Treason Against Individual States," Kentucky Law Journal: Vol. 101 : Iss. 2 , Article 3.)
ዛሬ የሰብአዊ መብት ተሟጋች እንደሆነች የምትገልፀው አሜሪካም የእንግሊዝ ቅኝ ግዛት በነበረችበት ጊዜ በተመሳሳይ ሂደት ያለፈች ሲሆን የእንግሊዝ ህግ በተለይም የሀገር ክህደትን በተመለከተ የወጣው ህግ (Statute of 25 Edward III or Treason Act of 1351) ለረዥም ጊዜ በሥራ ላይ ቆይቷል፡፡ በ1776 ኮንቲነንታል ኮንግረስ (Continental Congress) የሀገር ክህደት ወንጀልን ቅርፅ ለማስያዝ ይችላል ያለውንና በሁሉም ቅኝ ግዛቶች የሚተገበር ውሳኔ ያሳለፈ ሲሆን በውሳኔውም ዩናይትድ እስቴትስ ቅኝ ቅዛቶች አባል የሆነ ወይም የቅኝ ግዛቶቹን ጥቅም እንዲያስከብር የተመደበ ሰው በቅኝ ግዛቶቹ ላይ ጦርነት ያወጀ ወይም ለቅኝ ግዛቶቹ ጠላቶች ድጋፍ ወይም እርዳታ የሰጠ ከሆነ የሀገር ክህደት ወንጀል እንደሚፈፅም አስቀምጧል፡፡ ሆኖም ለሀገር ክህደት የሚሰጠው ትርጉም መስፋቱን ማቆም ያልቻለ ከመሆኑም በላይ ለአገዛዙ ምቹ ያልሆነ የፖለቲካ አመለካከት እራሱ የሀገር ክህደት ወንጀል ተደርጎ እስከመቆጠር ደርሶ ነበር፡፡ ከዚህ ሁሉ ሂደት በኋላ የሀገር ክህደት ወንጀልን ለዳኞች መተው የግለሰብ ነፃነትን ይጎዳል በሚል እምነት በህገመንግስት ማርቀቅ ሂደት ወንጀሉ ጠባብ ትርጉም እንዲሰጠው ሊደረግ ችሏል፡፡ (McConkie, J. Taylor (2013) "State Treason: The History and Validity of Treason Against Individual States," Kentucky Law Journal: Vol. 101 : Iss. 2 , Article 3.)
ወደ ሀገራችን ስንመጣ በታሪክ በቀደምትነት የሚጠቀሰው ፍትሀነገስት ስለከሀዲነት ያካተተው ሀሳብ ቢኖርም ከእምነት ጋር የተያያዘ እንጂ የሀገር ክህደት በዘመናዊው የህግ መስክ ያለውን እንደምታ የያዘ አልነበረም፡፡ ሆኖም በሀገራችን በሀገር ጠላት በተለይ ከውጪ ጠላት ጋር ትስስር መፍጠር አዲስ አልነበረም፡፡ በጣልያን ወረራ ወቅት ከወራሪው ጋር ተባብረው በወገናቸውና በሀገራቸው ላይ በተፃራሪ ከመቆም አልፈው ለሀገራቸው የሚቆሙ ዜጎችን ለጠላት አሳልፈው እስከመስጠት የደረሱ እንደነበሩ ታሪክ ምስክር ነው፡፡ ለጣልያን ገብረው የነበሩ መሳፍን አብረው ለመስራት የፈቀዱ ቢሆንም የፋሺስት ስርአት ዘረኛ ከመሆኑ አንፃር ያሰቡትን ባያገኙም ወርሀዊ ገንዘብ ማግኘት ችለው ነበር፡፡ ለአብነት እራሱ ሀይሉ ተ/ሀይማት አራት ሺ (4000) ሊሬ እንዲሁም እራስ ጌታቸው አባተ ደግሞ ሰባት ሺ (7000) ሊሬ ወርሃዊ አበል ይቀበሉ ነበር፡፡ በተጨማሪም በስተመጨረሻ ወራሪው ከህዝቡ የሚገጥመው ተቃውሞ እየበረታ ሲመጣ ተቃውሞውን ለማለዘብ እና ህዝቡን ለመያዝ የኢትዮጵያን ዜጎች ለመጠቀም ሞክረዋል፡፡
ለአብነት ራስ ሀይሉን ወደ ጎጃም፣ ደጃች ሀ/ስላሴ ጉግሳን ወደ ትግራይ፣ ደጃች አያሌው ብሩን የአማራ ግዛት ጠቅላይ እንደራሴ አድርጎ ሾሞ ነበር፡፡ (ባህሩ ዘውዴ፣የኢትዮጵያ ታሪክ ከ1847 እስከ 1983፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ፣ 1999፣ ገጽ 175፣176)
ከዚህም ግንዛቤ በመውሰድ ይመስላል በሀገራችን በዘመናዊ መልክ ህግጋት በተረቀቁበት በ1950ቹ ሥራ ላይ በዋለው የወንጀለኛ መቅጫ ህግ የሀገር ክህደት ወንጀልን ጨምሮ ሌሎች በሀገር ላይ የሚፈፀሙ የወንጀል ድርጊቶችን በወንጀልነት እንዲካተቱ ተደርጎ ነበር፡፡ ይህ ህግ ለረጅም ጊዜ በሥራ ላይ የቆየ ሲሆን በ1996 ዓ.ም አሁን በሥራ ላይ ባለው ተተክቷል፡፡
የሀገር ክህደት ወንጀል እና የሚያስከትለው ቅጣት በኢትዮጵያ
በሀገራችን የሀገር ክህደት ወንጀል በተደራጀ ምልኩ በወንጀልነት የተደነገገው በ1952 ዓ.ም በወጣ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ሲሆን ይህ ህግ በ1996 ዓ.ም በወጣው የወንጀል ህግ ተተክቷል፡፡ በቀደመው የወንጀለኛ መቅጫ ህግም ሆነ በአሁኑ የወንጀል ህግ የሀገር ክህደት ወንጀል የተገለፀው “ክዳት” የሚል ቃል ነው፡፡ በተለያዩ ሀገራት በህግ ለሀገር ክህደት የሚሰጠው ትርጓሜ የሚጋራው ነገር ቢኖርም እንደየሀገራቱ ተጨባጭ ሁኔታ ልዩነት መኖሩም አይካድም፡፡ በሀገራችን የወንጀል ህጉ ክዳትን በሶስት ከፍሎ አስቀምጧል፡፡
ሀገር ለብዙዎች በቃል ከሚነገረው በላይ ከስሜት ጋር ጥልቅ ቁርኝት ያለው ነገር ነው፡፡ ሰዎች ለሀገራቸው ካላቸው ፍቅር በመነጨም ሀገራቸው ከሌሎች የተሻለች ትሆን ዘንድ ሲጥሩ እና አልፎም ችግር ሲገጥም ለሀገራቸው መስዋዕትነት ሲከፍሉ ማየት የነባራዊ አለም እውነታ ነው፡፡ በአንፃሩ ጥቂቶች በተለያየ ምክንያት የሀገራቸው ጥቅም ተፃራሪ ሆነው የሚገኙበትም ሁኔታ አለ፡፡ ሁሉም በሚባል ደረጃ ሀገራት መሰል ድርጊቶችን ከወንጀሎች ሁሉ በበለጠ ክብደት ሰጥተው የሚያወግዟቸውና ተፈፅመውም ሲገኙ ከባድ ቅጣት የሚያስከትሉ ናቸው፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ በሀገር ላይ ከሚፈፀሙ ወንጀሎች በጉልህ የሚነሳው የሀገር ክህደት ወንጀል ምንነት፣ ታሪካዊ አመጣጥ እና በሀገራችን ያለውን የህግ ማዕቀፍ የምንመለከት ይሆናል፡፡
የሀገር ክህደት (Treason) ምንነት እና ታሪካዊ አመጣጥ
የሀገር ክህደት ወንጀል በታሪክ በጉልህ የሚታወቅና አሁን ባለበት ደረጃ ለመድረስ ተለያዩ የታሪክ ሂደቶችን ያለፈ ነው፡፡ "Treason" የሚለው ቃል “tradere” ከሚለው የላቲን ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም አሳልፎ መስጠት እንደማለት ነው፡፡(free encyclopedia) በጥንት የሮም ታሪክ የሀገር ክህደት ትርጉም ሰፋ ተደርጎ የሚተረጎም ነበር፡፡ “ይኸውም ማንኛውም ሮማዊ በማንኛውም ሁኔታ ለሀገሩ ተቃራኒ ከሆነ በተለይም ከውጪ ጠላት ጋር ከተባበረ የክህደት ወንጀል እንደፈፀመ የሚቆጠር ሲሆን ፈፃሚው “Perduelli” ጠላት ይባል ነበር፡፡ በሂደት ቀድሞ “Perduelli” በሚል ይታወቅ የነበረው “crimen mnajestatis” የተተካ ሲሆን የሮማን ህዝብና ንጉሰነገስት ክብር መንካትን ያካትት ነበር፡፡ ይሁንና በኋላኛው ሂደት ውስጥ የተከሳሹን መብት ለመጠበቅ ጥረት ይደረግ ነበር፡፡ ለአብነትም ተከሳሹ በአንድ ሰው ምስክርነት ብቻ እንዳይቀጣ የማድረግና ጥፋተኛ ቢባል እንኳን ከሀገር እንዲወጣ እድል እስከመስጠት ይደርስ ነበር፡፡((1959) "Historical Concept of Treason: English, American," Indiana Law Journal: Vol. 35)
በቀደመው የእንግሊዝ ታሪክ ውስጥ ተጠቃሽ በሆነው ንጉስ ኤድዋርድ ሶስተኛ (Edward III, 1312- 1377) የሀገር ክህደት (Treason) በአግባቡ ትርጉም ያልተሰጠው እና ንጉሳዊ አስተዳደሩን ለማስደሰት በዘፈቀደ የሚተረጎም (constructive treasons) የነበረ በመሆኑ ግለሰቦች የተከለከለውን ድርጊት አውቀው ከመፈፀም ለመታቀብ ግራ የሚጋቡበት ሁኔታ ነበር፡፡ ከዚህም አልፎ ለወንጀሉ ግልፅ ትርጉም አለመኖሩ የንጉሳዊው አስተዳደር አገልጋዮች ሰዎችን እየያዙ ለመፍታት ገንዘብ እስከመጠየቅ እንዲደርሱ እድል የፈጠረ ነበር፡፡ ይህንን በዘፈቀደ የሚደረግ ትርጉምን ለመከላከል ይቻል ዘንድም ፓርላማው ህግ (Statute of 25 Edward III or Treason Act of 1351) ለማውጣት በቅቷል:: (McConkie, J. Taylor (2013) "State Treason: The History and Validity of Treason Against Individual States," Kentucky Law Journal: Vol. 101 : Iss. 2 , Article 3.)
ዛሬ የሰብአዊ መብት ተሟጋች እንደሆነች የምትገልፀው አሜሪካም የእንግሊዝ ቅኝ ግዛት በነበረችበት ጊዜ በተመሳሳይ ሂደት ያለፈች ሲሆን የእንግሊዝ ህግ በተለይም የሀገር ክህደትን በተመለከተ የወጣው ህግ (Statute of 25 Edward III or Treason Act of 1351) ለረዥም ጊዜ በሥራ ላይ ቆይቷል፡፡ በ1776 ኮንቲነንታል ኮንግረስ (Continental Congress) የሀገር ክህደት ወንጀልን ቅርፅ ለማስያዝ ይችላል ያለውንና በሁሉም ቅኝ ግዛቶች የሚተገበር ውሳኔ ያሳለፈ ሲሆን በውሳኔውም ዩናይትድ እስቴትስ ቅኝ ቅዛቶች አባል የሆነ ወይም የቅኝ ግዛቶቹን ጥቅም እንዲያስከብር የተመደበ ሰው በቅኝ ግዛቶቹ ላይ ጦርነት ያወጀ ወይም ለቅኝ ግዛቶቹ ጠላቶች ድጋፍ ወይም እርዳታ የሰጠ ከሆነ የሀገር ክህደት ወንጀል እንደሚፈፅም አስቀምጧል፡፡ ሆኖም ለሀገር ክህደት የሚሰጠው ትርጉም መስፋቱን ማቆም ያልቻለ ከመሆኑም በላይ ለአገዛዙ ምቹ ያልሆነ የፖለቲካ አመለካከት እራሱ የሀገር ክህደት ወንጀል ተደርጎ እስከመቆጠር ደርሶ ነበር፡፡ ከዚህ ሁሉ ሂደት በኋላ የሀገር ክህደት ወንጀልን ለዳኞች መተው የግለሰብ ነፃነትን ይጎዳል በሚል እምነት በህገመንግስት ማርቀቅ ሂደት ወንጀሉ ጠባብ ትርጉም እንዲሰጠው ሊደረግ ችሏል፡፡ (McConkie, J. Taylor (2013) "State Treason: The History and Validity of Treason Against Individual States," Kentucky Law Journal: Vol. 101 : Iss. 2 , Article 3.)
ወደ ሀገራችን ስንመጣ በታሪክ በቀደምትነት የሚጠቀሰው ፍትሀነገስት ስለከሀዲነት ያካተተው ሀሳብ ቢኖርም ከእምነት ጋር የተያያዘ እንጂ የሀገር ክህደት በዘመናዊው የህግ መስክ ያለውን እንደምታ የያዘ አልነበረም፡፡ ሆኖም በሀገራችን በሀገር ጠላት በተለይ ከውጪ ጠላት ጋር ትስስር መፍጠር አዲስ አልነበረም፡፡ በጣልያን ወረራ ወቅት ከወራሪው ጋር ተባብረው በወገናቸውና በሀገራቸው ላይ በተፃራሪ ከመቆም አልፈው ለሀገራቸው የሚቆሙ ዜጎችን ለጠላት አሳልፈው እስከመስጠት የደረሱ እንደነበሩ ታሪክ ምስክር ነው፡፡ ለጣልያን ገብረው የነበሩ መሳፍን አብረው ለመስራት የፈቀዱ ቢሆንም የፋሺስት ስርአት ዘረኛ ከመሆኑ አንፃር ያሰቡትን ባያገኙም ወርሀዊ ገንዘብ ማግኘት ችለው ነበር፡፡ ለአብነት እራሱ ሀይሉ ተ/ሀይማት አራት ሺ (4000) ሊሬ እንዲሁም እራስ ጌታቸው አባተ ደግሞ ሰባት ሺ (7000) ሊሬ ወርሃዊ አበል ይቀበሉ ነበር፡፡ በተጨማሪም በስተመጨረሻ ወራሪው ከህዝቡ የሚገጥመው ተቃውሞ እየበረታ ሲመጣ ተቃውሞውን ለማለዘብ እና ህዝቡን ለመያዝ የኢትዮጵያን ዜጎች ለመጠቀም ሞክረዋል፡፡
ለአብነት ራስ ሀይሉን ወደ ጎጃም፣ ደጃች ሀ/ስላሴ ጉግሳን ወደ ትግራይ፣ ደጃች አያሌው ብሩን የአማራ ግዛት ጠቅላይ እንደራሴ አድርጎ ሾሞ ነበር፡፡ (ባህሩ ዘውዴ፣የኢትዮጵያ ታሪክ ከ1847 እስከ 1983፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ፣ 1999፣ ገጽ 175፣176)
ከዚህም ግንዛቤ በመውሰድ ይመስላል በሀገራችን በዘመናዊ መልክ ህግጋት በተረቀቁበት በ1950ቹ ሥራ ላይ በዋለው የወንጀለኛ መቅጫ ህግ የሀገር ክህደት ወንጀልን ጨምሮ ሌሎች በሀገር ላይ የሚፈፀሙ የወንጀል ድርጊቶችን በወንጀልነት እንዲካተቱ ተደርጎ ነበር፡፡ ይህ ህግ ለረጅም ጊዜ በሥራ ላይ የቆየ ሲሆን በ1996 ዓ.ም አሁን በሥራ ላይ ባለው ተተክቷል፡፡
የሀገር ክህደት ወንጀል እና የሚያስከትለው ቅጣት በኢትዮጵያ
በሀገራችን የሀገር ክህደት ወንጀል በተደራጀ ምልኩ በወንጀልነት የተደነገገው በ1952 ዓ.ም በወጣ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ሲሆን ይህ ህግ በ1996 ዓ.ም በወጣው የወንጀል ህግ ተተክቷል፡፡ በቀደመው የወንጀለኛ መቅጫ ህግም ሆነ በአሁኑ የወንጀል ህግ የሀገር ክህደት ወንጀል የተገለፀው “ክዳት” የሚል ቃል ነው፡፡ በተለያዩ ሀገራት በህግ ለሀገር ክህደት የሚሰጠው ትርጓሜ የሚጋራው ነገር ቢኖርም እንደየሀገራቱ ተጨባጭ ሁኔታ ልዩነት መኖሩም አይካድም፡፡ በሀገራችን የወንጀል ህጉ ክዳትን በሶስት ከፍሎ አስቀምጧል፡፡
የመጀመሪያው ክፍ ያለ ክዳት ሲሆን በወንጀል ህግ አንቀፅ 248 መሰረት ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የሆነ ወይም የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም እንዲያስከብር በግልፅ አደራ የተጣለበት ሰው
የጦር መሳሪያ በመያዝ ወይም በፀብ ድርጊት ኢትዮጵያን የተቃወመ እንደሆነ
ከኢትዮጵያ ጋር ጦርንት ከሚያደርግ ሀይል ጋር ወይም ለዚሁ ሀይል ጥቅም ከሚሰራ ሰው ወይም ድርጅት ጋር በመተባበር ወይም ሚስጥራዊ ግንኙነት በማድረግ ይኸው ሀይል እንዲመቸውና እንዲቀናው በማናቸውም አኳኋን የረዳ እንደሆነ ወይም
ዕቃዎችን፣ የጦር መሳሪያዎችን፣ ፕላኖችን፣ማስረጃ የሚሆኑ ፅሁፎችን ወይም ለሀገሩ መከላከያ የሚያገለግሉ ማንኛዎቹንም ነገሮች በቀጥታ ወይም በእጅ አዙር ለጠላት አሳልፎ በመስጠት ወይም በአገልግሎቶችና ይህን የመሳሰሉ ዕቃዎችን ለጠላት በማቅረብ ጠላትን የደገፈ እንደሆነ ከፍ ያለ ክዳት ይፈፅማል፡፡ ይህ ወንጀል መፈፀሙ ሲረጋገጥም ከአምስት አመት እስከ ሀያ አምስት አመት በሚደርስ ፅኑ እስራት የሚያስቀጣ ሲሆን ነገሩ ከባድ በሆነ ጊዜ በእድሜ ልክ ፅኑ እስራት ወይም በሞት ሊያስቀጣ ይችላል፡፡
ሁለተኛው የክዳት ወንጀል ሲሆን በወንጀል ህጉ አንቀፅ 249 መሰረት ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የሆነ ወይም የኢትዮጵያን ጥቅም እንዲያስከብር በግልፅ አደራ የተጣለበት ሰው አስቦ
የኢትዮጵያን ጥቅም ለማስጠበቅ በምስጢር እንዲጠብቅና እንዳይገልፅ የተደረገውን ምስጢር፣ ሰነድ፣ የመላላክ ጉዳይ ወይም አንድ ውሳኔ ለህዝብ ወይም ለውጭ ሀገር መንግስት፣ የፖለቲካ ድርጅት፣ ሌላ ድርጅት ወይም ወኪል የገለፀ፣ አሳልፎ የሰጠ፣ ወሬውን ያስተላለፈ ወይም በግልፅ እንዲነገር ያደረገ እንደሆነ
የኢትዮጵያ እንደራሴ ወይም መልዕክተኛ ሆኖ ከውጭ ሀገር መንግስት ጋር እንዲፈፅም የተላከበትን ወይም ለኢትዮጵያ ጥቅም ሊከራከርበትና ሊፈፅም የሚገባውን ጉዳይ ግልፅ በሆነ አይነት እንዲሰናከል የደረገ እንደሆነ
የኢትዮጵያን ደህንነት፣ ነፃነት ወይም ዋነኛ ጥቅሞች የሚመለከቱትን ሰነዶች፣ ፅሁፎች ወይም ማስረጃዎች ያበላሸ፣ ያጠፋ፣ የደበቀ፣ እንዲጠፋ ያደረገ ወይም ወደ ሀሰተኛነት የለወጠ እንደሆነ
የክዳት ወንጀል ይፈፅማል፡፡ ይህ ወንጀል መፈፀሙ ሲረጋገጥም ከአስራ አምስት አመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት ሊያስቀጣ ይችላል፡፡ ሆኖም አድራጎቱ የኢትዮጵያን ህልውና ወይም ነፃነት በቀጥታ ከባድ አደጋ ላይ የሚጥል ከሆነ ቅጣቱ የሚከብድ ሲሆን ጉዳዩን የሚመለከተው ፍርድ ቤት ከአስር አመት እስከ ሀያ አምስት አመት ሊድርስ የሚችል ፅኑ እስራት መወሰን እንዲችል በህግ ተፈቅዶለታል፡፡
ከላይ የተጠቀሰው ቅጣት የተቀመጠው ሆነ ብሎ እና አስቦ ወንጀሉን ለፈፀመ ሰው ነው፡፡ ሆኖም ከላይ የተጠቀሱ ድርጊቶች በቸልተኝነት ጭምር ሊፈፀሙ የሚችሉ መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት ህጉ ቅጣት አስቀምጧል፡፡ ይኸውም ቅጣት ከስድስት ወር ያላነሰ ቀላል እስራት ሲሆን የነገሩ ከባድነት እየታየ ቅጣቱ እስከ አምስት አመት ፅኑ እስራት ሊደርስ ይችላል፡፡
ሶስተኛው የኢኮኖሚ ክዳት ሲሆን የወንጀል ህግ አንቀፅ 250 መሰረት ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የሆነ ወይም የኢትዮጵያን ጥቅም እንዲያስከብር በግልፅ አደራ የተጣለበት ሰው አስቦ
ስለለኢትዮጵያ ወይም ስለመከላከያ ሀይል ከፍተኛ ጥቅም ሲባል በምሲጢር የሚጠብቀውን ኢኮኖሚያዊ ጠባይ ያለውን የመላላክ ግንኙነት፣ ውሳኔ፣ የተደረገ ነገር ወይም ሰነድ ለህዝብ ወይም ለውጭ አገር ሰው የገለፀ፣ አሳልፎ የሰጠ፣ ይዘቱን ያስተላለፈ ወይም እነዚሁን እንዲያገኙ ያደረገ እንደሆነ
እንዲጠብቃቸው በሀላፊነት የተሰጡትን ዕቃዎች፣ መሳሪያዎች ወይም እነዚህን የመሳሰሉትን ሌሎች ነገሮች የገለፀ ወይም አሳልፎ የሰጠ እንደሆነ
ከኢትዮጵያ ጋር ጦርነት የሚያደርግ መንግስት ባወጣው ብድር ጉዳይ የተካፈለ ወይም ለብድሩ የሚውል ገንዘብ ወይም ንብረት ያዋጣ እንደሆነ
የኢኮኖሚ ክዳት ይፈፅማል፡፡ ይህ ድርጊት መፈፀሙ ከተረጋገጠም በአስር አመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት ያስቀጣል፡፡ ከባድ ሆኖ በተገኘ ጊዜ ደግሞ ቅጣቱ እስከ ሀያ አመት ፅኑ እስራት ሊደርስ ይችላል፡፡
ከላይ የተጠቀሰው ቅጣት የተቀመጠው ሆነ ብሎ እና አስቦ ወንጀሉን ለፈፀመ ሰው ነው፡፡ ሆኖም በክዳት ላይ እንደተጠቀሰው ሁሉ በኢኮኖሚ ክዳት ውስጥ የተጠቀሱት ድርጊቶች በቸልተኝነት ጭምር ሊፈፀሙ የሚችሉ መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት ህጉ ቅጣት አስቀምጧል፡፡ ይኸውም ቅጣት ከሶስት ወር ያላነሰ ቀላል እስራት ነው፡፡
ከላይ ከቀረበው የድንጋጌዎቹ ይዘት መረዳት የሚገባው የተጠቀሱት ድርጊቶች የክዳት ወንጀል የሚሆኑት በኢትዮጵያዊ ወይም የኢትዮጵያን ጥቅም እንዲያስከብር በግልፅ አደራ የተጣለበት ሰው ሲፈፀሙ ነው፡፡ በተጨማሪም በሀገራችን ህግ የክዳት ወንጀል የሚያካትተው በድንጋጌዎቹ የተጠቀሱትን ፍሬ ነገሮች በመሆኑ አንድ ኢትዮጵያዊ ወይም የኢትዮጵያን ጥቅን እንዲያስከብር አደራ የተሰጠው ሰው በክዳት ወንጀል ሊቀጣ የሚችለው ከላይ በተጠቀሱት ድንጋጌዎች የተመለከቱትን ድርጊቶች ሲፈፅም ብቻ ነው፡፡
ሆኖም በሀገር ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን በተለይ ደግሞ ከውጪ ሀይል ጋር በተገናኘ የሚፈፀሙ የወንጀል ድርጊቶች ሁሉ የሀገር ክህደት ወንጀል አድርጎ የመቁጠር ዝንባሌ ይስተዋላል፡፡ ይሁንና የወንጀል ህጋችን ወንጀሎችን ለይቶ ያስቀመጠ እንደመሆኑ ድንጋጌዎቹ ያስቀመጡትን ፍሬ ነገሮችን መመልከት የወንጀሎቹን ልዩነት ለመረዳት መፍትሄ ነው፡፡
ለምሳሌ በወንጀል ህግ አንቀፅ 251 መሰረት ከጠላት ጋር መተባበር በወንጀል ህጋችን እራሱን የቻለ ወንጀል ሲሆን ይህ ወንጀል ተፈፀመ የሚባለው ኢትዮጵያዊ የሆነ ወይም የኢትዮጵያን ጥቅም እንዲያስከብር በግልፅ አደራ የተጣለበት ሰው ኢትዮጵያ በጦርነት ላይ በምትገኝበት ጊዜ ወይም ግዛቷ በሙሉ ወይም በከፊል በጠላት በተወረረበት ጊዜ የጠላትን አላማ ለማሳካት በማሰብ በምክርም ሆነ በተግባር የደገፈ እንደሆነ በተለይም በጠላት ስም የሲቪል የአስተዳደር ሥራዎችን የሰራ ወይም ከጠላት ቁጥጥር ለማምለጥ የሚፈልጉ የወገን ተዋጊዎችን ወይም ስደተኞች ለጠላት ያጋለጠ እና ሌሎች በድንጋጌው የተመለከቱ ድርጊቶችን የፈፀመ ከሆነ ነው፡፡ልክ እንደ ክዳት ወንጀል ሁሉ ይህ ወንጀል የሚፈፀመው ኢትዮጵያዊ በሆነ ወይም የኢትዮጵያን ጥቅም እንዲያከብር በግልፅ አደራ በተጣለበት ሰው መሆኑ ከክዳት ጋር የሚያመሳስለው ቢሆንም ከጠላት ጋር የመተባበር ወንጀል የሚፈፀምበት ሁኔታ የተለየ ያደርገዋል፡፡ ማለትም የሀገር ክህደት ወንጀል በማንኛውም ጊዜ የሚፈፀም ወንጀል ሲሆን ከጠላት ጋር መተባበር ወንጀል ግን የሚደረገው ሀገራችን በጦርነት ላይ በምትገኝበት ወይም ግዛቷ በሙሉ ወይም በከፊል በጠላት በተወረረበት ጊዜ የሚፈፀም ወንጀል መሆኑን ከድንጋጌው መረዳት ይቻላል፡፡ ስለሆነም የክዳት ወንጀልን ከሌሎች መለየት አስፈላጊ ነው፡፡
በአጠቃላይ የሀገር ክህደት ወንጀል ለሀገር ከመታመን ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው ሲሆን እንደሌሎች ወንጀሎች በማንኛውም ሰው የሚፈፀም ሳይሆን ሊፈፀም የሚችለውም ኢትዮጵያዊ ወይም የኢትዮጵያን ጥቅም እንዲያስከብር ሀላፊነት በተሰጠው ሰው ብቻ ነው፡፡ በዚህም ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለሀገሩ ታማኝ እንዲሆን፣ ከክዳት ወንጀል በመታቀብ የሀገሩን ጥቅም አሳልፎ እንዳይሰጥ እንዲሁም እራሱንም ከወንጀል ተጠያቂነት እንዲጠብቅ እናሳስባለን፡፡
በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት
የጦር መሳሪያ በመያዝ ወይም በፀብ ድርጊት ኢትዮጵያን የተቃወመ እንደሆነ
ከኢትዮጵያ ጋር ጦርንት ከሚያደርግ ሀይል ጋር ወይም ለዚሁ ሀይል ጥቅም ከሚሰራ ሰው ወይም ድርጅት ጋር በመተባበር ወይም ሚስጥራዊ ግንኙነት በማድረግ ይኸው ሀይል እንዲመቸውና እንዲቀናው በማናቸውም አኳኋን የረዳ እንደሆነ ወይም
ዕቃዎችን፣ የጦር መሳሪያዎችን፣ ፕላኖችን፣ማስረጃ የሚሆኑ ፅሁፎችን ወይም ለሀገሩ መከላከያ የሚያገለግሉ ማንኛዎቹንም ነገሮች በቀጥታ ወይም በእጅ አዙር ለጠላት አሳልፎ በመስጠት ወይም በአገልግሎቶችና ይህን የመሳሰሉ ዕቃዎችን ለጠላት በማቅረብ ጠላትን የደገፈ እንደሆነ ከፍ ያለ ክዳት ይፈፅማል፡፡ ይህ ወንጀል መፈፀሙ ሲረጋገጥም ከአምስት አመት እስከ ሀያ አምስት አመት በሚደርስ ፅኑ እስራት የሚያስቀጣ ሲሆን ነገሩ ከባድ በሆነ ጊዜ በእድሜ ልክ ፅኑ እስራት ወይም በሞት ሊያስቀጣ ይችላል፡፡
ሁለተኛው የክዳት ወንጀል ሲሆን በወንጀል ህጉ አንቀፅ 249 መሰረት ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የሆነ ወይም የኢትዮጵያን ጥቅም እንዲያስከብር በግልፅ አደራ የተጣለበት ሰው አስቦ
የኢትዮጵያን ጥቅም ለማስጠበቅ በምስጢር እንዲጠብቅና እንዳይገልፅ የተደረገውን ምስጢር፣ ሰነድ፣ የመላላክ ጉዳይ ወይም አንድ ውሳኔ ለህዝብ ወይም ለውጭ ሀገር መንግስት፣ የፖለቲካ ድርጅት፣ ሌላ ድርጅት ወይም ወኪል የገለፀ፣ አሳልፎ የሰጠ፣ ወሬውን ያስተላለፈ ወይም በግልፅ እንዲነገር ያደረገ እንደሆነ
የኢትዮጵያ እንደራሴ ወይም መልዕክተኛ ሆኖ ከውጭ ሀገር መንግስት ጋር እንዲፈፅም የተላከበትን ወይም ለኢትዮጵያ ጥቅም ሊከራከርበትና ሊፈፅም የሚገባውን ጉዳይ ግልፅ በሆነ አይነት እንዲሰናከል የደረገ እንደሆነ
የኢትዮጵያን ደህንነት፣ ነፃነት ወይም ዋነኛ ጥቅሞች የሚመለከቱትን ሰነዶች፣ ፅሁፎች ወይም ማስረጃዎች ያበላሸ፣ ያጠፋ፣ የደበቀ፣ እንዲጠፋ ያደረገ ወይም ወደ ሀሰተኛነት የለወጠ እንደሆነ
የክዳት ወንጀል ይፈፅማል፡፡ ይህ ወንጀል መፈፀሙ ሲረጋገጥም ከአስራ አምስት አመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት ሊያስቀጣ ይችላል፡፡ ሆኖም አድራጎቱ የኢትዮጵያን ህልውና ወይም ነፃነት በቀጥታ ከባድ አደጋ ላይ የሚጥል ከሆነ ቅጣቱ የሚከብድ ሲሆን ጉዳዩን የሚመለከተው ፍርድ ቤት ከአስር አመት እስከ ሀያ አምስት አመት ሊድርስ የሚችል ፅኑ እስራት መወሰን እንዲችል በህግ ተፈቅዶለታል፡፡
ከላይ የተጠቀሰው ቅጣት የተቀመጠው ሆነ ብሎ እና አስቦ ወንጀሉን ለፈፀመ ሰው ነው፡፡ ሆኖም ከላይ የተጠቀሱ ድርጊቶች በቸልተኝነት ጭምር ሊፈፀሙ የሚችሉ መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት ህጉ ቅጣት አስቀምጧል፡፡ ይኸውም ቅጣት ከስድስት ወር ያላነሰ ቀላል እስራት ሲሆን የነገሩ ከባድነት እየታየ ቅጣቱ እስከ አምስት አመት ፅኑ እስራት ሊደርስ ይችላል፡፡
ሶስተኛው የኢኮኖሚ ክዳት ሲሆን የወንጀል ህግ አንቀፅ 250 መሰረት ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የሆነ ወይም የኢትዮጵያን ጥቅም እንዲያስከብር በግልፅ አደራ የተጣለበት ሰው አስቦ
ስለለኢትዮጵያ ወይም ስለመከላከያ ሀይል ከፍተኛ ጥቅም ሲባል በምሲጢር የሚጠብቀውን ኢኮኖሚያዊ ጠባይ ያለውን የመላላክ ግንኙነት፣ ውሳኔ፣ የተደረገ ነገር ወይም ሰነድ ለህዝብ ወይም ለውጭ አገር ሰው የገለፀ፣ አሳልፎ የሰጠ፣ ይዘቱን ያስተላለፈ ወይም እነዚሁን እንዲያገኙ ያደረገ እንደሆነ
እንዲጠብቃቸው በሀላፊነት የተሰጡትን ዕቃዎች፣ መሳሪያዎች ወይም እነዚህን የመሳሰሉትን ሌሎች ነገሮች የገለፀ ወይም አሳልፎ የሰጠ እንደሆነ
ከኢትዮጵያ ጋር ጦርነት የሚያደርግ መንግስት ባወጣው ብድር ጉዳይ የተካፈለ ወይም ለብድሩ የሚውል ገንዘብ ወይም ንብረት ያዋጣ እንደሆነ
የኢኮኖሚ ክዳት ይፈፅማል፡፡ ይህ ድርጊት መፈፀሙ ከተረጋገጠም በአስር አመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት ያስቀጣል፡፡ ከባድ ሆኖ በተገኘ ጊዜ ደግሞ ቅጣቱ እስከ ሀያ አመት ፅኑ እስራት ሊደርስ ይችላል፡፡
ከላይ የተጠቀሰው ቅጣት የተቀመጠው ሆነ ብሎ እና አስቦ ወንጀሉን ለፈፀመ ሰው ነው፡፡ ሆኖም በክዳት ላይ እንደተጠቀሰው ሁሉ በኢኮኖሚ ክዳት ውስጥ የተጠቀሱት ድርጊቶች በቸልተኝነት ጭምር ሊፈፀሙ የሚችሉ መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት ህጉ ቅጣት አስቀምጧል፡፡ ይኸውም ቅጣት ከሶስት ወር ያላነሰ ቀላል እስራት ነው፡፡
ከላይ ከቀረበው የድንጋጌዎቹ ይዘት መረዳት የሚገባው የተጠቀሱት ድርጊቶች የክዳት ወንጀል የሚሆኑት በኢትዮጵያዊ ወይም የኢትዮጵያን ጥቅም እንዲያስከብር በግልፅ አደራ የተጣለበት ሰው ሲፈፀሙ ነው፡፡ በተጨማሪም በሀገራችን ህግ የክዳት ወንጀል የሚያካትተው በድንጋጌዎቹ የተጠቀሱትን ፍሬ ነገሮች በመሆኑ አንድ ኢትዮጵያዊ ወይም የኢትዮጵያን ጥቅን እንዲያስከብር አደራ የተሰጠው ሰው በክዳት ወንጀል ሊቀጣ የሚችለው ከላይ በተጠቀሱት ድንጋጌዎች የተመለከቱትን ድርጊቶች ሲፈፅም ብቻ ነው፡፡
ሆኖም በሀገር ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን በተለይ ደግሞ ከውጪ ሀይል ጋር በተገናኘ የሚፈፀሙ የወንጀል ድርጊቶች ሁሉ የሀገር ክህደት ወንጀል አድርጎ የመቁጠር ዝንባሌ ይስተዋላል፡፡ ይሁንና የወንጀል ህጋችን ወንጀሎችን ለይቶ ያስቀመጠ እንደመሆኑ ድንጋጌዎቹ ያስቀመጡትን ፍሬ ነገሮችን መመልከት የወንጀሎቹን ልዩነት ለመረዳት መፍትሄ ነው፡፡
ለምሳሌ በወንጀል ህግ አንቀፅ 251 መሰረት ከጠላት ጋር መተባበር በወንጀል ህጋችን እራሱን የቻለ ወንጀል ሲሆን ይህ ወንጀል ተፈፀመ የሚባለው ኢትዮጵያዊ የሆነ ወይም የኢትዮጵያን ጥቅም እንዲያስከብር በግልፅ አደራ የተጣለበት ሰው ኢትዮጵያ በጦርነት ላይ በምትገኝበት ጊዜ ወይም ግዛቷ በሙሉ ወይም በከፊል በጠላት በተወረረበት ጊዜ የጠላትን አላማ ለማሳካት በማሰብ በምክርም ሆነ በተግባር የደገፈ እንደሆነ በተለይም በጠላት ስም የሲቪል የአስተዳደር ሥራዎችን የሰራ ወይም ከጠላት ቁጥጥር ለማምለጥ የሚፈልጉ የወገን ተዋጊዎችን ወይም ስደተኞች ለጠላት ያጋለጠ እና ሌሎች በድንጋጌው የተመለከቱ ድርጊቶችን የፈፀመ ከሆነ ነው፡፡ልክ እንደ ክዳት ወንጀል ሁሉ ይህ ወንጀል የሚፈፀመው ኢትዮጵያዊ በሆነ ወይም የኢትዮጵያን ጥቅም እንዲያከብር በግልፅ አደራ በተጣለበት ሰው መሆኑ ከክዳት ጋር የሚያመሳስለው ቢሆንም ከጠላት ጋር የመተባበር ወንጀል የሚፈፀምበት ሁኔታ የተለየ ያደርገዋል፡፡ ማለትም የሀገር ክህደት ወንጀል በማንኛውም ጊዜ የሚፈፀም ወንጀል ሲሆን ከጠላት ጋር መተባበር ወንጀል ግን የሚደረገው ሀገራችን በጦርነት ላይ በምትገኝበት ወይም ግዛቷ በሙሉ ወይም በከፊል በጠላት በተወረረበት ጊዜ የሚፈፀም ወንጀል መሆኑን ከድንጋጌው መረዳት ይቻላል፡፡ ስለሆነም የክዳት ወንጀልን ከሌሎች መለየት አስፈላጊ ነው፡፡
በአጠቃላይ የሀገር ክህደት ወንጀል ለሀገር ከመታመን ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው ሲሆን እንደሌሎች ወንጀሎች በማንኛውም ሰው የሚፈፀም ሳይሆን ሊፈፀም የሚችለውም ኢትዮጵያዊ ወይም የኢትዮጵያን ጥቅም እንዲያስከብር ሀላፊነት በተሰጠው ሰው ብቻ ነው፡፡ በዚህም ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለሀገሩ ታማኝ እንዲሆን፣ ከክዳት ወንጀል በመታቀብ የሀገሩን ጥቅም አሳልፎ እንዳይሰጥ እንዲሁም እራሱንም ከወንጀል ተጠያቂነት እንዲጠብቅ እናሳስባለን፡፡
በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት
የተጋቡ ሰዎች ስለሚያካሂዱት የንግድ ሥራ በአዲስ ንግድ ህግ እይታ
መግቢያ
ሴቶች ለዘመናት በቤተሰብ፤ በመሀበረስብ እንዲሁም በሀገር ደረጃ የሚያበረክቱት አስተዋጾ ምንም እንኮን ከፍተኛ ቢሆንም በተለያዩ ኋላ ቀር ባህሎች፤ እምነቶች እና አስተሳሰቦች ምክንያት በህበረተሰቡ ውስጥ ያሚሠጣቸው ዋጋ እና ቦታ አነስተኛ ሲሆን ሴቶች ህጽናትን ከማሳደግ እና የቤት ውስጥ ስራዎችን ከመስራት በሰተቀር ወደ ወጪ ወጥተው ሌሎች ወንዶች የሚሰሯቸውን ስራዎች መስራት ይችላሉ በማለት የማይታመንባቸው ሲሆን በተለይም ንብረትን በማፍራት፤ በማስተዳደር እና በመቆጣጠር በኩል ምንም አይነት መብት ሳይኖራቸው ለዘመናት ተጨቁነዋል፡፡ በአለማችን እንዲሁም በአገራችን ይህን የተዛባ አመለካከት ለማስተካከል ከተደረገ ብዙ ትግል እና እንቅስቃሴዎች በኋላ በህብረተሰብ እና በመንግስታት ውስጥ የአመለካከት ለውጥ በመምጣቱ በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ጭቆና እና መድሎ ለማስወገድ እና ሴቶች በማንኛውም ረገድ ከወንዶች ጋር እኩል መሆናቸውን ያሚያረጋግጡ አለማቀፍ ስምምነቶችን እና ህጎችን በማጽደቅ በየአገራቱ ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡ አገራችንም ህገ መንግስቱን ጨምሮ የተለያዩ አለማቀፍ ስምምነቶችን እና ህጎችን ከማጽደቅ ጀምሮ የተለያዩ ህጎችን እና ፖሊሲዎችን በማጽደቅ ወደ ስራ ገብታለች፡፡ ከዚህም ውስጥ የተሻሻለው የንግድ ህግ አንዱ ሲሆን ይህም ህግ የተጋቡ ሰዎች የንግድ ስራን ለመስራት የሁለቱም ፍቃድ እና ስምምነት እንደሚያስፈልጋቸው የሚገልጽ ሲሆን ይህም ሴቶች በትዳር ውስጥ በማንኛውም ያንግድ እንቅስቃሴ ከወንዶች እኩል መበት እንዳላቸው ያመለክታል ይህም ጹፍ በተሻሻለው የንግድ ህግ የተጋቡ ሰዎች ሰለሚያደርጉት የንግድ ስራ በአጭሩ ለመዳሰስ ይሞክራል፡፡
ስለ ባል እና ሚስት የጋራ ሀብት አሰተዳዳር
አገራችን ሴቶች ላይ በተለያዩ ኋላ ቀር ባህሎች፤እምነቶች እና አስተሳሰቦች ምክንያት ያሚደርስባቸውን ጉዳቶች፤መድሎዎች እና በደሎችን ለማስቀረት እና ከወንዶች ጋር በማንኛውም ራገድ እኩል መሆናቸውን ለማረጋገጥ እንዲሁም ለሀገር እድገት እና ብልጽግና ያሚያበረክቱትን አስተዋጾ ለማሰደግ የተለያዩ አሰራሮችን ፖሊሲዎችን እና ህጎችን አውጥታለች፡፡ከዚህም ውስጥ ህገመንግስቱ በዋናነት ይጠቀሳል በህገ መንግስቱ አንቀጽ 34/1 ስር ሴቶች በጋብቻ አፈጻጸም ውቅት በጋብቻ ዘመን እና በፍቺ ጊዜ ከወንዶች እኩል መብት እንዳለቸው እንዲሁም በህግመንግስቱ አንቅጽ 35 ስር ሴቶች በማንኛውም ሁኔታ ከወንዶች ጋር እኩል መብት እንዳለቸው በተለይም ንብረት የማፍራት ፤ማስተዳደር ፤የመቆጣተር ፤የመጠቀም ና የማስተላለፍ መብት ከወንዶች እኩል እንዳለቸው ደንግጎ ይገኛል፡፡ የተሻሻለው የፌዴራል ያቤተሰብ ህግም ሴቶች ከትዳር በፊት፤በትዳር ውስጥ እንዲሁም በፊቺ ወቅት ከወንዶች ጋር እኩል መብት እንዳለቸው ደንግጎ ይገኛል፡፡
በአጠቃላይ በብተሰብ ህጉ ባል እና ሚስት በትዳር ውስጥ ሳሉ ከግል ጥረታቸው እና ከግል ወይም ከጋራ ንብረታቸው የገኙት ገቢ እንዲሁም በሽያጭ እና በልውውጥ የሚያፈሩት ሀብት ተቃራኒ ማስረጃ ካልቀረበ በስተቀር እንደ ጋራ ንብረታቸ ያሚቆጠር በመሆኑ ማንኛውንም እንቅስቃሴ ለማድረግ የጋራ ስመምነታቸው እንደ ሚያስፈልግ በህጉ ተደናግጎ ይገኛል፡፡ በዚሁ ህግ አንቀጽ 68 ስር የጋራ ሀብትን ማስተዳደር በተመለከተ ከባል እና ከሚስት አንዱ የጋራ ሀብታቻውን በሙሉ ወይም በከፊል እንዲያስተዳድር ግልጽ ስምምነት ከሌለ በስተቀር ባል እና ሚስቱ የጋራ ሀብታቻውን በጋራ ያስተዳድራሉ በማለት ደንግጓል፡፡ በህጉ አንቀጽ 69 ላይም ከተጋቢዎቹ አንዱ የጋራ ሀብታቻውን በሚያስተዳድርበት ውቅት የሀብቱን አስተዳዳር በተመለከተ ለሌለኛው ተጋቢ መረጃ የመስጠት ግዴታ እንዳለበት ያስቀምጣል በተጨማሪም በህጉ አንቀጽ 68 ባል እና ሚስት የጋራ ሀብትቸውን በተመለከተ ፤-
የማይንቀሳቀስ የጋረ ሀብት የሆነን ንብረት ለመሸጥ፤ ለመለወጥ ፤ለመከራየት ፤በመያዣ ወይም በዋስትና ለመስጠት በሌላ በማንኛውም ሁኔታ በዚህ ንብረት ላይ ሌሎች ሰዎች መብት እንዲያገኙ ለማድረግ
የዋጋ ግምታቸው አምስት መቶ ብር በላይ ሆኑ የማይንቀሳቀሱ የጋራ ንብረቶችን ወይም የገንዘብ ሰነዶችን ለመሸጥ ወይም ለመለወጥ፤ለማበደር ፤ለመበደር ፤ወይም ለሌላ ሰው ዋስ ለመሆን፤በመያዣ ወይም በዋስትን ለመስጠት በሌላ በማንኛውም ሁኔታ በዚህ ንብረት ላይ ሌሎች ሰዎች መብት እንዲያገኙ ለማድረግ
ከተጋቢዎቹ አንድኛው ያለ ስምምነት ከላይ የተጠቀሰው የውል ግዴታ ውስጥ ገብቶ የተገኘ እንደ ሆነ ሌላኛው ተጋቢ ለፍርድ ቤት በሚያቀርበው ጥያቄ ግዴታው ሊፈርስ ይችላል ግዴታው እንዲፈርስለት የሚቀርበው ግዴታው መገባቱ ካወቀበት ቀን ጀምሮ ጥያቄ በስድስት ወር ውስጥ ማቅረብ ሲኖሩበት ነገር ግን በሌላ በማንኛውም ሁኔታ ግዴታው ከተገባ ከሁለት አመት በሏላ ሊቀርብ አይችልም በማለት አስቀምጧል፡፡
ያገቡ ሰዎች የንግድ ሥራ ለመሥራት ስላላቸው መብት
አዲሱ የንግድ ህግ አንቀጽ 15 ያገቡ ሰዎች የንግድ ሥራ ለመሥራት ስላላቸው መብት አስመልክቶ ባል ወይም ሚስት ካልተቃወመ በስተቀር ያገባ ሰው የሚሰራው የንግድ ሥራ እንደ ባል ና ሚስት የጋራ የንግድ ሥራ ይቆጠራል በማለት የሚያስቀምጥ ሲሆን ነገር ግን በህጉ አንቀጽ 16 ስር ከባል ወይም ከሚስት መካከል አንዱ የንግድ ስራውን በመቃወም ከሚመጣው ተጠያቂነት እራሱን መጠበቅ እንደሚችል ያስቀመጠ፡፡
በዚሁ ህግ መሰረት ተቃውሞውንም ለሚነግደው ባል ወይም ሚስት በማንኛውም መንገድ እንዲደርሰው ማድረግ እንደሚችል ያስቀምጣል ሲሆን ነገር ግን የተደረገው መቃወሚያ በንግድ መዝገብ ላይ ካል ገባ በስተቀር ሦስተኛ ወገኖችን መቃወሚያ ሊሆን እንዳማይችል ድንግጎ ይገኛል፡፡ ይሁን እና በንግድ እንቅስቃሴው ላይ ተቃውሞ መኖሩን የሚያቅ ከሆነ የተደረገው መቃወሚያ በንግድ መዝገብ ላይ ባይገባም ተቃውሞው በሶስተኛ ወገን ላይም ተቀባይነት ይኖረዋል ፡፡ በንግድ ህጉ አንቀጽ 17 መሰረት የሚነግደው ባል ወይም ሚስት ተቃውሞው የቤተሰቡን ጥቅም የሚጎዳ መስሎ የታየው እንደሆነ መቃወሚያው እንዲነሳለት ጉዲዩን ለሽምግሌና ዳኞች ማቅረብ የሚችል ሲሆን ጉዳዩ የቀረበላቸው ዳኞችም መቃወሚያው እንዲነሳ ከወሰኑ ተቃውሞው የተነሳለት ነጋዴ ባል ወይም ሚስት ይህንኑ በንግድ መዝገብ እንዲገባ ማድረግ አለበት፡፡
መቃወሚያው ስለሚኖረው ውጤት
በአዲሱ የንግድ ህግ አንቀጽ 20 መሰረት አንዱ ለሌላው ሠራተኛ መሆኑ ማስረጃ ካሌቀረበ በስተቀር ባሌና ሚስት በአንድነት በንግድ ቤቱ ውስጥ ተባብረው በሚሰሩበት ጊዜ ነጋዴው ባል ወይም ሚስት የተዋዋለው ዕዳ እንደ ባሌና ሚስት የጋራ ዕዳ ተቆጥሮ ከጋራ ንብረት እና ከባል ና ሚስት የግል ንብረት እንዲ ከፈል መጠየቅ እንደሚችሉ ያስቀምጣል፡፡በተጨማሪም በህጉ አንቀጽ 18 ስር የሚነግደው ባል ወይም ሚስት የተዋዋለው ዕዳ እንደ ባልና ሚስት የጋራ ዕዳ ተቆጥሮ ከባል ወይም ከሚስት የግል ንብረትና የጋራ ንብረት እንዲከፈልሉ መጠየቅ ይችላሉ በማለት አስቀምጦል፡፡ ነገር ግን ባል ወይም ሚስት በህጉ መሰረት በንግድ ስራው ላይ አስቀድመው ተቃውሞ አቅርበው በንግድ መዝገብ ላይ ያስመዘገቡ እንደሆነ ወይንም ባያስመዝገቡም አስቀድሞ መቃወሚያው መኖሩ የታወቀ እንደሆነ የሚነግደው ባል ወይም ሚስት እዳ የሚከፈለው ከዚሁ ሰው የግል ንብረት ላይ ብቻ ይሆናል በማለት አዲሱ የንግድ ህግ ላይ ተቀምጦ ያገኛል፡፡ በአጠቃላይ ባል እና ሚስት በትዳር ውስጥ ሆነው ያሚያደርጉትን ማንኛውንም እንቅስቃስ በጋራ ስምምነት
መግቢያ
ሴቶች ለዘመናት በቤተሰብ፤ በመሀበረስብ እንዲሁም በሀገር ደረጃ የሚያበረክቱት አስተዋጾ ምንም እንኮን ከፍተኛ ቢሆንም በተለያዩ ኋላ ቀር ባህሎች፤ እምነቶች እና አስተሳሰቦች ምክንያት በህበረተሰቡ ውስጥ ያሚሠጣቸው ዋጋ እና ቦታ አነስተኛ ሲሆን ሴቶች ህጽናትን ከማሳደግ እና የቤት ውስጥ ስራዎችን ከመስራት በሰተቀር ወደ ወጪ ወጥተው ሌሎች ወንዶች የሚሰሯቸውን ስራዎች መስራት ይችላሉ በማለት የማይታመንባቸው ሲሆን በተለይም ንብረትን በማፍራት፤ በማስተዳደር እና በመቆጣጠር በኩል ምንም አይነት መብት ሳይኖራቸው ለዘመናት ተጨቁነዋል፡፡ በአለማችን እንዲሁም በአገራችን ይህን የተዛባ አመለካከት ለማስተካከል ከተደረገ ብዙ ትግል እና እንቅስቃሴዎች በኋላ በህብረተሰብ እና በመንግስታት ውስጥ የአመለካከት ለውጥ በመምጣቱ በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ጭቆና እና መድሎ ለማስወገድ እና ሴቶች በማንኛውም ረገድ ከወንዶች ጋር እኩል መሆናቸውን ያሚያረጋግጡ አለማቀፍ ስምምነቶችን እና ህጎችን በማጽደቅ በየአገራቱ ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡ አገራችንም ህገ መንግስቱን ጨምሮ የተለያዩ አለማቀፍ ስምምነቶችን እና ህጎችን ከማጽደቅ ጀምሮ የተለያዩ ህጎችን እና ፖሊሲዎችን በማጽደቅ ወደ ስራ ገብታለች፡፡ ከዚህም ውስጥ የተሻሻለው የንግድ ህግ አንዱ ሲሆን ይህም ህግ የተጋቡ ሰዎች የንግድ ስራን ለመስራት የሁለቱም ፍቃድ እና ስምምነት እንደሚያስፈልጋቸው የሚገልጽ ሲሆን ይህም ሴቶች በትዳር ውስጥ በማንኛውም ያንግድ እንቅስቃሴ ከወንዶች እኩል መበት እንዳላቸው ያመለክታል ይህም ጹፍ በተሻሻለው የንግድ ህግ የተጋቡ ሰዎች ሰለሚያደርጉት የንግድ ስራ በአጭሩ ለመዳሰስ ይሞክራል፡፡
ስለ ባል እና ሚስት የጋራ ሀብት አሰተዳዳር
አገራችን ሴቶች ላይ በተለያዩ ኋላ ቀር ባህሎች፤እምነቶች እና አስተሳሰቦች ምክንያት ያሚደርስባቸውን ጉዳቶች፤መድሎዎች እና በደሎችን ለማስቀረት እና ከወንዶች ጋር በማንኛውም ራገድ እኩል መሆናቸውን ለማረጋገጥ እንዲሁም ለሀገር እድገት እና ብልጽግና ያሚያበረክቱትን አስተዋጾ ለማሰደግ የተለያዩ አሰራሮችን ፖሊሲዎችን እና ህጎችን አውጥታለች፡፡ከዚህም ውስጥ ህገመንግስቱ በዋናነት ይጠቀሳል በህገ መንግስቱ አንቀጽ 34/1 ስር ሴቶች በጋብቻ አፈጻጸም ውቅት በጋብቻ ዘመን እና በፍቺ ጊዜ ከወንዶች እኩል መብት እንዳለቸው እንዲሁም በህግመንግስቱ አንቅጽ 35 ስር ሴቶች በማንኛውም ሁኔታ ከወንዶች ጋር እኩል መብት እንዳለቸው በተለይም ንብረት የማፍራት ፤ማስተዳደር ፤የመቆጣተር ፤የመጠቀም ና የማስተላለፍ መብት ከወንዶች እኩል እንዳለቸው ደንግጎ ይገኛል፡፡ የተሻሻለው የፌዴራል ያቤተሰብ ህግም ሴቶች ከትዳር በፊት፤በትዳር ውስጥ እንዲሁም በፊቺ ወቅት ከወንዶች ጋር እኩል መብት እንዳለቸው ደንግጎ ይገኛል፡፡
በአጠቃላይ በብተሰብ ህጉ ባል እና ሚስት በትዳር ውስጥ ሳሉ ከግል ጥረታቸው እና ከግል ወይም ከጋራ ንብረታቸው የገኙት ገቢ እንዲሁም በሽያጭ እና በልውውጥ የሚያፈሩት ሀብት ተቃራኒ ማስረጃ ካልቀረበ በስተቀር እንደ ጋራ ንብረታቸ ያሚቆጠር በመሆኑ ማንኛውንም እንቅስቃሴ ለማድረግ የጋራ ስመምነታቸው እንደ ሚያስፈልግ በህጉ ተደናግጎ ይገኛል፡፡ በዚሁ ህግ አንቀጽ 68 ስር የጋራ ሀብትን ማስተዳደር በተመለከተ ከባል እና ከሚስት አንዱ የጋራ ሀብታቻውን በሙሉ ወይም በከፊል እንዲያስተዳድር ግልጽ ስምምነት ከሌለ በስተቀር ባል እና ሚስቱ የጋራ ሀብታቻውን በጋራ ያስተዳድራሉ በማለት ደንግጓል፡፡ በህጉ አንቀጽ 69 ላይም ከተጋቢዎቹ አንዱ የጋራ ሀብታቻውን በሚያስተዳድርበት ውቅት የሀብቱን አስተዳዳር በተመለከተ ለሌለኛው ተጋቢ መረጃ የመስጠት ግዴታ እንዳለበት ያስቀምጣል በተጨማሪም በህጉ አንቀጽ 68 ባል እና ሚስት የጋራ ሀብትቸውን በተመለከተ ፤-
የማይንቀሳቀስ የጋረ ሀብት የሆነን ንብረት ለመሸጥ፤ ለመለወጥ ፤ለመከራየት ፤በመያዣ ወይም በዋስትና ለመስጠት በሌላ በማንኛውም ሁኔታ በዚህ ንብረት ላይ ሌሎች ሰዎች መብት እንዲያገኙ ለማድረግ
የዋጋ ግምታቸው አምስት መቶ ብር በላይ ሆኑ የማይንቀሳቀሱ የጋራ ንብረቶችን ወይም የገንዘብ ሰነዶችን ለመሸጥ ወይም ለመለወጥ፤ለማበደር ፤ለመበደር ፤ወይም ለሌላ ሰው ዋስ ለመሆን፤በመያዣ ወይም በዋስትን ለመስጠት በሌላ በማንኛውም ሁኔታ በዚህ ንብረት ላይ ሌሎች ሰዎች መብት እንዲያገኙ ለማድረግ
ከተጋቢዎቹ አንድኛው ያለ ስምምነት ከላይ የተጠቀሰው የውል ግዴታ ውስጥ ገብቶ የተገኘ እንደ ሆነ ሌላኛው ተጋቢ ለፍርድ ቤት በሚያቀርበው ጥያቄ ግዴታው ሊፈርስ ይችላል ግዴታው እንዲፈርስለት የሚቀርበው ግዴታው መገባቱ ካወቀበት ቀን ጀምሮ ጥያቄ በስድስት ወር ውስጥ ማቅረብ ሲኖሩበት ነገር ግን በሌላ በማንኛውም ሁኔታ ግዴታው ከተገባ ከሁለት አመት በሏላ ሊቀርብ አይችልም በማለት አስቀምጧል፡፡
ያገቡ ሰዎች የንግድ ሥራ ለመሥራት ስላላቸው መብት
አዲሱ የንግድ ህግ አንቀጽ 15 ያገቡ ሰዎች የንግድ ሥራ ለመሥራት ስላላቸው መብት አስመልክቶ ባል ወይም ሚስት ካልተቃወመ በስተቀር ያገባ ሰው የሚሰራው የንግድ ሥራ እንደ ባል ና ሚስት የጋራ የንግድ ሥራ ይቆጠራል በማለት የሚያስቀምጥ ሲሆን ነገር ግን በህጉ አንቀጽ 16 ስር ከባል ወይም ከሚስት መካከል አንዱ የንግድ ስራውን በመቃወም ከሚመጣው ተጠያቂነት እራሱን መጠበቅ እንደሚችል ያስቀመጠ፡፡
በዚሁ ህግ መሰረት ተቃውሞውንም ለሚነግደው ባል ወይም ሚስት በማንኛውም መንገድ እንዲደርሰው ማድረግ እንደሚችል ያስቀምጣል ሲሆን ነገር ግን የተደረገው መቃወሚያ በንግድ መዝገብ ላይ ካል ገባ በስተቀር ሦስተኛ ወገኖችን መቃወሚያ ሊሆን እንዳማይችል ድንግጎ ይገኛል፡፡ ይሁን እና በንግድ እንቅስቃሴው ላይ ተቃውሞ መኖሩን የሚያቅ ከሆነ የተደረገው መቃወሚያ በንግድ መዝገብ ላይ ባይገባም ተቃውሞው በሶስተኛ ወገን ላይም ተቀባይነት ይኖረዋል ፡፡ በንግድ ህጉ አንቀጽ 17 መሰረት የሚነግደው ባል ወይም ሚስት ተቃውሞው የቤተሰቡን ጥቅም የሚጎዳ መስሎ የታየው እንደሆነ መቃወሚያው እንዲነሳለት ጉዲዩን ለሽምግሌና ዳኞች ማቅረብ የሚችል ሲሆን ጉዳዩ የቀረበላቸው ዳኞችም መቃወሚያው እንዲነሳ ከወሰኑ ተቃውሞው የተነሳለት ነጋዴ ባል ወይም ሚስት ይህንኑ በንግድ መዝገብ እንዲገባ ማድረግ አለበት፡፡
መቃወሚያው ስለሚኖረው ውጤት
በአዲሱ የንግድ ህግ አንቀጽ 20 መሰረት አንዱ ለሌላው ሠራተኛ መሆኑ ማስረጃ ካሌቀረበ በስተቀር ባሌና ሚስት በአንድነት በንግድ ቤቱ ውስጥ ተባብረው በሚሰሩበት ጊዜ ነጋዴው ባል ወይም ሚስት የተዋዋለው ዕዳ እንደ ባሌና ሚስት የጋራ ዕዳ ተቆጥሮ ከጋራ ንብረት እና ከባል ና ሚስት የግል ንብረት እንዲ ከፈል መጠየቅ እንደሚችሉ ያስቀምጣል፡፡በተጨማሪም በህጉ አንቀጽ 18 ስር የሚነግደው ባል ወይም ሚስት የተዋዋለው ዕዳ እንደ ባልና ሚስት የጋራ ዕዳ ተቆጥሮ ከባል ወይም ከሚስት የግል ንብረትና የጋራ ንብረት እንዲከፈልሉ መጠየቅ ይችላሉ በማለት አስቀምጦል፡፡ ነገር ግን ባል ወይም ሚስት በህጉ መሰረት በንግድ ስራው ላይ አስቀድመው ተቃውሞ አቅርበው በንግድ መዝገብ ላይ ያስመዘገቡ እንደሆነ ወይንም ባያስመዝገቡም አስቀድሞ መቃወሚያው መኖሩ የታወቀ እንደሆነ የሚነግደው ባል ወይም ሚስት እዳ የሚከፈለው ከዚሁ ሰው የግል ንብረት ላይ ብቻ ይሆናል በማለት አዲሱ የንግድ ህግ ላይ ተቀምጦ ያገኛል፡፡ በአጠቃላይ ባል እና ሚስት በትዳር ውስጥ ሆነው ያሚያደርጉትን ማንኛውንም እንቅስቃስ በጋራ ስምምነት
እና መግባባት ማከናወን ያለባቸው ሲሆን አንዱ የሚያከናውነው ተግባር ሌላኛውን ተጋቢ ሊጎዳ ስለሚችል እያንዳንዱ እንቅስቃሳቸው በጋራ ስምምነት እና መግባባት ላይ ያተመሰረተ መሆን ይገባዋል ፡፡
በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት
በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት
JOB DESCRIPTION
Awash Insurance Vacancy
Head, Legal & Advisory Services
Job Overview
Salary Offer As per Company Scale
Experience Level Senior
Total Years Experience 7
Date Posted December 26, 2021
Deadline Date January 1, 2022
Key Responsibilities
In collaboration with pertinent managers, provide leadership and ensure efficient & effective management of legal and advisory services;
Coordinates the provision of legal advisory services;
Monitors the management of defense and intervention cases as well as recovery cases;
Supervises the observance of service delivery standards in the provision of legal services;
Provides guidance for the efficient and cost effective resolution of defense and intervention cases as well as recovery cases;
Monitors the change in the laws and practices that impact the insurance business and advise same to the Company;
Verifies pleadings and petitions to be submitted to court;
Supports Company units on drafting agreements, policies and procedures;
Represents the Company on negotiations and submit settlement proposals to the Company;
Reviews progress of outstanding litigations and submit regular report to the Management;
Designs legal compliance checklist and monitors its implementation;
Coordinates tailored interventions on coaching, mentoring and trainings for the staff members in the unit.
Job Requirement
Educational Qualification: LL. M or LL. B Degree in law
Experience Requirement: Nine years experience for LL.M or Thirteen years experience for LL.B
Additional Requirement:Fluency in English, Amharic and Afan Oromo.
Age:Below 45 years
Place of work: Addis Ababa
Salary & Benefits:Negotiable salary with attractive benefits package
How To Apply
Interested applicants should send a non-returnable CV and copies of relevant credentials together with their hand written application within seven days of appearance of this announcement in the Newspaper to:
Human Capital Management
Awash Insurance Company S.C.
P.O. Box 12637, Addis Ababa
Only short – listed applicants will be contacted.
Hand delivered applications will not be acceptable.
Awash Insurance Vacancy
Head, Legal & Advisory Services
Job Overview
Salary Offer As per Company Scale
Experience Level Senior
Total Years Experience 7
Date Posted December 26, 2021
Deadline Date January 1, 2022
Key Responsibilities
In collaboration with pertinent managers, provide leadership and ensure efficient & effective management of legal and advisory services;
Coordinates the provision of legal advisory services;
Monitors the management of defense and intervention cases as well as recovery cases;
Supervises the observance of service delivery standards in the provision of legal services;
Provides guidance for the efficient and cost effective resolution of defense and intervention cases as well as recovery cases;
Monitors the change in the laws and practices that impact the insurance business and advise same to the Company;
Verifies pleadings and petitions to be submitted to court;
Supports Company units on drafting agreements, policies and procedures;
Represents the Company on negotiations and submit settlement proposals to the Company;
Reviews progress of outstanding litigations and submit regular report to the Management;
Designs legal compliance checklist and monitors its implementation;
Coordinates tailored interventions on coaching, mentoring and trainings for the staff members in the unit.
Job Requirement
Educational Qualification: LL. M or LL. B Degree in law
Experience Requirement: Nine years experience for LL.M or Thirteen years experience for LL.B
Additional Requirement:Fluency in English, Amharic and Afan Oromo.
Age:Below 45 years
Place of work: Addis Ababa
Salary & Benefits:Negotiable salary with attractive benefits package
How To Apply
Interested applicants should send a non-returnable CV and copies of relevant credentials together with their hand written application within seven days of appearance of this announcement in the Newspaper to:
Human Capital Management
Awash Insurance Company S.C.
P.O. Box 12637, Addis Ababa
Only short – listed applicants will be contacted.
Hand delivered applications will not be acceptable.
Forwarded from Entrust Consult 📗ኢንትረስት
በቀጣዮቹ 4 ዓመታት 70 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ብሔራዊ መታወቂያን ይይዛሉ ተባለ🔷
December 27, 2021
“የብሔራዊ መታወቂያ ዓላማ የቀበሌ መታወቂያን መተካት አይደለም”- ዮዳሄ ዘሚካኤል፤ የፕሮጀክቱ ስራ አስኪያጅ
ከ 10 ዓመት በፊት የተወጠነው የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮጀክት አሁን በሙከራ ትግበራ ላይ ይገኛል፡፡ በሚቀጥለው ዓመት ወደ ዋና ሥራ እንደሚገባ በተገለጸው በዚህ ፕሮጀክት በቀጣይ አራት ዓመታት ከ 70 ሚሊዮን የሚልቁ ኢትዮጵያውያ ብሔራዊ መታወቂያ ይኖራቸዋል ተብሏል፡፡
ከአል ዐይን አማርኛ ጋር ባደረጉት ቆይታ ብሔራዊ መታወቂያ ሲባል ኢትዮጵያ ውስጥ ያለ ማንኛውም ዜጋም ሆነ ነዋሪ የትኛውንም አገልግሎት ሲያገኝ እራሱን የሚለይበት እና የሚያስተዋውቅበት መንገድ እንደሆነ የገለጹት የፕሮጀክቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ዮዳሄ ዘሚካኤል መታወቂያውን በ2018 ዓ.ም ህፃናትን ሳይጨምር 95 ከመቶ ለሚሆኑ ዜጎች ለማዳረስ እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡
ብሔራዊ መታወቂያ ማንኛውም ዜጋ ወይም ነዋሪ ሊኖረው የሚገባው መታወቂያ እንደሆነ ያነሱት ዋና ሥራ አስኪያጁ ብሔራዊ መታወቂያ በካርድ ከሚሰጠው ይለያል ብለዋል፤ እኔነትን የሚያረጋግጥ የመረጃ ስርዓት እንደሆነ በመጠቆም፡፡
ራስን ለማረጋገጥ የሚያስፈልግ ማንኛውንም የመረጃ ስርዓት “ብሔራዊ መታወቂያ” ብሎ ጠቅለል አድርጎ መጥራት እንደሚቻልም አንስተዋል የፕሮጀክቱ ኃላፊ፡፡
ብሔራዊ መታወቂያ በዋናነት ከአገልግሎት ሰጭዎች ጋር የመስራት ጉዳይ እንደሆነ ያነሱት አቶ ዮዳሄ፤ ከአገልግሎት ሰጭዎች ጋር በሚሰራበት ጊዜ፤ አንዳንዶቹ አገልግሎት ሰጭዎች መታወቂያ ማተም ሊፈልጉ እና አንዳንዶች ደግሞ በ“ዲጂታል ብቻ ይበቃናል” ሊሉ እንደሚችሉም አስታውሰዋል፡፡
እንደ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ያሉ የመታወቂያ ካርድ የሚያትሙ አገልግሎት ሰጭዎች ላይ የብሔራዊ መታወቂያ ቁጥር እንደሚቀመጥም ነው የተገለጸው፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም ተማሪዎች መስጠት የጀመረውን መታወቂያ እንደ አብነት ያነሱት ዋና ስራ አስኪጁ የብሔራዊ መታወቁያ ዓላማ የቀበሌ ወይም የነዋሪ መታወቂያን መተካት እንዳልሆነ አነስተዋል፡፡ ከዛ ይልቅ ብሔራዊ መታወቂያ በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ማናቸውንም አገልግሎት ሰጭዎችን ማስተሳሰር ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ለአል ዐይን አማርኛ ተናግረዋል፡፡
አለፈለገ ሰላም
ለአብነት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የነዋሪነት መታወቂያ ሲሰጥ፤ ይህንን መታወቂያ ከሌሎቹ ጋር ማስተሳሰር የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮጀክት ስራ እንደሆነም ተነስቷል፡፡
“አንድ ሰው አንድ ነው” በሚል ስልት ባዮሜትሪክ የሚባል ዳታ፤ የእጅ እና የዐይን አሻራ፣ የፊት ፎቶ ከተያዝ በኋላ ብሔራዊ መታወቂያ ካዘጋጀው ልዩ ቁጥር ጋር እንደሚያያዝ ነው የገለጹት አቶ ዮዳሄ፡፡
ይህ ልዩ ቁጥር ከአሻራ ጋር የሚያያዝ ሲሆን፤ የትኛውም አገልግሎት ሰጭ ጋር በመሄድ አገልግሎት ማግኘት ቢያስፈልግ፤ አገልግሎት ሰጭው የራሱን አገልግሎት ልዩ ቁጥር ከብሔራዊ መታወቂያ ጋር ያተሳስራል ተብሏል፡፡
አገልግሎት ሰጭው ከአንድ ዘርፍ ወደ ሌላ ዘርፍ ፤ከአንድ ሱቅ ወደሌላ ሱቅ፤ ከአንድ ከተማ ወደ ሌላ ከተማ ቢሄድም የብሔራዊ መታወቂያ ቁጥር እንደማይቀየርና በዛ ቁጥር መሰረት እንደሚተሳሰር ተገልጿል፡፡
የፕሮጀክቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ዮዳሄ ዘሚካኤል ከአራት ዓመታት በኋላ በ2018 ዓ.ም 70 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ ዲጂታል መታወቂያ እንዲይዝ መታቀዱን ተናግረዋል፡፡ የብሔራዊ መታወቂያ ቁጥርን በአካል በሚሰጥ እና መታወቂያ ላይ ያለውን መረጃ በመውሰድ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ በያዝነው ዓመት “አነስ አነስ ያሉ የሙከራ ትግበራዎችን” ከአገልግሎት ሰጭዎች ጋር እንደሚሰራም ነው፤ በቀጣዩ ዓመት ወደ ዋና ትግበራ ይገባል ያሉት ዋና ስራ አስኪያጁ የተናገሩት፡፡
ከአገልግሎት ሰጭዎች ጋር ፕሮጀክት በመቅረጽ እንደሚሰራ ያነሱት ዋና ሥራ አስኪያጁ ፤ ባንክ እንደምሳሌ ቢወሰድ ባንኩ አንድ የተለየ አገልግሎት ለማግኘት ደንበኛው ወደ ባንኩ ቢሄድ ቅድሚያ “የብሔራዊ መታወቂያ አሻራህን ሰጥተህ ነው ይህንን አገልግሎት የምንሰጥህ እንዲል “የማስቻል ስራ ይሰራል ነው የተባለው፡፡ በዚህም መሰረት 10 ዲጂት ቁጥር ያለው የብሄራዊ መታወቂያ ቁጥር ከሌሎች ሴክተሮችም ጋር እየተሳሰረ እንደሚሄድ ተገልጿል፡፡
ብሔራዊ መታወቂያ የግድ በኪስ ተይዞ የሚኬድ እንዳልሆነ የገለጹት ዋና ስራ አስኪጁ፤ ምናልባት የዛሬ አምስት ወይም 1 0 ዓመት ሁሉም መታወቂያዎች በብሔራዊ መታወቂያ ይቀየሩ ቢባል ካርዱን የማተም ሥራው አንድ በመቶ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡
የሥራው 99 በመቶ ዳታውን መሰብሰብ እና ከዛ ከሲስተሞች ጋር ተናቦ ማረጋገጫ የመስጠት ሲሆን ካርድ መስጠት ግን እስካሁን በሕግ ደረጃ እንደሌለ ተገልጿል፡፡ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮጀክት ነዋሪነት ወይም አድራሻ የማረጋገጥ ስራ አይሰራም ብለዋል፡፡ አዲስ አቅጣጫ ካልመጣ በስተቀር አሁን ያሉት መታወቂያዎች ባሉበት እንደሚቀጥሉና በነሱ ላይ የብሔራዊ መታወቂያ ልዩ ቁጥር እንደሚቀመጥ አስቀምጠዋል ስራ አስኪያጁ፡፡
https://t.me/GudayAsfetsami
December 27, 2021
“የብሔራዊ መታወቂያ ዓላማ የቀበሌ መታወቂያን መተካት አይደለም”- ዮዳሄ ዘሚካኤል፤ የፕሮጀክቱ ስራ አስኪያጅ
ከ 10 ዓመት በፊት የተወጠነው የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮጀክት አሁን በሙከራ ትግበራ ላይ ይገኛል፡፡ በሚቀጥለው ዓመት ወደ ዋና ሥራ እንደሚገባ በተገለጸው በዚህ ፕሮጀክት በቀጣይ አራት ዓመታት ከ 70 ሚሊዮን የሚልቁ ኢትዮጵያውያ ብሔራዊ መታወቂያ ይኖራቸዋል ተብሏል፡፡
ከአል ዐይን አማርኛ ጋር ባደረጉት ቆይታ ብሔራዊ መታወቂያ ሲባል ኢትዮጵያ ውስጥ ያለ ማንኛውም ዜጋም ሆነ ነዋሪ የትኛውንም አገልግሎት ሲያገኝ እራሱን የሚለይበት እና የሚያስተዋውቅበት መንገድ እንደሆነ የገለጹት የፕሮጀክቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ዮዳሄ ዘሚካኤል መታወቂያውን በ2018 ዓ.ም ህፃናትን ሳይጨምር 95 ከመቶ ለሚሆኑ ዜጎች ለማዳረስ እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡
ብሔራዊ መታወቂያ ማንኛውም ዜጋ ወይም ነዋሪ ሊኖረው የሚገባው መታወቂያ እንደሆነ ያነሱት ዋና ሥራ አስኪያጁ ብሔራዊ መታወቂያ በካርድ ከሚሰጠው ይለያል ብለዋል፤ እኔነትን የሚያረጋግጥ የመረጃ ስርዓት እንደሆነ በመጠቆም፡፡
ራስን ለማረጋገጥ የሚያስፈልግ ማንኛውንም የመረጃ ስርዓት “ብሔራዊ መታወቂያ” ብሎ ጠቅለል አድርጎ መጥራት እንደሚቻልም አንስተዋል የፕሮጀክቱ ኃላፊ፡፡
ብሔራዊ መታወቂያ በዋናነት ከአገልግሎት ሰጭዎች ጋር የመስራት ጉዳይ እንደሆነ ያነሱት አቶ ዮዳሄ፤ ከአገልግሎት ሰጭዎች ጋር በሚሰራበት ጊዜ፤ አንዳንዶቹ አገልግሎት ሰጭዎች መታወቂያ ማተም ሊፈልጉ እና አንዳንዶች ደግሞ በ“ዲጂታል ብቻ ይበቃናል” ሊሉ እንደሚችሉም አስታውሰዋል፡፡
እንደ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ያሉ የመታወቂያ ካርድ የሚያትሙ አገልግሎት ሰጭዎች ላይ የብሔራዊ መታወቂያ ቁጥር እንደሚቀመጥም ነው የተገለጸው፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም ተማሪዎች መስጠት የጀመረውን መታወቂያ እንደ አብነት ያነሱት ዋና ስራ አስኪጁ የብሔራዊ መታወቁያ ዓላማ የቀበሌ ወይም የነዋሪ መታወቂያን መተካት እንዳልሆነ አነስተዋል፡፡ ከዛ ይልቅ ብሔራዊ መታወቂያ በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ማናቸውንም አገልግሎት ሰጭዎችን ማስተሳሰር ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ለአል ዐይን አማርኛ ተናግረዋል፡፡
አለፈለገ ሰላም
ለአብነት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የነዋሪነት መታወቂያ ሲሰጥ፤ ይህንን መታወቂያ ከሌሎቹ ጋር ማስተሳሰር የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮጀክት ስራ እንደሆነም ተነስቷል፡፡
“አንድ ሰው አንድ ነው” በሚል ስልት ባዮሜትሪክ የሚባል ዳታ፤ የእጅ እና የዐይን አሻራ፣ የፊት ፎቶ ከተያዝ በኋላ ብሔራዊ መታወቂያ ካዘጋጀው ልዩ ቁጥር ጋር እንደሚያያዝ ነው የገለጹት አቶ ዮዳሄ፡፡
ይህ ልዩ ቁጥር ከአሻራ ጋር የሚያያዝ ሲሆን፤ የትኛውም አገልግሎት ሰጭ ጋር በመሄድ አገልግሎት ማግኘት ቢያስፈልግ፤ አገልግሎት ሰጭው የራሱን አገልግሎት ልዩ ቁጥር ከብሔራዊ መታወቂያ ጋር ያተሳስራል ተብሏል፡፡
አገልግሎት ሰጭው ከአንድ ዘርፍ ወደ ሌላ ዘርፍ ፤ከአንድ ሱቅ ወደሌላ ሱቅ፤ ከአንድ ከተማ ወደ ሌላ ከተማ ቢሄድም የብሔራዊ መታወቂያ ቁጥር እንደማይቀየርና በዛ ቁጥር መሰረት እንደሚተሳሰር ተገልጿል፡፡
የፕሮጀክቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ዮዳሄ ዘሚካኤል ከአራት ዓመታት በኋላ በ2018 ዓ.ም 70 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ ዲጂታል መታወቂያ እንዲይዝ መታቀዱን ተናግረዋል፡፡ የብሔራዊ መታወቂያ ቁጥርን በአካል በሚሰጥ እና መታወቂያ ላይ ያለውን መረጃ በመውሰድ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ በያዝነው ዓመት “አነስ አነስ ያሉ የሙከራ ትግበራዎችን” ከአገልግሎት ሰጭዎች ጋር እንደሚሰራም ነው፤ በቀጣዩ ዓመት ወደ ዋና ትግበራ ይገባል ያሉት ዋና ስራ አስኪያጁ የተናገሩት፡፡
ከአገልግሎት ሰጭዎች ጋር ፕሮጀክት በመቅረጽ እንደሚሰራ ያነሱት ዋና ሥራ አስኪያጁ ፤ ባንክ እንደምሳሌ ቢወሰድ ባንኩ አንድ የተለየ አገልግሎት ለማግኘት ደንበኛው ወደ ባንኩ ቢሄድ ቅድሚያ “የብሔራዊ መታወቂያ አሻራህን ሰጥተህ ነው ይህንን አገልግሎት የምንሰጥህ እንዲል “የማስቻል ስራ ይሰራል ነው የተባለው፡፡ በዚህም መሰረት 10 ዲጂት ቁጥር ያለው የብሄራዊ መታወቂያ ቁጥር ከሌሎች ሴክተሮችም ጋር እየተሳሰረ እንደሚሄድ ተገልጿል፡፡
ብሔራዊ መታወቂያ የግድ በኪስ ተይዞ የሚኬድ እንዳልሆነ የገለጹት ዋና ስራ አስኪጁ፤ ምናልባት የዛሬ አምስት ወይም 1 0 ዓመት ሁሉም መታወቂያዎች በብሔራዊ መታወቂያ ይቀየሩ ቢባል ካርዱን የማተም ሥራው አንድ በመቶ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡
የሥራው 99 በመቶ ዳታውን መሰብሰብ እና ከዛ ከሲስተሞች ጋር ተናቦ ማረጋገጫ የመስጠት ሲሆን ካርድ መስጠት ግን እስካሁን በሕግ ደረጃ እንደሌለ ተገልጿል፡፡ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮጀክት ነዋሪነት ወይም አድራሻ የማረጋገጥ ስራ አይሰራም ብለዋል፡፡ አዲስ አቅጣጫ ካልመጣ በስተቀር አሁን ያሉት መታወቂያዎች ባሉበት እንደሚቀጥሉና በነሱ ላይ የብሔራዊ መታወቂያ ልዩ ቁጥር እንደሚቀመጥ አስቀምጠዋል ስራ አስኪያጁ፡፡
https://t.me/GudayAsfetsami
በአዲሱ የንግድ ህግ ውስጥ ስለአክሲዮን ማህበር የተካከተቱ መሰረታዊ ነጥቦች
መግቢያ
አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ኑሮው ከእጅ ወደ አፍ መሆኑ ይታወቃል። ሻል ያለ ደረጃ ላይ የሚገኙት ጥቂቶችም ቢሆኑ ትርጉም ያለው ተቀማጭ ገንዘብ የላቸውም ሊባል ይችላል። በመሆኑም አገራችን ሥራ ላይ ሊውል (ኢንቨስት ሊደርግ) የሚችል ካፒታል ከፍተኛ እጥረት አለባት። በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ በሚገኝ አገር ውስጥ እድገት ለማምጣት ዜጎች በተናጠል ያላቸውን እጅግ ውስን ሀብት አስተባብሮ ወደ ሥራ ማስገባት የግድ ይላል። ይህ እንዲሳካ ደግሞ ዜጎች የቆጠቡትን ትንሽ ገንዘብ በንግድ ማኅበር ውስጥ ካስገቡ በኋላ ለምዝበራ እና ጭቆና እንዳይዳረጉ የሚከላከል ሕግ መኖር አለበት።
የ1952ቱ ንግድ ህግ በኩባንያዎች ውስጥ አነስተኛ ድርሻ ይዘው የሚገቡትን ባለሃብቶች ከዘረፋ፣ ካልተገባ ጭቆና ወይም በደል ለመታደግ ያለሙ ድንጋጌዎች በበቂ ሁኔታ አላካተተም። በዚህም የተነሳ ኢኮኖሚው ያፈራውን አነስተኛ ካፒታል አሟጦ በተደራጀ መልክ ሥራ ላይ ማዋል አስቸጋሪ ሆኖ ቆይቷል። አልፎ ተርፎም ይህ ክፍተት አገሮች ለንግድ ምን ያህል አመቺ እንደሆኑ በሚለካው በዓለም ባንክ የሚደረግ ምዘና ኢትዮጵያ በየዓመቱ በጣም ዝቅተኛ ውጤት እንድታገኝ አድርጓል። በዚህም የተነሳ አገራችን የውጭ ኢንቨስትመንት ለመሳብ በምታደርገው ጥረት ላይ ዕንቅፋት ሆኖ ቆይቷል።በመሆኑም አዲሱ የንግድ ህግ ከቀድሞው የንግድ ህግ በተሸለ ሁኔታ የማህበር አባላትን መብት በሚያስጠብቅ ሁኔታ የህግ ድንጋጌዎችን አካቶ በስራ ላይ ውሏል፡፡
የአክሲዮን ማህበር በቀድሞው እና በአዲሱ የንግድ ህግ ከተካተቱ የንግድ ማህበራት አይነቶች ውስጥ አንዱ ሲሆን ማህበሩ የመጠሪያ ስም ኖሮት ከስሙ መጨረሻ ላይ “የአክሲዮን ማህበር” የሚል ሀረግ በመጨመር በንግድ መዝገብ እንደተመዘገቡ የሕግ ሰውነት እንደሚያገኝ በአዲሱ የንግድ ህግ አንቀፅ 174፣175፤246 ተመልክቷል፡፡በዚህ አጭር የንቃተ ህግ ፅሁፍ በአዲሱ የንግዱ ህግ ስለአክሲዮን ማህበር የተካተቱ አንዳንድ ነጥቦችን በወፍ በረር ለማየት ይሞከራል፡፡
የአክሲዮን ማህበር ትርጉም
የአክሲዮን ማህበር ማለት ዋና ገንዘቡ ወይም ካፒታሉ አስቀድሞ ተወስኖ በአክሲዮን የተከፋፈለና ኃላፊነቱ በማህበሩ ሀብት ብቻ የተወሰነ ማህበር ሲሆን የአባላት ቁጥር ከአምስት ባለአክሲዮኖች በታች መሆን የሌለበት የንግድ ማህበር አይነት ነው፡፡ የባለአክሲዮኖች ኃላፊነት ለማህበሩ ቃል የገቡትን መዋጮ በመክፈል የተወሰነ ሆኖ በሌላ ሕግ በተለየ ሁኔታ ካልተደነገገ በስተቀር፣ የማህበሩ ዋና ገንዘብ ወይም ካፒታል ከሃምሳ ሺህ የኢትዮጵያ ብር ያነሰ ሊሆን እንደማይችል እና እያንዳንደ አክሲዮን ላይ የሚጻፈው ዋጋ ከአንድ መቶ ብር በታች ሊሆን እንደማይችል በንግድ ህጉ አንቀፅ 245/1/ እና 2 ስር ሰፍሯል፡፡
የአክሲዮን ማህበር አባላት ሃላፊነት የተወሰነ ነው ማለት ማህበሩ ከሦስተኛ ወገኖች ማለትም ከአበዳሪዎች፣ከደንበኞቹ እና ከሠራተኞቹ ወ.ዘ.ተ ጋር በሚያደርገው ግንኙነት ጉዳት ቢደርስ የማህበሩ አባላት (ባለአክሲዮኖች) ሃላፊነት እስከ ምን ድረስ ነው? የሚለውን ይመለከታል፡፡ ይኸውም የማህበሩ አባላት ሃላፊነት ለማህበሩ ካፒታል ባዋጡት ወይም በሚያዋጡት መጠን ብቻ ተጠያቂ እንደሚሆኑ ከንግድ ህጉ ድንጋጌ መረዳት ይቻላል፡፡:: ይህም ማለት አባላቱ ማህበሩ ሲመሠረት ወይም ከተመሰረተ በኋላ ለሽያጭ ከቀረበው የአክሲዮን ድርሻ ውስጥ በገዙት የአክሲዮን መጠን ብቻ ተጠያቂ የሚሆኑ ሲሆን አባሉ የሚጠበቅበትን መዋጮ ያልከፈለ እንደሆነ አክሲዮን ማህበሩ በእዳ ሲያዝ እንዲከፍል ይገደዳል፡፡ የአክሲዮን ማህበሩ ሃብት ጉዳቱን ለመካስ በቂ ሆኖ ባይገኝ ወደ ባለአክሲዮኖቹ ንብረት መሄድ አይቻልም ማለት ነው፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ የአባላቱ የግል እዳ ከኩባንያው ሃብት አይከፈልም፡፡
• የአክሲዮን ማህበር ጥቅም/ አስፈላጊነት
የአክሲዮን ማህበራት በሃገራችን መበራከት ሀገራዊ እና ግለሰባዊ ፋይዳ አለው፡፡ ሀገራዊ ፋይዳውን ስናይ አክሲዮን ማህበር ትልልቅና ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ የሚጠይቁ የንግድ ዘርፎች(ለምሳሌ ባንክ፣መድን ድርጅት፣በግብርና ዘርፍ፣በቤቶች ግንባታ ወዘተ ) ላይ ለመሰማራት የሚረዳ የማህበር አይነት በመሆኑ የእነዚህ ግዙፍ ኢንዱስትሪዎች በሃገራችን መፈጠር ሀገራችን መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገሮች ተርታ ለመሰለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት በከፍተኛ ደረጃ ያግዛል፡፡ በሌላ በኩል የግለሰቦችን ስራ ፈጣሪነት ያበረታታል፡፡ ይህ ሲባል ግለሰቦች የሀገርን ኢኮኖሚ እድገት ሊያፋጥን የሚችል የንግድ ሃሳብ አመንጭተው ካፒታል ከህዝቡ በመሰብሰብ ለመስራት የሚያስችል በመሆኑ ሙያዊ ብቃታቸውን ተጠቅመው የሚሰሩ ስራ ፈጣሪዎች ተገቢውን ክፍያ እንዲያገኙ የሚያበረታታ ሲሆን ለማህበሩ መፈጠር የደም ስር የሆነውን ካፒታል ያዋጡ ሰዎች ደግሞ ወደ ፊት ማህበሩ የሚያስገኘውን ትርፍ የድርሻቸውን በመውሰድ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮቻቸውን እንዲፈቱ ያስችላል፡፡በአጠቃላይ አክሲዮን ማህበር ባለሀብቱን (capitalist) ከስራ ፈጣሪ (entrepreneur) ጋር የሚያገናኝ በመሆኑ ጠቀሜታው የጎላ ነው ፡፡
• የአክሲዮን ማህበራት አቋቋም
የአክሲዮን ማህበራት በሁለት አይነት መንገድ ሊቋቋሙ ይችላሉ፡፡ እነዚህም፡-
1. ለህዝብ ክፍት የሆነ የአክስዮን ማህበር ፡- በአደራጅ አማካኝነት የሚቋቋም ሲሆን አደራጁ ለሕዝብ ክፍት የሆነ ማህበር ምስረታን ያነሳሳል፤ መግለጫ አዘጋጅቶ ሰዎች ማህበሩን እንዲቀላቀሉ ይጋብዛል ወይም በአጠቃላይ የማህበሩን ምስረታ ዓላማ አድርጎ ይህንኑ ለማስፈጸም በመንቀሳቀስ ማህበሩ የማይመሰረት ከሆነ ባለመመስረቱ ምክንያት ለሚመጣ ጉዳት ኃላፊነት ይወስዳል፡፡ የአክሲዮን ማህበራት በአንድ ወይም ከዚያ በላይ በሆኑ የተፈጥሮ ሰዎች ወይም ሕጋዊ ሰውነት ባላቸው ሰዎች ሊደራጁ የሚችል ሆኖ የአክሲዮን ማህበር አባላት ቁጥር ከአምስት ባለአክሲዮኖች በታች መሆን የለበትም፡፡
አደራጆቹ ለህዝብ አክሲዮን በመሸጥ አክሲዮን ማህበራት ሲያቋቁሙ ሊከተሏቸው ወይም መፈፀም ያለባቸውን ድርጊቶች እና ሊያሟሉ ስለሚገባቸው ሁኔታዎች በንግድ ህጉ አንቀጽ 249፣ 250 እና 251 ስር ተመልክቷል፡፡በአጠቃላይ በዚህ አይነት መንገድ የሚቋቋም አክሲዮን የንግድ ሀሳቡ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ የሚጠይቅ ከሆነ ገንዘቡን ትንሽ ሠዎችን በማሣመን መሰብሰብ ስለሚያስቸግር ለሕዝብ አክሲዮን በመሸጥ አክሲዮን ማህበሩን ማቋቋም ይችላሉ፡፡
2. በመሥራቾች መካከል የሚደረግ መቋቋም
ይኸኛው የአክስዮን ማህበር አይነት ምስረታ የሚደረገው የተወሰኑ ሰዎች ለሕዝብ ጥሪ ሳያደርጉ የአክሲዮን ማህበር ምስረታን የተመለከቱ የንግድ ህግ ድንጋጌዎችን በማሟላት በመካከላቸው የአክሲዮን ማህበር የሚያቋቁሙበት ነው።በተመሳሳይ በሌላ ህግ የተለየ ቁጥር ካልተወሰነ በስተቀር የአክሲዮን ማህበር መሥራቾች ቢያንስ አምስት መሆን እንዳለባቸው በንግድ ህጉ አንቀፅ 252 ስር ተደንግጓል፡፡
• የማህበሩ አመሰራረት
ለአክሲዮን ማህበር ምስረታ ከሚያስፈልጉ ጠቅላላ ሁኔታዎች ውስጥ የማህበሩ ዋና ገንዘብ በሙሉ ለማዋጣት መፈረም ፤እና ለጥሬ ገንዘብ በተሠጡ አክሲዮኖች ላይ ከተፃፈው ዋጋ ውስጥ ቢያንስ አንድ አራተኛው በመመስረት ላይ ባለው ማህበር ስም በተከፈተ ዝግ የባንክ ሒሳብ መቀመጥ ያለበት መሆኑ ይገኙበታል፡፡የተቀመጠውን ገንዘብ ማህበሩ በንግድ መዝገብ ሳይመዘገብ ከተቀመጠበት ሒሳብ ማውጣት አይቻልም፡፡
መግቢያ
አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ኑሮው ከእጅ ወደ አፍ መሆኑ ይታወቃል። ሻል ያለ ደረጃ ላይ የሚገኙት ጥቂቶችም ቢሆኑ ትርጉም ያለው ተቀማጭ ገንዘብ የላቸውም ሊባል ይችላል። በመሆኑም አገራችን ሥራ ላይ ሊውል (ኢንቨስት ሊደርግ) የሚችል ካፒታል ከፍተኛ እጥረት አለባት። በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ በሚገኝ አገር ውስጥ እድገት ለማምጣት ዜጎች በተናጠል ያላቸውን እጅግ ውስን ሀብት አስተባብሮ ወደ ሥራ ማስገባት የግድ ይላል። ይህ እንዲሳካ ደግሞ ዜጎች የቆጠቡትን ትንሽ ገንዘብ በንግድ ማኅበር ውስጥ ካስገቡ በኋላ ለምዝበራ እና ጭቆና እንዳይዳረጉ የሚከላከል ሕግ መኖር አለበት።
የ1952ቱ ንግድ ህግ በኩባንያዎች ውስጥ አነስተኛ ድርሻ ይዘው የሚገቡትን ባለሃብቶች ከዘረፋ፣ ካልተገባ ጭቆና ወይም በደል ለመታደግ ያለሙ ድንጋጌዎች በበቂ ሁኔታ አላካተተም። በዚህም የተነሳ ኢኮኖሚው ያፈራውን አነስተኛ ካፒታል አሟጦ በተደራጀ መልክ ሥራ ላይ ማዋል አስቸጋሪ ሆኖ ቆይቷል። አልፎ ተርፎም ይህ ክፍተት አገሮች ለንግድ ምን ያህል አመቺ እንደሆኑ በሚለካው በዓለም ባንክ የሚደረግ ምዘና ኢትዮጵያ በየዓመቱ በጣም ዝቅተኛ ውጤት እንድታገኝ አድርጓል። በዚህም የተነሳ አገራችን የውጭ ኢንቨስትመንት ለመሳብ በምታደርገው ጥረት ላይ ዕንቅፋት ሆኖ ቆይቷል።በመሆኑም አዲሱ የንግድ ህግ ከቀድሞው የንግድ ህግ በተሸለ ሁኔታ የማህበር አባላትን መብት በሚያስጠብቅ ሁኔታ የህግ ድንጋጌዎችን አካቶ በስራ ላይ ውሏል፡፡
የአክሲዮን ማህበር በቀድሞው እና በአዲሱ የንግድ ህግ ከተካተቱ የንግድ ማህበራት አይነቶች ውስጥ አንዱ ሲሆን ማህበሩ የመጠሪያ ስም ኖሮት ከስሙ መጨረሻ ላይ “የአክሲዮን ማህበር” የሚል ሀረግ በመጨመር በንግድ መዝገብ እንደተመዘገቡ የሕግ ሰውነት እንደሚያገኝ በአዲሱ የንግድ ህግ አንቀፅ 174፣175፤246 ተመልክቷል፡፡በዚህ አጭር የንቃተ ህግ ፅሁፍ በአዲሱ የንግዱ ህግ ስለአክሲዮን ማህበር የተካተቱ አንዳንድ ነጥቦችን በወፍ በረር ለማየት ይሞከራል፡፡
የአክሲዮን ማህበር ትርጉም
የአክሲዮን ማህበር ማለት ዋና ገንዘቡ ወይም ካፒታሉ አስቀድሞ ተወስኖ በአክሲዮን የተከፋፈለና ኃላፊነቱ በማህበሩ ሀብት ብቻ የተወሰነ ማህበር ሲሆን የአባላት ቁጥር ከአምስት ባለአክሲዮኖች በታች መሆን የሌለበት የንግድ ማህበር አይነት ነው፡፡ የባለአክሲዮኖች ኃላፊነት ለማህበሩ ቃል የገቡትን መዋጮ በመክፈል የተወሰነ ሆኖ በሌላ ሕግ በተለየ ሁኔታ ካልተደነገገ በስተቀር፣ የማህበሩ ዋና ገንዘብ ወይም ካፒታል ከሃምሳ ሺህ የኢትዮጵያ ብር ያነሰ ሊሆን እንደማይችል እና እያንዳንደ አክሲዮን ላይ የሚጻፈው ዋጋ ከአንድ መቶ ብር በታች ሊሆን እንደማይችል በንግድ ህጉ አንቀፅ 245/1/ እና 2 ስር ሰፍሯል፡፡
የአክሲዮን ማህበር አባላት ሃላፊነት የተወሰነ ነው ማለት ማህበሩ ከሦስተኛ ወገኖች ማለትም ከአበዳሪዎች፣ከደንበኞቹ እና ከሠራተኞቹ ወ.ዘ.ተ ጋር በሚያደርገው ግንኙነት ጉዳት ቢደርስ የማህበሩ አባላት (ባለአክሲዮኖች) ሃላፊነት እስከ ምን ድረስ ነው? የሚለውን ይመለከታል፡፡ ይኸውም የማህበሩ አባላት ሃላፊነት ለማህበሩ ካፒታል ባዋጡት ወይም በሚያዋጡት መጠን ብቻ ተጠያቂ እንደሚሆኑ ከንግድ ህጉ ድንጋጌ መረዳት ይቻላል፡፡:: ይህም ማለት አባላቱ ማህበሩ ሲመሠረት ወይም ከተመሰረተ በኋላ ለሽያጭ ከቀረበው የአክሲዮን ድርሻ ውስጥ በገዙት የአክሲዮን መጠን ብቻ ተጠያቂ የሚሆኑ ሲሆን አባሉ የሚጠበቅበትን መዋጮ ያልከፈለ እንደሆነ አክሲዮን ማህበሩ በእዳ ሲያዝ እንዲከፍል ይገደዳል፡፡ የአክሲዮን ማህበሩ ሃብት ጉዳቱን ለመካስ በቂ ሆኖ ባይገኝ ወደ ባለአክሲዮኖቹ ንብረት መሄድ አይቻልም ማለት ነው፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ የአባላቱ የግል እዳ ከኩባንያው ሃብት አይከፈልም፡፡
• የአክሲዮን ማህበር ጥቅም/ አስፈላጊነት
የአክሲዮን ማህበራት በሃገራችን መበራከት ሀገራዊ እና ግለሰባዊ ፋይዳ አለው፡፡ ሀገራዊ ፋይዳውን ስናይ አክሲዮን ማህበር ትልልቅና ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ የሚጠይቁ የንግድ ዘርፎች(ለምሳሌ ባንክ፣መድን ድርጅት፣በግብርና ዘርፍ፣በቤቶች ግንባታ ወዘተ ) ላይ ለመሰማራት የሚረዳ የማህበር አይነት በመሆኑ የእነዚህ ግዙፍ ኢንዱስትሪዎች በሃገራችን መፈጠር ሀገራችን መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገሮች ተርታ ለመሰለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት በከፍተኛ ደረጃ ያግዛል፡፡ በሌላ በኩል የግለሰቦችን ስራ ፈጣሪነት ያበረታታል፡፡ ይህ ሲባል ግለሰቦች የሀገርን ኢኮኖሚ እድገት ሊያፋጥን የሚችል የንግድ ሃሳብ አመንጭተው ካፒታል ከህዝቡ በመሰብሰብ ለመስራት የሚያስችል በመሆኑ ሙያዊ ብቃታቸውን ተጠቅመው የሚሰሩ ስራ ፈጣሪዎች ተገቢውን ክፍያ እንዲያገኙ የሚያበረታታ ሲሆን ለማህበሩ መፈጠር የደም ስር የሆነውን ካፒታል ያዋጡ ሰዎች ደግሞ ወደ ፊት ማህበሩ የሚያስገኘውን ትርፍ የድርሻቸውን በመውሰድ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮቻቸውን እንዲፈቱ ያስችላል፡፡በአጠቃላይ አክሲዮን ማህበር ባለሀብቱን (capitalist) ከስራ ፈጣሪ (entrepreneur) ጋር የሚያገናኝ በመሆኑ ጠቀሜታው የጎላ ነው ፡፡
• የአክሲዮን ማህበራት አቋቋም
የአክሲዮን ማህበራት በሁለት አይነት መንገድ ሊቋቋሙ ይችላሉ፡፡ እነዚህም፡-
1. ለህዝብ ክፍት የሆነ የአክስዮን ማህበር ፡- በአደራጅ አማካኝነት የሚቋቋም ሲሆን አደራጁ ለሕዝብ ክፍት የሆነ ማህበር ምስረታን ያነሳሳል፤ መግለጫ አዘጋጅቶ ሰዎች ማህበሩን እንዲቀላቀሉ ይጋብዛል ወይም በአጠቃላይ የማህበሩን ምስረታ ዓላማ አድርጎ ይህንኑ ለማስፈጸም በመንቀሳቀስ ማህበሩ የማይመሰረት ከሆነ ባለመመስረቱ ምክንያት ለሚመጣ ጉዳት ኃላፊነት ይወስዳል፡፡ የአክሲዮን ማህበራት በአንድ ወይም ከዚያ በላይ በሆኑ የተፈጥሮ ሰዎች ወይም ሕጋዊ ሰውነት ባላቸው ሰዎች ሊደራጁ የሚችል ሆኖ የአክሲዮን ማህበር አባላት ቁጥር ከአምስት ባለአክሲዮኖች በታች መሆን የለበትም፡፡
አደራጆቹ ለህዝብ አክሲዮን በመሸጥ አክሲዮን ማህበራት ሲያቋቁሙ ሊከተሏቸው ወይም መፈፀም ያለባቸውን ድርጊቶች እና ሊያሟሉ ስለሚገባቸው ሁኔታዎች በንግድ ህጉ አንቀጽ 249፣ 250 እና 251 ስር ተመልክቷል፡፡በአጠቃላይ በዚህ አይነት መንገድ የሚቋቋም አክሲዮን የንግድ ሀሳቡ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ የሚጠይቅ ከሆነ ገንዘቡን ትንሽ ሠዎችን በማሣመን መሰብሰብ ስለሚያስቸግር ለሕዝብ አክሲዮን በመሸጥ አክሲዮን ማህበሩን ማቋቋም ይችላሉ፡፡
2. በመሥራቾች መካከል የሚደረግ መቋቋም
ይኸኛው የአክስዮን ማህበር አይነት ምስረታ የሚደረገው የተወሰኑ ሰዎች ለሕዝብ ጥሪ ሳያደርጉ የአክሲዮን ማህበር ምስረታን የተመለከቱ የንግድ ህግ ድንጋጌዎችን በማሟላት በመካከላቸው የአክሲዮን ማህበር የሚያቋቁሙበት ነው።በተመሳሳይ በሌላ ህግ የተለየ ቁጥር ካልተወሰነ በስተቀር የአክሲዮን ማህበር መሥራቾች ቢያንስ አምስት መሆን እንዳለባቸው በንግድ ህጉ አንቀፅ 252 ስር ተደንግጓል፡፡
• የማህበሩ አመሰራረት
ለአክሲዮን ማህበር ምስረታ ከሚያስፈልጉ ጠቅላላ ሁኔታዎች ውስጥ የማህበሩ ዋና ገንዘብ በሙሉ ለማዋጣት መፈረም ፤እና ለጥሬ ገንዘብ በተሠጡ አክሲዮኖች ላይ ከተፃፈው ዋጋ ውስጥ ቢያንስ አንድ አራተኛው በመመስረት ላይ ባለው ማህበር ስም በተከፈተ ዝግ የባንክ ሒሳብ መቀመጥ ያለበት መሆኑ ይገኙበታል፡፡የተቀመጠውን ገንዘብ ማህበሩ በንግድ መዝገብ ሳይመዘገብ ከተቀመጠበት ሒሳብ ማውጣት አይቻልም፡፡
በሌላ በኩል የአክሲዮን ሽያጭ ገንዘብ ባንክ መቀመጥ ከጀመረበት ቀን አንስቶ በንግድ ህጉ አንቀጽ 259 መሠረት በሚቀርበው የማህበሩ መግለጫ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ማህበሩን ማስመዝገብ ካልተቻለ በማህበሩ አባልነት መቀጠል የማይፈልጉ ፈራሚዎች ገንዘባቸው ከባንክ ወለድ ጋር እንዲመለስላቸው መጠየቅ ይችላሉ፡፡ገንዘቡ እንዲመለስ ጥያቄ ከቀረበበት ቀን ጀምሮ በ30 ቀናት ውስጥ አደራጆች በንግድ ማህበር መዝጋቢው አካል መዋጮው እንዲመለስ ማሳወቅ አለባቸው፡፡ መዝጋቢው አካልም ለጥያቄ አቅራቢው ፈራሚ መዋጮው እንዲመለስለት የሚመለከተውን ባንክ ማሳወቅ ይኖርበታል፡፡ ሆኖም የማህበሩ ምስረታ በቀሪዎቹ ፈራሚዎች ሊቀጥል ይችላሉ።
• የማህበሩ በንግድ መዝገብ መመዝገብ
የአክሲዮን ማህበሩ የተቋቋመው በምንም ዓይነት ቢሆንም በንግድ መዝገብ መግባት ያለበት ሲሆን ማህበሩ የሕግ ሰውነት የሚያገኘው በምዝገባ ይሆናል። ከምዝገባው ማመልከቻ ጋር በሰነድ አረጋጋጭ የተረጋገጠ የመመስረቻ ጽሁፍ፣ ማህበሩ ለሕዝብ ክፍት የሆነ እንደሆነ የማህበሩ መግለጫ፣ የዓይነት መዋጮዎች እና የምስረታ ኦዲት ሪፖርቶች እንዲሁም የፈራሚዎች ጉባዔ ቃለጉባዔ ተያይዞ መቅረብ አለበት፡፡ የአክሲዮን ማህበር የባለአክሲዮኖችን መዝገብ በወረቀት ወይም ለረጅም ዘመን በሚቆይ የኤላክትሮኒክ ዘዴ መያዝ ይችላል።
አክሲዮኖች የሚወጡበት ዘዴ በማህበሩ የመመስረቻ ፅሁፍ ወይም ማሻሻያው ሊወሰን የሚችል ሆኖ በወረቀት ወይም በግዑዝ አልባ ማለትም ይህንን ስራ እንዲሰራ በህግ ሥልጣን በተሰጠው ተቋም በኤሌክትሮኒክ ዘዴ ተፈጥሮ በኤለክትሮኒክ የአክሲዮን ሂሳብ የሚያዝ አክሲዮን ሊሆን ይችላል፡፡መዝገቡ የባለአክሲዮኖችን ስም፣ አድራሻ፣ዜግነት፣ የአክሲዮኖችን ብዛትና መለያ ቁጥር፣ የተከፈለውን ገንዘብ መጠንና ባለአክሲዮኖቹ የተመዘገቡበትን ቀን መያዝ አለበት።
የአክሲዮኖች አይነት
አክሲዮኖች በሚገዙበት ሁኔታ ላይ መሰረት በማድረግ በጥሬ ገንዘብ የሚገዙ አክሲዮኖች እና በአይነት መዋጮ የሚደረጉ ተብለው ሊከፈሉ እንደሚችሉ ከንግድ ህጉ አንቀፅ 281 እና 282 መገንዘብ ይቻላል፡፡
በጥሬ ገንዘብ የሚገዙ አክሲዮኖች በተፈረሙ ጊዜ እጅግ ቢያንስ ከተጻፈባቸው ዋጋ አንድ አራተኛ ወይም በማህበሩ መመስረቻ ጽሁፍ ከፍ ያለ መጠን ተወስኖ ከሆነ ይኸው ዋጋ በሙሉ መከፈል አለበት።በመመስረቻ ጽሁፍ ያነሰ ጊዜ ካልተወሰነ በስተቀር፤ ያልተከፈለው የአክሲዮኖች ዋጋ ማህበሩ በንግድ መዝገብ ከተመዘገበበት ቀን ጀምሮ እስከ አምስት ዓመት መከፈል አለበት፡፡
በዓይነት መዋጮ የተደረገ እንደሆነ የአይነት ማዋጮ የከፈለ ፈራሚ የባለሙያ ግምት ሪፖርት ማቅረብ አለበት።የግምት ሪፖርቱ መዋጮ የተደረጉትን ንብረቶች፣ የእያንዳንዱን የዋጋ ግምት እና የአገማመቱን ዘዴ በዝርዝር መገለፅ ያለበት ሆኖ ሪፖርቱም ከመመስረቻ ጽሁፍ ጋር መያያዝ ይኖርበታል።
በሌላ በኩል ከሚያስገኙት ጥቅም አንፃር የአክሲዮን ማህበራትን በሁለት ከፍሎ ማየት የሚቻል ሲሆን እነዚህም ልዩ መብት የሚያስገኙ አክሲዮኖች እና ትርፍ ብቻ የሚያስገኙ አክሲዮኖች ናቸው፡፡ ልዩ መብት የሚያስገኙ አክሲዮኖች የሚሰጡት ልዩ ጥቅም ወደ ፊት የሚወጡትን አክሲዮኖች በቅድሚያ የመግዛትን፣ ከትርፍ በቅድሚያ የመከፈልን ወይም የማህበሩ ንብረት በሚጣራበት ጊዜ መዋጮ ሲመለስ ወይም ተራፊ ሀብት ሲከፋፈል በቅድሚያ ክፍያ የማግኘትንና የመሳሰሉትን ሊያካትት ይችላል። ትርፍ ብቻ የሚያስገኙ አክስዮኖች ደግሞ ማህበሩ ዋናው ገንዘቡን ሳይቀንስ ካገኘው ትርፍ ወይም ካስቀመጠው መጠባበቂያ ገንዘብ ለባለአክሲዮኖች በአክሲዮኖቻቸው ላይ የተጻፈውን ዋጋ የሚመለስበት ነው፡፡
በተጨማሪም በአዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 267 እንደተገለጸዉ በሚወጡበት መንገድ ላይ መሰረት በማድረግ በባለአክሲዮን ስም የሚወጡ የአክስዮን አይነቶች በባለአክሲዮን ስም የሚመዘገቡ ሲሆን ላምጪው የሚል አክሲዮኖች ሌላኞቹ የአክሲዮን አይነቶች ናቸው፡፡ ተቃራኒ ስምምነት ቢኖርም እንኳን አዲሱ የንግድ ሕግ ከመውጣቱ በፊት ላምጪው የሚል አክሲዮኖች በሚገኙባቸው ማህበሮች ለአምጪው በሚል የወጡ አክሲዮኖች ባለቤት የሆነ ማንኛውም ሰው አክሲዮኖቹ በስም በሚመዘገብ እንዲለወጡለት ማህበሩ ዘንድ በመቅረብ ይህ አዋጅ በነጋሪት ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሦስት ዓመት ውስጥ ማመልከት አለበት።
• የማህበሩ ስራ አመራር
የአክሲዮን ማህበራት የስራ አመራር የዳይሬክተሮች ቦርድ እና ተቆጣጣሪ ቦርድ ይኖራቸዋል፡፡የአክሲዮን ማህበር በባለአክሲዮኖች የሚመረጡ ቢያንስ ሦስት ቢበዛ አስራ ሦስት ዳይሬክተሮች እንደሚኖሩት እና ከዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት መካከል ከሦስት ሁለት እጅ (2/3ኛ) በማህበሩ የዕለት ተዕለት ሥራ አመራር ውስጥ የሥራ አስፈጻሚነት (ኤክስኪዩቲቭ) ሚና የሌላቸው መሆን እንዳለባቸው በንግድ ህጉ አንቀፅ 296 ስር ተደንግጓል፡፡ በተጨማሪ የማኅበር አባል ያልሆነ ሰዉ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባል ሆኖ ሊመረጥ ይችላል፡፡ እንዲሁም የዳይሬክተሮች ቦርድ በሕግ፣ በማህበሩ መመስረቻ ጽሁፍ ወይም በባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባዔ ውሳኔዎች የሚሰጥ ሀላፊነት እና ሥልጣን ይኖረዋል።ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በንግድ ህጉ ዝርዝር ሀላፊነቶች እና ስልጣን ተካቶ ይገኛል፡፡ በተጨማሪም የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ኃላፊነታቸውን ባለመወጣታቸው ለሚደርሰው ጉዳት ለማህበሩ በአንድነትና በተናጠል ተጠያቂ እንደሚሆኑ በንግድ ህጉ አንቀፅ 325 እና ተከታዮቹ ተመልክቷል።
በሌላ በከል የአክሲዮን ማህበራት ተቆጣጣሪ ቦርድ በጠቅላላ ጉባዔ የሚሾሙ ቁጥራቸው ከሦስት ያላነሱ ከአምስት ያልበለጡ አባላት ሊኖሩቱ የሚችል ሲሆን ጠቅላላ ጉባዔው የተቆጣጣሪ ቦርድ አባላትን በማንኛውም ጊዜ ሊሽራቸው ይችላል፡፡
የተቆጣጣሪ ቦርድ አባል ሆነው መመረጥ የሚችሉት ባለአክሲዮኖች ብቻ ሲሆኑ የተቆጣጣሪ ቦርዱ ተጠሪነት ለባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባዔ ይሆናል።የተቆጣጣሪ ቦርድ አባላት ስልጣን ፣ ተግባር እና ሀላፈነቶች በንግድ ህጉ አንቀፅ 332 እና ተከታዮቹ ተዘርዝሮ የሚገኝ ሲሆን ለሥራው አስፈላጊ የሆኑ ሰነዶችንና ሌሎች መረጃዎችን የማስቀረብ እና የመመርመር አንዱ ተግባር ነው ፡፡
ስለማህበሩ መፍረስ እና ማህበሩ የሚፈርስባቸው ምክንያቶች
የአክሲዮን ማህበር በሚከተሉት ምክንያቶች ሊፈርስ ይችላል፡--
የባለአክሲዮኖች ቁጥር በሕግ ከተፈቀደው ዝቅ ሲልና በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ሌላ አባል መተካት ባለመቻሉ ምክንያት ጥቅም አለኝ በሚል ሰው በቀረበ ማመልከቻ መሠረት የንግድ ማህበራትን የሚመዘግበው አካል ማህበሩ እንዲፈርስ ሲወስን፤የአስተዲደር አካላት የሌሉት በመሆኑ ምክንያት ጥቅም አለኝ በሚል ሰው ጠያቂነት የንግድ ማህበራትን የሚመዘግበው አካል ማህበሩ እንደፈርስ ሲወስን እና ማህበሩ የዋና ገንዘቡን ሦስት አራተኛ በኪሣራ ሲያጣ ናቸው።እንዲሁም በንግድ ህጉ እንቀፅ 181 የተዘረዘሩ የአጠቃላይ የንግድ ማህበራት መፍረስ ምክንያቶች ለአክሲዮን ማህበር መፍረስ ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡
በንግድ ሕጉ መሠረት ማህበሩ እንዲፈርስ በማህበሩ የተወሰነ እንደሆነ የመፍረሱ ውሳኔ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በሃያ አንድ ቀናት ውስጥ ማህበሩ እንዲፈርስ ስለመወሰኑ ሰፊ ስርጭት ባለው ጋዜጣና በማህበሩ ድረ ገጽ በይፋ መገለጽ ያለበት ሲሆን ማስታወቂያውም “በመጣራት ላይ ያለ” የሚል ሀረግ ተጨምሮበት የማህበሩን ስም፣ የዋና ገንዘቡን መጠን፣ የፈረሰበትን ምክንያት፣ የሂሳብ አጣሪውን ስምና አድራሻ እንዲሁም የሥልጣን ወሰን መያዝ አለበት። እንዲሁም ማህበሩ እንዲፈርስ የተሰጠው ውሳኔ እና በውሳኔው መሠረት ሒሳብ
• የማህበሩ በንግድ መዝገብ መመዝገብ
የአክሲዮን ማህበሩ የተቋቋመው በምንም ዓይነት ቢሆንም በንግድ መዝገብ መግባት ያለበት ሲሆን ማህበሩ የሕግ ሰውነት የሚያገኘው በምዝገባ ይሆናል። ከምዝገባው ማመልከቻ ጋር በሰነድ አረጋጋጭ የተረጋገጠ የመመስረቻ ጽሁፍ፣ ማህበሩ ለሕዝብ ክፍት የሆነ እንደሆነ የማህበሩ መግለጫ፣ የዓይነት መዋጮዎች እና የምስረታ ኦዲት ሪፖርቶች እንዲሁም የፈራሚዎች ጉባዔ ቃለጉባዔ ተያይዞ መቅረብ አለበት፡፡ የአክሲዮን ማህበር የባለአክሲዮኖችን መዝገብ በወረቀት ወይም ለረጅም ዘመን በሚቆይ የኤላክትሮኒክ ዘዴ መያዝ ይችላል።
አክሲዮኖች የሚወጡበት ዘዴ በማህበሩ የመመስረቻ ፅሁፍ ወይም ማሻሻያው ሊወሰን የሚችል ሆኖ በወረቀት ወይም በግዑዝ አልባ ማለትም ይህንን ስራ እንዲሰራ በህግ ሥልጣን በተሰጠው ተቋም በኤሌክትሮኒክ ዘዴ ተፈጥሮ በኤለክትሮኒክ የአክሲዮን ሂሳብ የሚያዝ አክሲዮን ሊሆን ይችላል፡፡መዝገቡ የባለአክሲዮኖችን ስም፣ አድራሻ፣ዜግነት፣ የአክሲዮኖችን ብዛትና መለያ ቁጥር፣ የተከፈለውን ገንዘብ መጠንና ባለአክሲዮኖቹ የተመዘገቡበትን ቀን መያዝ አለበት።
የአክሲዮኖች አይነት
አክሲዮኖች በሚገዙበት ሁኔታ ላይ መሰረት በማድረግ በጥሬ ገንዘብ የሚገዙ አክሲዮኖች እና በአይነት መዋጮ የሚደረጉ ተብለው ሊከፈሉ እንደሚችሉ ከንግድ ህጉ አንቀፅ 281 እና 282 መገንዘብ ይቻላል፡፡
በጥሬ ገንዘብ የሚገዙ አክሲዮኖች በተፈረሙ ጊዜ እጅግ ቢያንስ ከተጻፈባቸው ዋጋ አንድ አራተኛ ወይም በማህበሩ መመስረቻ ጽሁፍ ከፍ ያለ መጠን ተወስኖ ከሆነ ይኸው ዋጋ በሙሉ መከፈል አለበት።በመመስረቻ ጽሁፍ ያነሰ ጊዜ ካልተወሰነ በስተቀር፤ ያልተከፈለው የአክሲዮኖች ዋጋ ማህበሩ በንግድ መዝገብ ከተመዘገበበት ቀን ጀምሮ እስከ አምስት ዓመት መከፈል አለበት፡፡
በዓይነት መዋጮ የተደረገ እንደሆነ የአይነት ማዋጮ የከፈለ ፈራሚ የባለሙያ ግምት ሪፖርት ማቅረብ አለበት።የግምት ሪፖርቱ መዋጮ የተደረጉትን ንብረቶች፣ የእያንዳንዱን የዋጋ ግምት እና የአገማመቱን ዘዴ በዝርዝር መገለፅ ያለበት ሆኖ ሪፖርቱም ከመመስረቻ ጽሁፍ ጋር መያያዝ ይኖርበታል።
በሌላ በኩል ከሚያስገኙት ጥቅም አንፃር የአክሲዮን ማህበራትን በሁለት ከፍሎ ማየት የሚቻል ሲሆን እነዚህም ልዩ መብት የሚያስገኙ አክሲዮኖች እና ትርፍ ብቻ የሚያስገኙ አክሲዮኖች ናቸው፡፡ ልዩ መብት የሚያስገኙ አክሲዮኖች የሚሰጡት ልዩ ጥቅም ወደ ፊት የሚወጡትን አክሲዮኖች በቅድሚያ የመግዛትን፣ ከትርፍ በቅድሚያ የመከፈልን ወይም የማህበሩ ንብረት በሚጣራበት ጊዜ መዋጮ ሲመለስ ወይም ተራፊ ሀብት ሲከፋፈል በቅድሚያ ክፍያ የማግኘትንና የመሳሰሉትን ሊያካትት ይችላል። ትርፍ ብቻ የሚያስገኙ አክስዮኖች ደግሞ ማህበሩ ዋናው ገንዘቡን ሳይቀንስ ካገኘው ትርፍ ወይም ካስቀመጠው መጠባበቂያ ገንዘብ ለባለአክሲዮኖች በአክሲዮኖቻቸው ላይ የተጻፈውን ዋጋ የሚመለስበት ነው፡፡
በተጨማሪም በአዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 267 እንደተገለጸዉ በሚወጡበት መንገድ ላይ መሰረት በማድረግ በባለአክሲዮን ስም የሚወጡ የአክስዮን አይነቶች በባለአክሲዮን ስም የሚመዘገቡ ሲሆን ላምጪው የሚል አክሲዮኖች ሌላኞቹ የአክሲዮን አይነቶች ናቸው፡፡ ተቃራኒ ስምምነት ቢኖርም እንኳን አዲሱ የንግድ ሕግ ከመውጣቱ በፊት ላምጪው የሚል አክሲዮኖች በሚገኙባቸው ማህበሮች ለአምጪው በሚል የወጡ አክሲዮኖች ባለቤት የሆነ ማንኛውም ሰው አክሲዮኖቹ በስም በሚመዘገብ እንዲለወጡለት ማህበሩ ዘንድ በመቅረብ ይህ አዋጅ በነጋሪት ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሦስት ዓመት ውስጥ ማመልከት አለበት።
• የማህበሩ ስራ አመራር
የአክሲዮን ማህበራት የስራ አመራር የዳይሬክተሮች ቦርድ እና ተቆጣጣሪ ቦርድ ይኖራቸዋል፡፡የአክሲዮን ማህበር በባለአክሲዮኖች የሚመረጡ ቢያንስ ሦስት ቢበዛ አስራ ሦስት ዳይሬክተሮች እንደሚኖሩት እና ከዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት መካከል ከሦስት ሁለት እጅ (2/3ኛ) በማህበሩ የዕለት ተዕለት ሥራ አመራር ውስጥ የሥራ አስፈጻሚነት (ኤክስኪዩቲቭ) ሚና የሌላቸው መሆን እንዳለባቸው በንግድ ህጉ አንቀፅ 296 ስር ተደንግጓል፡፡ በተጨማሪ የማኅበር አባል ያልሆነ ሰዉ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባል ሆኖ ሊመረጥ ይችላል፡፡ እንዲሁም የዳይሬክተሮች ቦርድ በሕግ፣ በማህበሩ መመስረቻ ጽሁፍ ወይም በባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባዔ ውሳኔዎች የሚሰጥ ሀላፊነት እና ሥልጣን ይኖረዋል።ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በንግድ ህጉ ዝርዝር ሀላፊነቶች እና ስልጣን ተካቶ ይገኛል፡፡ በተጨማሪም የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ኃላፊነታቸውን ባለመወጣታቸው ለሚደርሰው ጉዳት ለማህበሩ በአንድነትና በተናጠል ተጠያቂ እንደሚሆኑ በንግድ ህጉ አንቀፅ 325 እና ተከታዮቹ ተመልክቷል።
በሌላ በከል የአክሲዮን ማህበራት ተቆጣጣሪ ቦርድ በጠቅላላ ጉባዔ የሚሾሙ ቁጥራቸው ከሦስት ያላነሱ ከአምስት ያልበለጡ አባላት ሊኖሩቱ የሚችል ሲሆን ጠቅላላ ጉባዔው የተቆጣጣሪ ቦርድ አባላትን በማንኛውም ጊዜ ሊሽራቸው ይችላል፡፡
የተቆጣጣሪ ቦርድ አባል ሆነው መመረጥ የሚችሉት ባለአክሲዮኖች ብቻ ሲሆኑ የተቆጣጣሪ ቦርዱ ተጠሪነት ለባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባዔ ይሆናል።የተቆጣጣሪ ቦርድ አባላት ስልጣን ፣ ተግባር እና ሀላፈነቶች በንግድ ህጉ አንቀፅ 332 እና ተከታዮቹ ተዘርዝሮ የሚገኝ ሲሆን ለሥራው አስፈላጊ የሆኑ ሰነዶችንና ሌሎች መረጃዎችን የማስቀረብ እና የመመርመር አንዱ ተግባር ነው ፡፡
ስለማህበሩ መፍረስ እና ማህበሩ የሚፈርስባቸው ምክንያቶች
የአክሲዮን ማህበር በሚከተሉት ምክንያቶች ሊፈርስ ይችላል፡--
የባለአክሲዮኖች ቁጥር በሕግ ከተፈቀደው ዝቅ ሲልና በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ሌላ አባል መተካት ባለመቻሉ ምክንያት ጥቅም አለኝ በሚል ሰው በቀረበ ማመልከቻ መሠረት የንግድ ማህበራትን የሚመዘግበው አካል ማህበሩ እንዲፈርስ ሲወስን፤የአስተዲደር አካላት የሌሉት በመሆኑ ምክንያት ጥቅም አለኝ በሚል ሰው ጠያቂነት የንግድ ማህበራትን የሚመዘግበው አካል ማህበሩ እንደፈርስ ሲወስን እና ማህበሩ የዋና ገንዘቡን ሦስት አራተኛ በኪሣራ ሲያጣ ናቸው።እንዲሁም በንግድ ህጉ እንቀፅ 181 የተዘረዘሩ የአጠቃላይ የንግድ ማህበራት መፍረስ ምክንያቶች ለአክሲዮን ማህበር መፍረስ ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡
በንግድ ሕጉ መሠረት ማህበሩ እንዲፈርስ በማህበሩ የተወሰነ እንደሆነ የመፍረሱ ውሳኔ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በሃያ አንድ ቀናት ውስጥ ማህበሩ እንዲፈርስ ስለመወሰኑ ሰፊ ስርጭት ባለው ጋዜጣና በማህበሩ ድረ ገጽ በይፋ መገለጽ ያለበት ሲሆን ማስታወቂያውም “በመጣራት ላይ ያለ” የሚል ሀረግ ተጨምሮበት የማህበሩን ስም፣ የዋና ገንዘቡን መጠን፣ የፈረሰበትን ምክንያት፣ የሂሳብ አጣሪውን ስምና አድራሻ እንዲሁም የሥልጣን ወሰን መያዝ አለበት። እንዲሁም ማህበሩ እንዲፈርስ የተሰጠው ውሳኔ እና በውሳኔው መሠረት ሒሳብ
አጣሪ መሾሙን የሚያመለክቱ ሰነድች በማህበሩ ዋና መሥሪያ ቤት መቀመጥ እንዲሁም በንግድ መዝገብ መመዝገብ አለባቸው፡፡
የንቃተ ህግ፣ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት
የንቃተ ህግ፣ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት
Legal Advisor
Reach Ethiopia
Addis Ababa
Terms of Reference for Legal Advisor to provide on call legal services External Announcement Brief introduction REACH Ethiopia is a non-political, non-religious, non-racial, and non-profit-making development Organization that has been registered by Charities and Societies Agency as Ethiopian Residents Charity bearing certificate No. 3020. REACH Ethiopia envisions contributing the development and wellbeing of humanity through innovation and maximizing the utilization of opportunity available for the generation.
The major goal of REACH Ethiopia is health service delivery commitment and contributing its part to improve the general health service and wellbeing of the disadvantaged community in move towards the sustainable development goal. REACH Ethiopia is currently implementing USAID Urban TB LON and Eliminate TB Projects in 2 City Administration (Addis Ababa and Dire Dawa) and 3 Regional States (Harari, Sidama and SNNPR) to contribute toward ending Tuberculosis through finding missing people with TB to access early diagnosis, care and treatment services. There is a project funded by Stop TB Partnership - TB REACH WAVE 9 Grant - on improving the treatment outcome of DR-TB Patients in the two TICs (Alert and St. Peter’s Hospitals) in Addis Ababa.
REACH Ethiopia invites qualified and experienced applicants for Legal Advisor post who will advise and represent the organization on all legal matters on part -time basis.
Job Summary In consultation with the REACH Ethiopia, the Legal Advisor shall provide call/parttime based legal advisory services, including writing proceedings and representing the organization on legal cases as legal cases emerge. Responsibilities Give accurate and timely counseling to REACH Ethiopia management on a variety of legal topics (labor law, ChSA proclamations, partnerships, international ventures, etc.); Review and give advice on internal governance policies and regularly monitor compliance; Review, evaluate and advise on different risk factors regarding business decisions and operations; Provide advice to REACH Ethiopia on effective risk management techniques and offer proactive advice on possible/emerging legal issues. Communicate and negotiate with external parties, regarding legal issues, (regulators, external counsel, public authority etc.), creating relations of trust; Draft and solidify agreements, contracts and other legal documents to ensure the REACH Ethiopia’s full legal rights; Provide clarification on legal language or specifications to REACH Ethiopia Staff; Maintain current knowledge of alterations in legislation. Other related activity assigned by the immediate supervisor Number of positions : One Educational Requirements: Requirements Licensed and proven experience as a Legal Advisor in business environment; Demonstrated ability to create legal response with defensive or proactive strategies; High degree of professional ethics and integrity; Sound judgement and ability to analyze situations and information; LLM from accredited Law school; Minimum of 5 years of practical experience in providing consultancy services in the legal...
Required Experience:
Senior Level (5+ years experience
https://t.me/lawsocieties
Reach Ethiopia
Addis Ababa
Terms of Reference for Legal Advisor to provide on call legal services External Announcement Brief introduction REACH Ethiopia is a non-political, non-religious, non-racial, and non-profit-making development Organization that has been registered by Charities and Societies Agency as Ethiopian Residents Charity bearing certificate No. 3020. REACH Ethiopia envisions contributing the development and wellbeing of humanity through innovation and maximizing the utilization of opportunity available for the generation.
The major goal of REACH Ethiopia is health service delivery commitment and contributing its part to improve the general health service and wellbeing of the disadvantaged community in move towards the sustainable development goal. REACH Ethiopia is currently implementing USAID Urban TB LON and Eliminate TB Projects in 2 City Administration (Addis Ababa and Dire Dawa) and 3 Regional States (Harari, Sidama and SNNPR) to contribute toward ending Tuberculosis through finding missing people with TB to access early diagnosis, care and treatment services. There is a project funded by Stop TB Partnership - TB REACH WAVE 9 Grant - on improving the treatment outcome of DR-TB Patients in the two TICs (Alert and St. Peter’s Hospitals) in Addis Ababa.
REACH Ethiopia invites qualified and experienced applicants for Legal Advisor post who will advise and represent the organization on all legal matters on part -time basis.
Job Summary In consultation with the REACH Ethiopia, the Legal Advisor shall provide call/parttime based legal advisory services, including writing proceedings and representing the organization on legal cases as legal cases emerge. Responsibilities Give accurate and timely counseling to REACH Ethiopia management on a variety of legal topics (labor law, ChSA proclamations, partnerships, international ventures, etc.); Review and give advice on internal governance policies and regularly monitor compliance; Review, evaluate and advise on different risk factors regarding business decisions and operations; Provide advice to REACH Ethiopia on effective risk management techniques and offer proactive advice on possible/emerging legal issues. Communicate and negotiate with external parties, regarding legal issues, (regulators, external counsel, public authority etc.), creating relations of trust; Draft and solidify agreements, contracts and other legal documents to ensure the REACH Ethiopia’s full legal rights; Provide clarification on legal language or specifications to REACH Ethiopia Staff; Maintain current knowledge of alterations in legislation. Other related activity assigned by the immediate supervisor Number of positions : One Educational Requirements: Requirements Licensed and proven experience as a Legal Advisor in business environment; Demonstrated ability to create legal response with defensive or proactive strategies; High degree of professional ethics and integrity; Sound judgement and ability to analyze situations and information; LLM from accredited Law school; Minimum of 5 years of practical experience in providing consultancy services in the legal...
Required Experience:
Senior Level (5+ years experience
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/